Telegram Web Link
#SamaraUniversity

በ2018 ዓ.ም ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት አዲስ ግቢ ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 19 እስከ 20/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ስምንት 3x4 መጠን የሆኑ ፎቶግራፎች፣
➫ ብሔራዊ የፋይዳ መታወቂያ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣
➫ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

በ2018 ዓ.ም በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ ለምትመደቡ ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ ይደረጋል ተብሏል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በኢትዮጵያና በቻይና መንግስታት መካከል በትምህርት መስክ ያለው የትብብር ግንኙነት እየተጠናከረ መምጣቱ ተገለጸ፤
ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ ከቻይናዋ ሻንዢ ግዛት ምክትል ገዢ ዋንግ ዢአዎ የተመራ ልዑካን ቡድን ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ የትብብር ግንኙነት መኖሩን ጠቅሰዋል፡፡

በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የትብብር ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ወደ ስትራጂካው አጋርነት መሸጋገሩንም ክቡር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል፡፡

የቻይና የስልጣኔ ማዕከል የሆነችው የሻንዢ ግዛት ከኢትዮጵያ ጋር በባቡር ፣ በቴክኒክና ሙያ እና በሌሎችም መስኮች የትብብር ግንኙነት እንዳላትና ትምህርት ሚኒስቴር ከግዛቲቱ ጋር ያለውን ትብብር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍም ማጠናከር እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን መከታተል ይችላሉ።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#JinkaUniversity

በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት አዲስ ግቢ ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 18 እና 19/2018 ዓ.ም  መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3x4 መጠን የሆኑ ፎቶግራፎች፣
➫ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#MattuUniversity

በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት አዲስ ገቢ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በመቱ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ
➫ በ2018 ዓ.ም መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
➫ በ2017 ዓ.ም በመቱ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት የተከታትላችሁና ያለፋችሁ በበደሌ ካምፓስ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3x4 መጠን የሆኑ ፎቶግራፎች፣
➫ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በኒውክሊየር ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በኒውክሊየር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት እየሰጠ እንደሚገኝ ያስታወሱት ተቋሙ ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር)፤ በመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን ለመቀበል የተለያዩ ዝግጅቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን ገልፀዋል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት ትምህርቱን ለመስጠት የሚያስችሉ የህንጻ እና የላብራቶሪ ግንባታ እንዲሁም የመምህራን ስልጠና ሲደረግ መቆየቱን ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል፡፡

በተመሳሳይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በኒውክሊየር ሳይንስ በሁለተኛ ዲግሪ ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎችን በተያዘው ዓመት ለመጀመርያ ጊዜ እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡

መንግሥት የኒውክለር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ መንገድ ለመጠቀም የሚደረግን ጥረት የመምራትና የማስተባበር ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሙ ይታወቃል፡፡

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለዘርፉ የሚያስፈልገውን የሰው ኃይል ለማፍራት እንደሚሠሩ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል ይሸፍናል፡፡ - MOE

ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተመለከት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ደብዳቤ ልኳል፡፡

በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ሥራ አስፈጻማ ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ (ዶ/ር) የተፈረመው ደብዳቤው፤ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል እንደሚሸፍንና ተማሪዎች የተማሩትን ይዘቶች የሚፈተኑ መሆኑን ይገልጻል፡፡

ብሔራዊ ፈተናው ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ይዘቶችን መሠረት ያደረገ እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትምህርት ቤቶች 9ኛ ክፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት፤ ሌሎቹ ደግሞ በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት የተማሩ በመሆኑ ፈተናው ከሁለቱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ የሆኑ ይዘቶች ተጣጥሞ የሚወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትግበራ በማካሔድ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱ ይታወቃል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#National_ID

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል።

" ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል።

" ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል።

ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#National_ID

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#ቴምርፕሮፐርቲስ

⩩ 100% ለሚከፍሉ ከ30% እስከ 35% የሚደርስ ታላቅ እውነተኛ ቅናሽ አዘጋጅተናል።
⩩ እንዲሁም 40% ለሚከፍሉ፣ ከከፈሉት ላይ የ20% ቅናሽ አዘጋጅተናል።

📍 ሊሴ ገ/ማርያም

ባለ 1 መኝታ
👉 66 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 7,590,000
                 ቅድመ ክፍያ = 10% (759,000)
👉 71 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 8,165,000
                 ቅድመ ክፍያ = 10% (816,500)

ባለ 2 መኝታ
👉 78 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 8,970,000
                 ቅድመ ክፍያ = 10% (897,000)
👉 99ካሬ ሙሉ ክፍያ = 11,385,000
                ቅድመ ክፍያ = 10% (1,138,500)

ባለ 3 መኝታ
👉 132 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 14,520,000
                   ቅድመ ክፍያ 10% (1,452,000)
👉 146 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 16,060,000
                   ቅድመ ክፍያ = 10% (1,606,000)

📍 አያት (ፈረስ ቤት)

ባለ 2 መኝታ
👉 88 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 8,360,000
                 ቅድመ ክፍያ = 10% (836,000)

ባለ 3 መኝታ
👉 108 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 10,260,000
                   ቅድመ ክፍያ = 10% (1,026,000)
👉 121 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 11,495,000
                   ቅድመ ክፍያ = 10% (1,149,500)
👉 137 ካሬ ሙሉ ክፍያ = 15,070,000
                   ቅድመ ክፍያ = 10% (1,570,000)

📍 ተክለሐይማኖት (ሱማሌ ተራ)

ባለ 3መኝታ
👉 110ካሬ ሙሉ ክፍያ = 12,100,000ብር
                  ቅድመ ክፍያ = 10% (1,210,000) ብር

📍ሀይሌ ጋርመንት
ባለ 3መኝታ
👉 139ካሬ ሙሉ ክፋያ =14,595,000 ብር
           ቅድመ ክፋያ 10%= (1,459,500ብር)

⩩ ቀሪውን 90%፤ በግንባታ ሂደት፤ ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ፤ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት።

ለበለጠ መረጃ ይደውሉልን!
+251936650128
+251994495655
#EthiopianDefenceUniversity

የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁና በ2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታችሁን ለመከታተል የምትፈልጉ አመልካቾች የምዝገባ ቀናት ጥቅምት 13 እና 14/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

የምዝገባ ቦታ፦
ቢሾፍቱ በሚገኘው የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ ሬጅስትራር ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 19

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦

➫ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ኮፒ፣
➫ የመጀመሪያ ዲግሪ ዋናውና ኮፒው፣
➫ Student Copy ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከተማሩበት የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ኦፊሺያል ትራንስክሪፕት

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
ATC NEWS
#MattuUniversity በ2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት አዲስ ገቢ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በመቱ ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥቅምት 17 እና 18/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ ➫ በ2018 ዓ.ም መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ…
#MattuUniversity #ማስተካኪያ

የምዝገባ ቦታ

➫ በ2018 ዓ.ም መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት መደበኛ ተማሪዎች በዋናው ግቢ

➫ በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በመቱ ዩኒቨርሲቲ በደሌ ካምፓስ የተከታትላችሁና ያለፋችሁ በበደሌ ካምፓስ ፤ በመቱ ካምፓስ የተከታተላችሁና ያለፋችሁ በመቱ ካምፓስ

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#Update

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል።

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡ 

1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ

ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ኬሚስትሪ፣
- ፊዝክስና ባዮሎጂ

ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ታሪክ፣
- ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።

2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡

3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
2025/10/23 09:22:21
Back to Top
HTML Embed Code: