Telegram Web Link
🚘አሐዱ:ባንክ የኢንሹራንስ ክፍያን በተመለከተ የሁለትዮሽ ስምምነት አደረገ!

አሐዱ:ባንክ በተነሣበት ከብዙዎች ለብዙዎች መርሕ ለብዙዎች ለመድረስ አጠናክሮ በመቀጠል ከኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ ጋር በዋናው መሥሪያ ቤት ሐመር አዳራሽ ግንቦት 11/2017 ዓ.ም ስምምነት አደረገ::

የኢንሹራንስ ደንበኞች ለመኪናቸው የሚከፍሉትን ዓመታዊ የአረቦን ክፍያ 22% ብቻ በአሐዱ፡ባንክ በኩል ከቆጠቡ ባንኩ ፋይናንስ በማድረግ ዓመታዊ የኢንሹራንስ ክፍያቸውን እንደሚከፍልላቸው እና በ9 ወራት ጊዜ ውስጥ መክፈል የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን የአሐዱ:ባንክ ተ/ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሲሳይ ገብሩ በአፅንኦት ተናግረዋል::

የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽመልስ ገብረ ጊዮርጊስ በበኩላቸው፤ ከተለመደው አሠራር ወጣ ብለን ውጤት እና እድገት ላይ በማተኮር ተባብረን በመሥራት የጋራ ደንበኞቻችንን ለማገልገል አጋርነታችን እጅጉን ወሳኝ ነው በማለት ገልጸዋል::

አሐዱ ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች!

የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ!
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube
#AhaduBank #አሐዱ_ባንክ #MSME
📱QR በመጠቀም ክፍያዎን ይፈፅሙ!

የስልክዎን ካሜራ ብቻ በመጠቀም QR የመክፈያ ኮዶችን ስካን በማድረግ ክፍያዎን በቀላሉ ይፈፅሙ!

በዲጂታል ባንኪንግ ዘመንዎን ይዋጁ!

አሐዱ ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች!

#AhaduBank #አሐዱ_ባንክ #DigitalBanking #QRPayment
💼 We are Hiring

☑️Interested and qualified applicants shall apply via the following link only https://forms.gle/awU2ewg9YSNC2SEY9
☑️Only Shortlisted Candidates will be communicated.
☑️If you need more information, please call us on +251-11-5-260-795
☑️Application Deadline Date May, 28 2025

Ahadu Bank
Inclusive Intermediation

Join Our Social Medias
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #Vacancy
🆔 የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል?

❗️እንግዲያውስ በአቅራቢያዎ በሚገኙ በተመረጡ የአሐዱ ባንክ ቅንጫፎች በመሄድ ዛሬውኑ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያዎን በእጆ ያስገቡ!


✔️አገልግሎቱን ከታች በተጠቀሱት ቅርንጫፎቻችን ያገኛሉ።
👉አዳማ
👉ኃይሌ ገ/ሥላሴ
👉ቱሉ ዲምቱ
👉ኮተቤ 02
👉ኮተቤ ካራሎ
👉መርካቶ አዳራሽ
👉ሰአሊተ ምሕረት
👉አራዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ
👉መገናኛ ቅርንጫፎች
አገልግሎቱን እየሰጠን እንገኛለን።

🔜በቅርቡ:-በ
ጎንደር ማራኪ
ባህር ዳር ቅድስት ኪዳነ ምሕረት
ጣና
ደብረ ማርቆስ
ቅዱስ ሩፋኤል
ላፍቶ
ቢሾፍቱ መናኸሪያ
ካዎ ጦና
አሶሳ :- ቅርንጫፎቻችን አገልግሎት መስጠት የሚጀምሩ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች

የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ!

Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #ፋይዳ #National_Id
፵፬ ጥንዶች ሊሞሸሩ ነው!

በአትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ(ኢጃት) ፕሮጀክት ሥር በሆነው ጃን ቃና አዘጋጅነት የ44 ጥንዶች የብዙኃን ጋብቻ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ግንቦት 19/2017 ዓ.ም በቶታል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ፡፡

አሐዱ ባንክም ከብዙዎች ለብዙዎች በሚለው መርሑ የብዙኃን ጋብቻ አጋር በመሆን የጥንዶች የቁጠባ ሒሳብን አስተዋውቋል::

አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች

የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ!

Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #ኢጃት #ጃን_ቃና #ጥንዶች_የቁጠባሒሳብ
💼 We are Hiring

☑️Interested and qualified applicants shall apply via the following link only https://forms.gle/n5dSvGesT6pugAyk7
☑️Only Shortlisted Candidates will be communicated.
☑️If you need more information, please call us on +251-11-5-260-795
☑️Application Deadline Date June, 06 2025

Ahadu Bank
Inclusive Intermediation

Join Our Social Medias
Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #Vacancy
፵፬ ጥንዶች ተሞሸሩ!

በአትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ(ኢጃት) ፕሮጀክት ሥር በሆነው ጃን ቃና አዘጋጅነት የ44 ጥንዶች የብዙኃን ጋብቻ ሥነ ሥርዓት ግንቦት 21/2017 ዓ.ም በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተፈጸመ፡፡

አሐዱ ባንክም ከብዙዎች ለብዙዎች በሚለው መርሑ የብዙኃን ጋብቻ አጋር በመሆን ደስታውን ገልጿል::

አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች

የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ!

Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #ኢጃት #ጃን_ቃና #ጥንዶች_የቁጠባሒሳብ
አሐዱ፡ባንክ ከኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓል ንዋዮች ገበያ ጋር ውጤታማ ውይይት አደረገ!!

የአሐዱ፡ባንክ የቦርድ ዳሬክተር አቶ አንተነህ ሰብስቤ፣ የቦርድ አመራሮችን እና የማኔጅንት አባላት በተገኙበት ከኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓል ንዋዮች ገበያ መ/ቤት (Ethiopian securities Exchange) ከመጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በዋናው መሥሪያ ቤት ሐመር አዳራሽ ግንቦት 22/2017 ዓ.ም ውጤታማ ውይይት አደረጉ::
ከኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓል ንዋዮች ገበያ ዋና ዳሬክተር ዶ/ር ጥላሁን እስማኤልን ጨምሮ የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የሰነድ ሙዓል ንዋዮች ገበያ ምንነት፣ እንዴት እንደሚሰራና ባንኮች ከዚህ ተቋም ጋር ቢሰሩ በምን ዓይነት መልኩ ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ ሰፊ ማብራሪያዎች በመሥሪያ ቤቱ ባለሙያዎች አማካይነት ተሰጥቷል፡፡ ውይይቱን ተከትሎ በባንኩ የዳሬክተሮች ቦርድ እና የማኔጅመንት አባላት ከጉዳዩ ጋር ተያያዥ የሆኑ ጥያቄዎችና ሃሳቦች ቀርበው የጋራ ውይይት ተደርጓል፡፡
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የአሐዱ ባንክ የቦርድ ዳሬክተር አቶ አንተነህ ሰብስቤ እንደገለጹት የሰነድ ሙዓል ንዋዮች ገበያ (securities Exchange) የፋይናንስ ተቋማትን የማሳደግ አቅም ያለው እንደሆነና ፤ አሐዱ፡ባንክም ተተኳሪ ቡድን ተቋቁሞ በቦርድ ደረጃ የቅድመ-ዝግጅትና የጥናት ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አብራርተዋል:
አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች

የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ!

Website|Facebook|Instagram|LinkedIn|YouTube

#አሐዱባንክ #AhaduBank #EthiopianSecuritiesExchange
2025/07/05 19:56:16
Back to Top
HTML Embed Code: