#የሕፃኑን_ሕይወት_እንታደግ
ሕፃን ተመስገን ደስታው ይባላል የ13 ዓመት ልጅ ሲሆን የሚተዳደረዉ ሱቅ በደረቴ በመሥራትና ማደሪያዉን ዘበኛ ጋር አድርጎ ነበር። እናትና አባቱ ላልይበላ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ሁለቱም በሽተኞች በመሆናቸዉ ከሚያገኘዉ ገንዘብ በመቆጠብ በመጠኑ ይረዳቸዉ ነበር። ነገር ግን አሁን ላይ ከፍተኛ የደም ማነስ ተብሎ የሰዉ ደም ቢወስድም በአፉና በአፍንጫዉ ደም እየፈሰሰ ስላስቸገረው ከወልድያ ሆስፒታል ወደ ደሴ ሆስፒታል ከዚያም ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሄዶ እንዲታከም ሪፈር የተፃፈለት ሲሆን፤ ይህን ህጻን የሚያሳክመው አቅም ያለው ቤተሰብ ባለመኖሩ በበጎ አድራጊዎች እርዳታ አዲስ አበባ ቢሄድም የህክምና ዉጤቱ የደም ካንሰር ያሳያል ስለተባለና ህክምናዉም ለረዝም ጊዜ የሚቆይ ስለሆነ የምትችሉትን እንድትረዱት ስንል በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ባህሩ ዋሴ ➛ 1000327114895
ለበለጠ መረጃ ➛ 0975121276
ሕፃን ተመስገን ደስታው ይባላል የ13 ዓመት ልጅ ሲሆን የሚተዳደረዉ ሱቅ በደረቴ በመሥራትና ማደሪያዉን ዘበኛ ጋር አድርጎ ነበር። እናትና አባቱ ላልይበላ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ሁለቱም በሽተኞች በመሆናቸዉ ከሚያገኘዉ ገንዘብ በመቆጠብ በመጠኑ ይረዳቸዉ ነበር። ነገር ግን አሁን ላይ ከፍተኛ የደም ማነስ ተብሎ የሰዉ ደም ቢወስድም በአፉና በአፍንጫዉ ደም እየፈሰሰ ስላስቸገረው ከወልድያ ሆስፒታል ወደ ደሴ ሆስፒታል ከዚያም ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሄዶ እንዲታከም ሪፈር የተፃፈለት ሲሆን፤ ይህን ህጻን የሚያሳክመው አቅም ያለው ቤተሰብ ባለመኖሩ በበጎ አድራጊዎች እርዳታ አዲስ አበባ ቢሄድም የህክምና ዉጤቱ የደም ካንሰር ያሳያል ስለተባለና ህክምናዉም ለረዝም ጊዜ የሚቆይ ስለሆነ የምትችሉትን እንድትረዱት ስንል በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ባህሩ ዋሴ ➛ 1000327114895
ለበለጠ መረጃ ➛ 0975121276
💔123❤29👍2😍1🏆1
የመስቀል በዓል ስጦታ ስጡኝ
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
🙏24❤15💯3
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ እውነትም [ወንጌልም] ወደ ዓለም ኹሉ ደርሷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም [ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው] ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በኹሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ [በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና] ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት [የረባት፣ የጠቀማት] ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
ሞታችንን በሞቱ ለሻረበት ለሰላማችን መገኛ፤ ኃይላችን፣ መድኃኒታችን፣ መመኪያችንና መጠጊያችን ለሆነን በዓለ መስቀል እንኳን አደረሰን።
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ)
ሞታችንን በሞቱ ለሻረበት ለሰላማችን መገኛ፤ ኃይላችን፣ መድኃኒታችን፣ መመኪያችንና መጠጊያችን ለሆነን በዓለ መስቀል እንኳን አደረሰን።
❤72🙏11
"ወንዶች እንደ ቆስጠንጢኖስ፥ ሴቶች እን እሌኒ"
መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን መስከረም 2018 ዓም
https://youtube.com/watch?v=jzvc8muh6KA&si=PxzRBDKfl2RkTHsp
መጋቤ ጥበባት ስለ ነገረ መስቀል ምን አሉ?
ሊንኩን ተጭነው ያድምጡ!
መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን መስከረም 2018 ዓም
https://youtube.com/watch?v=jzvc8muh6KA&si=PxzRBDKfl2RkTHsp
መጋቤ ጥበባት ስለ ነገረ መስቀል ምን አሉ?
ሊንኩን ተጭነው ያድምጡ!
YouTube
ወንዶች እንደ ቆስጠንጢኖስ፥ ሴቶች እንደ እሌኒ || መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን || መስከረም 2018 ዓ/ም
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
👍12❤8🙏4
የመስቀል በዓል ስጦታ ስጡኝ
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
❤18💔8👍5
መስቀል ዕፀ ሕይወት ነው።
መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው።
መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው።
መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው።
መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው።
መስቀል ርኵሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው። የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው።
መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደእርሱ ሊቀር በው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው።
መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው። ጳውሎስ ውጊያችሁ ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምን እንዳለው መስቀል የጦር መሣርያ ነው።
መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበላው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው።
መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው።
መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራውን ውኃ በቀር በረሐ ያጣፈጠ ነው።
መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው።
መስቀል ለሚጋደሉ የድል አክሊል፤ ወደ በጉ ሰርግ ለተጠሩትም የሰርግ ልብሳቸው ነው።
መስቀል የማይነጥፍ ምንጭ፣ በቁዔትም ጥቅምም የሞላበት የክብር ጉድጓድ ነው።
(ውዳሴ መስቀል - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው።
መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው።
መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው።
መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው።
መስቀል ርኵሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው። የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው።
መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደእርሱ ሊቀር በው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው።
መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው። ጳውሎስ ውጊያችሁ ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምን እንዳለው መስቀል የጦር መሣርያ ነው።
መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበላው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው።
መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው።
መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራውን ውኃ በቀር በረሐ ያጣፈጠ ነው።
መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው።
መስቀል ለሚጋደሉ የድል አክሊል፤ ወደ በጉ ሰርግ ለተጠሩትም የሰርግ ልብሳቸው ነው።
መስቀል የማይነጥፍ ምንጭ፣ በቁዔትም ጥቅምም የሞላበት የክብር ጉድጓድ ነው።
(ውዳሴ መስቀል - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
❤88🙏10😍6🏆2👍1
በሐሰት ወሬ አትሸበሩ‼
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሀገረ ስብከቱ አመራሮች "ከተማዋ ሰላም ናት" በሚል ፕሮፓጋንዳ እንዲሠሩ መመሪያ ወርዷል የሚል መረጃ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር ተመልክተናል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሚመሩት ሀገረ ስብከት ቤተክርስቲያን የሰጠቻቸውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ከመወጣት ያለፈ ያስተላለፉት መልእክትም ሆነ የተላለፈላቸው መመሪያ የለም።
ብፁዕነታቸው የኹሉም አባት በመሆናቸው የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘር ወዘተ ልዩነት ሳያደርጉ እኩል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አሁንም እያገለገሉ የሚገኙ ሃይማኖታቸውን በምግባር የገለጡ አባት ናቸው።
የመንግሥትም ሆነ የፋኖ ታጣቂዎች ባሉበት ኹሉ የማስተማርና የመመገብ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ከመስጠት የተቆጠቡበትጊዜ የለም።
በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚሰነዘሩ አሉባልታዎች አገልግሎታቸውን ማስቆም አይቻልም።
በፈጠራ ወሬ አባትን መክሰስ ምን ለማትረፍ? የት ለመድረስ? እንደሆነ የሚያውቁት የሀሰት መረጃውን ያሠራጩት ሰዎች ብቻ ናቸው።
(የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሀገረ ስብከቱ አመራሮች "ከተማዋ ሰላም ናት" በሚል ፕሮፓጋንዳ እንዲሠሩ መመሪያ ወርዷል የሚል መረጃ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር ተመልክተናል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሚመሩት ሀገረ ስብከት ቤተክርስቲያን የሰጠቻቸውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ከመወጣት ያለፈ ያስተላለፉት መልእክትም ሆነ የተላለፈላቸው መመሪያ የለም።
ብፁዕነታቸው የኹሉም አባት በመሆናቸው የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘር ወዘተ ልዩነት ሳያደርጉ እኩል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አሁንም እያገለገሉ የሚገኙ ሃይማኖታቸውን በምግባር የገለጡ አባት ናቸው።
የመንግሥትም ሆነ የፋኖ ታጣቂዎች ባሉበት ኹሉ የማስተማርና የመመገብ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ከመስጠት የተቆጠቡበትጊዜ የለም።
በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚሰነዘሩ አሉባልታዎች አገልግሎታቸውን ማስቆም አይቻልም።
በፈጠራ ወሬ አባትን መክሰስ ምን ለማትረፍ? የት ለመድረስ? እንደሆነ የሚያውቁት የሀሰት መረጃውን ያሠራጩት ሰዎች ብቻ ናቸው።
(የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
❤66🙏19💔4
ቅዱስ መስቀል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡
ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ሆኖ ተገኘ፡፡
የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ የእውነት ወንጌልም ወደ ዓለም ሁሉ ደርሷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በሁሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት ወይም የረባትና የጠቀማት ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡
ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ሆኖ ተገኘ፡፡
የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ የእውነት ወንጌልም ወደ ዓለም ሁሉ ደርሷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በሁሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት ወይም የረባትና የጠቀማት ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
❤73🙏13👍5💯1🏆1
፩
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እርሱ ለገበሬው ዝናብና ጠልን በነፃ ስለ ሰጠ ገበሬው ማረስና መዝራት ትቶ አይተኛም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ኃጢአተኞችን የሚያድን መድኃኒት (ንስሐ) በእጃችን ስላለ ለኃጢአት ሥርየት መለመንን አንተው፡፡ ዘወትር መጸለይንም አንስነፍ፡፡
አንድ ገበሬ ዘር ባይዘራ ዝናቡ መዝነቡ ምንም ጥቅም እንደማይሰጠው ሁሉ ኃጢአተኛም ስለ ኃጢአቱ ተጸጽቶ ምሕረትን ካልለመነ ንስሐም ካልገባ ንስሐ መኖሩ ብቻ አያድነውም። ይልቅስ እርሱ ‹‹ቊስላችሁን አሳዩኝ እኔም አድናችኋለሁ›› ይላልና እንለምነው ዘንድ ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ እርሱ በምሕረቱ ይጎበኘናል፤ በቸርነቱም ያድነናል፡፡
እንግዲህ በወዳጅነት መጸጸታችሁን ንገሩት፡፡ እርሱም ይቀበላችኋል፡፡ ‹‹ወደኔ ተመለሱ እኔም ወደእናንተ እመለሳለሁ›› ብሎ በነቢዩ ነግሮናልና፡፡ እንዲህ ልቡናችሁን ወደ ጸሎት መልሱ፤ ቸርነቱም ሊቀበላችሁ ወደ እናንተ ይመለከታል፡፡ በንስሓ መንገድ ተመላለሱ ያን ጊዜ ቸርነቱ ያበራላችኋል፡፡
ነገር ግን አንድ ቀን ተጸጽታችሁ በሌላ ቀን ደግሞ ኃጢአተኞች አትሁኑ፤ አንድ ቀን የኃጢአተኞች ተባባሪ ሌላ ቀን ደግሞ ተነሳሒ አትሁኑ፡፡ ለቅሶአቸሁና ጸጸታችሁ አንድ ቀን ብቻ አይሁን፡፡ አንድ ቀን ‹‹በድያለሁ፣ ወድቄአለሁ› ብላችሁ ሌላ ቀን ደግሞ ‹‹ነገ እንሞታለንና ዛሬ እንብላ እንጠጣም›› አትበሉ፡፡
ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡
የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡
ይቀጥላል....
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እርሱ ለገበሬው ዝናብና ጠልን በነፃ ስለ ሰጠ ገበሬው ማረስና መዝራት ትቶ አይተኛም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ኃጢአተኞችን የሚያድን መድኃኒት (ንስሐ) በእጃችን ስላለ ለኃጢአት ሥርየት መለመንን አንተው፡፡ ዘወትር መጸለይንም አንስነፍ፡፡
አንድ ገበሬ ዘር ባይዘራ ዝናቡ መዝነቡ ምንም ጥቅም እንደማይሰጠው ሁሉ ኃጢአተኛም ስለ ኃጢአቱ ተጸጽቶ ምሕረትን ካልለመነ ንስሐም ካልገባ ንስሐ መኖሩ ብቻ አያድነውም። ይልቅስ እርሱ ‹‹ቊስላችሁን አሳዩኝ እኔም አድናችኋለሁ›› ይላልና እንለምነው ዘንድ ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ እርሱ በምሕረቱ ይጎበኘናል፤ በቸርነቱም ያድነናል፡፡
እንግዲህ በወዳጅነት መጸጸታችሁን ንገሩት፡፡ እርሱም ይቀበላችኋል፡፡ ‹‹ወደኔ ተመለሱ እኔም ወደእናንተ እመለሳለሁ›› ብሎ በነቢዩ ነግሮናልና፡፡ እንዲህ ልቡናችሁን ወደ ጸሎት መልሱ፤ ቸርነቱም ሊቀበላችሁ ወደ እናንተ ይመለከታል፡፡ በንስሓ መንገድ ተመላለሱ ያን ጊዜ ቸርነቱ ያበራላችኋል፡፡
ነገር ግን አንድ ቀን ተጸጽታችሁ በሌላ ቀን ደግሞ ኃጢአተኞች አትሁኑ፤ አንድ ቀን የኃጢአተኞች ተባባሪ ሌላ ቀን ደግሞ ተነሳሒ አትሁኑ፡፡ ለቅሶአቸሁና ጸጸታችሁ አንድ ቀን ብቻ አይሁን፡፡ አንድ ቀን ‹‹በድያለሁ፣ ወድቄአለሁ› ብላችሁ ሌላ ቀን ደግሞ ‹‹ነገ እንሞታለንና ዛሬ እንብላ እንጠጣም›› አትበሉ፡፡
ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡
የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡
ይቀጥላል....
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
❤47🙏29💯2
፪
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡
እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡
በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡
ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡
እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡
ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡
እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡
በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡
ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡
እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡
ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
❤72🙏12👍6
«ግሸን ደብረ ከርቤ»
ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ መስቀለኛ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ መጥቶ በዚህ ቅዱስ ስፍራ ሲያርፍ ደብረ- ነገሥት መባልዋ ቀርቶ ''ደብረ- ከርቤ'' ተባለች፡፡
የግሸኗ እመቤት ወላዲተ አምላክ ከደጇ በረከት ታሳትፈን።
ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ መስቀለኛ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ መጥቶ በዚህ ቅዱስ ስፍራ ሲያርፍ ደብረ- ነገሥት መባልዋ ቀርቶ ''ደብረ- ከርቤ'' ተባለች፡፡
የግሸኗ እመቤት ወላዲተ አምላክ ከደጇ በረከት ታሳትፈን።
❤157🙏12🕊2💯1
❤216🙏40
❤197💯41🙏38💔14
“ምን ፍሬ አፈራን?” በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ልጆቼ! እስኪ ፍቀዱልኝና ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ትመላለሳላችሁ፡፡ መልካም ነው፡፡ ግን ምን ለውጥ አመጣችሁ? ምን ፍሬ አፈራችሁ? ታገለግላላችሁን? ከአገልግሎታችሁ ምን ረብሕ አገኛችሁ?
ጥቅምን ካገኛችሁ በእውነት ምልልሳችሁ የጥበበኛ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ወንጌላውያን እንዲህ እያስተማሩን ሳለ የማንለወጥ ከሆነ ግን የእስከ አሁን ምልልሳችን የአይሁድ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ አይሁዳውያን ሕገ ኦሪትን የተሰጠቻቸው ኃጢአታቸውን በእርሷ መስታወትነት አይተው ንስሐ እንዲገቡባት ነበር፡፡ እነርሱ ግን የንስሐ ፍሬ ሳያፈሩባት እንዲሁ ይመኩባት ነበር፡፡ ስለሆነም ለሕይወት የተሰጠቻቸው ሕግ ሞት ሆና አገኟት፡፡ እኛም እንዲህ ለኵነኔ ያይደለ ለጽድቅ የተሰጠችን ወንጌል ፍሬ የማናፈራበት ከሆነ ከአይሁዳውያን የባሰ ቅጣት ትፈርድብናለች፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ላስረዳችሁ፡፡ አንድ የሚታገል ሰው (wrestler) በየጊዜው ተጋጣሚውን እንደምን ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፡፡ ተጋጣሚውም በቀላሉ ማሸነፍ ይቻሏል፡፡ በየጊዜው ራሱን የሚያሻሽል (Update) የሚያደርግ ሐኪም ጐበዝ አዋቂና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል፡፡ በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምን ፍሬ አፈራን?
እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን የቆዩትን ምእመናን አይደለም፡፡ እየተናገርኩ ያለሁት ከልጅነታችን አንሥተን በቤቱ ለምንመላለስ እንጂ፡፡ ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው? አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናት ያነጹልን ለምንድነው? ዝም ብለን እንድንሰባሰብ ነውን? እንደዚህማ በገበያ ቦታም መሰባሰብ አንችላለን፡፡ አበው አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹለን ቃሉን እንድንማርበት፣ በተማርነው ቃልም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራበት፣ ሥጋ ወደሙን እንድንቀበልበተ፣ እርስ በእርሳችን እንድንተራረምበት እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም፡፡
ታዲያ ምን ፍሬ አፈራን?
(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ ገጽ 127-128 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
ልጆቼ! እስኪ ፍቀዱልኝና ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ትመላለሳላችሁ፡፡ መልካም ነው፡፡ ግን ምን ለውጥ አመጣችሁ? ምን ፍሬ አፈራችሁ? ታገለግላላችሁን? ከአገልግሎታችሁ ምን ረብሕ አገኛችሁ?
ጥቅምን ካገኛችሁ በእውነት ምልልሳችሁ የጥበበኛ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ወንጌላውያን እንዲህ እያስተማሩን ሳለ የማንለወጥ ከሆነ ግን የእስከ አሁን ምልልሳችን የአይሁድ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ አይሁዳውያን ሕገ ኦሪትን የተሰጠቻቸው ኃጢአታቸውን በእርሷ መስታወትነት አይተው ንስሐ እንዲገቡባት ነበር፡፡ እነርሱ ግን የንስሐ ፍሬ ሳያፈሩባት እንዲሁ ይመኩባት ነበር፡፡ ስለሆነም ለሕይወት የተሰጠቻቸው ሕግ ሞት ሆና አገኟት፡፡ እኛም እንዲህ ለኵነኔ ያይደለ ለጽድቅ የተሰጠችን ወንጌል ፍሬ የማናፈራበት ከሆነ ከአይሁዳውያን የባሰ ቅጣት ትፈርድብናለች፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ላስረዳችሁ፡፡ አንድ የሚታገል ሰው (wrestler) በየጊዜው ተጋጣሚውን እንደምን ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፡፡ ተጋጣሚውም በቀላሉ ማሸነፍ ይቻሏል፡፡ በየጊዜው ራሱን የሚያሻሽል (Update) የሚያደርግ ሐኪም ጐበዝ አዋቂና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል፡፡ በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምን ፍሬ አፈራን?
እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን የቆዩትን ምእመናን አይደለም፡፡ እየተናገርኩ ያለሁት ከልጅነታችን አንሥተን በቤቱ ለምንመላለስ እንጂ፡፡ ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው? አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናት ያነጹልን ለምንድነው? ዝም ብለን እንድንሰባሰብ ነውን? እንደዚህማ በገበያ ቦታም መሰባሰብ አንችላለን፡፡ አበው አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹለን ቃሉን እንድንማርበት፣ በተማርነው ቃልም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራበት፣ ሥጋ ወደሙን እንድንቀበልበተ፣ እርስ በእርሳችን እንድንተራረምበት እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም፡፡
ታዲያ ምን ፍሬ አፈራን?
(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ ገጽ 127-128 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
❤125🙏33👍8
❤167🙏31😍3🏆2👍1🕊1