Telegram Web Link
ባስልዮስ ሆይ! ንገረኝ...

በዚህ ዓለም የሥራ መስክ ገበሬ መርከብ ለመንዳት የማይነሣው፣ ወይም ወታደሩ የግብርናን ሥራ የማይሠራው፣ ወይም ሙያው መርከብ ነጂ የኾነ ሰው ጦር እንዲመራ እልፍ ጊዜ ቢጎተትም እንኳ እሺ የማይለው ለምንድን ነው? እያንዳንዱ ያለችሎታው ቢሰማራ የሚከተለውን አደጋ አስቀድሞ ስለሚያይ አይደለምን? ታዲያ ጥፋቱ ቁሳቁስና ንብረት በሚኾንበት ኹኔታ አስቀድመን ብዙ የምናስብና ግፊትና ግዴታን የማንቀበል ኾነን ሳለ፥ ክህነትን እንዴት እንደሚይዙትና እንደሚያገለግሉበት ለማያውቁ ቅጣቱ ዘለዓለማዊ በኾነበት ኹኔታ ግን ያለብዙ ማሰብና ማሰላሰል እንዲሁ በዘፈቀደ ወደዚህ ዓይነት ታላቅ አደጋ ውስጥ ዘለን እንገባለንን? የሌሎች ሰዎች ግፊትስ ምክንያት ሊኾነን ይችላልን? አንድ ቀን ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ የኾነው እግዚአብሔር ይጠይቀናል፡፡ ይህ ሰበብም አያድነንም፡፡ ከምድራዊ ነገሮች ይልቅ በመንፈሳዊ ነገሮች ላይ ይበልጥ ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናልና፡፡ በትንንሽ ነገሮች ላይ ጠንቃቆች ስንኾን እንታያለንና፡፡ እስኪ ንገረኝ! አንድ ሰው የቤት ሥራ ሙያ ሳይኖረው ብትሠራልን ስንለው እሺ ብሎ ቢመጣና ከዚያ በኋላ ግን ዕንጨቱንና ድንጋዩን ቢያበላሽና የሠራው ነገር ወዲያውኑ ተበታትኖ ቢወድቅ በራሱ ፈልጎ አለመምጣቱና በሌሎች ግፊት ሥራውን መጀመሩ በቂ ምክንያት ሊኾነው ይችላልን? በጭራሽ! የሌሎችን ግፊትና ጥሪ አልቀበልም ማለት ነበረበትና በርግጥም ተጠያቂ ነው፡፡

ታዲያ እንዲህ ዕንጨትና ድንጋይ ለሚያበላሽ ሰው በጥፋቱ ከመጠየቅና ከመቀጣት ለመዳን ምንም ምክንያት ከሌለው፥ ነፍሳትን የሚያጠፋ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በግድየለሽነት የሚያንጽ ሰው’ማ እንዴት? የሌሎች ግፊትና ማስገደድ በቂ ምክንያት ይኾነኛል ብሎ ሊያስብ ይችላልን? እንዲህ ብሎ ማሰብስ ሞኝነት አይደለምን?

ፈቃደኛ ያልኾነን ሰው ማንም ሊያስገድደው እንደማይችል ለማሳየት ብዬ ሐተታ መስጠት አያስፈልገኝም፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት እንደ ተናገርኩት ይህ ፈቃደኛ ያልኾነ ሰው እጅግ ተጭነዉትና ግድ ብለዉት ሌሎች ብዙ መንገዶችንም ተጠቅመው ወደዚህ ኃላፊነት አመጡት እንበል፡፡ ታዲያ ይህ ከቅጣት ሊታደገው ይችላልን? እማልድሃለሁ፤ በፍጹም ራሳችንን አናታልል! ሕፃናት ሳይቀሩ በቀላሉ በሚያውቁት ነገር ላይ እንደማናውቅ ኾነን አናስመስል፡፡ እንደማናውቅ ማስመሰላችን በዚያች ዕለት ላይ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም አይጠቅመንምና፡፡

(በእንተ ክህነት፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ 4፥2
በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመው)

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma

✍️Comment @Channel_admin09
ማስታወቂያ

መምህር ይትባረክ ጋሻው ከፍተኛ የባህል ፈውስ መድህኒት አዋቂ እና ቀማሚ  ይፈልጋሉ?
እንግዲያውስ፦ በውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ለሚኖሩም መምጣት ሳያስፈልግ ባሉበት እንሰራለን 
የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
0917468918
0917468918
1 👉ለመፍትሄ ሀብት
2 👉ለህማም
3 👉ለመስተፋቅር
4 👉ቡዳ ለበላው
5 👉ለገበያ
6 👉የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 👉ነገረ ሚስጥራት(ሚስጥር የሚነግር)
8 👉ነገረ ራዕይ(ራዕይ የሚያሳይ)
9 👉ለዓቃቤ ርዕስ
10👉ለመክስት
11 👉ለቀለም(ለትምህርት)
12 👉ሰላቢ የማያስጠጋ
13 👉ለመፍትሔ ስራይ
14 👉ጋኔን ለያዘው ሰው
15 👉ለሁሉ ሠናይ
16 👉ለቁራኛ
17 👉ለአምፅኦ ብእሲት(ፍቅረኛ ላጣ ወይም ላጣች የሚሰራ)
18 👉ለመድፍነ ፀር
19 👉ሌባ የማያስነካ
20 👉ለበረከት
21 👉ለከብት መስተሐድር(ከብት እንደረይጠፋ)
22 👉አፍዝዝ አደንግዝ
23 👉ለጠላት (ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ)
24 👉ለግርማ ሞገስ
25 👉መርበቡተ ሰለሞን
26 👉ለዓይነ ጥላ
27 👉ምስሐበ ንዋይ ወምስሐበ ሰብእ
28 👉ለሁሉ መስተፋቅር
29 👉ጸሎተ ዕለታት
30 👉ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
31 👉ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
32 👉ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
33 👉ለድምፅ
34 👉ለብልት
35 👉በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ሰወች ደግሞ ከምንሰራቸው ስራዎች በጥቂቱ
0917468918
0917468918

      💚💛❤️ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ 💚💛❤️
🌼🌻🌼🌻
👉የመኖሪያ ፍቃድ ላላገኙ ሙሉ ስማቸውን ብቻ በመላክ በምንሰራው ስራ በጥቂት ቀናት መፍትሄ እንሰጣለን ለዚህም ብዙ ምቅክሮች አሉ
👉ከሀገር ውጪ ሆነ በሀገር ውስጥ የስራ እድል ላጡ
👉ንግድ ጀምረው[ሱቅ ከፍተው] አልሳካ ላላቸው
👉ገንዘብ ለሚያባክኑ ገንዘብ አልበረክት ላላቸው
👉ሰውፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ በጥቂት ጊዜ ውስጥ በምንሰራው ሰራ ደፋርና በራስ የመተማመን ችሎታ እንዲኖሮት እናደርጋለን
👉ለሀብት ለገንዘብ ለንብረት ሚሆንም አለን
👉ለስንፈተ ወሲብ መፍትሄ  የረጅም አመት ልምድ አለን ለውጪ ሀገር ለሚኖሩትም እየሰራን ነው
👉ፍቅረኛ አልያዝ ላላቸውም አለን
👉ትምህርት አልገባ ላለው ቶሎ የመርሳት ችግር ላለበት በሚደገም እና በሚነበብ ፅሁፍ ብቻ እጅግ በጣም ልዩ የሆነ ስራ እንሰራለን
👉መስተፋቅርም አለን ፣የህዝብ መስተፋቅር
👉ከሀገር መውጣት እየፈለጉ ላልተሳካላቸውም ወደኛ ቢመጡ እንሰራሎታለን  💚💛❤️      
ባጠቃላይ እነዚህ የገለፅናቸው ጥቂቶቹ ናቸው እርሶ ምን እንድንሰራሎት ይፈልጋሉ ?በውስጥ መስመር ያማክሩን ። ከሀገር ውጪ ላላችውም መፍትሄ በልዩ ሁኔታ አለን ብቻ ይምጡ ያማክሩን ያስተውሉ እኛ ምንሰራው በጥንታዊው ከአባቶቻችን በተማርነው ጥበብ ብራናውን አንብበን እፅዋትን ቀጥፈን አዘጋጅተን ነውና ሀገራችን ካሏት ጥበብ ጥቂቱ ነው እንኳን ለነዚህ እና አባቶቻችን በደመና ይሄዱ አልነበር እፀመሰውር ሰርተው እራሳቸውን ይደብቁ አልነበር እኛ ጥበብ ንቀን ፈረንጅ አምላኪ ሆነን ነው እንጂ ጥበቡ አሁንም አለ ይምጡ ያማክሩን ።
ለምንኛውም ጥያቄ እንዲሁም ለመነጋገር በሜሴጅ በውስጥ መስመር ይፃፉልኝ ወይም በቴሌግራም መሪጌታ ይትባረክ ጋሻው ብላችሁ ታገኙናላችሁ
ወይም በስልክ ቁጥር ይደውሉልን
0917468918
0917468918
“ልጆቼ! ሰዎች ክፋትን እየሠሩ ብትመለከትዋቸው በፍጹም አትጥሏቸው፡፡ ሰው ክፋቱ እንጂ እርሱ ራሱ አይጠላምና፡፡ የሐሰት ትምህርቱ እንጂ እርሱ ራሱ አይጠላምና፡፡ ምክንያቱም እርሱ ራሱ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ እጅግ መልካም ፍጥረት ነው፡፡ ክፉ ሥራው ግን ከዲያብሎስ ነው፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር ሥራና የዲያብሎስ ሥራ ለይተን እንወቅ፤ እንረዳ፤ ከዚያም ማቀላቀልን እንተዋለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ወገኖቹ አይሁድ ክርስቶስን እንዳንገላቱት፣ እንደዘበቱበት፣ እንዳሳደዱት፣ እልፍ ወትእልፊት ጸያፍ ነገርም እንደተናገሩበት ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ ግን እንዲህ በማድረጋቸው ጠላቸው? በፍጹም! እንዳውም ስለ እነርሱ ይረገም ዘንድ ይጸልይ ነበር /ሮሜ.9፥3/፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል እነዚህ ሰዎች በነቢያት ደም የሰከሩ መኾናቸውን ጠንቅቆ ቢያውቅም ይጸልይላቸው ነበር /ሕዝ.9፥8/፡፡ ሙሴ እነዚህ ሰዎች ኃጢአት እንደ ሠሩ ቢያውቅም ስለ እነርሱ ከሕይወት መጽሐፍ ይደመሰስ ዘንድ ይለምን ነበር /ዘጸ.32፥32/፡፡ ለምን? ሰዎቹ መዳን የሚገባቸው /ሮሜ.10፥1/ ደግሞም በሥላሴ አምሳል የተፈጠሩ እጅግ ግሩማን ናቸውና የሥላሴ ፍጥረት አይጠላም፤ ክፉ ሥራቸው ግን ከክፉው (ከዲያብሎስ) ነውና ይጠሉታል፡፡

ልጆቼ! አንድ የጤና ባለሙያ ታማሚውን ጠልቶ ፊቱ የሚያዞርበት ከኾነ፣ ታማሚውም ሐኪሙን አታሳዩኝ እያለ ከጠላው እንደምን ከበሽታው መዳን ይቻለዋል? እኛስ ክፉ የሚሠሩትን የምንጠላቸው ከኾነ እንደምን ከክፉ ሥራቸው ልናወጣቸው እንችላለን?

ልጆቼ! እንግዲያውስ በክፉ በሽታ የተያዘውን ወንድማችን ከበሽታው እንዲፈወስ ልንረዳው ይገባናል እንጂ ጤነኞች የምንኾን እኛ ሌላ በሽታ የምንጨምርበት ልንኾን አይገባንም፡፡ ከበሽታው ምንም የማይፈወስ ቢኾን እንኳ ከእኛ የሚጠበቀውን ኹሉ በማድረግ እስከ መጨረሻው ልንጥርለት ይገባናል፡፡ እስኪ ይሁዳን አስታውሱት! የታመመው ሊድን በማይችል በሽታ ነበር፡፡ ግን መፈወስ የማይችል ነው ብሎ ክርስቶስ ተወው? በፍጹም! እስከ መጨረሻይቱ ደቂቃ ታገሠው፤ ደግሞም እንዲመለስ ይገስጸው ነበር እንጂ፡፡ እኛም ይህን ከአባታችን ልንማር ይገባናል፡፡ ክፋትን የሚሠሩ ሰዎች ስናይ ፈጥነን አንተዋቸው፡፡ የሚቻለንን ኹሉ እናድርግላቸው እንጂ፡፡ ባይመለሱ እንኳ ሽልማታችን አይቀርብንም፡፡ ይህም ብቻ ሳይኾን ክፋትን የሚሠራት እኁ በእኛ እንዲደነቅ እናደርገዋለን፡፡ ምክንያቱም እንዲህ በክፋት የሰከሩ ሰዎች ተአምራትን አድርገን፣ ሙትን አስነሥተን ከምናሳያቸው ይልቅ በትኅትናችን፣ በጨዋነታችን፣ በትዕግሥታችን እጅግ ይማረካሉና፡፡ አንድ ሙት ማስነሣት ምን ይደንቃል? ዓለም ኹሉ በከመ ቅጽበት ይነሣ የለምን?

ሰዎች ከፍቅር በላይ በምንም መንገድ ከክፋታቸው ልንመልሳቸው አንችልም፡፡ ፍቅር ሰዎችን ከአውሬነታቸው መልሳ ሰዎች እንዲኾኑ የታደርግ ታላቅ መምህርት ናት፡፡ እንግዲያውስ ብዝሕ ያላቸውን በረከቶች በእኛ ላይ እንዲጐርፉ፣ ደግሞም መቼም የማይገማና የማይበላሽ ፍሬአቸውን በጊዜው እንድንበላ የግብረገብነት ኹሉ ራስ የምትኾንን ፍቅር በልባችን ውሳጤ እንትከላት፡፡ ይህን እንድናደርግ ሰውን በመውደዱ ሰው የኾነው ክርስቶስ ይርዳን አሜን፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(የቅዱስ ጳውሎስ መልእክትን 1ቆሮ 13፡1-7 በተረጎመበት ድርሳኑ በ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ )

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE

🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma

✍️Comment @Channel_admin09
2025/07/01 14:32:34
Back to Top
HTML Embed Code: