Telegram Web Link
#AAU

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ የተማሪዎች ምርቃት ስነ-ስርዓት እና የተቋሙን የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም ያከብራል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በዕለቱ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማሯቸውን 75ኛ ባች ተማሪዎች ያስመርቃል።

ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 75 ዓመታት በትምህርት ልህቀት፣ በአመራር ልማት እንዲሁም በሀገር ግንባታ ያደረገው ዘላቂ እና ዘርፈ ብዙ አበርክቶ ይዘከራል ተብሏል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከ75 ዓመታት በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በመባል ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ፤ የፈጠራ፣ ምርምር እና የዕውቀት መፍለቂያ በመሆን በርካታ መሪዎች፣ ባለሙያዎች እና ምሁራንን አፍርቷል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ነባር የክረምት ተማሪዎች የ2017 የትምህርት ዘመን የምዝገባ ጊዜ ከሐምሌ 14-16/2017 ዓ.ም ስለሆነ በተጠቀሱት ቀናት ውስጥ በመገኘት በዩኒቨርስቲዉ ሬጅስትራር ጽ/ቤት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ (ዩንቨርሲቲው)

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በነዳጅ እጥረት ምክንያት በክልሉ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን ወደ ፈተና ማዕከላት ማጓጓዝ መቸገሩን አሳወቀ፡፡

ቢሮው ትናንት ሰኔ 19/2017 ዓ.ም ለትምህርት ሚኒስቴር እና ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በጻፈው ደብዳቤ እንዳለው፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች በሚገኙ 247 የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ36 ሺህ በላይ ተማሪዎች ከቀናት በኋላ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ መዘጋጀታቸውን ገልጿል፡፡

ተፈታኞቹን ወደ ሰባት የፈተና ማዕከላት ለማጓጓዝ እና ከፈተናው በኃላ ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ የትራንስፖርት ወጪ ባለው መደበኛ ታሪፍ ተሰልቶ ወደ እያንዳንዱ ወረዳ የተላከ ቢሆንም፤ አሁን በክልሉ ባለው የነዳጅ እጥረት ምክንያት ተማሪዎቹን ወደ ፈተና ማዕከላት ማጓጓዝ አለመቻሉን ቢሮ አስረድቷል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ያወጣው መርሐግብር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ሰኔ 21 እና 22/2017 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች (የፈተና ማዕከላት) እንደሚገቡ ያሳያል፡፡

"ተማሪዎቹ በተረጋጋ ሁኔታ ፈተናቸውን ወስድው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ፥ ትምህርት ሚኒስቴር እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት ጋር በመሆን ነዳጅ ወደ ትግራይ እንዲገባ በማድረግ ችግሩን እንዲፈታልን" ሲል ቢሮው ጠይቋል፡፡

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
💡Big ideas start small. Like Bill Gates, you can build the next big thing. Ready?

Apply here 👉 https://www.tg-me.com/Founderacademyapplicationguide
ውድ ደንበኞቻችን ከዚህ በታቹ ካሉት website ላይ ማዘዝ የምትፈልጉትን ማንኛውንም እቃ photo  screenshots በinbox  ይላኩልን 

👨‍💻   Amazon.ae
👨‍💻    Shein.com
👨‍💻    Zara.com
👨‍💻   Noon.com
👨‍💻   Sephora.com

በ 7 ቀን ውስጥ ያሉበት ቦታ ድረስ በነፃ እናደርሳለን

📞0946362749( @eden16mg)

join our telegram channel 🫴🫴

https://www.tg-me.com/edmart24
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም በኦላይን ፈተና መስጫ ጣቢያ በሚሰጠው የፈተና ገለጻ/Orientation/ ላይ መገኘት እንደሚገባቸው ተገለጸ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በኦላይን ለመስጠት በቂ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በከተማ አስተዳደሩ የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በኦላይን ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸዉን እንዲሁም ፈተናው ከሰኞ ጀምሮ እንደሚሰጥ የገለጹ ሲሆን ተማሪዎች በፈተና መስጫ ጣቢያዎች በወጣው መርሀ ግብር መሰረት በመገኘት ፈተናዉን ሊወስዱ ይገባል ብለዋል፡፡

አቶ ዲናኦል አክለዉም የፈተና አሰጣጡን አስመልክቶ ገለጻ በፈተና ጣቢያዎች የሚሰጥ መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ፣ የሁለተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ፣ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ29/10/2017 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ፣ የሁለተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ29/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 በኦላይን ፈተና መስጫ ጣቢያዎች በመገኘት የሚሰጠውን የፈተና ገለጻ/Orientation/ መከታተልና የመፈተኛ ቦታቸዉንና ክፍላቸዉን ማየት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ።

በቢሮው የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ታገሰ ለፋና ዲጂታል እንደገለጹት፤ ዘንድሮ 35 ሺህ 246 የክልሉ ተማሪዎች ሀገር አቀፉን የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ።

ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች ወደ ተዘጋጁ የፈተና ማዕከላት መግባት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ለ35 ሺህ 246 ተማሪዎች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለመስጠት የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

በበይነ መረብ ፈተና ለሚወስዱ 7 ሺህ 211 ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲዎች እና በአዳሪ ትምህርት ቤቶች ዘጠኝ ማዕከላት መዘጋጀታቸውን ገልጸው፤ ተማሪዎቹ ስለ ፈተና አሰጣጡ ስልጠና ማግኘታቸውን አስታውሰዋል።

በወረቀት የሚፈተኑ 28 ሺህ 35 ተማሪዎች ደግሞ በአቅራቢያቸው በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ልምምድ አድርገዋል ብለዋል።

በወረቀት የሚፈተኑ ሁሉም ተማሪዎች ፈተውን የሚወስዱት በዩኒቨርሲቲዎች ብቻ መሆኑንም አመላክተዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በአዲስ አበባ የ28 ትምህርት ቤቶች እውቅና ለምን ተሰረዘ?

በየሁለት ዓመቱ በሚደረገዉ የእዉቀና እድሳት ከደረጃ በታች ሆነው የተገኙ 28 ትምህርት ቤቶች እዉቅና መሰረዙን፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሥራ አስኪያጅ ኢዘዲን ሙስባህ ገለፁ።

ከደረጃ በታች በሆኑ ትምህርት ቤቶች ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ስለማይሰጥ እና ትወልድን አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ፤ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም፤ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው ባለመሻሻሉ ብሎም ዝቅተኛ እና ከደረጃ በታች በመሆኑ እውቅናቸው ተሰርዟልም ነው ያሉት።

ወላጆች ይህን በመገንዘብ ልጆቻቸዉን በሌሎች ትምሀርት ቤት እንዲያስመዘግቡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር አሳውቋልም ብለዋል።

የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል እና የትምህርት ጥራት ችግሮችን መቅረፍ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ75ኛ ጊዜ ተማሪዎቹን ዛሬ ያስመርቃል


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን ተመራቂዎች ለ75ኛ ጊዜ ያስመርቃል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮች፣ የተመራቂ ቤተሰቦች እና የክብር እንግዶች እንደሚገኙ ከወጣው መርሐ-ግብር ለመረዳታ ተችሏል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት 3334 የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 2859 የሁለተኛ ዲግሪ፣ 304 የሦስተኛ ዲግሪ እና 352 የስፕሻሊቲ እና ሰብ-ስፔሻሊቲ በአጠቃላይ 6849 ተማሪዎችን ያስመርቃል፡፡

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ይጀምራል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
2025/06/30 08:24:11
Back to Top
HTML Embed Code: