++ ዛሬ ነገ ነው? ++
‘‘አባዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ
አባት እየተበሳጨ ‘ምንድን ነው የምትለኝ?’ አለ፡፡
ልጅ ‘ዛሬ ነገ ነው ወይ?’
አባት እንቅልፉ ስላልቀቀው ‘ሂድና እናትህን ጠይቃት በቃ ልተኛበት’ አለና እየተበሳጨ ፊቱን ሸፈነ፡፡
ልጅ ወደ እናት ሔዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት
‘’እማዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ እናት ፈገግ አለች
‘ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?’’ አለች የልጅዋን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች
‘ትናንት አስተማሪያችን ‘ነገ ትምህርት የለም’ ብላን ነበር ፤ ዛሬ ነገ ነው?’’
እናት ‘እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው’ አለች እየሳቀች፡፡
ይህ ለሕጻኑ ጥያቄ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም፡፡ ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው፡፡ ለነገ እንማራለን ፣ ለነገ እንሠራለን ፣ ለነገ እንገነባለን፡፡ የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ፡፡ ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን፡፡ ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን፡፡ እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን፡፡ መጽሐፍ ‘’ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና’ ‘ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ! ይላል፡፡ /ያዕ 4፡15 ፤ ማቴ 6፡34/
ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሣሪያም አንዱ ‘ነገ’ በሚል ቃል ማዘናጋት ነው፡፡ ነገ እማራለሁ ፣ ነገ እሔዳለሁ ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ ፣ ነገ ንስሓ እገባለሁ ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሠራለሁ ነገ ነገ ነገ
ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉሥ በመቅሠፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር፡፡ በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ ፦ ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው፡፡ ፈርኦንም ፦ ነገ አለ፡፡
እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው፡፡ ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት ክፉ አመል አለብህ ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ ፣ አልስተካከል ያለህ ድክመት ፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? ‘አቤቱ አሁን አድን’ ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ
ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ ፣ ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ ፣ ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም፡፡ ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግሥቱም መልሳችን ነገ ነው፡፡ ‘ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው’ እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሠራ የማንፈልገውን እየሠራን እንኖራለን፡፡ ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም ‘የተወደደው ሰዓት አሁን ነው’ መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትሥጥ፡፡ ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው፡፡ ማንም ሊሠራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት፡፡
አሁኑኑ ተነሥ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመሥራት ፣ ክፉውን ነገር ለመተው ነገ አደርገዋለሁ አትበል
ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅህ ‘ነገ አደርገዋለሁ’ ብለህ ነበር ፤ ዛሬም ‘ነገ’ አትበል ምክንያቱም ሕጻኑ እንዳለው ‘ዛሬ ነገ ነው’
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 8 /2012 ዓ.ም.
ቪክቶሪያ አውስትራሊያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
‘‘አባዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ አለ አቡሽ አባቱን ከተኛበት እየቀሰቀሰ
አባት እየተበሳጨ ‘ምንድን ነው የምትለኝ?’ አለ፡፡
ልጅ ‘ዛሬ ነገ ነው ወይ?’
አባት እንቅልፉ ስላልቀቀው ‘ሂድና እናትህን ጠይቃት በቃ ልተኛበት’ አለና እየተበሳጨ ፊቱን ሸፈነ፡፡
ልጅ ወደ እናት ሔዶ ያንኑ ጥያቄ ደገመላት
‘’እማዬ ዛሬ ነገ ነው?’’ እናት ፈገግ አለች
‘ምን ማለት ነው ደግሞ ዛሬ ነገ ነው? ማለት?’’ አለች የልጅዋን የተጋለጠ ደረት እየሸፈነች
‘ትናንት አስተማሪያችን ‘ነገ ትምህርት የለም’ ብላን ነበር ፤ ዛሬ ነገ ነው?’’
እናት ‘እ እ አዎ ልክ ነህ ዛሬ ነገ ነው’ አለች እየሳቀች፡፡
ይህ ለሕጻኑ ጥያቄ የተሰጠ መልስ ለእኛም ሳያስፈልገን አይቀርም፡፡ ብዙዎቻችን የምንኖረው ለነገ ነው፡፡ ለነገ እንማራለን ፣ ለነገ እንሠራለን ፣ ለነገ እንገነባለን፡፡ የተፈጠርነው ለዘላለማዊነት ነውና እንደምንኖር አስበን ማቀዳችን ባልከፋ፡፡ ነገር ግን ላላየነው ነገ ስናስብ ያየናትን ዛሬ እንዘነጋታለን፡፡ ለነገ ደመና የዛሬን ፀሐይ እንገፋታለን፡፡ እንዳቀድን እንዳለምን ለመኖር ስንዘጋጅ እንሞታለን፡፡ መጽሐፍ ‘’ነገ ወደዚህ ከተማ እንሄዳለን በዚያም ዓመት እንኖራለን እንነግድማለን እናተርፍማለን የምትሉ እናንተ፥ ተመልከቱ፥ ነገ የሚሆነውን አታውቁምና’ ‘ነገ ለራሱ ያስባልና ለነገ አትጨነቁ! ይላል፡፡ /ያዕ 4፡15 ፤ ማቴ 6፡34/
ሰይጣን ከሚጠቀምበት ሰውን ማጥቂያ መሣሪያም አንዱ ‘ነገ’ በሚል ቃል ማዘናጋት ነው፡፡ ነገ እማራለሁ ፣ ነገ እሔዳለሁ ፣ ነገ የታመመ እጠይቃለሁ ፣ ነገ ንስሓ እገባለሁ ፣ ነገ ወደ እግዚአብሔር እመለሳለሁ ፣ ነገ ይሄንን መልካም ነገር እሠራለሁ ነገ ነገ ነገ
ፈርኦን የሚባለው ጨካኝ ንጉሥ በመቅሠፍት ጓጉንቸር ተወርሮ ነበር፡፡ በመጨረሻም እስራኤልን እለቃለሁ ሲል ሙሴ ፦ ጓጉንቸሮቹ ከቤትህ እንዲጠፉ መቼ ልጸልይልህ? አለው፡፡ ፈርኦንም ፦ ነገ አለ፡፡
እንግዲህ ዛሬን ከጓጉንቸሮች ጋር ማደር ፈልጓል ማለት ነው፡፡ ወዳጄ በሕይወትህ ውስጥ ጓጉንቸሮች ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት ክፉ አመል አለብህ ፣ ምን ዕረፍት ያሳጣህ ፣ ሰላም የነሳህ ነገር አለ? አልላቀቅ ያለህ ሱስ ፣ አልስተካከል ያለህ ድክመት ፣ አልድን ያለህ ቁስል ምንድን ነው? እርሱን መቼ ትላቀቀዋለህ? መቼ መዳን ትሻለህ? ነገ ካልከኝ ፈርኦን መሆንህ ነው? ‘አቤቱ አሁን አድን’ ካልክ ደግሞ እንደ ዳዊት ትሰማለህ
ነገ ይህንን ሱስ እተዋለሁ ፣ ነገ ይህን ልማድ እላቀቃለሁ ፣ ነገ ይህን መልካም ነገር አደርጋለሁ የሚል ቀጠሮ ሠርቶ አያውቅም፡፡ ነገ እንላለን እንጂ የሚገርመው በማግሥቱም መልሳችን ነገ ነው፡፡ ‘ዱቤ ዛሬ የለም ነገ ነው’ እንደሚለው የብልጥ ባለሱቅ ማስታወቂያ ነገ ስንሔድ ነገ እየተባለ የምንፈልገውን ሳንሠራ የማንፈልገውን እየሠራን እንኖራለን፡፡ ወዳጄ ነገ የአንተ አይደለችም ‘የተወደደው ሰዓት አሁን ነው’ መኖርህን ሳታውቅ ቀጠሮ አትሥጥ፡፡ ኃይልህ በአሁን ላይ ብቻ ነው፡፡ ማንም ሊሠራባት የማይችላት ሌሊት ሳትመጣ አሁንን ተጠቀምባት፡፡
አሁኑኑ ተነሥ ያሰብከውን መልካም ነገር ለመሥራት ፣ ክፉውን ነገር ለመተው ነገ አደርገዋለሁ አትበል
ትናንት ኅሊናህ ሲጠይቅህ ‘ነገ አደርገዋለሁ’ ብለህ ነበር ፤ ዛሬም ‘ነገ’ አትበል ምክንያቱም ሕጻኑ እንዳለው ‘ዛሬ ነገ ነው’
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 8 /2012 ዓ.ም.
ቪክቶሪያ አውስትራሊያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
+ ጌታ ያልተወለደባት ሥፍራ +
ጌታችን በተወለደባት ከተማ ቤተልሔም በተደጋጋሚ በአስጎብኚነት ሔጄ ተሳልሜያለሁ:: የተቀደሰችውን ጌታ የተወለደባትንና ኮከብ የቆመባትን ሥፍራ በተሳለምኩ ቁጥር ግን ሁሌ ትዝ የሚለኝ አንድ የዓለማችን ቁጥር አንድ ዕድለ ቢስ ቦታ አለ::
የዓለም መድኃኒት የተኛበትን በረት በሰልፍ የዓለም ሕዝብ ቆሞ ሲሳለም የቱ ጋር እንደሆነ ባላውቅም ትዝ እያለኝ የሚያሳዝነኝ አፍ ቢኖረው ጮኾ የሚያለቅስ አንድ ቦታ አለ:: ስለቦታው ላስታውሳችሁ::
ጌታን ለመወለድ የቀረበችው ድንግል ማርያምና ዮሴፍ በዚያች ምሽት ማደሪያ ፍለጋ ሲንከራተቱ ቆይተው ነበር:: ወደ አንድ የእንግዶች ማደሪያ ቤት ሔደው ሲጠይቁ ቦታ የለንም ብለው ከበር መለሱአቸው:: ስለዚህ ዮሴፍና ድንግል ማርያም ያንን የእንግዶች ማደሪያ ትተው ወደ ከብቶች በረት ገሰገሱ:: በዚያ ግርግም ውስጥም የዓለም መድኃኒት ክርስቶስ ተወለደ::
እስቲ ዛሬ ለከብቶቹ በረት "በጎል ሰከበ" (በበረት ተኛ) እያልን መዘመራችንን ትተን ጌታ ላልተወለደበት የእንግዶች ማደሪያ ሥፍራ ትንሽ አብረን እናልቅስለት:: በዓለማችን እጅግ ዕድለ ቢስ ስለሆነው ስለዚያ ቤት ጥቂት ሙሾ ማውረድ አማረኝ::
የዚያ ቤት ባለቤቶች ያንን ሌሊት ከደጃፋቸው የቆመችው አንዲት ልትወልድ የተቃረበች ወጣት ነበረች:: "ቦታ የለንም" ብለው ሲመልሱአት ምንም አልመሰላቸውም ትንሽ እንኳን ቅር አላላቸውም ነበር:: በማኅፀንዋ ያለው ጨለማውን ዓለም የሚያበራ ፀሐይ : የዓለምን ጥም የሚያረካ ውኃ : በደሙ ዓለምን የሚያጥብ መድኃኒት እንደሆነ አላወቁም ነበርና “ቦታ የለንም" አሉ::
እናንተ የዓለማችን ዕድለ ቢስ ሰዎች ሆይ ያቺን ምሽት ማንን ከበር እንደመለሳችሁ እስቲ እኔ ልንገራችሁ::
ከበር የቆመችው ማን እንደሆነች : በማሕፀንዋ የያዘችው ማን እንደሆነ ብታውቁ ኖሮ ቀድማችሁ ያስገባችሁዋቸውን እንግዶች ሁሉ "በሕግ አምላክ
ውጡልን" ብላችሁ ማስወጣታችሁ አይቀርም ነበርና ትሰሙ እንደሆን እኔ ልንገራችሁ:: ብታውቁአት ኖሮ እንደ ዘመድዋ ኤልሳቤጥ "የጌታችን እናት ወደ እኛ ትመጪ ዘንድ እኛ ምን ነን?" ትሉአት ነበር::
እናንተ የእንግዶች ማደሪያ ባለቤቶች ሆይ! እርግጥ ነው እናንተ ከበር የመለሳችሁት አንዲት የፀነሰች የገሊላ ናዝሬት እንግዳን ብቻ ነበር:: ለእርስዋ ቦታ የለም ብሎ መናገርም ቀላል ነገር መስሎአችሁ ሊሆን ይችላል::
እመኑኝ ለእርስዋ "አንቺን ለማሳደር ቦታ የለንም" ስትሉአት ግን ማንን እንደመለሳችሁት አላወቃችሁም:: እርግጥ ነው ቦታው በእንግዳ ተይዞአል ትሉኝ ይሆናል:: ግን ደግሞ ለመውለድ ለተቃረበች ወጣት ሥፍራ ቢጠፋ እንኳን የራስንም አልጋ ቢሆን መልቀቅ አይገባም ነበር? ለአንዲት ለምትወልድ እናት ቸርነት ማድረግ ሰብአዊ ግዴታ አይደለምን? ብታደርጉት ኖሮ የምታገኙት ከጠበቃችሁት በላይ በሆነ ነበር::
እርስዋን ብታስገቡአት ኖሮ የሰማይና ምድሩ ንጉሥ ኢየሱስ ከቤታችሁ ይገባ ነበር:: በቤታችሁ ውስጥ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ መሰላል ተዘርግቶ እልፍኛችሁ በመላእክት ዝማሬ : በእረኞች ደስታ በሰብአ ሰገል ሥጦታ ይጥለቀለቅ ነበር:: እናንተ ከሞታችሁም በኁዋላ ጭምር ለዘመናት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የዓለም ሕዝብ እየመጣ የቤታችሁን ወለል ይስም : በደጃፋችሁ ይንከባለል ነበር:: አቤት ድንግል ማርያምን "ቦታ የለንም” ብሎ ከደጅ መመለስ የሚያስከፍለው ዋጋ የሚያሳጣው ጸጋ እንዴት ያለ ነው?! ምነው እንደ እናንተ በዚያ ዘመን በኖርኩና ድንግል ማርያምን ከደጄ ቆማ አግኝቻት ከአልጋዬ ወርጄ በተቀበልኩዋት!
እመኑኝ ለድንግሊቱ ማርያም ቦታ የለኝም ያለ ሰው ቦታ ያጣው ለኢየሱስ ነው:: እርስዋን ወደ ቤቱ ግቢ ያላት ሰው ግን ጌታን ወደ ቤቱ ያስገባዋል:: ጌታ ያለው ደግሞ ሁሉም አለው:: አይ እናንተዬ! ሌላ እንግዳ ከምታግበሰብሱ ለአንዲት ድንግል ቦታ ብትሠጡአት ኖሮ ቤታችሁ ሰማይ ይሆን ነበር::
የፍልስጤም ግዛት በሆነችዋ የቤተልሔም ከተማ ስመላለስና ስሳለም ብኖርም ድንግልን ከደጅ የመለሱትን ሰዎች ቤት አድራሻ እስከዛሬ ድረስ እዚህ ነው ብሎ የሚነግረኝ ሰው አላገኘሁም:: ለነገሩ ለእርስዋ ሥፍራ ያጣ ሰው ምን አድራሻ አለው? መቼም ከሞቱ ሁለት ሺህ ዓመት ያለፋቸው ቢሆንም እኔ ግን ዛሬም ድረስ ሳስባቸው ስለ ተሳሳተ ውሳኔያቸውና ዕድለ ቢስነታቸው አዝናለሁ::
ድንግሊቱን ላስጠጋውና ልጅዋን ወልዳ ላስተኛችበት በረት "በጎል በጎል ሰብዓ ሰገል" እያልኩ ስዘምርለት ባድርም ድንግሊቱን ከደጅ ቦታ የለም ብሎ ለመለሰውና ጌታ ላልተወለደበት ሥፍራ ግን ለዘላለም አዝናለሁ!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 25 2013 ዓ ም
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
ጌታችን በተወለደባት ከተማ ቤተልሔም በተደጋጋሚ በአስጎብኚነት ሔጄ ተሳልሜያለሁ:: የተቀደሰችውን ጌታ የተወለደባትንና ኮከብ የቆመባትን ሥፍራ በተሳለምኩ ቁጥር ግን ሁሌ ትዝ የሚለኝ አንድ የዓለማችን ቁጥር አንድ ዕድለ ቢስ ቦታ አለ::
የዓለም መድኃኒት የተኛበትን በረት በሰልፍ የዓለም ሕዝብ ቆሞ ሲሳለም የቱ ጋር እንደሆነ ባላውቅም ትዝ እያለኝ የሚያሳዝነኝ አፍ ቢኖረው ጮኾ የሚያለቅስ አንድ ቦታ አለ:: ስለቦታው ላስታውሳችሁ::
ጌታን ለመወለድ የቀረበችው ድንግል ማርያምና ዮሴፍ በዚያች ምሽት ማደሪያ ፍለጋ ሲንከራተቱ ቆይተው ነበር:: ወደ አንድ የእንግዶች ማደሪያ ቤት ሔደው ሲጠይቁ ቦታ የለንም ብለው ከበር መለሱአቸው:: ስለዚህ ዮሴፍና ድንግል ማርያም ያንን የእንግዶች ማደሪያ ትተው ወደ ከብቶች በረት ገሰገሱ:: በዚያ ግርግም ውስጥም የዓለም መድኃኒት ክርስቶስ ተወለደ::
እስቲ ዛሬ ለከብቶቹ በረት "በጎል ሰከበ" (በበረት ተኛ) እያልን መዘመራችንን ትተን ጌታ ላልተወለደበት የእንግዶች ማደሪያ ሥፍራ ትንሽ አብረን እናልቅስለት:: በዓለማችን እጅግ ዕድለ ቢስ ስለሆነው ስለዚያ ቤት ጥቂት ሙሾ ማውረድ አማረኝ::
የዚያ ቤት ባለቤቶች ያንን ሌሊት ከደጃፋቸው የቆመችው አንዲት ልትወልድ የተቃረበች ወጣት ነበረች:: "ቦታ የለንም" ብለው ሲመልሱአት ምንም አልመሰላቸውም ትንሽ እንኳን ቅር አላላቸውም ነበር:: በማኅፀንዋ ያለው ጨለማውን ዓለም የሚያበራ ፀሐይ : የዓለምን ጥም የሚያረካ ውኃ : በደሙ ዓለምን የሚያጥብ መድኃኒት እንደሆነ አላወቁም ነበርና “ቦታ የለንም" አሉ::
እናንተ የዓለማችን ዕድለ ቢስ ሰዎች ሆይ ያቺን ምሽት ማንን ከበር እንደመለሳችሁ እስቲ እኔ ልንገራችሁ::
ከበር የቆመችው ማን እንደሆነች : በማሕፀንዋ የያዘችው ማን እንደሆነ ብታውቁ ኖሮ ቀድማችሁ ያስገባችሁዋቸውን እንግዶች ሁሉ "በሕግ አምላክ
ውጡልን" ብላችሁ ማስወጣታችሁ አይቀርም ነበርና ትሰሙ እንደሆን እኔ ልንገራችሁ:: ብታውቁአት ኖሮ እንደ ዘመድዋ ኤልሳቤጥ "የጌታችን እናት ወደ እኛ ትመጪ ዘንድ እኛ ምን ነን?" ትሉአት ነበር::
እናንተ የእንግዶች ማደሪያ ባለቤቶች ሆይ! እርግጥ ነው እናንተ ከበር የመለሳችሁት አንዲት የፀነሰች የገሊላ ናዝሬት እንግዳን ብቻ ነበር:: ለእርስዋ ቦታ የለም ብሎ መናገርም ቀላል ነገር መስሎአችሁ ሊሆን ይችላል::
እመኑኝ ለእርስዋ "አንቺን ለማሳደር ቦታ የለንም" ስትሉአት ግን ማንን እንደመለሳችሁት አላወቃችሁም:: እርግጥ ነው ቦታው በእንግዳ ተይዞአል ትሉኝ ይሆናል:: ግን ደግሞ ለመውለድ ለተቃረበች ወጣት ሥፍራ ቢጠፋ እንኳን የራስንም አልጋ ቢሆን መልቀቅ አይገባም ነበር? ለአንዲት ለምትወልድ እናት ቸርነት ማድረግ ሰብአዊ ግዴታ አይደለምን? ብታደርጉት ኖሮ የምታገኙት ከጠበቃችሁት በላይ በሆነ ነበር::
እርስዋን ብታስገቡአት ኖሮ የሰማይና ምድሩ ንጉሥ ኢየሱስ ከቤታችሁ ይገባ ነበር:: በቤታችሁ ውስጥ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ መሰላል ተዘርግቶ እልፍኛችሁ በመላእክት ዝማሬ : በእረኞች ደስታ በሰብአ ሰገል ሥጦታ ይጥለቀለቅ ነበር:: እናንተ ከሞታችሁም በኁዋላ ጭምር ለዘመናት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የዓለም ሕዝብ እየመጣ የቤታችሁን ወለል ይስም : በደጃፋችሁ ይንከባለል ነበር:: አቤት ድንግል ማርያምን "ቦታ የለንም” ብሎ ከደጅ መመለስ የሚያስከፍለው ዋጋ የሚያሳጣው ጸጋ እንዴት ያለ ነው?! ምነው እንደ እናንተ በዚያ ዘመን በኖርኩና ድንግል ማርያምን ከደጄ ቆማ አግኝቻት ከአልጋዬ ወርጄ በተቀበልኩዋት!
እመኑኝ ለድንግሊቱ ማርያም ቦታ የለኝም ያለ ሰው ቦታ ያጣው ለኢየሱስ ነው:: እርስዋን ወደ ቤቱ ግቢ ያላት ሰው ግን ጌታን ወደ ቤቱ ያስገባዋል:: ጌታ ያለው ደግሞ ሁሉም አለው:: አይ እናንተዬ! ሌላ እንግዳ ከምታግበሰብሱ ለአንዲት ድንግል ቦታ ብትሠጡአት ኖሮ ቤታችሁ ሰማይ ይሆን ነበር::
የፍልስጤም ግዛት በሆነችዋ የቤተልሔም ከተማ ስመላለስና ስሳለም ብኖርም ድንግልን ከደጅ የመለሱትን ሰዎች ቤት አድራሻ እስከዛሬ ድረስ እዚህ ነው ብሎ የሚነግረኝ ሰው አላገኘሁም:: ለነገሩ ለእርስዋ ሥፍራ ያጣ ሰው ምን አድራሻ አለው? መቼም ከሞቱ ሁለት ሺህ ዓመት ያለፋቸው ቢሆንም እኔ ግን ዛሬም ድረስ ሳስባቸው ስለ ተሳሳተ ውሳኔያቸውና ዕድለ ቢስነታቸው አዝናለሁ::
ድንግሊቱን ላስጠጋውና ልጅዋን ወልዳ ላስተኛችበት በረት "በጎል በጎል ሰብዓ ሰገል" እያልኩ ስዘምርለት ባድርም ድንግሊቱን ከደጅ ቦታ የለም ብሎ ለመለሰውና ጌታ ላልተወለደበት ሥፍራ ግን ለዘላለም አዝናለሁ!
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ታኅሣሥ 25 2013 ዓ ም
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
Audio
+ተግባራዊ ክርስትና ተከታታይ ትምህርት
+ መንፈሳዊ አገልግሎት +
ክፍል አምስት~፭
መ/ር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
+ መንፈሳዊ አገልግሎት +
ክፍል አምስት~፭
መ/ር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ! "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
የፌስቡክ ገጽ :- https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
የቴሌግራም ቻናል : https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
የዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
"ሰይጣን የማይነካው ዕቃ "
በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ።
የበዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ።
ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ።
"እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ
በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው "
ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው።
ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው።
" የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው።
ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት።
ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት።
ይህን ግዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት።
በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም። አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ።
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ»
«በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!
ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
በአንድ ሐገር ድንገት የአንድ" ጠንቋይ ዝና ከዳር ዳር ተሰማ ። ሰውዬው የማያሳየው ምትሐት የለም። አንበሳ ላለ አንበሳ፣ ነብር ላለ ነብር፣ የሞተ ዘመዴን ላለ የሞተ ዘመዱን፣ የጠፋብኝን ዕቃ ከቤት ፈልገህ አምጣልኝ ላለ ዕቃውን ያመጣለታል። እንደሚታወቀው አጋንንት ከክብራቸው የተዋረዱ መላእክት ናቸው። መላእክት ደግሞ በፈለጉት ሁኔታ መገለጥ ይችላሉ። ይህ ጠንቋይ የሚሰጣቸውን ገጸ ባሕርይ ተቀብለው አንዴ አንበሳ፣ አንዴ ነብር፣ አንዴ ሰው እየሆኑ የሚተውኑት እንግዲህ አጋንንቱ ነበሩ።
የበዚህ ጠንቋይ ዝና ወደ ንጉሱ ደረሰ። ንጉሱ ደግሞ ክርስቲያን ቢሆንም ከመጸሐፍ ቅዱስ ይልቅ እንዲህ ያለ ተአምር እዚህ ቦታ ተፈጸመ ሲባል ለማየተት የሚሮጥ ሰው ነበር። ተአምር የሚወድ ሰው ደግሞ ክርስቲያንም ቢሆን ሰይጣን በሚሰራው ምትሐት መታለሉ የማይቀር ነው። ስለዚህ ይህ ንጉስ የተማረውን መጽሐፍ ቅዱስ ዘንግቶ በጠንቋዩ ምትሐት አመነ።
ይህንን የሰሙ የንጉሱ ንስሐ አባት ነገሩን ሰምተው ወደ ቤተ መንግሥት ሲሮጡ ደረሱ። ሲደርሱ ንጉሡ ከቁም ነገር አልቆጠራቸውም። እሱ የጠንቋይ ትርዒት ማየት ቀጠለ።
"እስቲ አሁን ደግሞ እእእ ነጭ ፈረስ አምጣልኝ" ማለቱን ቀጠለ
በነገሩ ያዘኑት "ኧረ ንጉሥ ሆይ ይተዉ፡ ይህ እኮ የሰይጣን ምትሐት ነው "
ብለው ሊያስረዱት ሲሉ በቁጣ አስቆማቸው።
ተአምር የሚከተል ሰው መቼስ ቢነግሩት አይሰማም። ጭራሽ እንዲያው ለንስሐ አባቱ እንዲህ አላቸው።
" የሰይጣን ስራ ነው አትበሉ፤ ቅናት ነው ይኼማ,,,, ይልቅ እርስዎም የሚፈልጉትን ነገር ይጠይቁት ያምጣልዎት!"አላቸው።
ጠንቋዩ «የፈለጉትን ላምጣልውት,,,,,ምን ይፈልጋሉ,,,, " የሞተ ዘመድ አለዎት,,,,, ወይስ ከቤትዎ,,,, » አላቸው በኩራት።
ካህኑ ውስጣቸው በመንፈሳዊ ቅናት ተቃጠለ። « እንግዲያውስ የፈለኩትን ማምጣት ከቻልህ ወደ ቤተ መቅደስ ሔደህ ልብሰ ተክህኖዬ ውስጥ መስቀል አለ እርሱን ይዘህልኝ ና » አሉት።
ይህን ግዜ ጠንቋዩ ገና ድግምቱን ሲጀምር አጋንንቱ እላዩ ላይ ሰፍረው ጣሉት።
በካህኑ ፊት ወደቀ። ሰይጣን ምንም ነገር ማምጣት ይችል ይሆናል። መስቀሉን ግን ማምጣት አይችልም። አባቶቻችን ሰይጣን እንኳን መስቀል ቀርቶ መስቀለኛ መንገድም አይወድም ይላሉ።
የጌታችን ቅዱስ መስቀል ሆይ ቅዱስ ዳዊት እንዳለ «ብከ ንወግዖሙ ለኩሎሙ ጸርነ»
«በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን!
ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ስድብ ኃጢአት ባይሆን ኖሮ መሰደብ የሚገባው ዲያቢሎስ ነው:: ፍጥረት ሁሉ ስድብ ቢያዋጣ ለዲያቢሎስ የሚመጥን አይሆንም:: የክፋት ምንጭ ለሆነ ለእርሱ ሁሉም ክፉ ቃል መገለጫው ነው::
ይሁንና ቅዱስ ሚካኤል ይህንን ክፉ ጠላት ደፍሮ አልሰደበውም:: "እግዚአሔር ይገሥጽህ!" አለው:: (ይሁ 1:9)
እንደ ሚካኤል ንጹሕ በእኛ ዘን ማን አለ? እንደ ዲያቢሎስስ ክፉ በእኛ ዘንድ ማን አለ?
መልእክቱ ግልጽ ነው:: አንሆንም እንጂ እንደ ሚካኤል ንጹሕ ብንሆን እንኳን እንደ ሰይጣን የከፋን ሰው እንኳን መሳደብ አንችልም::
የመላእክት አለቃ ሚካኤል ከሥልጣኑ የወረደውን የቀድሞውን የመላእክት አለቃ ዲያቢሎስን አንድም ክፉ ቃል አልተናገረውም:: አንዱ ከሥልጣኑ ወድቆ ሌላው ሲሾም አዲሱ ተሿሚ ስለወደቀው ምን እንደሚል እናውቃለን:: አንደበቱ ስድብ በመናገር ያልረከሰው ቅዱስ ሚካኤል ግን ወድቆ በማያርፈው ዲያቢሎስ ላይ የስድብን ቃል አልተናገረም::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Deacon Henok Haile
የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ
FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
Telegram: https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
ይሁንና ቅዱስ ሚካኤል ይህንን ክፉ ጠላት ደፍሮ አልሰደበውም:: "እግዚአሔር ይገሥጽህ!" አለው:: (ይሁ 1:9)
እንደ ሚካኤል ንጹሕ በእኛ ዘን ማን አለ? እንደ ዲያቢሎስስ ክፉ በእኛ ዘንድ ማን አለ?
መልእክቱ ግልጽ ነው:: አንሆንም እንጂ እንደ ሚካኤል ንጹሕ ብንሆን እንኳን እንደ ሰይጣን የከፋን ሰው እንኳን መሳደብ አንችልም::
የመላእክት አለቃ ሚካኤል ከሥልጣኑ የወረደውን የቀድሞውን የመላእክት አለቃ ዲያቢሎስን አንድም ክፉ ቃል አልተናገረውም:: አንዱ ከሥልጣኑ ወድቆ ሌላው ሲሾም አዲሱ ተሿሚ ስለወደቀው ምን እንደሚል እናውቃለን:: አንደበቱ ስድብ በመናገር ያልረከሰው ቅዱስ ሚካኤል ግን ወድቆ በማያርፈው ዲያቢሎስ ላይ የስድብን ቃል አልተናገረም::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
Deacon Henok Haile
የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ
FB: https://www.facebook.com/officialHenokhaile/
Telegram: https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile
Instagram: https://www.instagram.com/p/CBnMF0nnhcQ/?igshid=549jvl607bv4
Youtube: https://www.youtube.com/channel/UCOaVsWC05aUjeqIEW3fWj7g
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ለአራት ቀናት ብቻ ለሞተው አልዓዛር ያለቀሰ ጌታ ለዘመናት በኃጢአት ለሞትን ለእኛ ምንኛ ያለቅስ ይሆን? ሰውነታች በበደል ለረከሰ ፣ በምኞት መቃብር ለተቀበርን ፣ በዝሙት ለተበላሸን ፣ በጥላቻ ለሸተትን ለእኛ ክርስቶስ ምንኛ ያለቅስ ይሆን? የኃጢአት ድንጋይ ተጭኖን ፣ የፍትወት መግነዝ ተጠምጥሞብን ላለን ለእኛ የጌታ ዕንባ ምን ያህል ይፈስስልን ይሆን? አልዓዛርስ ውጣ ቢባል ይወጣል ፣ ካለንበት ኃጢአት መቃብር መውጣት ለማንፈልግ ለእኛ ጌታ እንደምን ያለቅስ ይሆን? የእኛ ሞት ከአልዓዛር ሞት በላይ ዘልቆ የማይሰማው ይመስላችኋል? እንዴት አይሰማውም? ለአልዓዛር ዕንባውን ያፈሰሰው ጌታ ለእኛ እኮ ያፈሰሰው ደሙን ነው ።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሕዝቡም_ይጠብቁት_ነበር_የሉቃስ_ወንጌል_ክፍል_ዐስር_Part_10_በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ_HD
<unknown>
የሉቃስ ወንጌል ተከታታይ ትምህርት ክፍል {፲}
+ሕዝቡም ይጠብቁት ነበር +
💖በመምህር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ💖
+ሕዝቡም ይጠብቁት ነበር +
💖በመምህር ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ💖
የጌታ_መልአክ_የሉቃስ_ወንጌል_ክፍል_አምስት_Part_5_በዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ_HD
<unknown>
የሉቃስ ወን ጌል ተከታታይ ትምህርት ክፍል አምስት| ፭|
[የጌታ መላአክ]
🌻 በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 🌻
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile👈
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile 👈
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile 👈
[የጌታ መላአክ]
🌻 በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 🌻
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile👈
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile 👈
👉 https://www.tg-me.com/deaconhenokhaile 👈
++ አባቶቻችን እንዲህ አሉ ++
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
ቅዱስ ባስልዮስ
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD)
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)
‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ
"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
ቅዱስ ባስልዮስ
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD)
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)
‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ
"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ከፀሐይ አጠገብ የነበረው ኮከብ
የአምላክ ሰው መሆንና ተወልዶ የማደጉ ዜና ሲነገር ሁልጊዜም የሚዘነጋ ክብሩ ግን ከብዙ ቅዱሳን ክብር የሚበልጥ አንድ ታላቅ ሰው ዛሬ በልቡናዬ ውል አለ፡፡ መቼም ከፀሐይ አጠገብ ያለ ኮከብ በፀሐይ ብርሃን ምክንያት መሸፈኑ አይቀርምና በተወለደው የጽድቅ ፀሐይ ፣ የሰላም ንጉሥ በልደቱ ደስታ ተውጠን ፣ በገብርኤል ብሥራት ፣ በድንግል ምስጋና ፣ በመላእክት ዝማሬ ተስበን የዘነጋነውን ፣ ድምቀት ሳያንሰው የተሸፈነውን ኮከብ የቅዱስ ዮሴፍን ነገር ባሰብኩኝ ጊዜ ክብሩን ለመናገር ልቡናዬ ተጨነቀ፡፡
በቅድስናው እያመንን ፣ ውለታውንም እያወቅን የምንዘነጋውን ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች የድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለማቃለል ስሙን በክፉ ማስረጃነት ሲያነሱብን ከእነርሱ ሸሸን ብለን ሳናውቅ ከበረከቱ የሸሸነውን ጻድቅ ዛሬ ልዘክረው ብል ልቤ በጥፋተኝነት ስሜት ተጨነቀብኝ፡፡
ስለ እርሱ ብዙ ያልዘመርንበትን ፣ ብዙ ያልተቀኘንበትን ዘመን ሳስብ ‘ላዕከ ማርያም ቅዱስ ዮሴፍ ሆይ ስለረሳንህ ቀኛችን ትርሳን ፣ ስላላሰብንህም ምላሳችን ከትናጋችን ይጣበቅ’ ብዬ ይቅርታውን ለመለመን ተመኘሁ፡፡
ቅዱስ ዮሴፍን ማን ብለን እንጥራው? እርሱ እንደሆን እንደ አብርሃም ዘመዶቹን የተወ አማኝ ፣ እንደ ይስሐቅ የታዘዘውን ብቻ ያደረገ ትሑት ፣ እንደ ያዕቆብ በእምነት ግብጽ የወረደ ስደተኛ ነውና እርሱን ለመግለፅ እንደምን ያለ ቋንቋ እንጠቀም ይሆን?
እስቲ ንገሩኝ? ‘መልካሙን እረኛ’ ክርስቶስን የጠበቀውን እረኛ ቅዱስ ዮሴፍን ከቶ በምን ቃል እንገልጸዋለን? የአብን ልጅ ያሳደገውን (ሐፃኔ ወልደ አብ) ቅዱስ ዮሴፍን በምን ቅኔ እናወድሰው?
ሕዝቅኤል ያያትን የእስራኤል አምላክ ገብቶባት ለዘላለም የተዘጋችውን ደጅ የጠበቀውን ታማኝ ዘብ ፤ ‘ከበሩ ደጀ ሰላም መንገድ በዚያ ይገባል በዚያም ይወጣል’ ተብሎ የተነገረለትን የተዘጋችው በር ደጀ ጠኚ ፣ ከታላቅዋ ተራራ ከድንግል ማርያም ያለ ሰው እጅ ድንጋይ ተፈንቅሎ ሲወርድ ቆሞ የተመለከተውን የሐዲስ ኪዳኑን ዳንኤል ከቶ እንዴት ባለ ቃል እንገልጸዋለን?
በቤተ ልሔም ግርግም ውስጥ በላምና አህያ መካከል የተኛውን ሕፃን የተመለከተውንና እንደ ነቢዩ ዕንባቆም
‘በማዕከለ ክልዔ እንስሳ ርኢኩከ’ /በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ/ ሊል የሚቻለውን የቅዱስ ዮሴፍን ክብር በምን አቅማችን እንግለጸው?
ወደ ግብጽ ወርዶ ለወገኖቹና ለዓለም ሁሉ ምግብን እንዳቆየው የብሉይ ኪዳኑ ዮሴፍ ወደ ግብጽ በመከራ ተሰድዶ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን ለሁላችን ላቆየልን ጻድቅ እንዴት ያለ የምስጋና ቃል እናዋጣ?
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለቅዱስ ዮሴፍ ዝክር ሐምሌ 26
ከብርሃን እናት ገፆች የተቆረሰ
(ወተዘከረኒ ለኃጥእ ገብርከ ተክለ ማርያም )
የአምላክ ሰው መሆንና ተወልዶ የማደጉ ዜና ሲነገር ሁልጊዜም የሚዘነጋ ክብሩ ግን ከብዙ ቅዱሳን ክብር የሚበልጥ አንድ ታላቅ ሰው ዛሬ በልቡናዬ ውል አለ፡፡ መቼም ከፀሐይ አጠገብ ያለ ኮከብ በፀሐይ ብርሃን ምክንያት መሸፈኑ አይቀርምና በተወለደው የጽድቅ ፀሐይ ፣ የሰላም ንጉሥ በልደቱ ደስታ ተውጠን ፣ በገብርኤል ብሥራት ፣ በድንግል ምስጋና ፣ በመላእክት ዝማሬ ተስበን የዘነጋነውን ፣ ድምቀት ሳያንሰው የተሸፈነውን ኮከብ የቅዱስ ዮሴፍን ነገር ባሰብኩኝ ጊዜ ክብሩን ለመናገር ልቡናዬ ተጨነቀ፡፡
በቅድስናው እያመንን ፣ ውለታውንም እያወቅን የምንዘነጋውን ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች የድንግል ማርያምን ዘለዓለማዊ ድንግልና ለማቃለል ስሙን በክፉ ማስረጃነት ሲያነሱብን ከእነርሱ ሸሸን ብለን ሳናውቅ ከበረከቱ የሸሸነውን ጻድቅ ዛሬ ልዘክረው ብል ልቤ በጥፋተኝነት ስሜት ተጨነቀብኝ፡፡
ስለ እርሱ ብዙ ያልዘመርንበትን ፣ ብዙ ያልተቀኘንበትን ዘመን ሳስብ ‘ላዕከ ማርያም ቅዱስ ዮሴፍ ሆይ ስለረሳንህ ቀኛችን ትርሳን ፣ ስላላሰብንህም ምላሳችን ከትናጋችን ይጣበቅ’ ብዬ ይቅርታውን ለመለመን ተመኘሁ፡፡
ቅዱስ ዮሴፍን ማን ብለን እንጥራው? እርሱ እንደሆን እንደ አብርሃም ዘመዶቹን የተወ አማኝ ፣ እንደ ይስሐቅ የታዘዘውን ብቻ ያደረገ ትሑት ፣ እንደ ያዕቆብ በእምነት ግብጽ የወረደ ስደተኛ ነውና እርሱን ለመግለፅ እንደምን ያለ ቋንቋ እንጠቀም ይሆን?
እስቲ ንገሩኝ? ‘መልካሙን እረኛ’ ክርስቶስን የጠበቀውን እረኛ ቅዱስ ዮሴፍን ከቶ በምን ቃል እንገልጸዋለን? የአብን ልጅ ያሳደገውን (ሐፃኔ ወልደ አብ) ቅዱስ ዮሴፍን በምን ቅኔ እናወድሰው?
ሕዝቅኤል ያያትን የእስራኤል አምላክ ገብቶባት ለዘላለም የተዘጋችውን ደጅ የጠበቀውን ታማኝ ዘብ ፤ ‘ከበሩ ደጀ ሰላም መንገድ በዚያ ይገባል በዚያም ይወጣል’ ተብሎ የተነገረለትን የተዘጋችው በር ደጀ ጠኚ ፣ ከታላቅዋ ተራራ ከድንግል ማርያም ያለ ሰው እጅ ድንጋይ ተፈንቅሎ ሲወርድ ቆሞ የተመለከተውን የሐዲስ ኪዳኑን ዳንኤል ከቶ እንዴት ባለ ቃል እንገልጸዋለን?
በቤተ ልሔም ግርግም ውስጥ በላምና አህያ መካከል የተኛውን ሕፃን የተመለከተውንና እንደ ነቢዩ ዕንባቆም
‘በማዕከለ ክልዔ እንስሳ ርኢኩከ’ /በሁለት እንስሳ መካከል አየሁህ/ ሊል የሚቻለውን የቅዱስ ዮሴፍን ክብር በምን አቅማችን እንግለጸው?
ወደ ግብጽ ወርዶ ለወገኖቹና ለዓለም ሁሉ ምግብን እንዳቆየው የብሉይ ኪዳኑ ዮሴፍ ወደ ግብጽ በመከራ ተሰድዶ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስን ለሁላችን ላቆየልን ጻድቅ እንዴት ያለ የምስጋና ቃል እናዋጣ?
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለቅዱስ ዮሴፍ ዝክር ሐምሌ 26
ከብርሃን እናት ገፆች የተቆረሰ
(ወተዘከረኒ ለኃጥእ ገብርከ ተክለ ማርያም )
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሠሯት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስትያን እናምናለን
https://youtube.com/watch?v=8herROCZp-0&feature=share
https://youtube.com/watch?v=8herROCZp-0&feature=share
YouTube
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሠሯት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስትያን እናምናለን
በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን::
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I-EjDdHv2Mbfsdw/videos
እግዚአብሔር ያክብርልን
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_BHX6I-EjDdHv2Mbfsdw/videos
እግዚአብሔር ያክብርልን