Telegram Web Link
የአክብሮት ሰላምታዬን በማስቀደም ከሰሞኑ በምድረ አሜሪካ ኦሪገን ግዛት ተካይዶ በነበረው 18ተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በተቀዳጀነው አንፀባራቂ ድል የተሰማኝን ደስታ ስገልፅ በተለይም በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ከመቼውም ጊዜ በላቀ ብሔራዊ ስሜታችን ሊጠናከር በሚገባበት በእዚህ ታሪካዊ እና ወሳኝ ሰዓት ይህን አኩሪ ድል ላስመዘገቡ ባለውለታ ውድ ጀግኖች አትሌቶቻችን እና እንዲሁም ይህ የተቀናጀ ውጤት እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዎፆ ላደረጉ ጀግናዋ አትሌት ኮማንደር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ ለአሰልጣኞች እና ለመላው የሉካን ቡድኑ አባላት በሙሉ ከፍ ያለ የአክብሮት ምስጋናዬን እያቀረብኩ ነው::

በእዚህ አጋጣሚ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክቴን ለማስተላለፍ እወዳለሁ::

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
በአትሌቲክሱ ዘርፍ በአገሬ አሜሪካ ኦሪገን ግዛት ላይ ተካሂዶ በነበረው በ18ተኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አራት /4/ ወርቅ፣ አራት /4/ ብር እና ሁለት /2/ ናህስ በጥቅሉ አስር /10/ ሜዳሊያዎችን በማንሳት አገራችን ኢትዮጵያ በዓለም የሁለተኛ ደረጃነትን እንድትይዝ እና ለዚህ አንጸባራቂ ድል እንድትበቃ ያስቻላችሁ መላው የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አባላት በሙሉ ከልብ ልናመሰግናችሁ እንወዳለን።

ኢትዮጵያ ስሟ በዓለም ከፍ ይል ዘንድ ብሎም ኢትዮጵያውያን ወደ ብሄራዊ ስሜታቸው ይመለሱ ዘንድ እንዲህ ያሉ አነቃቂ እና አርኪ ተግባሮች በሁሉም ዘርፎች ይደገሙ ዘንድ መልካም መሆኑን ለማስታወስ እወዳለሁ። ሁሉም ኢትዮጵያ ሲል ማየት ደስ ይላል።

4 🥇 4 🥈 2 🥉

#WorldAthleticsChamps

#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ለውዴ ውዱ ነሽ

በጎደለ ሞልተሽ፤ በጠፋው ተክተሽ፣
ሲዝል አበርትተሽ፤ ግራውን ደግፈሽ፣
የብቸኝነት ጉዞውን፤ በጥንድ ቀይረሽ፣
ባብሮነትሽ አጅበሽ፤
ሙሉ አደረግሽው፤ መልኩን አሳቅፈሽ
እራሱን ደግመሽ፣ እራስሽን ደግመሽ።

መኑ ከመ ሄዋን፤ እንደ ሚካኤል እናት፣
መኑ ከመ ሄዋን፤ እንደ ብሩክቲ እናት?
ሁሌም አብራው ያለች፤ እየሆነች ብርታት፣
ለብላቴናው ክብሩ፤ ለልቡም ዘውድ ናት።

እንደ ግጥሜ ርዕስ፤ እንደ ስንኝ ቋጠሮ፣
እንደ ጠቢብ ቅኔ፤ እንደ ፀሐይ ኑሮ፣
ልብሽ ብሩህ ነው፤ ዘውትር የሚፈካ፣
መልክሽ በለስ ነው፤ ውዴ ባንቺ 'ረካ።

የሰጠሽው ፀጋ፤ የሰማይ ላይ መና፣
እንደ ምድር ሃመልማል፤ የፈካ ነውና፣
ልቡን ፍቅር ሞላው፤ ደስታውም አበበ፣
ለውዴ ውዱ ነሽ፤ በመልክሽ ተዋበ!

እንደ ከዋክብ ብዙ፤ እንደ ጀምበር ውብ፣
አንድ ሰው እልፍ ነው፤ ከተቸረው ልብ!!
አንድ ሳለሽ ብዝተሽ፤ ሁሉን የሆንሽለት፣
ጤና ይስጥሽ አምላክ፤ ዘላለም ኑሪለት!

እንደ ምድር አሸዋ፤ እንደ አባይ ጅረት፣
አንድ ሰው ብዙ ነው፤ ፍቅር ከሞላበት!
በዝተሽ አበዛሽው፤ በርተሽ አፈካሽው፣
ከፊትም ከኋላም፤ በሁሉም ከበሽው።

#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
MAYA MUZIKA

የፊልም ዳይሬክተር፣ ተዋናይት፣ ፕሮዲዩሰር፣ እስክሪብት ጸሐፊ እና የማያ ፊልም ድርጅት ባለቤት የሆነችው አርቲስት አምለሰት ሙጬ በሙዚቃው ዘርፍ ላይም Executive Producer በመሆን Maya Muzika የሚል ዲጂታል ሚዲያ አቋቁማ ወደ ስራ ገብታለች። በቀጣይነትም በኪነጥበቡ ዘርፍ በፊልም እና በሌሎች የሚዲያ ስርጭቶች ላይ በስፋት ለመሳተፍ ዝግጅቶቿን በማጠናቀቅ ላይ ትገኛለች።

Maya Muzika አዳዲስ ሙዚቃዎችን በማሰራጨት ለአድማጭ ማቅረቡን ጀምሯል።

የMaya Music You Tube Channel Subscribe በማድረግ አዳዲስ ሙዚቃዎችን ያድምጡ።

https://youtube.com/channel/UCwoELuj5NvoHsBV4Q394ASQ
Forwarded from ሰኒ ባህላዊ አልባሳቶች አከፋፋይ
መልካም አዲስ አመት...!
🌼🌼🌼🌼

ሰኒ የአገር ባህል አልባሳት እና ቁሳቁስ አስመጪ!

ከኢትዮጵያ የአገር ባህል አልባሳቶችን እና የኢትዮጵያ ባህላዊ ቁሳቁሶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እናስመጣለን። የፈለጉበት አህጉር ሆነው ይዘዙን...!

የሚፈልጉትን የአገር ባህል ልብስ አልያም ቁስ ፎቶውን በውስጥ መስመር ይላኩልን እኛም ከጥራት ጋ ያሉበት አገር ድረስ በፍጥነት እንልክሎታለን።

በተጨማሪም ካሉበት አገር ሆነው ወደ ኢትዮጵያ ለወዳጅ ዘመድዎ መላክ የሚፈልጉትን ማንኛውንም አይነት እቃ በከተሞች እና ወደ ክፍለ አገሮች በፍጥነት እንልካለን።

እዚህ ይዘዙን👇
@mimiteshager
@seniclothesimporter
ለውዴ ውዱ ነሽ

በጎደለ ሞልተሽ በጠፋው ተክተሽ
ሲዝል አበርትተሽ ግራውን ደግፈሽ
የብቸኝነት ጉዞውን በጥንድ ቀይረሽ
ባብሮነትሽ አጅበሽ፤
ሙሉ አደረግሽው መልኩን አሳቅፈሽ
እራሱን ደግመሽ፣
እራስሽን ደግመሽ።

መኑ ከመ ሄዋን እንደ ሚካኤል እናት፣
መኑ ከመ ሄዋን እንደ የማርያም እናት፣
መኑ ከመ ሄዋን እንደ የማሁስ እናት፣
መኑ ከመ ሄዋን እንደ ዘዳዊት እናት?
ሁሌም አብራው ያለች እየሆነችው ብርታት
ለብላቴናው ክብሩ ለልቡም ዘውድ ናት።

እንደ ግጥሜ ርዕስ እንደ ስንኝ ቋጠሮ
እንደ ጠቢብ ቅኔ እንደ ፀሐይ ኑሮ፤
ልብሽ ብሩህ ነው ዘውትር የሚፈካ
መልክሽ በለስ ነው ውዴ ባንቺ 'ረካ።

የሰጠሽው ፀጋ እንደ ሰማይ መና፤
እንደ ምድር ሃመልማል የፈካ ነውና
ልቡን ፍቅር ሞላው ደስታውም አበበ
ለውዴ ውዱ ነሽ በመልክሽ ተዋበ!

እንደ ከዋክብ ብዙ እንደ ጀምበር ውብ
አንድ ሰው እልፍ ነው ከተቸረው ልብ!!
አንድ ሳለሽ ብዝተሽ ሁሉን የሆንሽለት፤
ጤና ይስጥሽ አምላክ ዘለዓለም ኑሪለት!

እንደ ምድር አሸዋ እንደ አባይ ጅረት
አንድ ሰው ብዙ ነው ፍቅር ከሞላበት
በዝተሽ አበዛሽው በርተሽ አፈካሽው
ከፊትም ከኋላም በሁሉም ከበሽው።

#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/

የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እና የአርቲስት አምለሰት ሙጬ የአብራክ ክፋይ የሆኑት ልጆች 4 ሲሆኑ ሁለት ወንድ እንዲሁም ሁለት ሴቶች ናቸው። ስማቸውም እንደየ የውልደት ቅደም ተከተላቸው፦ ሚካኤል ቴዎድሮስ፣ የማርያም ቴዎድሮስ፣ የማሁስ ቴዎድሮስ እና ዘዳዊት ቴዎድሮስ ይባላሉ።
የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ቦረና ላይ በድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችን ለመደገፍ "127ኛውን የአድዋ የድል በዓልን ለቦረና" በሚል መርህ እየተደረገ ባለው የእርዳታ ማሰባሰቢያ በኩል ለቦረና ወገኖቻችን ይውል ዘንድ የአንድ ሚሊየን ብር ድጋፍ በማድረግ ግንባር ቀደም ሆኗል። ይኼ ተግባር ለድርጅቶችና ለሌሎች አካላቶች ትልቅ የቤት ስራ ጥሎ የሚያልፍ ከመሆኑም በላይ የተጠቀሱትንም ያልተጠቀሱትንም አካሎች የሚያነቃቃ ትልቅ ተግባር መሆኑ ግልጽ ነው።

ሁሌም ለመስጠት የሚጣደፍ እጅ ከአመታቶች በፊት ካቴና ገብቶበት ነበር። ሁሌም ለወገኔ የሚለው ይኽ ሰው ከአመታቶች በፊት ኦሮሞ ጠል ተብሎ ነበር። ዛሬ ግን እሱ ከሁሉ ቀድሞ ለገሰ። ሁሌም ካልሰጠሁ የሚለው ይህ ሰው በሰሜን በደቡብ በምስራቅ በምዕራብ ሰው ተራበ ቢሉት ከኔ ወገን አይደለም ብሎ ዘግይቶ አያውቅም። ስስ ልቡ ለሁሉ እኩል ያዝናል! ለጋስ እጁ ለሁሉ ይዘረጋል።

#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
የቴዲ አፍሮ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ቁርኝት ክፍል (፩)

በኢትዮጵያ እንደ ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ለወገኖቹ የወገነ ፖለቲከኛም ሆነ የኪነጥበብ ሰው የለም። በተለያዩ ወቅቶች ለህዝባቸው ድጋፍ ለመሆን እና በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ያሉ መድሎዎችን ለመቋወም የተነሱ ግለሰቦች እና ተቋሞች በሚደርስባቸው ጫና አልያም በጥቅም የጀመሩትን ሳይጨርሱ የውሃ ሽታ ሆነው ቀርተዋል። ከሀገር ውጪ ይኖሩ የነበሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጓቾችም ሆኑ ጭቁኑን አገዛዝ በመሳሪያም በዲፕሎማሲም እንገረስሳለን ያሉ የግንቦት ሰባት ዋና አመራሮች ሳይቀሩ ትግሉ ተጠናቋል ብለው የገዢው ፓርቲ አገልጋይ ሆነው ህዝባቸውን የራስህ ጉዳይ ካሉት አመታቶች ተቆጠሩ። ቴዲ አፍሮ ግን ያለፉትን 20 አመታቶች ያለማንገራገር ከምስኪን ወገኖቹ ጋ ጸንቶ በመቆሙ ብዙ ከባድ የሆኑ መስዋዕትነቶችን ለብቻው ተጋፍጧል።

ቴዲ አፍሮ በልዩ ሁኔታ በግል ህይወቱ ላይ አልያም በስራዎቹ ዙሪያ የሚፈጠሩ አልመግባባቶችን ተጎድቶም ቢሆን በጊዜ የመቋጨት ልማድ ያለው ብልህ ሰው ነው። በወገኖቹ ላይ የሚደርሱ በመንግስታዊ እና በሌሎች በተደራጁ ቡድኖች የሚደርሱ መድሎዎችን፣ ዘር ተኮር ማፈናቀሎችን፣ ማንነት ላይ ያተኮሩ ጭፍጨፋዎችን፣ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን፣ ህገመንግስታዊ ስህተቶችን ብሎም የመብት ጥሰቶችን በግልጽ እና በቀዳሚነት በመቋወሙ ለአመታቶች ብቻውን ሲጨቆንና ኢፍትሃዊ የሆኑ ድርጊቶች በገዢው ቡድን ሲፈጸሙበት ቆይቷል። ከነዚህም ውስጥ በሀሰት ክስ ለ18 ወራቶች በእስር መቆየት፣ በሀገር ውስጥ የሚደረጉ የኮንሰርት ስራዎቹን ያለበቂ ምክኒያት መከልከል፣ በሚዲያዎች ላይ የኪነጥበብ ስራዎቹ እንዳይተላለፉ ማገድ፣ ከሀገር ለስራ የመውጣት መብቱን በመንፈግ በተደጋጋሚ ከኤርፖርት መመለስ እንዲሁም የአልበም የምረቃ ስነስርዓቱን እንዳይፈጽም ፍቃድ የለህም በሚል አግባባዊ ባልሆነ አካሄድ በዕለቱ (በምረቃው ዕለት) ቦታው ላይ በመገኘት በሀይል መሰረዝና በየመንገዱ እየተከታተሉ ድንገተኛ ፍተሻ ማድረግ ብሎም የስነልቦና ጉዳት ለማድረስ እና ውስጡን ሞቾት እንዲነሳው በማሰብ በሚንቀሳቀስባቸው ስፍራዎች ሁሉ የተለያዩ መከናዎችን በመመደብ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች እንዲከታተሉት ማድረግ እና የመሰሉ መንግስታዊ ውንብድናዎች ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው።

እንደ ሚታወቀው በቴዲ አፍሮ ልክ ግዙፍ ኮንሰርቶችን በኢትዮጵያ ያዘጋጀ አርቲስትም ሆነ መንግስታዊ ተቋም አልያም ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ ፕሮሞተሮች የሉም። የቴዲ አፍሮ ኮንሰርቶች በአገር ቤት በሚዘጋጁበት ወቅት በተለያዩ ዓለማት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ኮንሰርቱን ለመታደም በማሰብ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዛሉ። እንዲሁም ከክፍለ ሀገርም ኮንሰርቱ ወደተዘጋጀበት ከተማ ይጓዛሉ። ይሄ ደግሞ የከተማውን ገበያ የሚያነቃቃ ትልቅ አጋጣሚ ነው። ለምሳሌ ባህርዳር ላይ ተዘጋጅቶ በነበረው ኮንሰርት ላይ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ከመጡ ኢትዮጵያውያን በተጨማሪ ከአዲስ አበባ፣ ከጎንደር፣ ከኦሮሚያ ክልል እንዲሁም ከተለያዩ አከባቢዎች ወደ ከተማዋ በመግባታቸው በከተማዋ የሚገኙ ሆቴሎች በሙሉ አልጋቸው ለተከታታይ ሶስት ቀናት ተይዞ ቆይቷል። የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም በልዩ ሁኔታ ሲንቀሳቀሱ ነበር። የምግብ ሰጪ ድርጅቶችም ከወትሮው በተለየ መልኩ በሰዎች ተሞልተው ነበር። ይኼንን በወቅቱ ቦታው ላይ ተገኝቼ አስተውያለሁ። እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ባዘጋጃቸው መድረኮችም ተመሳሳይ ነገሮች ተፈጥረዋል። ልጁ ለአንድ አዳጊ ሀገር ትልቅ ሀብት ነው። ሆኖም ግን ይኼንን ውድ ሀብት ጨቋኞች አምርረው ተጣሉት። ከነርሱ የሚፈልገው አንዳች ቢኖር ድሃ ወገኖቹን ሠላም ሰጥተው፣ መብታቸውን አክብረው ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንዲያኖሩለት ብቻ ነው።

ቴዲ አፍሮ ሀገር ውስጥ ሊያዘጋጃቸው አስቦ የተሰረዙበት ኮንሰርቶች በቅድሚያ አስፈላጊውን ነገር ሁሉ አሟልቶ ፍቃድ ተሰጥቶት ብዙ ሚሊዮኖችን ወጪ ካደረገባቸው በኋላ በድንገት ከሚመለከተው አካል የሚደረጉ የኮንሰርት ክልከላዎች ቴዲ አፍሮን ምን ያህል እንዳከሰሩት ላሰላ ሰው በግለሰብ ደረጃ ይሄንን ሁሉ ኪሳራ መቋቋም በጣም ከባድ እንደሆነ ይረዳል። ቴዲ አፍሮ ግን በዚህ ሲያማርርና ሲቆጣ ተስተውሎ አያውቅም። ተደጋጋሚ ኪሳራዎች ደርሰውበትም ለህዝቤ ስል ያጣሁን ገንዘብ በካሴት ሽያጭ አገኘዋለሁ ብሎ በማሰብ እንኳን ካሴቱ ላይ የሁለት ብር ጭማሪ አድርጎ አያውቅም። ይልቁንም አንድ ጀማሪ ሙዚቀኛ በሚያከፋፍልበት ዋጋ ነው ስራውን ገበያ ላይ የሚበትነው። እሱማ ቢቻለው ለሁሉ በነጻ ቢያደል ደስታው ነበር። ኮንሰርቶቹንም ስንመለከት ከሱ በታች ተከታይ ያላቸው የሀገራችን ሙዚቀኞች የመግቢያ ዋጋቸውን ለመደበኛ 600 ብር ለVIP ደግሞ እስከ 3000 ብር ድረስ ሲያስከፍሉ አስተውለናል። ቴዲ አፍሮ ግን መደበኛ የመግቢያ ዋጋ 300 ብር የVIP ደግሞ 500 ብር ነበር ትልቁ የትኬት መሸጫ ዋጋው። ይኼም በዛ ብሎ ከአዘጋጆች ጋ ሲከራከር ነበር። ምን ያህል ህዝቡን ቢረዳው እና ቢወደው ነው ኪሱ የሚገባው ብር ሳያጓጓው በጣም እርካሽ በሚባል ዋጋ ያንን የመሰለ የመድረክ ስራን የሚያቀርብልን ብዬ ሳስብ አንዴ ጅማ ለኮንሰርት ሄዶ የተናገራት አንዲት ቃል ትዝ አለችኝ። "በከፈላችሁት ልክ ሳይሆን በምወዳችሁ ልክ ነው የምዘፍንላችሁ" ሲል ሙዚቃውን ሊታደሙ ለመጡ አድናቂዎቹ ተናግሮ ነበር። እውነትም በሚወደን ልክ አዜመልን። በሚወደን ልክ በመከራችን ወቅት ለምን ብሎ ቆመልን። በያንዳዷ የችግራችን ወቅት ፊትአውራሪ ሆነልን። አንደበታችን ተይዞ አቅማችን ተዳክሞ ተስፋ በቆረጥን ጊዜ እሱ ጉልበት ሆነን። ቴዲ አፍሮ ሸክማችንን እንደ ግል ሸክሙ ቆጥሮ ጨቋኞችን ተጋፈጠ።

ክፍል ሁለት ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይለጠፋል

#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
የክብር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እንዲህ ብሎ ነበር።

«የተማረ እንጂ የተባረከ መሪ ከለመንን ቆይተናል። የተማረ ከተገኘማ ጥሩ ነው የተባረከ ይሁን እንጂ። የተባረከ መሪ ግን ከተገኘ በጣም ጥሩ ነው ባይማርም እንኳን።»
ዕለተ ዓርብ፣ ዕለተ ስቅለት፣ መልካሙ ዓርብ

በዚህች ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕፀ መስቀል የተሰቀለባት ዕለት ናትና “ዕለተ ስቅለት”የእግዚአብሔር መልካምነት ለሰው ልጅ ድኅነት በፍቃዱ ራሱን አሳልፎ ለሞት በመስጠቱ የተገለጠባት ናትና “መልካሙ ዓርብ” ይባላል።

ዓርብ ነግህ (ሲነጋ)

በዚህች ዕለት በነጋ ጊዜ የአይሁድ ሊቃነ ካህናት ኢየሱስን ወደ ፍርድ አደባባይ ሊያወጡት፣ ለጲላጦስ አሳልፈው ይሰጡት ዘንድ እንዲሁም በፍርድ አደባባይ ይሰቅሉት ዘንድ የተማከሩበት ዕለት ነው።

“ሲነጋም ጊዜ የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ጌታችን ኢየሱስን ሊገድሉት ተማከሩ፤ አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጰንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት” እንዲል። (ማቴ.፳፯፥፩-፪)

መልካሙ ዐርብ 🙏🙏🙏
#ETHIOPIA ሚያዝያ 7/2009 ዓ.ም

ኢትዮጵያ የተሰኘው የክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ነጠላ ዜማ በህጋዊ የዩትዩብ ቻናሉ ከተለቀቀ ዛሬ ስድስተኛ አመቱን ደፈነ። ይኼ ሙዚቃ ሚያዝያ 7/2009 ዓ.ም ምሽት ላይ ነበር የተለቀቀው። በተለቀቀ በሰዓታት ውስጥ ግን ድፍን አዲስ አበባ ውስጥ ሙዚቃው በመዳረሱ ከተማይቱ አዲስ ዘመንን የምታከብር ያህል በየ ስፍራው እንደ ባህላዊ ዘፈን ይኼ ሙዚቃ በስፋት ሲደመጥ አነጋ።

በዕለቱ በመዲናይቱ የተለያዩ ስፍራዎች እየተዘዋወርኩ ለሊቱን ሙሉ ስሜቱን ለማጣጣም የሞከርኩ ሲሆን በየ ቦታው የሚታየው የህዝቡ ስሜት እጅግ ልዩ ነበር።

ይህ ኢትዮጵያ የተሰኘ ተወዳጅ ሙዚቃ ከተለቀቀ በስድስት አመታት ውስጥ ይሄንን መረጃ እስከ-ለጠፍንበት ሰዓት ድረስ በዩትዩብ ብቻ ሀያ አራት ሚልየን ዘጠኝ መቶ አርባ ሶስት ሺ አንድ መቶ አድማጮችን አግኝቷል። ይኼ ደግሞ በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ያለ ተንቀሳቃሽ ምስል እጀባ ብዙ ተመልካቾችን ያገኘ የመጀመሪያው ነጠላ ዜማ ነው። በተጨማሪም ባለፉት አመታቶች ውስጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ የሙዚቃ ሰንጠረዦች ላይ ክብረ-ወሰኖችን የሰበረ የዓለማችን ተወዳጅ ሙዚቃ ለመሆን በቅቷል።

ይኽ ሙዚቃ በወቅቱ በፈጠረው ትልቅ የሚዲያ ንቅናቄ የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ከወትሮው በተለየ መልኩ ለቴዲ አፍሮ ትልቅ ትኩረት እንዲሰጡት ያስቻለ ከመሆኑም በላይ ዛሬም ድረስ BBC, CNN, Al Jazeera, CGTN Africa, BBC Africa, የቻይናው CC TV እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃኖች ቴዲ አፍሮ በአፍሪካ እና በዓለም ላይ በሚገኙ አድናቂዎቹ ባለው ሰፊ ተቀባይነት ምክኒያት ስለሱ መዘገብ አትራፊ መሆኑን ተረድተው ስለሱ አዳዲስ መረጃዎችን መዘገብ ቀጥለዋል።

@TataAfro_official (ነፃ ብዕር)
2025/06/28 13:18:27
Back to Top
HTML Embed Code: