“ልጄ ሆይ ባለ መድኃኒትን ስማ ሕማምህን ቸል አትበል” መ.ሲራክ ፴፰፥፩
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
❤65🙏6💯2👍1
"ከበሮ ለምን ይጮኻል?"
የኔታ ለተማሪዎቻቸው አንድ ጥያቄ አቀረቡ "ልጆች ከበሮ ለምን ይጮኻል?" አሉ የኔታ "በቆዳ ስለተወጠረ ነው" አለ አንድ ተማሪ የዳዊት ማህደሩን በእጁ አንጠልጥሎ ለመመለስ እየቸኮለ። የኔታም "አይደለም አሉ" ሌላኛው ተማሪም "የኔታ ከእንጨት ስለ ተሠራ ነው" አለ የለበሰውን ለምድ ከፍ ከፍ እያደረገ የኔታም ትንሽ ዝም ካሉ በኋላ "አይደለም አሉ" ተማሪዎቹ ኹሉ ማውጣት ማውረድ ጀመሩ በሀሳብ ተወጠሩ።
ኹሉም የመጣለትን እና የገመተውን መናገር ቀጠለ ግን የሚመልስ ጠፋ። አንድ የኹሉንም ምላሽ በእርጋታ ይሰማ የነበረ ተማሪ እጁን አወጣ። "እሽ ልጄ" አሉ የኔታ ድምጹን ከፍ አደረገና "የኔታ እድሉን ስለ ሰጡኝ አመሰግናለሁ" ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ "የኔታ ከበሮ የሚጮኸው ባዶ ስለሆነ ነው!" አለ። የኔታም የልጁን ምላሽ በማድነቅ ከወንበራቸው በመነሳት "ልጄ ተባረክ" አሉ። ተማሪዎቹም በጭብጨባ አጀቡት።
የኔታም ቀጠል አደረጉና ልጆች "ባዶ የኾነ ነገር ሁሉ ይጮኻል በውስጡ የኾነ ነገር ያለው እቃ ግን አይጮኽም። የተማረም ሰው እንዲሁ ነው። እውቀት ያለው አይጮኽም፣ ጥበብ ያለው አይጮኽም፣ ምንጊዜም ባዶ የሆነ ሰው ሲጮኽ፣ ጥበብ የሌለው ሲፎክር እውቀት የሌለው ሲያቅራራ ይታያል። እና ልጆቼ እናንተ 'ባዶ' እንዳትሆኑ እውቀትን ጨምሩ፣ በእውቀት ላይ ጥበብን፣ በጥበብ ላይ እግዚአብሔርን መፍራት ጨምሩ። ምድራችንን በማስተማርና በመስበክ የሞሉ ግን 'ባዶ' የሆኑ። ምድሪቱን በዝማሬ የሞሉ በሃይማኖትና በምግባር ግን 'ባዶ' የሆኑ። ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚሉ ግን ጌታ የማያውቃቸው እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ እንሰሳ በደመ ነፍስ የሚኖሩ ሰዎች፣ በዝተዋልና" ብለው ቁጭ አሉ። ተማሪዎቹም የኔታን "ቃለ ሕይወትን ያሰማልን" ብለው ትምህርታቸውን ቀጠሉ።
የኔታ ለተማሪዎቻቸው አንድ ጥያቄ አቀረቡ "ልጆች ከበሮ ለምን ይጮኻል?" አሉ የኔታ "በቆዳ ስለተወጠረ ነው" አለ አንድ ተማሪ የዳዊት ማህደሩን በእጁ አንጠልጥሎ ለመመለስ እየቸኮለ። የኔታም "አይደለም አሉ" ሌላኛው ተማሪም "የኔታ ከእንጨት ስለ ተሠራ ነው" አለ የለበሰውን ለምድ ከፍ ከፍ እያደረገ የኔታም ትንሽ ዝም ካሉ በኋላ "አይደለም አሉ" ተማሪዎቹ ኹሉ ማውጣት ማውረድ ጀመሩ በሀሳብ ተወጠሩ።
ኹሉም የመጣለትን እና የገመተውን መናገር ቀጠለ ግን የሚመልስ ጠፋ። አንድ የኹሉንም ምላሽ በእርጋታ ይሰማ የነበረ ተማሪ እጁን አወጣ። "እሽ ልጄ" አሉ የኔታ ድምጹን ከፍ አደረገና "የኔታ እድሉን ስለ ሰጡኝ አመሰግናለሁ" ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ "የኔታ ከበሮ የሚጮኸው ባዶ ስለሆነ ነው!" አለ። የኔታም የልጁን ምላሽ በማድነቅ ከወንበራቸው በመነሳት "ልጄ ተባረክ" አሉ። ተማሪዎቹም በጭብጨባ አጀቡት።
የኔታም ቀጠል አደረጉና ልጆች "ባዶ የኾነ ነገር ሁሉ ይጮኻል በውስጡ የኾነ ነገር ያለው እቃ ግን አይጮኽም። የተማረም ሰው እንዲሁ ነው። እውቀት ያለው አይጮኽም፣ ጥበብ ያለው አይጮኽም፣ ምንጊዜም ባዶ የሆነ ሰው ሲጮኽ፣ ጥበብ የሌለው ሲፎክር እውቀት የሌለው ሲያቅራራ ይታያል። እና ልጆቼ እናንተ 'ባዶ' እንዳትሆኑ እውቀትን ጨምሩ፣ በእውቀት ላይ ጥበብን፣ በጥበብ ላይ እግዚአብሔርን መፍራት ጨምሩ። ምድራችንን በማስተማርና በመስበክ የሞሉ ግን 'ባዶ' የሆኑ። ምድሪቱን በዝማሬ የሞሉ በሃይማኖትና በምግባር ግን 'ባዶ' የሆኑ። ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚሉ ግን ጌታ የማያውቃቸው እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ እንሰሳ በደመ ነፍስ የሚኖሩ ሰዎች፣ በዝተዋልና" ብለው ቁጭ አሉ። ተማሪዎቹም የኔታን "ቃለ ሕይወትን ያሰማልን" ብለው ትምህርታቸውን ቀጠሉ።
❤200🙏24💔11🎉1
#ወርኃ_ጽጌ
(ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡
በዚህ በወርኃ ጽጌ (በዘመነ ጽጌ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ (የፈቃድ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ (ሉቃ. 7፡47) እንዲል፡፡
የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!
(ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን (ዘመነ ጽጌን) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልኮት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ ፡፡
በዚህ በወርኃ ጽጌ (በዘመነ ጽጌ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ (የፈቃድ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ (ሉቃ. 7፡47) እንዲል፡፡
የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ "ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ" (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡
እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!
❤198🙏24🕊1
ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ሰነፍ ሰው የለም፡፡ ወዳጄ “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ ዳግመኛም “ወርቅም ብርም የለኝም” ብሎ የተናገረ ጴጥሮስ ይወቅሰሃልና፡፡
"ምናምንቴ ነኝ" አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! "እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቴዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ይህን ከማድረግ ይልቅ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹ ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ምናምንቴ ነኝ" አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! "እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቴዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ ይህን ከማድረግ ይልቅ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹ ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
❤172🙏24😍2
Forwarded from ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ልጄ ሆይ ባለ መድኃኒትን ስማ ሕማምህን ቸል አትበል” መ.ሲራክ ፴፰፥፩
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
❤56🙏14👍4💔2🏆1
ቅናት ሰውን ወደ ዲያብሎስ ትለውጠዋለች፤ ስውን ክፉ ጋኔን ታደርገዋለች፡፡ የመጀመሪያው ነፍሰ ገዳይ [ቃኤል] የተነሣው ከቅናት ነው፡፡ ተፈጥሮውን (ሰው መኾኑን) የዘነጋው፣ ምድርንም ያረከሳት ከቅናት የተነሣ ነው፡፡ ከዚያም በኋላ ገና በሕይወተ ሥጋ እያሉ ዳታንን፣ ቆሬንና አቤሮንም፤ ሕዝቡንም ኹሉ ምድር አፏን ከፍታ የዋጠቻቸው ከቅናት የተነሣ ነው፡፡
“ቅናትን ተቃውሞ መናገር ቀላል ነው" የሚል ሰው ሊኖርይችላል፡፡ እኛ ግን ሰዎች ከዚህ ደዌ እንዴት መዳን እንደሚችሉም መናገር ይገባናል፡፡ እናስ ከዚህ ክፋት መላቀቅ የምንችለው እንዴት ነው? ዝሙት የፈጸመ ሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት እንደማይችል ኹሉ በቅናት የተያዘ ሰውም እንደዚሁ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት እንደማይችል ብናስብ ይህን ደዌ ከእኛ ማራቅ እንችላለን፡፡ ቅናት ከዝሙት የሚተናነስ አይደለምና፡፡ ቅናት እንደ ቅቡል ተደርጎ ነው የሚቈጠረው፤ ከዚህ የተነሣም ሰው እንደ ቀላል ነገር አድርጎ ነው የሚያስበው፡፡ ነገር ግን እውነተኛ ክፋቱ ምን እንደ ኾነ ቢገለፅ በቀላሉ ከእርሱ መራቅ በተቻለን ነበር፡፡
ስለዚህ ስለ መቅናትህ አልቅስ፤ ቃትት፤ አንባ፤ ከዚህ ደዌ ይፈውስህ ዘንድም እግዚአብሔርን ማልደው፡፡ የቅናት ኃጢአት እጅግ የከፋ እንደ ኾነ ከልብህ አስበውና ንስሓ ግባ፡፡ በዚህ አግባብ የምትሔድ ከኾነ ከዚህ ደዌም ፈጥነህ ትፈወሳለህ፡፡
“ቅናት (ምቀኝነት) ክፉ በደል እንደ ኾነ የማያውቅ ማን አለና?” የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ ክፉ በደል እንደ ኾነ'ማ የማያውቅ ሰው የለም፡፡ ዳሩ ግን እንደ ዝሙትና እንደ ግልሙትና አድርገው አይቈጥሩትም፡፡ ቢያንስ አንድ ሰው በሌላ ሰው ላይ ከቀና፥ ልክ ዝሙት እንደ ሠራ ሰው ኾኖ አምርሮ ራሱን ይወቅሳልን? ከዚህ ክፉ ደዌ እግዚአብሔር ምሕረት ያደርግለት ዘንድ የተማጸነው መቼ ነው? ማንም እንደዚህ አያደርግም፡፡ ይልቅስ ቢጾምና ጥቂት ገንዘብ ለጦም አዳሪዎች ቢሰጥ፥ ሺሕ ጊዜ ቀናተኛ ቢኾንም፥ ከበደል ኹሉ የሚከፋ አንዳች ኃጢአት እንደ ሠራ አያስብም፡፡ እንዴ! እስኪ ንገረኝ! ቃኤል እንደዚያ የኾነው በምን ምክንያት ነው? ዔሣውስ? የላባ ልጆችስ? የያዕቆብ ልጆችስ? ቆሬ፣ ዳታንና አቤሮን ከወገኖቻቸው ጋርስ እንዲያ የኾኑት በምን ምክንያት ነው? ማርያም እኅተ ሙሴስ? አሮንስ? ዲያብሎስ ራሱስ ቢኾን?
ከዚሁ ጋር ይህንንም አስተውል! ቅናት ሲይዝህ የገዛ ራስህን በሰይፍ ትወጋለህ እንጂ የምትቀናበትን ሰው አትጎዳውም፡፡ እስኪ ንገረኝ! ቃኤል በወንድሙ ላይ በመቅናቱ ምክንያት አቤልን ጎድቶታልን? እ? እርሱ ሳይፈልግ ፈጥኖ ወደ ገነት እንዲሔድ አይደል እንዴ ያደረገው? እርሱ ግን ስፍር ቍጥር በሌላቸው ክፉ ክፉ ነገሮች ነው የገዛ ራሱን የወጋው፡፡ ዔሣው ያዕቆብን የጎዳውስ የት ላይ ነው? ያዕቆብ ባለጸጋ አልኾነምን? ቍጥር የሌላቸውን በረከቶች አልተቀበለምን? ዔሣው ግን በወንድሙ ላይ ከቀና በኋላ ከአባቱ ቤት ውጹእ፣ በባዕድ አገርም ተቅበዥባዥ ኾነ፡፡ የቀኑበትና ቅናታቸውንም [በኋላ ገንዘቡን ቢመርጡም ቅሉ] ደሙን እስከ ማፍሰስ ድረስ እንዲማማሉ ቢያደርጋቸውም የያዕቆብ ልጆችስ ዮሴፍን የጎዱት የት ነው? እነርሱ ራሳቸው በረሃብ በትር የተገረፉ አይደለምን? እርሱ የግብጽ ንጉሥ ሲኾን እነርሱ ግን እጅግ ጽኑ መከራ የገጠማቸው አይደሉምን? ለምን መሰለህ፥ ይበልጥ በቀናህ ቍጥር፥ በቀናህበት ሰው ላይ እንዲያውም ይበልጥ በረከትን ታመጣለታለህ እንጂ አትጎዳውም፡፡ እነዚህን ኹሉ የሚመለከት እግዚአብሔር አለና፤ በደል ያልፈጸመው ሰው እንደተበደለ ሲያይ እርሱን የበለጠ ያከብረዋል፥ ከፍ ከፍ ያደርገዋል፤ አንተን ግን ይቀጣሃል፡፡
ይቀጥላል......
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመመው ድርሳን 40 ገጽ 330-333
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
“ቅናትን ተቃውሞ መናገር ቀላል ነው" የሚል ሰው ሊኖርይችላል፡፡ እኛ ግን ሰዎች ከዚህ ደዌ እንዴት መዳን እንደሚችሉም መናገር ይገባናል፡፡ እናስ ከዚህ ክፋት መላቀቅ የምንችለው እንዴት ነው? ዝሙት የፈጸመ ሰው ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት እንደማይችል ኹሉ በቅናት የተያዘ ሰውም እንደዚሁ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት እንደማይችል ብናስብ ይህን ደዌ ከእኛ ማራቅ እንችላለን፡፡ ቅናት ከዝሙት የሚተናነስ አይደለምና፡፡ ቅናት እንደ ቅቡል ተደርጎ ነው የሚቈጠረው፤ ከዚህ የተነሣም ሰው እንደ ቀላል ነገር አድርጎ ነው የሚያስበው፡፡ ነገር ግን እውነተኛ ክፋቱ ምን እንደ ኾነ ቢገለፅ በቀላሉ ከእርሱ መራቅ በተቻለን ነበር፡፡
ስለዚህ ስለ መቅናትህ አልቅስ፤ ቃትት፤ አንባ፤ ከዚህ ደዌ ይፈውስህ ዘንድም እግዚአብሔርን ማልደው፡፡ የቅናት ኃጢአት እጅግ የከፋ እንደ ኾነ ከልብህ አስበውና ንስሓ ግባ፡፡ በዚህ አግባብ የምትሔድ ከኾነ ከዚህ ደዌም ፈጥነህ ትፈወሳለህ፡፡
“ቅናት (ምቀኝነት) ክፉ በደል እንደ ኾነ የማያውቅ ማን አለና?” የሚል ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ ክፉ በደል እንደ ኾነ'ማ የማያውቅ ሰው የለም፡፡ ዳሩ ግን እንደ ዝሙትና እንደ ግልሙትና አድርገው አይቈጥሩትም፡፡ ቢያንስ አንድ ሰው በሌላ ሰው ላይ ከቀና፥ ልክ ዝሙት እንደ ሠራ ሰው ኾኖ አምርሮ ራሱን ይወቅሳልን? ከዚህ ክፉ ደዌ እግዚአብሔር ምሕረት ያደርግለት ዘንድ የተማጸነው መቼ ነው? ማንም እንደዚህ አያደርግም፡፡ ይልቅስ ቢጾምና ጥቂት ገንዘብ ለጦም አዳሪዎች ቢሰጥ፥ ሺሕ ጊዜ ቀናተኛ ቢኾንም፥ ከበደል ኹሉ የሚከፋ አንዳች ኃጢአት እንደ ሠራ አያስብም፡፡ እንዴ! እስኪ ንገረኝ! ቃኤል እንደዚያ የኾነው በምን ምክንያት ነው? ዔሣውስ? የላባ ልጆችስ? የያዕቆብ ልጆችስ? ቆሬ፣ ዳታንና አቤሮን ከወገኖቻቸው ጋርስ እንዲያ የኾኑት በምን ምክንያት ነው? ማርያም እኅተ ሙሴስ? አሮንስ? ዲያብሎስ ራሱስ ቢኾን?
ከዚሁ ጋር ይህንንም አስተውል! ቅናት ሲይዝህ የገዛ ራስህን በሰይፍ ትወጋለህ እንጂ የምትቀናበትን ሰው አትጎዳውም፡፡ እስኪ ንገረኝ! ቃኤል በወንድሙ ላይ በመቅናቱ ምክንያት አቤልን ጎድቶታልን? እ? እርሱ ሳይፈልግ ፈጥኖ ወደ ገነት እንዲሔድ አይደል እንዴ ያደረገው? እርሱ ግን ስፍር ቍጥር በሌላቸው ክፉ ክፉ ነገሮች ነው የገዛ ራሱን የወጋው፡፡ ዔሣው ያዕቆብን የጎዳውስ የት ላይ ነው? ያዕቆብ ባለጸጋ አልኾነምን? ቍጥር የሌላቸውን በረከቶች አልተቀበለምን? ዔሣው ግን በወንድሙ ላይ ከቀና በኋላ ከአባቱ ቤት ውጹእ፣ በባዕድ አገርም ተቅበዥባዥ ኾነ፡፡ የቀኑበትና ቅናታቸውንም [በኋላ ገንዘቡን ቢመርጡም ቅሉ] ደሙን እስከ ማፍሰስ ድረስ እንዲማማሉ ቢያደርጋቸውም የያዕቆብ ልጆችስ ዮሴፍን የጎዱት የት ነው? እነርሱ ራሳቸው በረሃብ በትር የተገረፉ አይደለምን? እርሱ የግብጽ ንጉሥ ሲኾን እነርሱ ግን እጅግ ጽኑ መከራ የገጠማቸው አይደሉምን? ለምን መሰለህ፥ ይበልጥ በቀናህ ቍጥር፥ በቀናህበት ሰው ላይ እንዲያውም ይበልጥ በረከትን ታመጣለታለህ እንጂ አትጎዳውም፡፡ እነዚህን ኹሉ የሚመለከት እግዚአብሔር አለና፤ በደል ያልፈጸመው ሰው እንደተበደለ ሲያይ እርሱን የበለጠ ያከብረዋል፥ ከፍ ከፍ ያደርገዋል፤ አንተን ግን ይቀጣሃል፡፡
ይቀጥላል......
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመመው ድርሳን 40 ገጽ 330-333
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
❤147🙏15😍8👌3🏆2
የቀጠለ..
“ጠላትህ ቢወድቅ ደስ አይበልህ፥ በመሰናከሉም ልብህ ሐሤት አያድርግ፡፡ እግዚአብሔር ያያልና፤ ደስም አያሰኘውምና፤ ቊጣውንም ከእርሱ ይመልሳልና'' እንዲል በጠላቶቻቸው ውድቀት ደስ ስለሚሰኙ ሰዎች እግዚአብሔር ቍጣውን የሚመልስ ከኾነ˖ ምንም በደል ባልሠሩ ሰዎች ላይ ይበልጥ ቍጣውን ይመልሳልና (ምሳሌ 24፥17-18)::
እንኪያስ ይህ ራሰ ብዙ የኾነውን አውሬ ፈጽመን ከእኛ እናቅ፡፡ የቅናት ራሶች (ዓይነቶች) በርግጥም ብዙ ናቸውና፡፡ የሚወደውን የሚወድ ሰው ከአንድ ቀራጭ የተሻለ ሥራ ካልሠራ፥ ምንም ያልበደለውን ሰው የሚጠላ ሰውስ ምን ተብሎ ሊጠራ ይችላል? ከአሕዛብ የባሰ ኾኖ ሳለስ እንዴት ከምረረ ገሃነም ማምለጥ ይቻለዋል? ስለዚህም ጭምር፥ ማለት መላእክትን ወይም ይልቅ የመላእክትን ጌታ እንድንመስል ታዘን እያለ ዲያብሎስን በመምሰላችን እጅግ አዝናለሁ። በእውነት በቤተ ክርስቲያን ሳይቀርብዙ ቅናት አለ፡፡ በዲያብሎስ ባርነት ሥር ካሉት ይልቅ ይበልጥ በእኛ ዘንድ ቅናት አለ፡፡ ስለዚህ እኛው ራሳችን ለራሳችን ሳይቀርማስተማር አለብን፡፡
እስኪ ንገረኝ! በባልንጀራህ ላይ የምትቀናው ለምንድን ነው? ሥልጣንንና በጎ ስምን ሲቀበል ስላየኸው ነውን? ክብርና ዝና ራሳቸውን ባልጠበቁ ሰዎች ላይ ምን ጉዳት እንደሚያመጣ አታስተውልምን? ወደ ትዕቢት፤ ወደ ውዳሴ ከንቱ፤ ወደ ዕብሪት፣ ወደ እንዝህላልነት፣ ይበልጥ ወደ ግድየለሽነት እንደሚወስዳቸው አታውቅምን? ይህ የምትቀናበት ሰው በእነዚህ ክፋቶች ከመያዙም በላይ ሥልጣኑና ዝናው ገና ከመታየታቸው የሚጠወልጉ ናቸው፡፡ እጅግ የሚከፋው ይህ ነውና፡- ከዚህ የሚመነጩ ክፋቶች የማያልፉ ሲኾኑ ከዚህ የሚገኘው ደስታ ግን እንደ ተባለው ገና ከመታየቱ የሚጠፋ ነው፡፡ ታዲያ ንገረኝ እስኪ፥ በዚህ ሰው ነው የምትቀናው?
“ባለ ሥልጣን ሲኾን'ኮ ብዙ ተዕዕኖ ያደርጋል፡፡ ኹሉንም ነገር እርሱ እንደ ወደደው ማድረግ ይችላል፡፡ የተቃወሙትን ይቀጣል፤ ያወደሱትን ደግሞ ይሾማል ይሸልማል፡፡ ማድረግ የሚፈልገውን የማድረግ ኃይልም አለው" ልትል ትችላለህ፡፡ እነዚህ ንግግሮች የዚህ ዓለምና ከምድር ጋር የተጣበቁ ሰዎች ንግግሮች ናቸው፡፡ መንፈሳዊውን ሰው ምንም ማንም ሊጎዳው አይችልምና፡፡
በምን መንገድ አብዝቶ ሊጎዳው ይችላል? ከሥልጣኑ ሊሽረው ይችላልን? ታዲያ ይኼ ምንድን ነው? ይህ በርትዕ ከተደረገ ጠቀመው እንጂ አልጎዳውምና፡፡ ሥልጣነ ክህነትን ሳይገባው የተቀበለን ሰው ያህል እግዚአብሔርን የሚያሳዝነው የለምና፡፡ ያለ ርትዕ ካደረገበት ግን ተጎጂው ካህኑ ሳይኾን ሌላው ነው። ያለ ርትዕ መከራን የሚቀበልና ይህንን በአኰቴት የሚታገሥ ሰው በእግዚአብሔር ፊት የበለጠ ባለሟልነትን (ሞገስን) ያገኛልና፡፡
ስለዚህ እንዴት ምግባርን ተላብሰን ራሳችንንም ክደን መኖር እንደ አለብን እንጂ እንዴት ሥልጣን፣ ክብርና ጌትነት ማግኘት እንዳለብን ዓላማ አድርገን አንያዝ፡፡ እግዚአብሔር የማይወዳቸውን ብዙ ነገሮች እንዲያደርጉ የሥልጣን ቦታዎች ሰዎችን ያባብላሉና፡፡ ሥልጣንን እንደሚገባ ለመጠቀምም ጽኑዕ የነፍስ (መንፈሳዊ) ብርታት ያስፈልጋልና፡፡ ሥልጣን የሌለው ሰው በፈቃዱም ይኹን ያለ ፈቃዱ ራሱን እንደሚገዛ ኹሉ፥ ጽንዓ ነፍስ ኖሮት ሥልጣን የሚይዝ ሰውም እንደዚሁ ፈቅዶም ይኹን ሳይፈቅድ ራሱን ይገዛል፡፡
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመመው ድርሳን 40 ገጽ 330-333
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
“ጠላትህ ቢወድቅ ደስ አይበልህ፥ በመሰናከሉም ልብህ ሐሤት አያድርግ፡፡ እግዚአብሔር ያያልና፤ ደስም አያሰኘውምና፤ ቊጣውንም ከእርሱ ይመልሳልና'' እንዲል በጠላቶቻቸው ውድቀት ደስ ስለሚሰኙ ሰዎች እግዚአብሔር ቍጣውን የሚመልስ ከኾነ˖ ምንም በደል ባልሠሩ ሰዎች ላይ ይበልጥ ቍጣውን ይመልሳልና (ምሳሌ 24፥17-18)::
እንኪያስ ይህ ራሰ ብዙ የኾነውን አውሬ ፈጽመን ከእኛ እናቅ፡፡ የቅናት ራሶች (ዓይነቶች) በርግጥም ብዙ ናቸውና፡፡ የሚወደውን የሚወድ ሰው ከአንድ ቀራጭ የተሻለ ሥራ ካልሠራ፥ ምንም ያልበደለውን ሰው የሚጠላ ሰውስ ምን ተብሎ ሊጠራ ይችላል? ከአሕዛብ የባሰ ኾኖ ሳለስ እንዴት ከምረረ ገሃነም ማምለጥ ይቻለዋል? ስለዚህም ጭምር፥ ማለት መላእክትን ወይም ይልቅ የመላእክትን ጌታ እንድንመስል ታዘን እያለ ዲያብሎስን በመምሰላችን እጅግ አዝናለሁ። በእውነት በቤተ ክርስቲያን ሳይቀርብዙ ቅናት አለ፡፡ በዲያብሎስ ባርነት ሥር ካሉት ይልቅ ይበልጥ በእኛ ዘንድ ቅናት አለ፡፡ ስለዚህ እኛው ራሳችን ለራሳችን ሳይቀርማስተማር አለብን፡፡
እስኪ ንገረኝ! በባልንጀራህ ላይ የምትቀናው ለምንድን ነው? ሥልጣንንና በጎ ስምን ሲቀበል ስላየኸው ነውን? ክብርና ዝና ራሳቸውን ባልጠበቁ ሰዎች ላይ ምን ጉዳት እንደሚያመጣ አታስተውልምን? ወደ ትዕቢት፤ ወደ ውዳሴ ከንቱ፤ ወደ ዕብሪት፣ ወደ እንዝህላልነት፣ ይበልጥ ወደ ግድየለሽነት እንደሚወስዳቸው አታውቅምን? ይህ የምትቀናበት ሰው በእነዚህ ክፋቶች ከመያዙም በላይ ሥልጣኑና ዝናው ገና ከመታየታቸው የሚጠወልጉ ናቸው፡፡ እጅግ የሚከፋው ይህ ነውና፡- ከዚህ የሚመነጩ ክፋቶች የማያልፉ ሲኾኑ ከዚህ የሚገኘው ደስታ ግን እንደ ተባለው ገና ከመታየቱ የሚጠፋ ነው፡፡ ታዲያ ንገረኝ እስኪ፥ በዚህ ሰው ነው የምትቀናው?
“ባለ ሥልጣን ሲኾን'ኮ ብዙ ተዕዕኖ ያደርጋል፡፡ ኹሉንም ነገር እርሱ እንደ ወደደው ማድረግ ይችላል፡፡ የተቃወሙትን ይቀጣል፤ ያወደሱትን ደግሞ ይሾማል ይሸልማል፡፡ ማድረግ የሚፈልገውን የማድረግ ኃይልም አለው" ልትል ትችላለህ፡፡ እነዚህ ንግግሮች የዚህ ዓለምና ከምድር ጋር የተጣበቁ ሰዎች ንግግሮች ናቸው፡፡ መንፈሳዊውን ሰው ምንም ማንም ሊጎዳው አይችልምና፡፡
በምን መንገድ አብዝቶ ሊጎዳው ይችላል? ከሥልጣኑ ሊሽረው ይችላልን? ታዲያ ይኼ ምንድን ነው? ይህ በርትዕ ከተደረገ ጠቀመው እንጂ አልጎዳውምና፡፡ ሥልጣነ ክህነትን ሳይገባው የተቀበለን ሰው ያህል እግዚአብሔርን የሚያሳዝነው የለምና፡፡ ያለ ርትዕ ካደረገበት ግን ተጎጂው ካህኑ ሳይኾን ሌላው ነው። ያለ ርትዕ መከራን የሚቀበልና ይህንን በአኰቴት የሚታገሥ ሰው በእግዚአብሔር ፊት የበለጠ ባለሟልነትን (ሞገስን) ያገኛልና፡፡
ስለዚህ እንዴት ምግባርን ተላብሰን ራሳችንንም ክደን መኖር እንደ አለብን እንጂ እንዴት ሥልጣን፣ ክብርና ጌትነት ማግኘት እንዳለብን ዓላማ አድርገን አንያዝ፡፡ እግዚአብሔር የማይወዳቸውን ብዙ ነገሮች እንዲያደርጉ የሥልጣን ቦታዎች ሰዎችን ያባብላሉና፡፡ ሥልጣንን እንደሚገባ ለመጠቀምም ጽኑዕ የነፍስ (መንፈሳዊ) ብርታት ያስፈልጋልና፡፡ ሥልጣን የሌለው ሰው በፈቃዱም ይኹን ያለ ፈቃዱ ራሱን እንደሚገዛ ኹሉ፥ ጽንዓ ነፍስ ኖሮት ሥልጣን የሚይዝ ሰውም እንደዚሁ ፈቅዶም ይኹን ሳይፈቅድ ራሱን ይገዛል፡፡
(የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመመው ድርሳን 40 ገጽ 330-333
ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
❤75👍9🙏7
አንድ ምድራዊ ንጉሥ "ጠላቱን ያልወደደ ሰው በሞት ይቀጣል" ብሎ አዋጅ ቢያውጅ ሁሉም ሰው በአካለ ሥጋ ላለመሞት ሲል ሕጉን ለመጠበቅ የሚፋጠን አይደለምን? ወዮ! ምድራውያን ነገሥታት በሥጋዊ ሞት እንዳይቀጡን ብለን ፈርተን የሚያወጡትን ሕግ ለመፈፀም የምንፋጠን ሆነን ሳለ፥ ለነገሥታት ንጉሥ ለእግዚአብሔር ሕግ አለመታዘዛችን እንደ ምን ያለ ወቀሳ ያመጣብን ይሆን?
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
❤149🙏32👍1🏆1
ሰማዕት ቅድስት አርሴማ
መስከረም ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ከቅድስት አርሴማ ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።
ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።
እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።
ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።
ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።
የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።
ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።
አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።
ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕት ቅድስት አርሴማ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘወርኅ መስከረም)
መስከረም ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን ከቅድስት አርሴማ ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።
ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።
እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።
ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።
ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።
የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።
ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።
አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።
ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕት ቅድስት አርሴማ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(ስንክሳር ዘወርኅ መስከረም)
❤143🙏19😍3👍2
ተወዳጆች ሆይ፦
ወጣቷ ሰማዕት በብዙ ነገር አርአያ ልትሆነን ይገባል፡፡
√ ስለ ክርስቶስ ስትል የከፈለችውን ሰማዕትነት፣
√ ድንግልናን በብጽዐት ለመጠበቅ ስትል
የተቀበለችውን መከራ፣
√ ወጣትነቷ ሳያጓጓት ለእምነቷ የከፈለችውን ዋጋ፣
√ ንጽሕናዋን ቅድስናዋን ለመጠበቅ ያሳየችው ጽናት፣
√ በሕይወቷ ሳለች ከሠራችውም በላይ በሰማዕትነቷ ያፈራችውን ፍሬ ልናስብና ልንማርባት ደግሞም እንደ ዓቅማችን ልንመስላት ይገባናል፡፡
ይህን እንድናደርግ ሰውን በመውደዱ ሰው የኾነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!!
እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
ወጣቷ ሰማዕት በብዙ ነገር አርአያ ልትሆነን ይገባል፡፡
√ ስለ ክርስቶስ ስትል የከፈለችውን ሰማዕትነት፣
√ ድንግልናን በብጽዐት ለመጠበቅ ስትል
የተቀበለችውን መከራ፣
√ ወጣትነቷ ሳያጓጓት ለእምነቷ የከፈለችውን ዋጋ፣
√ ንጽሕናዋን ቅድስናዋን ለመጠበቅ ያሳየችው ጽናት፣
√ በሕይወቷ ሳለች ከሠራችውም በላይ በሰማዕትነቷ ያፈራችውን ፍሬ ልናስብና ልንማርባት ደግሞም እንደ ዓቅማችን ልንመስላት ይገባናል፡፡
ይህን እንድናደርግ ሰውን በመውደዱ ሰው የኾነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን!!!
እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!
❤202🙏32👍1
"ሰማዕትነት ስር ነው፡፡ ክርስቲያኖች ደግሞ ከዚኽ ስር የሚያቆጠቁጡ ምርጥ ዘሮች ናቸው፡፡ ብዙ ዛፍ የሚያቆጠቁጥበት ስር በለም አፈር ስለሚሸፈን አይታይም፡፡ ከዚያ በሚያቆጠቁጡ ዛፎች ግን ስሩ እንዴት እንደተመቸው ይታወቃል፡፡ ሰማዕታትም በግዙፉ ዓይናችን እንደምን ያለ አክሊል ሽልማት እንደተቀበሉ አይታየንም፡፡ ፍሬያቸው ግን እነርሱን መስለው እነርሱን አኽለው በሚጋደሉ ምርጥ ዘሮች ይታወቃል፡፡
ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡
ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የሰማዕት ቅዱስ አርሴማ ረድኤት በረከት አይለየን!
ሰማዕታት አክብሩን ብለው አይናገሩም፡፡ ነገር ግን በክርስቲያኖች ልብ የሚዘሩት ፍሬ ምእመናንን በፍቅር ያስገድዳል፡፡ እነርሱን እንዲመስሉ ያሳስባል፡፡
ሰማዕታት እንደ ፍቅረኛ ናቸው፡፡ አንድ ሰው የፍቅረኛውን ስም በየአጋጣሚው ያነሣል፡፡ በዓይነ ሕሊናው ያስባል፡፡ በተለያየ መልኩ ያያል፡፡ ሰማዕታትም ለክርስቲያኖች እንደዚያ ናቸው፡፡ እጅግ የተወደዱና በፍጹም ከሕሊና የማይጠፉ ተወዳጆች ናቸው፡፡ የልጆቻችንን ስም በነርሱ ስም የምንሰይመው፣ ሥዕላቸውን ሥለን የምንተሻሸው የምንስመው ለሰማዕታቱ ያለንን ጥልቅ ፍቅር የምንገልጽበት መንገድ ስለኾነ ነው፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
የሰማዕት ቅዱስ አርሴማ ረድኤት በረከት አይለየን!
❤114🙏24👍2
“ልጄ ሆይ ባለ መድኃኒትን ስማ ሕማምህን ቸል አትበል” መ.ሲራክ ፴፰፥፩
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
በሚል መሪ ቃል የጣና ቅዱስ ቂርቆስ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት በአይነቱ ልዩ የሆነ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመገንባት ተነስተናል። እርሶም ለዚህ ፕሮጀክት ከታች በተቀመጡት የባንክ አማራጮች አበርክቶ በማድረግ አሻራዎትን ያሳርፉ።
ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምሥክር ጉባኤ ቤት
TANA KIRKOS GEDAM 4TU G/METSAHFIT
1000680619488 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
TANA KIDUS KIRKOS YE-ABATOCH ENA YE-ENATOCH ANDNET GEDAM YE-ARATU GUBAYAT METSAHIFT MISKIR GUBAE BET
219553568 አቢሲኒያ ባንክ
2011111181981013 አባይ ባንክ
0068829811701 አሐዱ ባንክ
5020827358011 ዳሸን ባንክ
ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥር
+251 982333444
+251 983333444
+251 984333444 ይደውሉ።
❤24🙏5
#መንፈሳዊ_ጉዞ_ወደ_አክሱም_ጽዮን
የወልድያ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የፈለገ ሰላም ሰንበት ት/ቤት የኅዳር ጽዮን በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ #ርዕሰ_አድባራት_ወገዳማት_አክሱም_ጽዮን_ማርያም #መንፈሳዊ_ጉዞ አዘጋጅቷል! እርስዎም በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዘዋል!
#በጉዞዉ_የሚጎበኙ_ቅዱሳን_ቦታዎች
➛ አብርሃ ወአጽብሐ
➛ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም
➛ ጽዋ ትመስክር (ማኅበረ ዶጌ)
➛ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም
➛ #የጉዞ_መነሻ ቀን ህዳር 19/2018 ዓ.ም ሲሆን #መመለሻ ህዳር 22 /2018 ዓ.ም
#ትኬቱ_የሚገኘው፦
➛ በሰ/ት/ቤቱ ልማት ተቋም ሱቅ
➛ በሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት
➛ አዳጎ ሀገረስብከት ሕንጻ ማኅበረ ቅዱሳን ሱቅ
#ለበለጠ_መረጃ
09-68-60-71-29
09-91-79-29-84
ሼር ይደረግ
የወልድያ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል የፈለገ ሰላም ሰንበት ት/ቤት የኅዳር ጽዮን በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ #ርዕሰ_አድባራት_ወገዳማት_አክሱም_ጽዮን_ማርያም #መንፈሳዊ_ጉዞ አዘጋጅቷል! እርስዎም በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዘዋል!
#በጉዞዉ_የሚጎበኙ_ቅዱሳን_ቦታዎች
➛ አብርሃ ወአጽብሐ
➛ ደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም
➛ ጽዋ ትመስክር (ማኅበረ ዶጌ)
➛ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም
➛ #የጉዞ_መነሻ ቀን ህዳር 19/2018 ዓ.ም ሲሆን #መመለሻ ህዳር 22 /2018 ዓ.ም
#ትኬቱ_የሚገኘው፦
➛ በሰ/ት/ቤቱ ልማት ተቋም ሱቅ
➛ በሰ/ት/ቤቱ ጽ/ቤት
➛ አዳጎ ሀገረስብከት ሕንጻ ማኅበረ ቅዱሳን ሱቅ
#ለበለጠ_መረጃ
09-68-60-71-29
09-91-79-29-84
ሼር ይደረግ
❤54
ንስሐ በቅዱስ ኤፍሬም
ወንድሞቼ ሆይ! ጊዜ ሳለልን ንስሐ እንግባና ለንስሐ የሚገባ ፍሬ እናፍራ፡፡ ጌታችን ምን እንዳለ እስኪ አድምጡ፡- “ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይኾናል” /ሉቃ.15፥7/፡፡
ወንድሞቼ ሆይ! ስለምን ታድያ በኃጢአት፣ በስንፍና፣ በንዝህላል እንደተያዘዝን እንቆያለን? ስለምንድነው ተስፋ ቆርጠን የምንቆዝመው? በእኛ ንስሐ መግባት ምክንያት በሰማያት ታላቅ ደስታ የሚሆን ከሆነ ምንድነው የሚያስፈራን? ቅዱሳን መላዕክት ስለ እኛ ንስሐ እጅግ ደስ የሚላቸው ከሆነ ስለምንድነው እኛ ልል ዘሊል፣ ደንታ ቢስና ፈዛዛ የምንሆነው? የመላዕክት ጌታ ንስሐ ግቡ እያለ አስተምሮን ሳለ ምንድነው የምንፈራው? የማይከፈሉ ሦስት፣ የማይጠቀለሉ አንድ የሚሆኑ ሥላሴ ንስሐ እንገባ ዘንድ እየጠሩን ሳለ እኛ ያለምንም የንስሐ ፍሬ እንቆይ ዘንድ አግባብ ነውን?
ተወዳጆች ሆይ! በዚህ ጊዜአዊ ዓለም ርኵሰት ጣዕም አንታለል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ ምረረ ገሃነም ይጠብቀናል፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለማዊው እሳት እንድን ዘንድ አሁን ጥቂት ብናለቅስ ይሻለናል፡፡
ተወዳጆች ሆይ! እስኪ እናስተውል፡፡ ስለምንናገረው ነገርም ችላ የሚለው ሰው ከቶ አይገኝ፡፡ ክርስቶስ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ይመጣልና፡፡ ክርስቶስ ድንገት በመጣ ጊዜ በዙፋኑ ላይ ተቀምጦም ለሁሉም እንደየሥራው ሲከፍለው ማየት አያስፈራምን? የዚያን ጊዜ ሁሉም የየራሱን ሸክም ይሸከማል፡፡እያንዳንዱ ሰው በዚህ ምድር የዘራውን ያጭዳል፡፡ ሁሉም ዕራቆቱ ይቆማል፡፡ ሁሉም ወደ ክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ይቀርባል፡፡ የዚያን ጊዜ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡ ወንድም ወንድሙን ወይም ጓደኛ ጓደኛውን መርዳት አይችልም፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ልጆች ወላጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ባሎች ሚስቶቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ሁሉም በፍርሐትና በረዐድ በመንቀጥቀጥም የእግዚአብሔርን ፍርድ ይጠብቃል እንጂ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡
ወንድሞቼ ሆይ! ታድያ ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የምንሰንፈው? ለምንድነው ልል ዘሊል የምንሆነው? ለምንድነው በምግባር በሃይማኖት የማንዘጋጀው? ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የማናስተውለው? ለምንድነው ቃለ ሕይወትን ለመስማት የማንቻኰለው? ስለምንድነው ቃለ እግዚአብሔርን የማንሰማው? ስለምንድነው ቃለ ክርስቶስን ችላ የምንለው? ቃሉ በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አትገነዘቡምን? ቃለ ነቢያት ቃለ ሐዋርያት በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አታውቁምን? ካላወቃችኁ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ያላቸውን አድምጡ “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል” /ሉቃ.10፥16/፡፡ ዳግመኛም በሌላ አንቀጽ እንዲህ ብሏል፡- “የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርኩት ቃል ርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል” /ዮሐ.12፥48/፡፡ በመጨረሻው ቀን የሚፈርድብን ቃሉስ የትኛው ነው? በወንጌሉ እንዲሁም በሐዋርያትና በነቢያት አድሮ የተናገረው ቃሉ፡፡ እንኪያስ ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ችላ የምንለው አንኹን፡፡ “ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም” ያለውን አንርሳው /ማቴ.24፥35/፡፡
እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ሆይ! ኑ! አስፈሪው ቀን ሳይመጣ ቃሉን ሰምተን ንስሐ እንግባ፡፡ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንቀበል፡፡ እግዚአብሔር ዛሬ ምሕረቱን እንድንቀበል እንዲህ እያለ ያበረታታናልና፡- “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ” ማቴ.11፡28፡፡ በዚህ ቃሉ ትዕግሥተኛው፣ አፍቃሪውና ሰው ወዳጁ ጌታ ሁላችንም እንድን ዘንድ ይጠራናል፡፡ የጠራው የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ አይደለም፤ “ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ” ብሎ ሁላችንም እንጂ፡፡ “ባለጸጋም ቢሆን ድኻም ቢሆን ሁሉም ወደ እኔ ይምጣ፡፡ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፡፡ ወደ እኔ የሚመጣውስ ማን ነው ትዕዛዛቴን የሚጠብቀው፤ ቃሌን የሚሰማው፤ በላከኝም የሚያምነው፡፡” የክርስቶስን ቃል ሰምቶ ንስሐ የሚገባው ንስሐም ገብቶ የንስሐን ፍሬ የሚያፈራ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ የማይሰማው ግን እጅግ ጐስቋላ ሰው ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- “በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው” /ዕብ.10፥31/፡፡
ወንድሞቼ ሆይ! ጊዜ ሳለልን ንስሐ እንግባና ለንስሐ የሚገባ ፍሬ እናፍራ፡፡ ጌታችን ምን እንዳለ እስኪ አድምጡ፡- “ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይኾናል” /ሉቃ.15፥7/፡፡
ወንድሞቼ ሆይ! ስለምን ታድያ በኃጢአት፣ በስንፍና፣ በንዝህላል እንደተያዘዝን እንቆያለን? ስለምንድነው ተስፋ ቆርጠን የምንቆዝመው? በእኛ ንስሐ መግባት ምክንያት በሰማያት ታላቅ ደስታ የሚሆን ከሆነ ምንድነው የሚያስፈራን? ቅዱሳን መላዕክት ስለ እኛ ንስሐ እጅግ ደስ የሚላቸው ከሆነ ስለምንድነው እኛ ልል ዘሊል፣ ደንታ ቢስና ፈዛዛ የምንሆነው? የመላዕክት ጌታ ንስሐ ግቡ እያለ አስተምሮን ሳለ ምንድነው የምንፈራው? የማይከፈሉ ሦስት፣ የማይጠቀለሉ አንድ የሚሆኑ ሥላሴ ንስሐ እንገባ ዘንድ እየጠሩን ሳለ እኛ ያለምንም የንስሐ ፍሬ እንቆይ ዘንድ አግባብ ነውን?
ተወዳጆች ሆይ! በዚህ ጊዜአዊ ዓለም ርኵሰት ጣዕም አንታለል፡፡ እንዲህ ካልሆነ ግን እሳቱ የማይጠፋ ትሉ የማያንቀላፋ ምረረ ገሃነም ይጠብቀናል፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለማዊው እሳት እንድን ዘንድ አሁን ጥቂት ብናለቅስ ይሻለናል፡፡
ተወዳጆች ሆይ! እስኪ እናስተውል፡፡ ስለምንናገረው ነገርም ችላ የሚለው ሰው ከቶ አይገኝ፡፡ ክርስቶስ ድንገት እንደ ብርሃን ብልጭታ ይመጣልና፡፡ ክርስቶስ ድንገት በመጣ ጊዜ በዙፋኑ ላይ ተቀምጦም ለሁሉም እንደየሥራው ሲከፍለው ማየት አያስፈራምን? የዚያን ጊዜ ሁሉም የየራሱን ሸክም ይሸከማል፡፡እያንዳንዱ ሰው በዚህ ምድር የዘራውን ያጭዳል፡፡ ሁሉም ዕራቆቱ ይቆማል፡፡ ሁሉም ወደ ክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ይቀርባል፡፡ የዚያን ጊዜ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡ ወንድም ወንድሙን ወይም ጓደኛ ጓደኛውን መርዳት አይችልም፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ልጆች ወላጆቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ባሎች ሚስቶቻቸውን መርዳት አይችሉም፡፡ ሁሉም በፍርሐትና በረዐድ በመንቀጥቀጥም የእግዚአብሔርን ፍርድ ይጠብቃል እንጂ ማንም ማንንም መርዳት አይችልም፡፡
ወንድሞቼ ሆይ! ታድያ ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የምንሰንፈው? ለምንድነው ልል ዘሊል የምንሆነው? ለምንድነው በምግባር በሃይማኖት የማንዘጋጀው? ለምንድነው ጊዜ ሳለልን የማናስተውለው? ለምንድነው ቃለ ሕይወትን ለመስማት የማንቻኰለው? ስለምንድነው ቃለ እግዚአብሔርን የማንሰማው? ስለምንድነው ቃለ ክርስቶስን ችላ የምንለው? ቃሉ በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አትገነዘቡምን? ቃለ ነቢያት ቃለ ሐዋርያት በዚያ ሰዓት እንደሚፈርድብን አታውቁምን? ካላወቃችኁ ጌታችን ለደቀ መዛሙርቱ ያላቸውን አድምጡ “የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል” /ሉቃ.10፥16/፡፡ ዳግመኛም በሌላ አንቀጽ እንዲህ ብሏል፡- “የሚጥለኝ ቃሌንም የማይቀበለው እርሱ የሚፈርድበት አለው፤ እኔ የተናገርኩት ቃል ርሱ በመጨረሻው ቀን ይፈርድበታል” /ዮሐ.12፥48/፡፡ በመጨረሻው ቀን የሚፈርድብን ቃሉስ የትኛው ነው? በወንጌሉ እንዲሁም በሐዋርያትና በነቢያት አድሮ የተናገረው ቃሉ፡፡ እንኪያስ ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ችላ የምንለው አንኹን፡፡ “ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ ቃሌ ግን አያልፍም” ያለውን አንርሳው /ማቴ.24፥35/፡፡
እንኪያስ እጅግ የምወዳችሁ ሆይ! ኑ! አስፈሪው ቀን ሳይመጣ ቃሉን ሰምተን ንስሐ እንግባ፡፡ የእግዚአብሔርን ምሕረት እንቀበል፡፡ እግዚአብሔር ዛሬ ምሕረቱን እንድንቀበል እንዲህ እያለ ያበረታታናልና፡- “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ” ማቴ.11፡28፡፡ በዚህ ቃሉ ትዕግሥተኛው፣ አፍቃሪውና ሰው ወዳጁ ጌታ ሁላችንም እንድን ዘንድ ይጠራናል፡፡ የጠራው የተወሰኑ ሰዎችን ብቻ አይደለም፤ “ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ” ብሎ ሁላችንም እንጂ፡፡ “ባለጸጋም ቢሆን ድኻም ቢሆን ሁሉም ወደ እኔ ይምጣ፡፡ ወደ እኔም የሚመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም፡፡ ወደ እኔ የሚመጣውስ ማን ነው ትዕዛዛቴን የሚጠብቀው፤ ቃሌን የሚሰማው፤ በላከኝም የሚያምነው፡፡” የክርስቶስን ቃል ሰምቶ ንስሐ የሚገባው ንስሐም ገብቶ የንስሐን ፍሬ የሚያፈራ ሰው ንዑድ ክቡር ነው፡፡ የማይሰማው ግን እጅግ ጐስቋላ ሰው ነው፡፡ እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡- “በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው” /ዕብ.10፥31/፡፡
❤102🙏11👍1