የአመቱ ምርጥ የመሃይም ንግግር:-

“መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ እስላም ያደርጋል”
አንድ ሰው ስለ ስእል እንዲህ አለ..

“ጌታችን መሰቀሉን በአእምሮዬ ሳስበው በልቤ ላይ እንደተሰቀለ ሆኖ መሳሉ አይቀርም.. በልቤ ላይ እንዲያ መሳሉ ሃጢአት ካልሆነ በዓይኔ ፊትም ተስሎ ማየቴ ሃጢአት ሊሆን አይችልም..”

ማን ቢል ጥሩ ነው ይሄንን..??😭😭

The one and only.. ኧኸ..?? ዶክተር ማርቲን ሉተር ነው.. ይመቸው😁😁 [against the heavenly prophets]
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ኧረ በጌታ አንዷ እህት ምን ብትል..??

“ከቤተሰቡ ያልተላቀቀ ወንድ እንኳን ላገባ አልጠብስም ራሱ”😭😭

እየወጣን ወንድሞች
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ኧረ እቺ ልጅ ማን ናት..??😁😁 በቃ ለፕሮቴስታንት አቃብያነ እምነት እንዲህ ያሉ እህቶቻችን አሉ እኛ ሌላ ነገር እንጀምር ሎል


https://vm.tiktok.com/ZMSPcLc3U/
ኢየሱስ ማን ነው..??

ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው።

- ክርስቶስ ነው ማለት ይጠበቅ የነበረው መሲሕ ነው.. የዳዊት ዘር ነው.. የሁሉ መደምደሚያ ነው።

- ክርስቶስ(መሲሕ) ደግሞ አንድ መልእክተኛ የዳዊት ዘር ብቻ ሳይሆን የአብ የባህሪ ልጁም ነው። ስለዚህም እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነው እንላለን።

ይሄንን የማያምን ዓለምን አያሸንፍም።

“ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?”
[1ኛ ዮሐንስ 5: 5]

@Apostolic_Answers
ጌታችን ኢየሱስ ሆይ..
“እኛ ግን ፈራን በአንተም ታመንን”

[መዝ 56(55):3]

መልካም ውሎ እናንተ የእግዚአብሔር ምርጦች የክርስቶስ ቤተሰቦች

@Apostolic_Answers
የዘይቱኗ እመቤት መነጋገሪያ ሆናለች ደግሞ ሰሞኑንም😁😁

በዘይቱን የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ከ50 ዓመት በፊት አካባቢ እመቤታችን ለ3 ዓመት ሙሉ በተከታታይ መገለጧ እና በቦታው በነበሩ ሙስሊሞችም ጭምር የተመሰከረለት የፈውስ እና ሌሎችም ተአምራት ምናምን መፈጠሩ እጅግ አነጋጋሪ ነው.. በሰዓቱ የነበሩ የዓይን ምስክሮች አሁንም ድረስ አሉ.. እና ሰዎች ከዚህ ነገር 2 ነገሮችን እያስቀመጡ ነው:

1. ክርስትና እውነትና ሕያው መሆኑን አስረጂ ከሆኑ ብዙ ምስክሮች ውስጥ አንዱ መሆን ይችላል ይሄ.. ያው የተገለጠችው የጌታ እናት እንጂ ሙሃመድ አይደለምና.. እና ኤቲስቶችንም አፍ ያስይዛል ተብሎ ይታሰባል..

2. ከክርስትናም ደግሞ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ የጌታ ቤተ ክርስቲያን ለመሆኗ አንዱ ማሳያም ጭምር ነው ይህ የሆነው በግብጽ ቤተ ክርስቲያን ላይ ነውና..(ያው እኛም በግብጽ በኩል ስለሆነ የመጣነው ፍትት በሉ ሎል)

ይህንን ተአምር ካቶሊካውያኑ ሳይቀር ተቀብለውታል በነገራችን ላይ.. ያው መርማሪዎችን ልከው አጣርተው ምናምን ማለተው ነው። እንዲህ ዓይነት የገነነ ተአምር በነገራችን ላይ የትም ያለ አይመስለኝም በካቶሊክም በኢስተርን ኦርቶዶክስም..

@Apostolic_Answers
ቅዱስ ሚካኤል

መልአክ ማለት መልእክተኛ ማለት ነው.. ስለዚህ መላእክት የእግዚአብሔር መልእክተኞች ሲሆኑ እንደሚታወቀው ሥጋ የሌላቸው መናፍስት ናቸው.. ከእነዚህም አንዳንዶች የእግዚአብሔር ዙፋኑ የተባሉ በዚያ ዙሪያ ያሉ ወደ እኛ የማይላኩ አሉ.. አጠቃላይ በጠፈር ላይ ሚሰሩ ይኖራሉ.. ወደ እኛ ደግሞ የሚላኩ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ ሊቃነ መላእክት እና መላእክት አሉ.. ቅዱስ ሚካኤል ያለው ከዚህ ከሦስተኛው ነው።

እነዚህ ወደ እኛ የሚመጡ መላእክት በኑሯችን ውስጥ በድኅነታችን ውስጥ ትልቅ ቦታ አላቸው.. በተለይ ቅዱስ ሚካኤል በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔርን ሕዝብ እስራኤልን ከእግዚአብሔር እየተላከ የሚረዳ መልአክ ነበር.. አሁን ደግሞ በሐዲስ ኪዳን እውነተኛውን የእግዚአብሔር ሕዝብ እኛን ያግዛል.. በሐዲስ ኪዳንም ስለ መላእክት እንዲህ ተብሏልና፡ "ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?"(ዕብ 1፡14)

ይህ ተወዳጅ የጌታ መልአክ አሁንም ያግዘን ዘንድ ጠላቶችንም ይዋጋልን ዘንድ ጸሎታችንንም ያሳርግልን ዘንድ ምንም የማይገባን ዓይነት ሰዎች ስለሆንን እግዚአብሔር በምህረቱ መልአኩን ይላክልን።

@Apostolic_Answers
ቅዱስ ሚካኤል ሁሉም ቦታ ይገኛል..??

ፍጡር ስለሆነ በሁሉ የሞላ አይደለም በሁሉ የሚገኘው ፈጣሪ ብቻ ነው። የሚለው የመጀመሪያው አጭሩ መልሳችን ይሆንና ግን ደግሞ አንድ ነገርን እናስታውስ:

ስእል ላይ እንደምታዩት ሁለት ዓይንና አፍንጫ ከዛም ሁለት እጅና እግር ምናምን የሆነ ልክ እንደኛ አይነት አይደለም። ለሰው ሲገለጥ በዛ መልኩ ሊገለጥ ይችላል እንጂ እርሱ መንፈስ ነው.. እና ምን..??

እናማ ለምሳሌ በአንድ ጊዜ ምን ያህል ቦታን እንደሚያካልል አናውቅም።

ስለዚህም በመንፈሳዊው አለም ብዙ ነገሮችን በእምነት ሆነን እናደርጋለን እነጂ እያንዳንዱን አሰራር እንወቅ አንልም

@Apostolic_Answers
ችግራችንን ካላወቅነው መፍትሄ አናገኝም..

ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር እንደራቅንና ወንጌልም መዳረስ ባለበት ልክ ለራሳችንም እንዳልተዳረሰ እኮ ማንም መጥቶ ሊነግረን አያስፈልገንም በቃ በግልጽ የሚታይ ነው.. መሠረታዊውን ትምህርት የሚያውቅ ምን ያህል ሰው ነው..?? የንስሐ አባት ይዞ በንስሐ የሚመላለስ ምን ያህል ሰው ነው..?? ከቅዱስ ምስጢር የሚካፈል ምን ያህል ሰው ነው..?? ጌታ ኢየሱስን ከልቡ እንደው የሚወደውና የሚታዘዘው ምን ያህል ሰው ነው..??

“ሚካኤል ሲባል ይደምቃል ኢየሱስ ሲባል ከሚደምቀው ይልቅ” የሚለውን ክርክር ትተነው በቃ ራሳችን ላይ እንስራ.. ያሉብንን ድክመቶች መካድ ማለት ድክመቶችን ላለመቅረፍ ወስኖ እንደመቀመጥ ነው.. እና ሁሉም በየቤቱም በየሚዲያውም እንደተሰጠው መጠን ሥራ መስራት ነው ያለበት.. ከዛ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ሚገርም ለውጥ እናመጣለን ራሳችን ላይ.. የማያከራክር ነገር አያከራክረን😁😁 መፍትሄው ላይ እናተኩር

@Apostolic_Answers
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል:

“እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።”
[ዮሐንስ 14: 28]

2 ነጥቦችን እናስቀምጥ

1️⃣ ጌታችን ኢየሱስ እኔ ወደ አብ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ አለ.. የምር ግን ጌታ ወደ አብ ሄደ..?? በሚገባ ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ በሥጋ በክብር አረገ በአባቱ ቀኝም ተቀመጠ.. ስለዚህም ቃሉን ጠብቋል.. እንዳለውም ወደ አባቱ ሄዷል..

ይህንን ቃሉን ከጠበቀ ደግሞ ቀጣይ የተናገረውንም እንደሚፈጽም እርግጠኞች ነን ይህም “ወደ እናንተም እመጣለሁ” ያለውን ነው.. ጌታ ኢየሱስ መሄድ ብቻ ሳይሆን ተመልሶም ደግሞ ይመጣል.. ከዛም ይወስደንና ሁል ጊዜ ከእርሱ ጋር እንኖራለን: “ስለዚህ እርስ በእርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ”(1ተሰ 4:17)

2️⃣”ከእኔ አብ ይበልጣል” አለ.. ለዚህ ብዙ ማብራሪያዎች ይሰጣሉ.. ጌታችን አምላክ እንደመሆኑ ከአብ በባህሪው በምንም ባያንስም ሰው እንደመሆኑ ግን ምንም እንኳን አምላክነቱን ባያጎድለውም ህልውናው የጀመረ ወይም የተፈጠረ ሥጋን ነው የተዋሐደውና ሲሞትም ሲደክምም ሲራብ ሲጠማም በዚሁ በሥጋው ነውና ይህ ነገር በአብ ዘንድ ስለሌለ እሱን ለማስረዳት ነው ተብሎ ይፈታል.. ሌሎች ማብራሪያዎችም አሉት ይህ ይበቃል ለጊዜው..

መልካም የጌታ ቀን

@Apostolic_Answers
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ይቅርታ ጋይስ እቺን ማሳወቅ ስላለብኝ ነው ስለሌሎችም መምህራን ሲባል..

አንዳንድ ሰዎች “እንደው እነ አክሊል ማይሆን ርእስ እንዲያነሱ ከጀርባ ሆነው ቀጥሉበት እያሉ የሚደግፏቸው መምህራን አሉ” እያሉ ነው.. እኔ እነዚህ በጥላቻ ያበዱ ሰዎች ምን እንደሚሻላቸው አላውቅም.. በጌታ ፊት ሆኜ የምነግራችሁ አንድም የሚታወቅ መምህር እንዲህ አድርጎ የሚያውቅ የለም.. እሱን ተዉትና በግሌ እኔን አክሊልን በቋሚነት የሚያወራኝም አንድም መምህር የለም..

አንዳንዴ “ከጀርባቸው ያሉት ተሐድሶዎች ናቸው” ይላሉ😁😁 አሁን ደግሞ የሆኑ መምህራን ናቸው ማለት ጀመሩ.. ያው ያልተመቻቸው መምህር ካለ በዚህ እያስመሰሉ ለመቀጥቀጥ ማለት ነው.. እኔ አንዳንዴ ክርስቲያን መሆናቸውንም እጠራጠራለሁ..

አውቃለሁ አንዳንድ በማነሳቸው አሳቦች ብዙ ሰዎች ከአጠገቤ ይርቃሉ እና ተቃዋሚም ይበዛል.. እውነቱን ለመናገር ሁሉንም የሚያስደስት ነገር ብቻ ማውራት ለኔ ቀላል ነው.. ከዛም የሃገር ወዳጆችም ይኖሩኛል ሁሉም በዙሪያዬ ይሆናል😁😁 ግን ለዚህ አልተጠራሁም.. ብዙዎቻችሁ ርቃችሁኝ(ያው ምንም ስለማትጎዱ) የተወሰኑ ነፍሳት ግን ጥያቄያቸው ተቀርፎ ወደ ቤተ ክርስቲያን ቢመለሱ ነው ፍላጎቴ.. ለማንኛውም እናንተንም ላለማስጨነቅ ለጊዜው ምንም አልልም..

የጌታ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን
“…በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
[ሮሜ 12: 2]

መታደስ..?? አዎን አሁን የሚያስፈልገን መታደስ የልብ ነው.. የሕይወት መታደስ.. እግዚአብሔርን ወደ መምሰል መታደስ እንጂ የሃይማኖት መታደስ አያስፈልገንም.. ከዚህ ቀደም እንዳልነውም ሰው ወደ ክርስትና የማይመጣው አንድም የኛን ያልታደሰ ሕይወት እያየ ነው.. የክርስቲያን መታወቂያው ክርስቶስን መምሰል እንጂ ስለ ስለ ክርስቶስ ማውራት ብቻ አይደለም።

ስለዚህም ከመዝሙረኛው ጋር ሆነን አምላካችንን እንዲህ እንበለው:

“አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥
የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።”
[መዝ 50(51): 10]

@Apostolic_Answers
በነገራችን ላይ ሕዝብ እኮ በጣም ትልቅ ሃብት ነው.. አስባችሁታል ኢትዮጵያ ውስጥ ይህንን ሁሉ በተለያዩ የሥራ ድርሻ ውስጥ ያሉ ክርስቲያኖችን ቤተ ክርስቲያኒቱ በተገባ መልኩ ይዛው ቢሆንና አንድነቱ ቢኖር ኖሮ..??

ምንም እንኳን የቤተ ክርስቲያን ሃብቷ ኢየሱስ ቢሆንም ምድር ላይ ላለው አሠራር ግን እመኑኝ በሁሉም መልካም ነገሮች እንደ ቤተ ክርስቲያን ጠንካራ መሆን የሚችልም አይኖርም ነበር።

@Apostolic_Answers
ምናልባት ለ1 ሰው ከጠቀመ..

ወደ እግዚአብሔር መመለስ እየፈለግሁ ከኃጢአት ግን መላቀቅ አልቻልኩም..??

ሃጢአተኝነትን እና ዓለማዊነትን የሚስክደው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው.. ጸጋውን ደግሞ በቅዱሳት ምስጢራት በኩል እንካፈላለን.. ታድያ ወደ ቅዱስ ምስጢር ሳንቀርብ እንዴት ሃይልን እናግኝ..??

@Apostolic_Answers
“ኧረ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል ፈራለሁ”

እና ምን ተሻለ..??

“በቃ ስለምፈራ አልቆርብም”

ይሄ የተቀደሰ ፍራቻ ሳይሆን ገዳይ ፍራቻ ነው.. በጣም የሚያስፈራው እንደውም አለመቀበል ነው.. የተቀደሰው ፍራቻ ግን ቅዱስ ቁርባንን በፍርሃትና በክብር በእምነት ሆነን እንድንቀበል የሚያደርገን ነው.. ንስሐ እንግባ ከቅዱስ ምስጢር እንካፈል..

እና አንዱ አድሚናችን ግሩፕ ላይ እንዲህ አለኝ:- “ቅዱስ ቁርባን መቀበልን የምንፈራውን ያህል እግዚአብሔርን ብንፈራ ኖሮ ፣ ሁልጊዜም እንቆርብ ነበር !"

@Apostolic_Answers
እኔኮ ሚገርመኝ ምእመናን😁😁

በአንዳንድ ምክንያቶች ሰይጣንን የሆነ ጭራቅ ሚያስፈራ ምናምን ነገር አድርገን እንስለውና ከዛ ሚያስፈራንም እንደዚህ ዓይነት ነገር እንዳይገለጥብን ነው ሎል..

የሚያስገርመው ግን እኛ እዛ ጋር ስንጠብቀው እሱ(ሰይጣን) ግን ለዓይናችን ምቹ ሆኖ ለሥጋችንም የተወደደ መስሎ ብርሃን መስሎ እየሸወደን ነው መሰል..

@Apostolic_Answers
2025/06/27 18:39:14
Back to Top
HTML Embed Code: