Telegram Web Link
37 A+ ያሳካችው ተመራቂ

ፈቲሃ አህመድ ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በዛሬው ዕለት ተመርቃለች።

ከአጠቃላይ ተመራቂዎች አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 4.00 እና 37A+ በማምጣት የሁለት ዋንጫዎች ተሸላሚ ሆናለች።

የ2017 ዓ.ም የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ውጤት ተሸላሚዋ ፈቲሃ፤ ይህን ውጤት ለማሳካት ከቤተሰቦቿ ጀምሮ ብዙ ዋጋ እንደተከፈለቀት ገልጻለች። እንደሷ ያሉ እህቶቿ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ምክሯን ለግሳለች።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#WallagaUniversity

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በጊምቢ እና በሻምቡ ካምፓሶች ያስተማራቸውን ከ500 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው ጊምቢ ካምፓስ 360 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና ስድስት ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ በአጠቃላይ 336 ተማሪዎችን አስመርቋል።

በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ሻምቡ ካምፓስ 170 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ፣ ስምንት ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም አንድ ተማሪ በሦስተኛ ዲግሪ በአጠቃላይ 179 ተማሪዎችን አስመርቋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#ማትሪክ_ደርሷል!
አትጨነቁ!
ለዝግጅታችሁ አሪፍ መፍትሄ እኛ ጋር አለ!

#ESSLCE_With_Model_Exams: ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም የማትሪክ ፈተና ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸውና ሙሉ ማብራርያ፣

#Concise_Summary_With_Model_Exams: ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ያሉትን ትምህርቶች አጫጭር ማስታወሻዎች፣

#Ethiopian_New_Curriculum_All_Subjects: በከፍተኛ ጥራት የተቀረጹ  ቪዲዮዎች፣ Virtual Labs  ፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ(AI) የታገዙ ትምህርቶች፣ እና እየተዝናኑ የሚማሩበትን ጌሞችን ያካተተ።

#Short_Notes: ለእያንዳንዱ ትምህርት  ዋና ነጥቦችን አጠቃሎ የያዘ

ይፍጠኑ ይህ እድል እንዳያልጥዎ
www.selectacademy.edu.et በመመዝገብ ዝግጅቶን አሁኑኑ ይጀምሩ።
መልካም እድል ለመላው ተፈታኞች

ለበለጠ መረጃ
+251 926 913 404 | 9521

Join Our Telegram

@Select_Academy
💡Big ideas start small. Like Bill Gates, you can build the next big thing. Ready?

Apply here 👉 https://www.tg-me.com/Founderacademyapplicationguide
ከትምህርት ገበታ ውጪ የነበሩ 300 ተማሪዎችን ሰብስበው የሚያስተምሩት በጎ አደራጊ
*********

አቶ አያሌው ታደሰ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው። ከ20 ዓመታት በፊት የበርካታ ልጆችን ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆን በመመልከታቸው የጀመሩት የበጎ አድራጎት ሥራ ዛሬ የ300 ተማሪዎችን ሙሉ ወጪ ሸፍነው ለማስተማር በቅቷል።

መነሻቸው በሐዋሳ የፍቅር ሀይቅ ዙሪያ ብዙ ልጆች በትምህርት ሰዓት ሜዳ ላይ ኳስ ሲጫወቱ ወይም ያለምንም ተግባር መመልከታቸው እንደሆነ የሚናገሩት አቶ አያሌው፤ ለምን ትምህርት ገበታ ላይ እንዳልተገኙ ልጆቹን ቀርበው እንዳናገሯቸውም ይገልፃሉ።

በጊዜው ከልጆቹ ምላሽ የሚያስተምራቸው አካል ማጣታቸውን የተረዱት አቶ አያሌው፤ ይህን ለመቀየር ውስጣቸው መነሳሳቱን እን ወደ ሥራው መግባታችውን ይገልጻሉ።

ሲመሰረት በ26 ተማሪዎች በሀዋሳ ዙሪያ ሎቄ አከባቢ የተከፈተው ት/ቤት በአሁን ወቅት 300 የሚደርሱ ልጆችን ሙሉ ወጪ በመሸፈን ያስተምራል።

ትምህርት ቤቱ የራሱ የምገባ መርሐ ግብር ያለው መሆኑንም አቶ አያሌው ተናግረዋል።

በአንድ ክፍል ውስጥ የሚማሩት ተማሪዎች ቁጥር 22 መሆኑን ጠቅሰው፤ ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ለመስጠት አስፈላጊ የሆኑ መሳሪያዎችን ያሟላ መሆኑንም አብራርተዋል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
#AksumUniversity
#ClassOf2025
#CommencementPhotos

‎አክሱም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 1155 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ 191 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

‎በዩኒቨርሲቲው የኢሌክትሪካልና ኮምፕዩተር ምህንድስና ፋካሊቲ ተማሪ የሆነው አክሊሉ አብርሃ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.96 በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ተማሪ የሆነችው ይብራለም ተኽላይ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.95 በማምጣት ከሴቶች ከፍተኛውን ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ አፈርን የሚያክምና ከፍተኛ ምርት መስጠት የሚችል የተፈጥሮ ማዳበሪያ እየመረትኩ ነው አለ።

ዩኒቨርሲቲው የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችለውንና የማምረት አቅሙ ከፍተኛ የሆነውን 'ኢሴኒያ ፈቲዳ' የተባለ ቨርም ዝርያ በመጠቀም የተፈጥሮ ማዳበሪያን በብዛት እያመረተ እንደሆነ ገልጿል፡፡

የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፈዬራ ዲንሳ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው ሰው ሰራሽ ማዳበሪያን ለመተካት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡

የተፈጥሮ ማዳበሪያ ምርቱን ወደ ሕብረተሰቡ ለማዳረስ ከአርሶ አደሩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲው የተፈጥሮ ሀብትና አካባቢ ጥበቃ ትምህርት ክፍል ተመራማሪና መምህር ታደሰ ግርማ በበኩላቸው÷ በጥናትና ምርምሮች በመታገዝ የተመረተው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለማህበረሰብ አገልግሎት እየቀረበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ተመራማሪው እንደገለጹት፥ በዚህ መልክ የሚዘጋጀው ማዳበሪያ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን በአፈር ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሊቆይ የምችል ነው።

በማዕከሉ የምርምር ስራዎችን በማከናወን፣ በማምረትና በማስተማር ለማህበረሰብ አገልግሎት እያዋልን እንገኛለን ነው ያሉት፡፡

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ አርሶ አደሮችም በማዕከሉ ሰልጥነው የተፈጥሮ ማዳበሪያውን በራሳቸው ማዘጋጀት መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ውጤቱም እያደር የሚታይ እንጂ የሚቋረጥ አለመሆኑን የገለጹት አርሶ አደሮቹ÷ የተፈጥሮ ማዳበሪያው ከሰው ሰራሽ ማዳበሪያ የበለጠ ምርታማ እንደሆነ አይተናል ብለዋል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
በአዲስ አበባ የሚገኙ 73 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ መረጃ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ይፋ ይሆናል አለ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን።

የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቢኒያም ኤሮ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ በሀገሪቱ የሚገኙ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።

ከ375 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ 85ቱ አስፈላጊውን መስፈርት ባለማሟላት ከትምህርት ሥርዓት ራሳቸውን በማግለል ተማሪዎቻቸውንና የተማሪዎችን ማስረጃ ስራ ላይ ለሚገኙ ተቋማት እያስተላለፉ ነው ብለዋል።

አብዛኛዎቹ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም ከህንጻ፣ ከመምህራን ሁኔታ፣ ከአጠቃላይ የትምህርት መሰረተ ልማት እና ከሰው ኃይል አንጻር ከፍተኛ ክፍተት እንዳለባቸው አንስተዋል።

ባለስልጣኑ ያወጣውን መስፈርት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙሉ በሙሉ እንደማያሟሉ ገልጸው÷ ተቋማቱን እየደገፍንና እያበቃን እንሄዳለን ነው ያሉት።

መንግስት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከትምህርት ሥርዓቱ የማስወጣት ፍላጎት እንደሌለው እና በማብቃት እውቅና እንዲያገኙ እንደሚሰራ እንዲሁም ከስራው የወጡት መስፈርቱን ሲያሟሉ በድጋሚ መመለስ እንደሚችሉ አስረድተዋል።

ተቋማቱ 50 በመቶ የዳግም ምዝገባ መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚጠበቅባቸው አስታውሰው÷ አሁን ላይ በመዲናዋ የሚገኙ 73 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የዳግም ምዝገባ መረጃ እስከተያዘው ወር መጨረሻ ድረስ ይፋ እንደሚሆንም ነው የተናገሩት።

በዳግም ምዝገባው የሚቀጥሉና የማይቀጥሉ ተቋማት መረጃ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ እና በክልሎች የተጀመረው የዳግም ምዝገባ ስራም በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://www.tg-me.com/atc_news
2025/06/27 21:25:00
Back to Top
HTML Embed Code: