"ወንዶች እንደ ቆስጠንጢኖስ፥ ሴቶች እን እሌኒ"
መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን መስከረም 2018 ዓም
https://youtube.com/watch?v=jzvc8muh6KA&si=PxzRBDKfl2RkTHsp
መጋቤ ጥበባት ስለ ነገረ መስቀል ምን አሉ?
ሊንኩን ተጭነው ያድምጡ!
መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን መስከረም 2018 ዓም
https://youtube.com/watch?v=jzvc8muh6KA&si=PxzRBDKfl2RkTHsp
መጋቤ ጥበባት ስለ ነገረ መስቀል ምን አሉ?
ሊንኩን ተጭነው ያድምጡ!
YouTube
ወንዶች እንደ ቆስጠንጢኖስ፥ ሴቶች እንደ እሌኒ || መጋቤ ጥበባት አክሊለ ብርሃን || መስከረም 2018 ዓ/ም
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
👍12❤8🙏4
የመስቀል በዓል ስጦታ ስጡኝ
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
በእመቤቴ 5 መጽሐፍ ቅዱስ ግዙልኝ 🙏 አዲስ ለተመሠረተ ሰነሰበት ት/ቤት ፈልጌው ነው 🙏
የአንዱ መጽሐፍ ቅዱስ ዋጋ 1350 ብር ነው።
@natansolo በውስጥ ኑ!
❤18💔8👍5
መስቀል ዕፀ ሕይወት ነው።
መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው።
መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው።
መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው።
መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው።
መስቀል ርኵሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው። የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው።
መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደእርሱ ሊቀር በው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው።
መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው። ጳውሎስ ውጊያችሁ ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምን እንዳለው መስቀል የጦር መሣርያ ነው።
መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበላው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው።
መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው።
መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራውን ውኃ በቀር በረሐ ያጣፈጠ ነው።
መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው።
መስቀል ለሚጋደሉ የድል አክሊል፤ ወደ በጉ ሰርግ ለተጠሩትም የሰርግ ልብሳቸው ነው።
መስቀል የማይነጥፍ ምንጭ፣ በቁዔትም ጥቅምም የሞላበት የክብር ጉድጓድ ነው።
(ውዳሴ መስቀል - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው።
መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው።
መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው።
መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው።
መስቀል ርኵሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው። የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው።
መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደእርሱ ሊቀር በው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው።
መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው። ጳውሎስ ውጊያችሁ ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምን እንዳለው መስቀል የጦር መሣርያ ነው።
መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበላው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው።
መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው።
መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራውን ውኃ በቀር በረሐ ያጣፈጠ ነው።
መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው።
መስቀል ለሚጋደሉ የድል አክሊል፤ ወደ በጉ ሰርግ ለተጠሩትም የሰርግ ልብሳቸው ነው።
መስቀል የማይነጥፍ ምንጭ፣ በቁዔትም ጥቅምም የሞላበት የክብር ጉድጓድ ነው።
(ውዳሴ መስቀል - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
❤88🙏10😍6🏆2👍1
በሐሰት ወሬ አትሸበሩ‼
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሀገረ ስብከቱ አመራሮች "ከተማዋ ሰላም ናት" በሚል ፕሮፓጋንዳ እንዲሠሩ መመሪያ ወርዷል የሚል መረጃ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር ተመልክተናል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሚመሩት ሀገረ ስብከት ቤተክርስቲያን የሰጠቻቸውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ከመወጣት ያለፈ ያስተላለፉት መልእክትም ሆነ የተላለፈላቸው መመሪያ የለም።
ብፁዕነታቸው የኹሉም አባት በመሆናቸው የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘር ወዘተ ልዩነት ሳያደርጉ እኩል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አሁንም እያገለገሉ የሚገኙ ሃይማኖታቸውን በምግባር የገለጡ አባት ናቸው።
የመንግሥትም ሆነ የፋኖ ታጣቂዎች ባሉበት ኹሉ የማስተማርና የመመገብ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ከመስጠት የተቆጠቡበትጊዜ የለም።
በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚሰነዘሩ አሉባልታዎች አገልግሎታቸውን ማስቆም አይቻልም።
በፈጠራ ወሬ አባትን መክሰስ ምን ለማትረፍ? የት ለመድረስ? እንደሆነ የሚያውቁት የሀሰት መረጃውን ያሠራጩት ሰዎች ብቻ ናቸው።
(የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሀገረ ስብከቱ አመራሮች "ከተማዋ ሰላም ናት" በሚል ፕሮፓጋንዳ እንዲሠሩ መመሪያ ወርዷል የሚል መረጃ በአንዳንድ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር ተመልክተናል።
ብፁዕ አቡነ ኤርምያስና የሚመሩት ሀገረ ስብከት ቤተክርስቲያን የሰጠቻቸውን መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ከመወጣት ያለፈ ያስተላለፉት መልእክትም ሆነ የተላለፈላቸው መመሪያ የለም።
ብፁዕነታቸው የኹሉም አባት በመሆናቸው የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ የዘር ወዘተ ልዩነት ሳያደርጉ እኩል አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አሁንም እያገለገሉ የሚገኙ ሃይማኖታቸውን በምግባር የገለጡ አባት ናቸው።
የመንግሥትም ሆነ የፋኖ ታጣቂዎች ባሉበት ኹሉ የማስተማርና የመመገብ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ከመስጠት የተቆጠቡበትጊዜ የለም።
በማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚሰነዘሩ አሉባልታዎች አገልግሎታቸውን ማስቆም አይቻልም።
በፈጠራ ወሬ አባትን መክሰስ ምን ለማትረፍ? የት ለመድረስ? እንደሆነ የሚያውቁት የሀሰት መረጃውን ያሠራጩት ሰዎች ብቻ ናቸው።
(የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
❤66🙏19💔4
ቅዱስ መስቀል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡
ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ሆኖ ተገኘ፡፡
የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ የእውነት ወንጌልም ወደ ዓለም ሁሉ ደርሷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በሁሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት ወይም የረባትና የጠቀማት ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡
ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ሆኖ ተገኘ፡፡
የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?
እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ የእውነት ወንጌልም ወደ ዓለም ሁሉ ደርሷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በሁሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡
ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት ወይም የረባትና የጠቀማት ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡፡
❤73🙏13👍5💯1🏆1
፩
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እርሱ ለገበሬው ዝናብና ጠልን በነፃ ስለ ሰጠ ገበሬው ማረስና መዝራት ትቶ አይተኛም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ኃጢአተኞችን የሚያድን መድኃኒት (ንስሐ) በእጃችን ስላለ ለኃጢአት ሥርየት መለመንን አንተው፡፡ ዘወትር መጸለይንም አንስነፍ፡፡
አንድ ገበሬ ዘር ባይዘራ ዝናቡ መዝነቡ ምንም ጥቅም እንደማይሰጠው ሁሉ ኃጢአተኛም ስለ ኃጢአቱ ተጸጽቶ ምሕረትን ካልለመነ ንስሐም ካልገባ ንስሐ መኖሩ ብቻ አያድነውም። ይልቅስ እርሱ ‹‹ቊስላችሁን አሳዩኝ እኔም አድናችኋለሁ›› ይላልና እንለምነው ዘንድ ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ እርሱ በምሕረቱ ይጎበኘናል፤ በቸርነቱም ያድነናል፡፡
እንግዲህ በወዳጅነት መጸጸታችሁን ንገሩት፡፡ እርሱም ይቀበላችኋል፡፡ ‹‹ወደኔ ተመለሱ እኔም ወደእናንተ እመለሳለሁ›› ብሎ በነቢዩ ነግሮናልና፡፡ እንዲህ ልቡናችሁን ወደ ጸሎት መልሱ፤ ቸርነቱም ሊቀበላችሁ ወደ እናንተ ይመለከታል፡፡ በንስሓ መንገድ ተመላለሱ ያን ጊዜ ቸርነቱ ያበራላችኋል፡፡
ነገር ግን አንድ ቀን ተጸጽታችሁ በሌላ ቀን ደግሞ ኃጢአተኞች አትሁኑ፤ አንድ ቀን የኃጢአተኞች ተባባሪ ሌላ ቀን ደግሞ ተነሳሒ አትሁኑ፡፡ ለቅሶአቸሁና ጸጸታችሁ አንድ ቀን ብቻ አይሁን፡፡ አንድ ቀን ‹‹በድያለሁ፣ ወድቄአለሁ› ብላችሁ ሌላ ቀን ደግሞ ‹‹ነገ እንሞታለንና ዛሬ እንብላ እንጠጣም›› አትበሉ፡፡
ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡
የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡
ይቀጥላል....
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እርሱ ለገበሬው ዝናብና ጠልን በነፃ ስለ ሰጠ ገበሬው ማረስና መዝራት ትቶ አይተኛም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ኃጢአተኞችን የሚያድን መድኃኒት (ንስሐ) በእጃችን ስላለ ለኃጢአት ሥርየት መለመንን አንተው፡፡ ዘወትር መጸለይንም አንስነፍ፡፡
አንድ ገበሬ ዘር ባይዘራ ዝናቡ መዝነቡ ምንም ጥቅም እንደማይሰጠው ሁሉ ኃጢአተኛም ስለ ኃጢአቱ ተጸጽቶ ምሕረትን ካልለመነ ንስሐም ካልገባ ንስሐ መኖሩ ብቻ አያድነውም። ይልቅስ እርሱ ‹‹ቊስላችሁን አሳዩኝ እኔም አድናችኋለሁ›› ይላልና እንለምነው ዘንድ ይገባል፡፡ ከዚያ በኋላ እርሱ በምሕረቱ ይጎበኘናል፤ በቸርነቱም ያድነናል፡፡
እንግዲህ በወዳጅነት መጸጸታችሁን ንገሩት፡፡ እርሱም ይቀበላችኋል፡፡ ‹‹ወደኔ ተመለሱ እኔም ወደእናንተ እመለሳለሁ›› ብሎ በነቢዩ ነግሮናልና፡፡ እንዲህ ልቡናችሁን ወደ ጸሎት መልሱ፤ ቸርነቱም ሊቀበላችሁ ወደ እናንተ ይመለከታል፡፡ በንስሓ መንገድ ተመላለሱ ያን ጊዜ ቸርነቱ ያበራላችኋል፡፡
ነገር ግን አንድ ቀን ተጸጽታችሁ በሌላ ቀን ደግሞ ኃጢአተኞች አትሁኑ፤ አንድ ቀን የኃጢአተኞች ተባባሪ ሌላ ቀን ደግሞ ተነሳሒ አትሁኑ፡፡ ለቅሶአቸሁና ጸጸታችሁ አንድ ቀን ብቻ አይሁን፡፡ አንድ ቀን ‹‹በድያለሁ፣ ወድቄአለሁ› ብላችሁ ሌላ ቀን ደግሞ ‹‹ነገ እንሞታለንና ዛሬ እንብላ እንጠጣም›› አትበሉ፡፡
ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ እንጂ ሁል ጊዜ በጥፋት መንገድ አትመላለሱ፤ ሞት ሳታስቡት በድንገት ይመጣባችኋልና፡፡ የሥጋ ምቾትም ንስሓን አይፈልግምና ለጥፋት ይዳርጋል፡፡
የመጨረሻው ቀን መጥቶ ሳያገኘን በንስሓ መንገድ እንመላለስ፡፡ የማይቀረው ሞት ሲመጣ ሁለተኛው ሞት እንዳያገኘን በቅድስና ሆነን እንጠብቅ፡፡ በሃይማኖት መጽናትም የድካማችንን ፍሬ እናግኝ። በዚህች ዓለም መልካሙን ሥራ ሠርተው ካለፉ ቅዱሳን ጋር የክብር አክሊል እንቀዳጅ ዘንድ፡፡ ሰው ታይቶ የሚጠፋውን የዚህን ዓለም አክሊል ለመቀዳጀት በወታደር እና በሠረገላ ጦርነት ይከፍታሉ፤ ጊዜአዊ የሆነ የዚህን ዓለም ደስታና ሐዘን ለመቅመስ ነው፡፡
ይቀጥላል....
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
❤47🙏29💯2
፪
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡
እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡
በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡
ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡
እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡
ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
በእንተ ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
እንግዲህ የዚህን ዓለም ዘውድ ለመቀዳጀት ሩጫው ይህን ያህል ከሆነ ዘላለማዊውን ክብር፣ ሰማያዊውን አክሊል ለመቀዳጀት ውድድሩ ምንኛ ታላቅ ይሆን? ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹የሚታገል ሁሉ በሁሉ ነገር ይታገሣል፤ እነርሱስ የሚጠፋውንና የሚያልፈውን አክሊል ያገኙ ዘንድ ይበረታሉ፤ እኛ ግን የማያልፈውን አክሊል ለማግኘት እንታገሣለን›› (1ቆሮ. 9፥25-26) አለን፡፡
እንግዲህ እርጉም በሆነው ጠላታችን ላይ ድል እስክናገኝ ድረስ ከተንኮል ሥራውም እስክናመልጥ ድረስ የተጋድሎአችንን መሣርያ ንጽሕና ማድረግ ይገባናል፡፡ ክፉ የሆነው ጠላታችን እኛ ትኁታን ስንሆን ይቀናብናልና ይዋጋናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ከጠላት ቀስት የምንድንበት የበለሳን መድኃኒት ሰጠን፡፡ ይኸውም እግዚአብሔር ያስተማረን የንስሓ መድኃኒት ነው፡፡
በእውነት ለቀረበ፣ ከልቡም ተጸጽቶ ለተመለሰ ይህ መድኃኒት ፍጹም የሚያድን ነው፡፡ ነገር ግን መድኃኒቱ የተሰረቀ በደል ያለበትን ገንዘብ በእጃቸው ይዘው፣ የረከሰ ሰውነታቸውን እየወደዱ በአፋቸው ብቻ ‹‹አድነን›› ለሚሉት አይደለም፡፡
ዳግመኛ በቀደመ ርኵሰታቸው የሚወቀሱትን የወቀሳ ድምፅ ስሙ፡፡ እንደዚሁም በመተላለፋቸው እራሳቸውን እየወቀሱ ዳግመኛ ወደ ጥፋት እንዳይመለሱ የሚጠነቀቁትን ስሙ፤ በግብርም እነርሱን ምሰሉ፡፡ ሕሊናን ሁሉ ወደሚመረምረው ወደ እርሱ ሁለት ልብ ሆናችሁ አትቅረቡ፡፡ የተሰወረውን ሁሉ ያውቃልና በሁለት መንገድ አትመላለሱ፡፡
እንግዲህ ንስሓ ለመግባት ፍጠኑ እንጂ ወደ አረንቋ አትመለሱ፡፡ በቸርነቱ ፍቅር ታጥባችሁ ንጹሐን ሁኑ እንጂ ዕዳችሁ ከተሰረዘላችሁ በኋላ ገንዘቡ እንደ ወደመበት ሰው ዳግመኛ ወደ ዕዳ አትግቡ፡፡
ከምርኮ የተለቀቀ ሰው በምንም መልኩ ዳግመኛ መማረክ፣ ወደ ምርኮው ቦታ ተመልሶ መሔድ አይፈልግም፡፡ ወይም ከግዞት ሥቃይ ከወጣ በኋላ ዳግመኛ መገዛት አይፈልግም፡፡ ነገር ግን ዳግመኛ ወደ ግዞት እንዳይገባ ይጸልያል፡፡ እንግዲህ እናንተም ከገዳይ ቀንበር ከወጣችሁ በኋላ ዳግመኛ እንዳትገዙ ጸልዩ፤ በጥልፍልፉ ወጥመድም እንዳትያዙ ትጉ፡፡
(ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ - በእንተ ንስሐ በዲያቆን መዝገቡ የተተረጎመ - ገጽ 31-34)
❤72🙏12👍6
«ግሸን ደብረ ከርቤ»
ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ መስቀለኛ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ መጥቶ በዚህ ቅዱስ ስፍራ ሲያርፍ ደብረ- ነገሥት መባልዋ ቀርቶ ''ደብረ- ከርቤ'' ተባለች፡፡
የግሸኗ እመቤት ወላዲተ አምላክ ከደጇ በረከት ታሳትፈን።
ግሸን ደብረከርቤ ዳግማዊት ጎልጎታ ከደሴ ከተማ 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በደቡብ ወሎ ዞን በአንባሰል ወረዳ ውስጥ በሃይቅ እና በመቅደላ በደላንታና በየጁ መካከል በበሽሎ ወንዝ አዋሳኝ ከፍተኛ በሆነ መስቀለኛ ተራራ ላይ የምትገኝ ገዳም ናት፡፡ የበሸሎን ወንዝ ተሻግረን ሰማይ ጥግ የደረሱ የሚመስሉትን ተራሮች ወጥተን በስተመጨረሻ መግቢያ አንድ በር የሆነ እና ከተራራው አናት ላይ በሚገኝ ስፋራ ላይ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም የታነጸ እና ግማደ መስቀሉ የሚገኝበት የእግዚአብሔር አብ አብያተ ክርስቲያናት እና ፈዋሽ ጸበል ይገኛሉ፡፡ በ1942 ዓ.ም አቡነ ሚካኤል ጳጳስ ዘጎንደር ከዚህም ጋር ''መንፈሳዊ መናኝ'' በመባል የሚታወቁት ደገኛ አባት ያሰሩት ቤተ ክርስቲያንም ይገኛል፡፡
ግሸን ይህን የአሁኑን መጠሪያ ስም ከማግኘትዋ በፊት በተለያየ መጠሪያ ስሞች ትታወቅ ነበር:: በመጀመሪያ በአጼ ድልነአድ ዘመነ መንግስት በ896 ዓ.ም ሃይቅ ደብረ እስጢፋኖስ ሲመሰረት ''ሐይቅ ደብረ ነጎድጓድ'' ተብሎ ሲሰየም ግሸንም በሃይቅ ግዛት ውስጥ ስለሆነች ስምዋ ''ደበረ - ነጎድጓድ'' ተባለች፡፡ ይህን መጠሪያ ስም እንደያዘች እስከ 11ኛው ክ/ዘመን ድረስ ቆየች፡፡ በ11ኛው ክ/ዘ በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው ጻድቁ ንጉስ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍሎ የሰራው ቤተ መቅደስ በእግዚአብሔር አብ ስም ይጠራ ስለነበር ግሸንም ''ደብረ እግዚአብሔር'' ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ነገር ግን በዚህ ስም በመጠራት ብዙም ሳይቆይ ስሟ ተለውጦ ''ደብረ ነገሥት'' ተባለች፡፡ ደብረ ነገስት የተባለችውም ነገስታቱ ይማጸኑባት የክብርና የማእረግ እቃዎች የሚያሰቀምጡባትና የነገስታቱ የመሳፍንቱ ልጆችም የቤተ መንግስት አስተዳደር የሚማሩባት ስፍራ ስለነበረች ነው፡፡ እንደገና ደግሞ በ1446 ዓ.ም ኢትዪጵያዊው ፈላስፋ እየተባሉ በሚጠሩት በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ግማደ መስቀሉ መጥቶ በዚህ ቅዱስ ስፍራ ሲያርፍ ደብረ- ነገሥት መባልዋ ቀርቶ ''ደብረ- ከርቤ'' ተባለች፡፡
የግሸኗ እመቤት ወላዲተ አምላክ ከደጇ በረከት ታሳትፈን።
❤158🙏12🕊2💯1
❤216🙏40
❤197💯41🙏38💔14
“ምን ፍሬ አፈራን?” በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ልጆቼ! እስኪ ፍቀዱልኝና ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ትመላለሳላችሁ፡፡ መልካም ነው፡፡ ግን ምን ለውጥ አመጣችሁ? ምን ፍሬ አፈራችሁ? ታገለግላላችሁን? ከአገልግሎታችሁ ምን ረብሕ አገኛችሁ?
ጥቅምን ካገኛችሁ በእውነት ምልልሳችሁ የጥበበኛ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ወንጌላውያን እንዲህ እያስተማሩን ሳለ የማንለወጥ ከሆነ ግን የእስከ አሁን ምልልሳችን የአይሁድ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ አይሁዳውያን ሕገ ኦሪትን የተሰጠቻቸው ኃጢአታቸውን በእርሷ መስታወትነት አይተው ንስሐ እንዲገቡባት ነበር፡፡ እነርሱ ግን የንስሐ ፍሬ ሳያፈሩባት እንዲሁ ይመኩባት ነበር፡፡ ስለሆነም ለሕይወት የተሰጠቻቸው ሕግ ሞት ሆና አገኟት፡፡ እኛም እንዲህ ለኵነኔ ያይደለ ለጽድቅ የተሰጠችን ወንጌል ፍሬ የማናፈራበት ከሆነ ከአይሁዳውያን የባሰ ቅጣት ትፈርድብናለች፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ላስረዳችሁ፡፡ አንድ የሚታገል ሰው (wrestler) በየጊዜው ተጋጣሚውን እንደምን ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፡፡ ተጋጣሚውም በቀላሉ ማሸነፍ ይቻሏል፡፡ በየጊዜው ራሱን የሚያሻሽል (Update) የሚያደርግ ሐኪም ጐበዝ አዋቂና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል፡፡ በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምን ፍሬ አፈራን?
እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን የቆዩትን ምእመናን አይደለም፡፡ እየተናገርኩ ያለሁት ከልጅነታችን አንሥተን በቤቱ ለምንመላለስ እንጂ፡፡ ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው? አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናት ያነጹልን ለምንድነው? ዝም ብለን እንድንሰባሰብ ነውን? እንደዚህማ በገበያ ቦታም መሰባሰብ አንችላለን፡፡ አበው አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹለን ቃሉን እንድንማርበት፣ በተማርነው ቃልም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራበት፣ ሥጋ ወደሙን እንድንቀበልበተ፣ እርስ በእርሳችን እንድንተራረምበት እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም፡፡
ታዲያ ምን ፍሬ አፈራን?
(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ ገጽ 127-128 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
ልጆቼ! እስኪ ፍቀዱልኝና ዛሬ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ትመላለሳላችሁ፡፡ መልካም ነው፡፡ ግን ምን ለውጥ አመጣችሁ? ምን ፍሬ አፈራችሁ? ታገለግላላችሁን? ከአገልግሎታችሁ ምን ረብሕ አገኛችሁ?
ጥቅምን ካገኛችሁ በእውነት ምልልሳችሁ የጥበበኛ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ወንጌላውያን እንዲህ እያስተማሩን ሳለ የማንለወጥ ከሆነ ግን የእስከ አሁን ምልልሳችን የአይሁድ ምልልስ ነበር ማለት ነው፡፡ አይሁዳውያን ሕገ ኦሪትን የተሰጠቻቸው ኃጢአታቸውን በእርሷ መስታወትነት አይተው ንስሐ እንዲገቡባት ነበር፡፡ እነርሱ ግን የንስሐ ፍሬ ሳያፈሩባት እንዲሁ ይመኩባት ነበር፡፡ ስለሆነም ለሕይወት የተሰጠቻቸው ሕግ ሞት ሆና አገኟት፡፡ እኛም እንዲህ ለኵነኔ ያይደለ ለጽድቅ የተሰጠችን ወንጌል ፍሬ የማናፈራበት ከሆነ ከአይሁዳውያን የባሰ ቅጣት ትፈርድብናለች፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ላስረዳችሁ፡፡ አንድ የሚታገል ሰው (wrestler) በየጊዜው ተጋጣሚውን እንደምን ማሸነፍ እንዳለበት ልምምድ የሚያደርግ ከሆነ ክህሎቱ ይዳብራል፡፡ ተጋጣሚውም በቀላሉ ማሸነፍ ይቻሏል፡፡ በየጊዜው ራሱን የሚያሻሽል (Update) የሚያደርግ ሐኪም ጐበዝ አዋቂና ሕመምተኞችን በአግባቡ የሚረዳ ይሆናል፡፡ በየቀኑ ቃሉ የሚነገረን እኛስ ምን ለውጥ አመጣን? ምን ፍሬ አፈራን?
እየተናገርኩ ያለሁት ለአንድ ዓመት ብቻ በቤተ ክርስቲያን የቆዩትን ምእመናን አይደለም፡፡ እየተናገርኩ ያለሁት ከልጅነታችን አንሥተን በቤቱ ለምንመላለስ እንጂ፡፡ ይህን ያህል ዘመን በቤቱ እየተመላለስን ፍሬ ካላፈራን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን ብንመጣ ምን ጥቅም አለው? አባቶቻችን አብያተ ክርስቲያናት ያነጹልን ለምንድነው? ዝም ብለን እንድንሰባሰብ ነውን? እንደዚህማ በገበያ ቦታም መሰባሰብ አንችላለን፡፡ አበው አብያተ ክርስቲያናትን ያነጹለን ቃሉን እንድንማርበት፣ በተማርነው ቃልም የንስሐ ፍሬ እንድናፈራበት፣ ሥጋ ወደሙን እንድንቀበልበተ፣ እርስ በእርሳችን እንድንተራረምበት እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም፡፡
ታዲያ ምን ፍሬ አፈራን?
(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ ገጽ 127-128 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
❤125🙏33👍8
❤168🙏31😍3🏆2👍1🕊1
#መስከረም_21
#ብዙኃን_ማርያም
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም 21 ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ሁለቱንም ታሪኮች ከዚህ ቀጥለን እንመለከታቸዋለን፤
#ጉባዔ_ኒቅያ
በ325 ዓ.ም አርዮስ የሚባል መ*ና**ፍ*ቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአር*ዮስ ክህ*ደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡
በዚህም መሠረት ከሚያዝያ 21 ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ 2348 ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡
ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር 9 ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ2348ቱ መካከል 318 ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ 318ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት 318ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው (ዘፍ.14፥14)፡፡
318ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር 9 ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም 21 ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "#ብዙኃን_ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡
#ዕፀ_መስቀል
በሌላ በኩል መስከረም 21 ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ1446 ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም 21 ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡
(በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው - #ማኅበረ_ቅዱሳን_ድረገጽ)
#ብዙኃን_ማርያም
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም 21 ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡ በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤ የመጀመሪያው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም የተሰባበሰቡት ቀን፤ ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡ ሁለቱንም ታሪኮች ከዚህ ቀጥለን እንመለከታቸዋለን፤
#ጉባዔ_ኒቅያ
በ325 ዓ.ም አርዮስ የሚባል መ*ና**ፍ*ቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡ ጊዜው ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአር*ዮስ ክህ*ደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡
በዚህም መሠረት ከሚያዝያ 21 ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ 2348 ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡ ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡ በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡
ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር 9 ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በእለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ2348ቱ መካከል 318 ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ንጉሡም "ሃይማኖት እንደ 318ቱ ሊቃውንት ይኹን" ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት 318ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው (ዘፍ.14፥14)፡፡
318ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት "ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡ ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር 9 ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት መስከረም 21 ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት "#ብዙኃን_ማርያም" እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡
#ዕፀ_መስቀል
በሌላ በኩል መስከረም 21 ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ1446 ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም 21 ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡
(በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው - #ማኅበረ_ቅዱሳን_ድረገጽ)
❤94🙏7👍3🏆3👌1
ጸጋ ክብርን የተመላሽ ቅድስት ድንግል ሆይ በጸሎትሽ ረዳትነት አምኜ ሳለሁ የማቸነፍ ጥሩር እንድለብስ የመለኮትንም ሰይፍ እንድታጠቅ አውቃለሁ፡፡
እርስ በርሳቸውም ይረዳዳሉ፡፡ የኔ ሃይማኖት ያንቺ ጸሎት የልዑል እግዚአብሔር ማዳን ዳግመኛም የኔ መታመን ያንቺ ልመና የልዑል አግዚአብሔር ይቅርታ እርስ በርሳቸው ይረዳዳሉ፡፡ እኔ ባንቺ አምኜ ሳለሁ ግዳጄን የማግኘቴ ተስፋ አንቺ ስለኔ ተግተሽ መለመንሽ እግዚአብሔርም ቸል ሳይልና ሳይነቅፍ ግዳጄን መስጠቱ እርስ በርሳቸው ይረዳዳሉ፡፡
እኔ በስምሽ እለምናለሁ አንቺም ስለኔ ትማልጃለሽ፡፡ ልጅሽም ስላንቺ የልመናዬን ዋጋ ይሰጠኛል እኔ ለፍቅርሽ ካልተጋሁ አንቺ እኔን ለማዳን አትተጊም፡፡ ልጅሽም እኔን ይቅር ለማለት አይተጋም፡፡
እኔ በስምሽ ግዳጄን ሁሉ ማግኘት እመኛለሁ፡፡ አንቺ ለኔ አማላጅ ነሽ፡፡ ልጅሽም ግዳጄን የሚሰጠኝ ነው፡፡ እኔ የተጸማሁ ነኝ፡፡ አንቺ የወርቅ መጥለቂያ ነሽ፡፡ ልጅሽም የሕይወት ውሃ አዘቅት ነው፡፡
የመለኮትን ዕንቁ ለመግዛት እኔ ነጋዴ ነኝ፡፡ አንቺ የሕይወት መርከብ ነሽ፡፡ ልጅሽም የበጎ ነገር ሁሉ ድልብ በውስጡ ያለበት የትርፍ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ ገደሉን ለማለፍ ወደ ብርሃን ሥፍራ ለመድረስ የቸኮልሁ ነኝ፡፡ አንቺ የመድኃኒት ድልድይ ነሽ፡፡ ልጅሽም ለተገፉት መጠጊያ የተድላ ደስታ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ የመንፈስ ቅዱስን ሀብት የምፈልግ ድሀ ነኝ፡፡ አንቺ የክብር ሁሉ መከማቻ ነሽ፡፡ ልጅሽም ለባለሟልነትና ለክብር ለማሞገስ የሽልማት ጌጽ ነው፡፡
እኔ እለምናለሁ አንቺ ጸሎቴን ታሳርጊያለሽ ልጅሽም ኃጢአቴን ያስተሠርያል፡፡ የልቤን ግዳጅ ይሰጠኛል፡፡ እኔ ቁስለኛ ነኝ አንቺ የመድኃኒት ሙዳይ ነሽ፡፡ ልጅሽም ባለ መድኃኒት ነው፡፡
እኔ ቁስለ ኃጢአቴ የሸተተ፡፡ የቅዱሳንንም መዓዛ ሽቱ የምሻ ነኝ፡፡ አንቺ ያማረ የተወደደ ሽቱ ብልቃጥ ነሽ፡፡ ልጅሽም ከሽቱ ሁሉ ይልቅ ያማረ የተወደደ የመለኮት ቅቤ ነው፡፡
እኔ የታረዝሁ የብርሃን ልብስ የምሻ ነኝ፡፡ አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ፡፡ ልጅሽም የማያልቅ የማያረጅ የሃይማኖት ልብስ ነው፡፡
በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ! ሁልጊዜ በዓይነ ልቡናዬ አይሻለሁ በሃሳቤም በየሥፍራው ሁሉ አገኝሻለሁ በተኛሁ ጊዜ እኔን ለመጠበቅ የነቃሽ ነሽ፡፡ ከመኝታዬም ስነቃ እኔን ለማንሣት የተዘጋጀሽ ነሽ፡፡
ስቀመጥም እኔን ለመምከር ትደርሻለሽ፡፡ በቆምሁም ጊዜ በቀኜ ትቆሚያለሽ በተናገርሁም ጊዜ አንደበቴን ለማጣፈጥ ታከናውኛለሽ፡፡ በዝምታዬም ጊዜ ለመጠበቄ ማሞገሻ ነሽ ኃሴትም ባደረግሁ ጊዜ ተድላ ደስታ ነሽ፡፡
ባዘንሁም በተቆረቆርሁ ጊዜ የኃዘኔ መጽናኛ ነሽ፡፡ ባለቀስሁም ጊዜ የልቅሶዬ መተዊያ ነሽ፡፡ በዘመርሁ ጊዜ ለእጄ እንደ መሰንቆ ለጣቶቼም እንደ በገና ነሽ፡፡
በተራብሁም ጊዜ ለሆዴ ትመግቢኛለሽ በተጸማሁም ጊዜ እኔን ለማርካት የሕይወት ውሃን የተመላሽ ነሽ፡፡ የተፍገምገምሁም ጊዜ እኔን ለመደገፍ እጅሽን ትዘረጊያለሽ፡፡ በወደቅሁም ጊዜ እጅሽን ዘርግተሽ ታነሺኛለሽ፡፡
ተባሕትዎም በያዝሁ ጊዜ እኔን ለመጎብኘት አታቋርጭም፡፡ በማኅበር መካከል ወደኔ ትደርሻለሽ በደከምሁም ጊዜ ድካሜን ታበረቻለሽ፡፡ በታመምሁም ጊዜ ሥጋዬን ከሞት ታድኛለሽ፡፡ በተቸገርሁም ጊዜ ከችግሬ ታድኝኛለሽ፡፡
በተጨነቅሁም ጊዜ ጭንቄን ታርቂያለሽ፡፡ በቆሰልሁም ጊዜ ቁስሌን ታጠጊያለሽ፡፡ በርኩሰቴም ጊዜ ንጹሕ ታደርጊኛለሽ፡፡ በበደልሁም ጊዜ ኃጢአቴን ታቃልያለሽ፡፡ በደኸየሁም ጊዜ ለድህነቴ ባለጸግነት ሀብቴ ነሽ፡፡
(#አርጋኖን #በአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ)
እርስ በርሳቸውም ይረዳዳሉ፡፡ የኔ ሃይማኖት ያንቺ ጸሎት የልዑል እግዚአብሔር ማዳን ዳግመኛም የኔ መታመን ያንቺ ልመና የልዑል አግዚአብሔር ይቅርታ እርስ በርሳቸው ይረዳዳሉ፡፡ እኔ ባንቺ አምኜ ሳለሁ ግዳጄን የማግኘቴ ተስፋ አንቺ ስለኔ ተግተሽ መለመንሽ እግዚአብሔርም ቸል ሳይልና ሳይነቅፍ ግዳጄን መስጠቱ እርስ በርሳቸው ይረዳዳሉ፡፡
እኔ በስምሽ እለምናለሁ አንቺም ስለኔ ትማልጃለሽ፡፡ ልጅሽም ስላንቺ የልመናዬን ዋጋ ይሰጠኛል እኔ ለፍቅርሽ ካልተጋሁ አንቺ እኔን ለማዳን አትተጊም፡፡ ልጅሽም እኔን ይቅር ለማለት አይተጋም፡፡
እኔ በስምሽ ግዳጄን ሁሉ ማግኘት እመኛለሁ፡፡ አንቺ ለኔ አማላጅ ነሽ፡፡ ልጅሽም ግዳጄን የሚሰጠኝ ነው፡፡ እኔ የተጸማሁ ነኝ፡፡ አንቺ የወርቅ መጥለቂያ ነሽ፡፡ ልጅሽም የሕይወት ውሃ አዘቅት ነው፡፡
የመለኮትን ዕንቁ ለመግዛት እኔ ነጋዴ ነኝ፡፡ አንቺ የሕይወት መርከብ ነሽ፡፡ ልጅሽም የበጎ ነገር ሁሉ ድልብ በውስጡ ያለበት የትርፍ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ ገደሉን ለማለፍ ወደ ብርሃን ሥፍራ ለመድረስ የቸኮልሁ ነኝ፡፡ አንቺ የመድኃኒት ድልድይ ነሽ፡፡ ልጅሽም ለተገፉት መጠጊያ የተድላ ደስታ ሥፍራ ነው፡፡
እኔ የመንፈስ ቅዱስን ሀብት የምፈልግ ድሀ ነኝ፡፡ አንቺ የክብር ሁሉ መከማቻ ነሽ፡፡ ልጅሽም ለባለሟልነትና ለክብር ለማሞገስ የሽልማት ጌጽ ነው፡፡
እኔ እለምናለሁ አንቺ ጸሎቴን ታሳርጊያለሽ ልጅሽም ኃጢአቴን ያስተሠርያል፡፡ የልቤን ግዳጅ ይሰጠኛል፡፡ እኔ ቁስለኛ ነኝ አንቺ የመድኃኒት ሙዳይ ነሽ፡፡ ልጅሽም ባለ መድኃኒት ነው፡፡
እኔ ቁስለ ኃጢአቴ የሸተተ፡፡ የቅዱሳንንም መዓዛ ሽቱ የምሻ ነኝ፡፡ አንቺ ያማረ የተወደደ ሽቱ ብልቃጥ ነሽ፡፡ ልጅሽም ከሽቱ ሁሉ ይልቅ ያማረ የተወደደ የመለኮት ቅቤ ነው፡፡
እኔ የታረዝሁ የብርሃን ልብስ የምሻ ነኝ፡፡ አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ፡፡ ልጅሽም የማያልቅ የማያረጅ የሃይማኖት ልብስ ነው፡፡
በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ የተመረጥሽ ድንግል እመቤቴ ማርያም ሆይ! ሁልጊዜ በዓይነ ልቡናዬ አይሻለሁ በሃሳቤም በየሥፍራው ሁሉ አገኝሻለሁ በተኛሁ ጊዜ እኔን ለመጠበቅ የነቃሽ ነሽ፡፡ ከመኝታዬም ስነቃ እኔን ለማንሣት የተዘጋጀሽ ነሽ፡፡
ስቀመጥም እኔን ለመምከር ትደርሻለሽ፡፡ በቆምሁም ጊዜ በቀኜ ትቆሚያለሽ በተናገርሁም ጊዜ አንደበቴን ለማጣፈጥ ታከናውኛለሽ፡፡ በዝምታዬም ጊዜ ለመጠበቄ ማሞገሻ ነሽ ኃሴትም ባደረግሁ ጊዜ ተድላ ደስታ ነሽ፡፡
ባዘንሁም በተቆረቆርሁ ጊዜ የኃዘኔ መጽናኛ ነሽ፡፡ ባለቀስሁም ጊዜ የልቅሶዬ መተዊያ ነሽ፡፡ በዘመርሁ ጊዜ ለእጄ እንደ መሰንቆ ለጣቶቼም እንደ በገና ነሽ፡፡
በተራብሁም ጊዜ ለሆዴ ትመግቢኛለሽ በተጸማሁም ጊዜ እኔን ለማርካት የሕይወት ውሃን የተመላሽ ነሽ፡፡ የተፍገምገምሁም ጊዜ እኔን ለመደገፍ እጅሽን ትዘረጊያለሽ፡፡ በወደቅሁም ጊዜ እጅሽን ዘርግተሽ ታነሺኛለሽ፡፡
ተባሕትዎም በያዝሁ ጊዜ እኔን ለመጎብኘት አታቋርጭም፡፡ በማኅበር መካከል ወደኔ ትደርሻለሽ በደከምሁም ጊዜ ድካሜን ታበረቻለሽ፡፡ በታመምሁም ጊዜ ሥጋዬን ከሞት ታድኛለሽ፡፡ በተቸገርሁም ጊዜ ከችግሬ ታድኝኛለሽ፡፡
በተጨነቅሁም ጊዜ ጭንቄን ታርቂያለሽ፡፡ በቆሰልሁም ጊዜ ቁስሌን ታጠጊያለሽ፡፡ በርኩሰቴም ጊዜ ንጹሕ ታደርጊኛለሽ፡፡ በበደልሁም ጊዜ ኃጢአቴን ታቃልያለሽ፡፡ በደኸየሁም ጊዜ ለድህነቴ ባለጸግነት ሀብቴ ነሽ፡፡
(#አርጋኖን #በአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ)
❤142🙏22👍5🕊4
በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ
ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ መኖር ለደከመህ፣ ሕይወት ለታከተህ፣ የሚሰማህ ላጣኸው፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ!
ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል። "በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" ሐዋ. ፲፮፥፳፰ አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል። ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል። ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም።
ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ? ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ? "ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ" ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. ፲፥፲፰) "ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ" ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? (፩ነገሥ. ፲፱፥፬) ዮናስንስ "አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው" ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ ፬፥፫)
ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም። ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው። አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: "ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል" ይላል መጽሐፍ:: ፩ኛ ቆሮ. ፲፥፲፫
ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል። እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ። ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል።
"የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር" ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው። የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም። "ጌታ አምላክህን አትፈታተነው" "ሒድ አንተ ሰይጣን" ብለህ ሰይጣንን ገሥፀው። ሰይጣን ክርስቶስን "ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ" ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ።
ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው። ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ። አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል። የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ። ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል። ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል። ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም። ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ?
"የሞተ ተገላገለ" ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው። "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል።
ወዳጄ "በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ" የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ። ሊፈውስህ የቆሰለ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ፣ ሊያረካህ የተጠማ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው። ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል። አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው። ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል?
ይቀጥላል ......
(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - የኤፌሶን ወንዝ ገጽ 9-14)
ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ መኖር ለደከመህ፣ ሕይወት ለታከተህ፣ የሚሰማህ ላጣኸው፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ!
ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል። "በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" ሐዋ. ፲፮፥፳፰ አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል። ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል። ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም።
ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ? ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ? "ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ" ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. ፲፥፲፰) "ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ" ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? (፩ነገሥ. ፲፱፥፬) ዮናስንስ "አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው" ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ ፬፥፫)
ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም። ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው። አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: "ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል" ይላል መጽሐፍ:: ፩ኛ ቆሮ. ፲፥፲፫
ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል። እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ። ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል።
"የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር" ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው። የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም። "ጌታ አምላክህን አትፈታተነው" "ሒድ አንተ ሰይጣን" ብለህ ሰይጣንን ገሥፀው። ሰይጣን ክርስቶስን "ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ" ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ።
ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው። ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ። አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል። የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ። ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል። ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል። ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም። ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ?
"የሞተ ተገላገለ" ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው። "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል።
ወዳጄ "በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ" የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ። ሊፈውስህ የቆሰለ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ፣ ሊያረካህ የተጠማ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው። ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል። አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው። ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል?
ይቀጥላል ......
(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ - የኤፌሶን ወንዝ ገጽ 9-14)
❤120🙏25👍2👌2😍2
