#ዋናው_እኔ_ነኝ
ብዙ የበደሉህ ዋኖች ይኖራሉ እንደ እኔ ግን አልበደለሁም፣ አንተን ያስከፉህ ቢሰለፉ ከፊት የምገኘው እኔ ነኝ፣ በኃጢአት ባህር መዋኘት ድሎት የሆናቸው ብዙ አሉ ዋናው ግን እኔ ነኝ፣ ልክ ባልሆነው ጎዳና የሚራመዱ አሉ መሪያቸው ግን እኔ ነኝ፣ አንተን በመቅረብ ፈንታ ጀርባ የሰጡህ አሉ እኔ ግን እብሳለሁ፣ ጌታዬ መድሃኒቴ ኢየሱስ አንተን የምትል ነፍሴ በስጋ ድካም ውስጥ ሳለ አለሁሽ ያልካት አንተ ነህ።
እኔ መማርህ እንዴት ያለ ምህረት ነው። የምህረትህ ድልድልነት ለእያንዳንዱ መንገዴ መሸጋገሪያ ሆኖኛል። እኔን ለማዳን ወደዚች አለም የመጣ አስታዋሼ አንተ ነህ። ከነ ኃጢያቴ እንዳልጠፋ እኔ ባለሁበት ተገኝተህ ያገኘኸን ፈላጊዬ ነህ፣ በሞት ጥላ ውስጥ ያለሁትን በደምህ ድምጽ የጠራኸኝ ባለውለታዬ አንተ ነህ፣ በምድረበዳው ብቻዬን ስባዝን ና ወደ እኔ ያልከኝ አስጠጊዬ አንተ ነህ።
እኔ ብቻ እንኳን በኃጢያት የጠፋው ብሆን የራስህ ጉዳይ ብለህ ከነበደሌ የማትተወኝ ለእኔ ብቻ እንኳን ብለህ ልትሞትልኝ የምትመጣ አፍቃሪዬ ነህ። ለእኔ ስትል ሰው የሆንክ አምላኬ ክርስቶስ ሆይ ክበር ተመስገን። እኔን ዋናውን ለማዳን ስትል ከሰው ተርታ ተገኝተህ በሰው ልክ የተመላለስክ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ተመስገን።
ወደ ክብሬ ልትመልሰኝ ክብርህን እንደመቀመት ሳትቆጥር ከላይ ከሰማያት የመጣህልኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ። እኔን ከማርከኝማ እኔን ይቅር ካልከኝማ ማንም ትምራለህ። እኔን ዋናውን ከተቀበልክማ መዳፍህ ሰፊ ነው ሁሉን ይቀበላል።
ለእኔ ስለሆነው በጎነትህ ክብር ይሁንልህ። አሜን
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤” 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ብዙ የበደሉህ ዋኖች ይኖራሉ እንደ እኔ ግን አልበደለሁም፣ አንተን ያስከፉህ ቢሰለፉ ከፊት የምገኘው እኔ ነኝ፣ በኃጢአት ባህር መዋኘት ድሎት የሆናቸው ብዙ አሉ ዋናው ግን እኔ ነኝ፣ ልክ ባልሆነው ጎዳና የሚራመዱ አሉ መሪያቸው ግን እኔ ነኝ፣ አንተን በመቅረብ ፈንታ ጀርባ የሰጡህ አሉ እኔ ግን እብሳለሁ፣ ጌታዬ መድሃኒቴ ኢየሱስ አንተን የምትል ነፍሴ በስጋ ድካም ውስጥ ሳለ አለሁሽ ያልካት አንተ ነህ።
እኔ መማርህ እንዴት ያለ ምህረት ነው። የምህረትህ ድልድልነት ለእያንዳንዱ መንገዴ መሸጋገሪያ ሆኖኛል። እኔን ለማዳን ወደዚች አለም የመጣ አስታዋሼ አንተ ነህ። ከነ ኃጢያቴ እንዳልጠፋ እኔ ባለሁበት ተገኝተህ ያገኘኸን ፈላጊዬ ነህ፣ በሞት ጥላ ውስጥ ያለሁትን በደምህ ድምጽ የጠራኸኝ ባለውለታዬ አንተ ነህ፣ በምድረበዳው ብቻዬን ስባዝን ና ወደ እኔ ያልከኝ አስጠጊዬ አንተ ነህ።
እኔ ብቻ እንኳን በኃጢያት የጠፋው ብሆን የራስህ ጉዳይ ብለህ ከነበደሌ የማትተወኝ ለእኔ ብቻ እንኳን ብለህ ልትሞትልኝ የምትመጣ አፍቃሪዬ ነህ። ለእኔ ስትል ሰው የሆንክ አምላኬ ክርስቶስ ሆይ ክበር ተመስገን። እኔን ዋናውን ለማዳን ስትል ከሰው ተርታ ተገኝተህ በሰው ልክ የተመላለስክ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ተመስገን።
ወደ ክብሬ ልትመልሰኝ ክብርህን እንደመቀመት ሳትቆጥር ከላይ ከሰማያት የመጣህልኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ። እኔን ከማርከኝማ እኔን ይቅር ካልከኝማ ማንም ትምራለህ። እኔን ዋናውን ከተቀበልክማ መዳፍህ ሰፊ ነው ሁሉን ይቀበላል።
ለእኔ ስለሆነው በጎነትህ ክብር ይሁንልህ። አሜን
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤” 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ኢየሱስ ክርስቶስ፡-
“ጨለማን ያሳደደው ብርሃን ዓለምን ሁሉ ያበራው ፋና የማይነዋወጥ መሰረትና የማይፈርስ ግንብ የማይሰበር መርከብና የማይሰረቅ ማህደር የለዘበ ቀንበርና የቀለለ ሽክም እርሱ ለአባቱ ኃይል ጥበቡም የሚሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
“ለሁሉ ያስባል፤ ሁሉንም ያጠግባል ለዕውራን ያዩ ዘንድ ብርሃንን ይሰጣቸዋል፡፡ የተዘጉ መስኮቶችን ይከፍታል ህሙማንን ይሰማቸዋል፡፡ የተደፈነችውን ጆሮ እንድትሰማ ያደርጋል፡፡ ከሰውነት የለምፅን ልብሶች ገፍፎ የስጋን መጎናፀፊያ ያለብሳል፡፡ የደረቀውን የእጅ ክንድ ያቀናል፣ የአንካሳውን እግር እንዲሄድ ያደርጋል ነፍስን ወደ ሕዋስዋ ይመልሳታል መንፈስንም በማደሪያዋ ያኖራታል፡፡ አለቆች ባሏቸው አጋንንት የእርያን መንጋ ያሰጥማል ከደከመችውም ሰውነት ደዌን ያርቃል፡፡
“ከክንፍህ የጽድቅ ፀሐይና የጥቅም ምንጭ የሚወጣ የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንተ ጌትነትና ክብር ምስጋናም ይገባሃል ለዘላለሙ አሜን፡፡”
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
“ጨለማን ያሳደደው ብርሃን ዓለምን ሁሉ ያበራው ፋና የማይነዋወጥ መሰረትና የማይፈርስ ግንብ የማይሰበር መርከብና የማይሰረቅ ማህደር የለዘበ ቀንበርና የቀለለ ሽክም እርሱ ለአባቱ ኃይል ጥበቡም የሚሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
“ለሁሉ ያስባል፤ ሁሉንም ያጠግባል ለዕውራን ያዩ ዘንድ ብርሃንን ይሰጣቸዋል፡፡ የተዘጉ መስኮቶችን ይከፍታል ህሙማንን ይሰማቸዋል፡፡ የተደፈነችውን ጆሮ እንድትሰማ ያደርጋል፡፡ ከሰውነት የለምፅን ልብሶች ገፍፎ የስጋን መጎናፀፊያ ያለብሳል፡፡ የደረቀውን የእጅ ክንድ ያቀናል፣ የአንካሳውን እግር እንዲሄድ ያደርጋል ነፍስን ወደ ሕዋስዋ ይመልሳታል መንፈስንም በማደሪያዋ ያኖራታል፡፡ አለቆች ባሏቸው አጋንንት የእርያን መንጋ ያሰጥማል ከደከመችውም ሰውነት ደዌን ያርቃል፡፡
“ከክንፍህ የጽድቅ ፀሐይና የጥቅም ምንጭ የሚወጣ የጽድቅ ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለአንተ ጌትነትና ክብር ምስጋናም ይገባሃል ለዘላለሙ አሜን፡፡”
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ቅዱሳን ለምን መከራ ይበዛባቸዋል?
ቅዱሳን ለምን በዓይነትም በብዛትም ልዩ ልዩ መከራዎች እንደሚደርስባቸው ለእናንተ ለምወዳችሁ የምነግራችሁ በቍጥር ስምንት ምክንያቶች አሉኝ፡፡ በመኾኑም በጣም ብዙ ምክንያቶች እያሉ አንድ ምክንያትስ እንኳን እንደሌለ አድርገን ከእንግዲህ ወዲህ በሚከሰቱ ነገሮች ብንሰናከል፣ ብንጠራጠርና ብንታወክ ምንም ይቅርታ ወይም ምሕረት እንደማይደረግልን በማወቅ በታላቅ ማስተዋል ኾነው ኹላቸውም ወደ እኔ ይዙሩ፡፡
ስለዚህ እግዚአብሔር መከራ እንዲርስባቸው የሚፈቅድበት የመጀመሪያው- ምክንያት፥ በሚያሠሩአቸው ምግባራትና በሚፈጽሙአቸው ተአምራት በቀላሉ ወደ ድፍረት እንዳይገቡ ነው፡፡
ሁለተኛ- ሌሎች ሰዎች [እነዚህ ቅዱሳን] ከሰዋዊ ባሕሪያቸው በላይ ግምት እንዳይሰጡአቸውና “ሰዎች ሳይኾኑ አማልክት ናቸው” ወደሚል ድምዳሜ እንዳይደርሱ ነው፡፡
ሦስተኛ- የእግዚአብሔር ኃይል ድል ሲያደርግ፣ ሲያሸንፍ እንዲገለጥና በዚህም በታመሙና በታሰሩ ሰዎች ቃሉ እንዲሰፋ ነው፡፡
አራተኛ- እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያገለግሉት ሹመት ሽልማትን ሽተው ሳይኾን እነዚህን የሚያህሉ መከራዎችን እንኳን ተቀብለው ለእግዚአብሔር ያላቸው ፍቅር ቅንጣትም ታህል እንዳልቀነሰ እንዲታወቅና ጽናታቸው እጅግ ደምቆ እንዲታይ ነው፡፡
አምስተኛ- ልቡናዎቻችን ስለ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን እንዲያውቁ ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ ጻድቅና የምግባሩ ሀብት የበዛለት ሰው እልፍ ጊዜ መከራዎችን ሲቀበል ብታይ ምንም እንኳን ወደህና ፈቅደህ ባይኾንም ሊመጣ ስላለው ፍርድ - ማለትም እነዚህ ሰዎች እነዚህን የሚያህሉ መከራዎችን የሚቀበሉት ለራሳቸው ካልኾነ፣ ያለ አንዳች ደመወዝና ክብር ካልኾነ፥ እግዚአብሔርም እንዲህ የሚደክሙትን ያለ አክሊል ሽልማት ይሰድዳቸው ዘንድ እንደዚህ ያለ ነገር ይደርስባቸው ዘንድ ባልፈቀደ ነበር ብለህ - ለማሰብ ትገደዳለህ፡፡ ለዚህ ዕለት ዕለት ለኾነ ድካማቸው ዋጋቸውን የማያሳጣቸው ከኾነ ግን፥ የዚህ ዓለም ሕይወት ካለፈ በኋላ ለአሁኑ ድካማቸው ዐሥበ ፃማቸውን (የትሩፋታቸውን ዋጋ) የሚቀበሉበት የኾነ ጊዜ ሊኖር ግድ ነው፡፡
ስድስተኛ- ብዙ ጸዋትወ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች እነዚህ ቅዱሳን ምን ምን መከራ ይደርስባቸው እንደ ነበር አስታውሰው መጽናናትን እንዲያገኙ ነው፡፡
ሰባተኛ- የእነዚህን ሰዎች ምግባር ጠቅሰን ስንነግራችሁና እያንዳንዳችሁን “ጳውሎስን ምሰሉት፤ ከጴጥሮስ የሚበልጥ ሥራን ሥሩ” ብለን ስንመክራችሁ ምግባራቸውን እየተመለከታችሁ “እንደ እኛ ሰዎች አልነበሩም” ብላችሁ እነርሱን አብነት ከማድረግ እንዳትሰንፉ ነው፡፡
ስምንተኛ- አንድን ሰው የተባረከ ነው ወይም በተቃራኒው ነው ብሎ ለመጥራት አስፈላጊ ኾኖ ሲገኝ ማንን ብሩክ፣ ማንን ደግሞ ኅዙን (ኀዘንተኛ) እና ርጉም አድርገን ልንቈጥር እንደሚገባ’ን እንድናውቅ ነው፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ቅዱሳን ለምን በዓይነትም በብዛትም ልዩ ልዩ መከራዎች እንደሚደርስባቸው ለእናንተ ለምወዳችሁ የምነግራችሁ በቍጥር ስምንት ምክንያቶች አሉኝ፡፡ በመኾኑም በጣም ብዙ ምክንያቶች እያሉ አንድ ምክንያትስ እንኳን እንደሌለ አድርገን ከእንግዲህ ወዲህ በሚከሰቱ ነገሮች ብንሰናከል፣ ብንጠራጠርና ብንታወክ ምንም ይቅርታ ወይም ምሕረት እንደማይደረግልን በማወቅ በታላቅ ማስተዋል ኾነው ኹላቸውም ወደ እኔ ይዙሩ፡፡
ስለዚህ እግዚአብሔር መከራ እንዲርስባቸው የሚፈቅድበት የመጀመሪያው- ምክንያት፥ በሚያሠሩአቸው ምግባራትና በሚፈጽሙአቸው ተአምራት በቀላሉ ወደ ድፍረት እንዳይገቡ ነው፡፡
ሁለተኛ- ሌሎች ሰዎች [እነዚህ ቅዱሳን] ከሰዋዊ ባሕሪያቸው በላይ ግምት እንዳይሰጡአቸውና “ሰዎች ሳይኾኑ አማልክት ናቸው” ወደሚል ድምዳሜ እንዳይደርሱ ነው፡፡
ሦስተኛ- የእግዚአብሔር ኃይል ድል ሲያደርግ፣ ሲያሸንፍ እንዲገለጥና በዚህም በታመሙና በታሰሩ ሰዎች ቃሉ እንዲሰፋ ነው፡፡
አራተኛ- እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን የሚያገለግሉት ሹመት ሽልማትን ሽተው ሳይኾን እነዚህን የሚያህሉ መከራዎችን እንኳን ተቀብለው ለእግዚአብሔር ያላቸው ፍቅር ቅንጣትም ታህል እንዳልቀነሰ እንዲታወቅና ጽናታቸው እጅግ ደምቆ እንዲታይ ነው፡፡
አምስተኛ- ልቡናዎቻችን ስለ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን እንዲያውቁ ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ ጻድቅና የምግባሩ ሀብት የበዛለት ሰው እልፍ ጊዜ መከራዎችን ሲቀበል ብታይ ምንም እንኳን ወደህና ፈቅደህ ባይኾንም ሊመጣ ስላለው ፍርድ - ማለትም እነዚህ ሰዎች እነዚህን የሚያህሉ መከራዎችን የሚቀበሉት ለራሳቸው ካልኾነ፣ ያለ አንዳች ደመወዝና ክብር ካልኾነ፥ እግዚአብሔርም እንዲህ የሚደክሙትን ያለ አክሊል ሽልማት ይሰድዳቸው ዘንድ እንደዚህ ያለ ነገር ይደርስባቸው ዘንድ ባልፈቀደ ነበር ብለህ - ለማሰብ ትገደዳለህ፡፡ ለዚህ ዕለት ዕለት ለኾነ ድካማቸው ዋጋቸውን የማያሳጣቸው ከኾነ ግን፥ የዚህ ዓለም ሕይወት ካለፈ በኋላ ለአሁኑ ድካማቸው ዐሥበ ፃማቸውን (የትሩፋታቸውን ዋጋ) የሚቀበሉበት የኾነ ጊዜ ሊኖር ግድ ነው፡፡
ስድስተኛ- ብዙ ጸዋትወ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች እነዚህ ቅዱሳን ምን ምን መከራ ይደርስባቸው እንደ ነበር አስታውሰው መጽናናትን እንዲያገኙ ነው፡፡
ሰባተኛ- የእነዚህን ሰዎች ምግባር ጠቅሰን ስንነግራችሁና እያንዳንዳችሁን “ጳውሎስን ምሰሉት፤ ከጴጥሮስ የሚበልጥ ሥራን ሥሩ” ብለን ስንመክራችሁ ምግባራቸውን እየተመለከታችሁ “እንደ እኛ ሰዎች አልነበሩም” ብላችሁ እነርሱን አብነት ከማድረግ እንዳትሰንፉ ነው፡፡
ስምንተኛ- አንድን ሰው የተባረከ ነው ወይም በተቃራኒው ነው ብሎ ለመጥራት አስፈላጊ ኾኖ ሲገኝ ማንን ብሩክ፣ ማንን ደግሞ ኅዙን (ኀዘንተኛ) እና ርጉም አድርገን ልንቈጥር እንደሚገባ’ን እንድናውቅ ነው፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
አጋንንት
ርኩሳንና ረቂቅ መናፍስት የሚጠሩበት መጠሪያ ሲሆን በብዙ ቁጥር አጋንንት ሲባሉ ጋኔን የተናጠል ስያሜያቸው ነው:: የአለቃቸው መጠሪያ ሰይጣን ሲሆን እርሱን የሚከተሉ ሠራዊቱ አጋንንት ተብለው ይጠራሉ፡፡
አጋንንት እነማን ናቸው?
በዕለተ እሁድ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ ሲፈጥራቸውም በብሩህ አእምሮ በረቂቅ ተፈጥሮ ፈጥሯቸው ነበርና በእምነት ይፈልጉኝ በአምልኮ ያቅርቡኝ በምስጋና ያክብሩኝ ተመራምረው ያግኙኝ እገለጽላቸዋለሁ ብሎ ተሰወረ፡፡ በዚህን ጊዜ ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚል ጥያቄ በመላእክት መካከል ተነስቶ ዓለመ መላእክት ተሸበረ፡፡
በመጀመሪያ ማዕረግ /በከፍታ ስፍራ/ ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ በላይ የተቀመጠው ሳጥናኤል የተባለው አለቃ ከነሰራዊቱ ነበር ወደ እርሱ የሚደርሰውን ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚለውን ከታች ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ የሚነሳውን ድምጽ በሰማ ጊዜ ከእርሱ በላይ በማዕረግ የተቀመጠ እንደሌለ አይቶ እኔ ፈጠርኋችሁ ልበላቸው ብሎ እሰበ አሰቦም አልቀረ እኔ ፈጠ ርኋችሁ አላቸው ኃጢአትን አደረገ ሐሰትንም ወለደ። /2ጴጥ2÷4/ ዮሐን 8፥44/ በዚህን ጊዜ የእርሱ ነገድ ሰራዊቱ ከሦስት ተከፋፈሉ፡፡
1ኛው - ከሰራዊቱ አንዱ እጅ አዎ ፈጠርከን ብሎ ተቀበለ ወድቆ ሰገደ
2ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ፈጥሮን ይሆን ሲለ ተጠራጠረ
3ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ምን አንተ ትፈጥረናለህ ስለምንበዛ እኛ ብንፈጥርህ እንጂ አሉ።
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ጨርሶ ሳያስክዳቸው ልገለጽላቸው አለ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የተባለውም አለቃ «ንቁም በበህላዊነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ» /የፈጠረንን እስክናውቅ ባለንበት እንጽና/ ብሎ በማወጅ የመላእክትን ዓለም አረጋጋ እግዚአብሔርም ከወደ ምስራቅ ብርሃን ገለፀላቸው /በብርሃን ጐርፍ ተገለፀላቸው/ ያን ጊዜ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአበሔር እያሉ ጮኹ ከድምጽም የተነሳ መድረኩ ተንቀጠቀጠ የክብሩንም መቅደስ የጣኑ ጢስ ሞላው /ት.ኢሳ 6፥3/ የመላእክትም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያመፀውን መልአክ ከነሰራዊቱ ሊዋጋ ለሰልፍ ወጣ በሰማይ ሰልፍ ሆነ / ራእ ዮሐ 12፥7/ የካዱትን መላእክት ተዋጋቸው ዲያብሎስም ድልን ተነስቶ ከነሰራዊቱ ወደ ምድር ተጣለ /ራእ ዮሐ 12፥9/
መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው የቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮት ግን አጋንንት በብዙ ልዩ ልዩ መጠሪያ የሚጠሩ የወደቀው መልአክና ሠራዊቶቹ መሆናቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ /ራእ 12፥9፣ ሕዝ. 28፥14፣ ኢሳ. 14፥12/ መልአካዊ ክብራቸውንና ሥልጣናቸውን ተገፈው የወደቁት መላእክት ስለመሆናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናገኛቸው ብዙ ማስረጃዎች በስፋት የሚገልጹት ሁለቱን
1.አጋንንት በኃጢአት ምክንያት የወደቁት መላአክት ስስመሆናቸው
«እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉት መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው. . .» /2ጴጥ. 2፥4/ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይመሰክራል :: /ሉቃ 10÷8 ማቴ 13:29/
2.አጋንንት በትዕቢት ምክንያት የወደቁት መሳአክት ስስመሆናቸው
«አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብን ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥህ፡፡ አንተም በልብህ ወደ ሰማይ አርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፡፡ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ ከደመ ናዎች ከፍታ በላይ አርጋለሁ:: በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጉድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ፡፡» /ኢሳ. 14፥12/ ይላል::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :-የአጋንንታዊ በሽታዎች ምስጢራዊነት እና በጠበል መፈወስ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ርኩሳንና ረቂቅ መናፍስት የሚጠሩበት መጠሪያ ሲሆን በብዙ ቁጥር አጋንንት ሲባሉ ጋኔን የተናጠል ስያሜያቸው ነው:: የአለቃቸው መጠሪያ ሰይጣን ሲሆን እርሱን የሚከተሉ ሠራዊቱ አጋንንት ተብለው ይጠራሉ፡፡
አጋንንት እነማን ናቸው?
በዕለተ እሁድ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ ሲፈጥራቸውም በብሩህ አእምሮ በረቂቅ ተፈጥሮ ፈጥሯቸው ነበርና በእምነት ይፈልጉኝ በአምልኮ ያቅርቡኝ በምስጋና ያክብሩኝ ተመራምረው ያግኙኝ እገለጽላቸዋለሁ ብሎ ተሰወረ፡፡ በዚህን ጊዜ ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚል ጥያቄ በመላእክት መካከል ተነስቶ ዓለመ መላእክት ተሸበረ፡፡
በመጀመሪያ ማዕረግ /በከፍታ ስፍራ/ ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ በላይ የተቀመጠው ሳጥናኤል የተባለው አለቃ ከነሰራዊቱ ነበር ወደ እርሱ የሚደርሰውን ማን ፈጠረን? ከየት ተገኘን? የሚለውን ከታች ከዘጠና ዘጠኙ ነገድ የሚነሳውን ድምጽ በሰማ ጊዜ ከእርሱ በላይ በማዕረግ የተቀመጠ እንደሌለ አይቶ እኔ ፈጠርኋችሁ ልበላቸው ብሎ እሰበ አሰቦም አልቀረ እኔ ፈጠ ርኋችሁ አላቸው ኃጢአትን አደረገ ሐሰትንም ወለደ። /2ጴጥ2÷4/ ዮሐን 8፥44/ በዚህን ጊዜ የእርሱ ነገድ ሰራዊቱ ከሦስት ተከፋፈሉ፡፡
1ኛው - ከሰራዊቱ አንዱ እጅ አዎ ፈጠርከን ብሎ ተቀበለ ወድቆ ሰገደ
2ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ፈጥሮን ይሆን ሲለ ተጠራጠረ
3ኛው -ከሰራዊቱ አንዱ እጅ ምን አንተ ትፈጥረናለህ ስለምንበዛ እኛ ብንፈጥርህ እንጂ አሉ።
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ጨርሶ ሳያስክዳቸው ልገለጽላቸው አለ፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የተባለውም አለቃ «ንቁም በበህላዊነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ» /የፈጠረንን እስክናውቅ ባለንበት እንጽና/ ብሎ በማወጅ የመላእክትን ዓለም አረጋጋ እግዚአብሔርም ከወደ ምስራቅ ብርሃን ገለፀላቸው /በብርሃን ጐርፍ ተገለፀላቸው/ ያን ጊዜ አንዱም ለአንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሰራዊት ጌታ እግዚአበሔር እያሉ ጮኹ ከድምጽም የተነሳ መድረኩ ተንቀጠቀጠ የክብሩንም መቅደስ የጣኑ ጢስ ሞላው /ት.ኢሳ 6፥3/ የመላእክትም አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያመፀውን መልአክ ከነሰራዊቱ ሊዋጋ ለሰልፍ ወጣ በሰማይ ሰልፍ ሆነ / ራእ ዮሐ 12፥7/ የካዱትን መላእክት ተዋጋቸው ዲያብሎስም ድልን ተነስቶ ከነሰራዊቱ ወደ ምድር ተጣለ /ራእ ዮሐ 12፥9/
መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው የቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮት ግን አጋንንት በብዙ ልዩ ልዩ መጠሪያ የሚጠሩ የወደቀው መልአክና ሠራዊቶቹ መሆናቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ /ራእ 12፥9፣ ሕዝ. 28፥14፣ ኢሳ. 14፥12/ መልአካዊ ክብራቸውንና ሥልጣናቸውን ተገፈው የወደቁት መላእክት ስለመሆናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ከምናገኛቸው ብዙ ማስረጃዎች በስፋት የሚገልጹት ሁለቱን
1.አጋንንት በኃጢአት ምክንያት የወደቁት መላአክት ስስመሆናቸው
«እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉት መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሀነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው. . .» /2ጴጥ. 2፥4/ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይመሰክራል :: /ሉቃ 10÷8 ማቴ 13:29/
2.አጋንንት በትዕቢት ምክንያት የወደቁት መሳአክት ስስመሆናቸው
«አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ አሕዛብን ያዋረድህ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቆረጥህ፡፡ አንተም በልብህ ወደ ሰማይ አርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፡፡ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ ከደመ ናዎች ከፍታ በላይ አርጋለሁ:: በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጉድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ፡፡» /ኢሳ. 14፥12/ ይላል::
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ :-የአጋንንታዊ በሽታዎች ምስጢራዊነት እና በጠበል መፈወስ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ሥርዓተ ቅዳሴ
ቅዳሴ ማለት ቀደሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን አመሰገነ፣ ባረከ፣ አከበረ፣ ለየ፣ ለእግዚአብሔር መርጦ ሰጠ ማለት ነው። ሥርዓት ማለት ደግሞ ሠርዐ፡ ሠራ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው። ትርጉሙ ሕግ: ደንብ አሠራር ማለት ነው። በአንድ ላይ አድርገን ስናነበው የምሥጋና ሥርዓት ማለት ነው የሚመሰገነው ደግሞ እግዚአብሔር ነው።
ቅዳሴ በሥርዓተ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት በኅብረት የሚጸለይ የኅብረት ጸሎት ነው፡፡ ከፀሎቶች ሁሉ የላቀ የፀሎት ክፍል ነው፡፡
ቅዳሴ፡-
• በሰማይ የሚገኘውን ሥርዓት በምድር መተግበር ነው።
• ቅዱስ ቁርባን የሚቀርብበት እግዚአብሔርን የምናመልክበት ሥርዓት ነው።
• በደስታ የምናከናውነው እግዚአብሔርን የምናመልክበት ጸሎት ነው።
• ቅዳሴ አባቶች ካህናት እና ምእመናን ያሳተፈ የምሥጋና ሥርዓት ነው። ስለዚህ ዘወትር ለቅዳሴና ለመንፈሳዊ ትምህርት ትኩረት ልትሰጡ ይገባል።
ጳጳሳት፣ ቀሳውስት፣ ዲቆናት በመቀደስ ምእመናን ደግሞ በማስቀደስ ይሳተፋሉ ከሁሉ በላይ አምላካችን የሚገኝበት እመቤታችን ቅድስት ማርያም የምትገኝበት መላእክት የሚገኙበት ሁሉም ቅዱሳን እንደተሰጣቸው ክብር የሚገኙበት ጸሎት ነው ስለዚህ ስናስቀድስ ብዙ በረከት እናገኝበታለን።
በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ መሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ፤ በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ተሟልተው ይገኙበታል። እዚህንም 5ቱን መሥዋዕቶች ማንኛውም ክርስተያን ለፈጣሪው የሚያቀርበው ነው፡፡
1. የቁርባን መስዋዕት፡-
በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ መለኮት ወይኑ ተለውጦ ደመ መለኮት የሚሆነው በቅዳሴው ጸሎት ነው። ሳናስቀድስ አንቆርብምና የቁርባን መስዋዕት የሚፈጸመው በሥርዓተ ቅዳሴ ብቻ ነው፡፡ መስዋዕቱም በቤተልሔም ይዘጋጃል፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ በቤተ-መቅደስ ውስጥ ደግሞ ይቀርባል ወይም ይታደላል፡፡ ጌታችን ሲወለደ በቤተልሔም ተወልዶ ቀራንዮ ለዓለም ሁሉ መስዋዕት ሆኗልና ቀራንዮ በተባለች በቤተክርስቲያን ቅዱሱ መስዋዕት ለሕዝብ ይታደላል።
2. የከንፈር መስዋዕት፡-
ካህኑ፣ ዲያቆኑና ሕዝቡ በመቀባበል በአንድነት ምስጋና ለፈጣሪያቸው የሚያቀርቡበት የከንፈራችን ፍሬ የሚሰዋበት የፀሎት ክፍል ፀሎተ ቅዳሴ ነው፡፡
3. የመብራት መስዋዕት፡-
በቅዳሴ ጊዜ የሚበራው ጧፍ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የሚሠጥ የመብራት መስዋዕት ነው፡፡ ምሳሌነቱም የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው። ይህውም ጌታችን ጨለማ ለሆነ ዓለም ብርሃን ሆኖ ብርሃንን ሊያበራ ወደ ዓለም መቷልና ነው፡፡
4. የዕጣን መስዋዕት፡-
የዕጣን ጸሎት ካህኑ ብቻ የሚያጥነው ሲሆን ይህውም በማዕጠንቱ አማካኝነት ቅዱሱን እጣን በመንበሩ፣ በቅዱሳን ስዕላቱ፣ በሕዝቡ መካከል ያጥናል። ይህውም የሕዝቡን ፀሎት ወደላይ ወደ ሥላሴ መንበር ይዞ ይወጣል።
በሰማይም ያሉ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሥላሴን መንበር እንደሚያጥኑ ሁሉ በምድርም ያለው ካህን የሰማያዊው ምሳሌ ነውና በምድር ያለውን መንበር በማጠን ለእግዚአብሔር የዕጣን መስዋዕት ያቀርባል፡፡
5. የሰውነት መስዋዕትነት፡-
በቅዳሴ ጊዜ አብዛኛውን ሰዓት ሙሉውን ማለት ይቻላል በመቆም የሚፀለይ የፀሎት ክፍል ነው፡፡ በመሐል 2 ጊዜያት ብቻ የስገዱ ትዕዛዝ ሲተላለፍ ሕዝቡ ሁሉ ፊቱን ወደ ፈጣሪው አዞሮ እራሱን አዋርዶ ይሰግዳል። በእግዚአብሔር ፊት መቆምም ሆነ መስገድ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ የሰውነት መሥዋዕት ነው፡፡
ይህ የጸሎት ክፍል (ቅዳሴ) በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፦
1. የዝግጅት ክፍል
2. የንባብና የትምህርት ክፍል
3. ፍሬ ቅዳሴ፦ ፍሬ ቅዳሴያት እንደየበዓሉ ይለዋወጣተሉ ብዛታቸውም ፲፬ (14) ናቸው። እነዚህም፡-
3.1. ቅዳሴ ዘሐዋርያት
3.2. ቅዳሴ እግዚእ
3.3. ቅዳሴ ማርያም
3.4. ቅዳሴ ዘዮሐንስ ወልደ ነጓድጓድ
3.5. ቅዳሴ ዘሠለስቱ ምዕት
3.6. ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ
3.7. ቅዳሴ ባስልዮስ
3.8. ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
3.9. ጎርጎርዮስ ካልእ
3.10. ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ
3.11. ቅዳሴ ዘዮሐንስ አፈወርቅ
3.12. ቅዳሴ ዘቄርሎስ
3.13. ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ
3.14. ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ
- የጌታችን በዓል ከሆነ (ቅዳሴ እግዚእ)
-የጌታችን ምጽአት፣ ጳጉሜ እሑድ ቀን ከዋለች ሰንበት (ቅዳሴ አትናቴዎስ)
-የእመቤታችን በዓል ከሆነ ቅዳሴ ማርያም (ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ)
-የመላእክትና የሐዋርያት በዓል ከሆነ (ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ)
-ከዘመነ ልደት እስከ ዘመነ ግዝረት (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልዕ)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ቅዳሴ ማለት ቀደሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን አመሰገነ፣ ባረከ፣ አከበረ፣ ለየ፣ ለእግዚአብሔር መርጦ ሰጠ ማለት ነው። ሥርዓት ማለት ደግሞ ሠርዐ፡ ሠራ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው። ትርጉሙ ሕግ: ደንብ አሠራር ማለት ነው። በአንድ ላይ አድርገን ስናነበው የምሥጋና ሥርዓት ማለት ነው የሚመሰገነው ደግሞ እግዚአብሔር ነው።
ቅዳሴ በሥርዓተ ቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት በኅብረት የሚጸለይ የኅብረት ጸሎት ነው፡፡ ከፀሎቶች ሁሉ የላቀ የፀሎት ክፍል ነው፡፡
ቅዳሴ፡-
• በሰማይ የሚገኘውን ሥርዓት በምድር መተግበር ነው።
• ቅዱስ ቁርባን የሚቀርብበት እግዚአብሔርን የምናመልክበት ሥርዓት ነው።
• በደስታ የምናከናውነው እግዚአብሔርን የምናመልክበት ጸሎት ነው።
• ቅዳሴ አባቶች ካህናት እና ምእመናን ያሳተፈ የምሥጋና ሥርዓት ነው። ስለዚህ ዘወትር ለቅዳሴና ለመንፈሳዊ ትምህርት ትኩረት ልትሰጡ ይገባል።
ጳጳሳት፣ ቀሳውስት፣ ዲቆናት በመቀደስ ምእመናን ደግሞ በማስቀደስ ይሳተፋሉ ከሁሉ በላይ አምላካችን የሚገኝበት እመቤታችን ቅድስት ማርያም የምትገኝበት መላእክት የሚገኙበት ሁሉም ቅዱሳን እንደተሰጣቸው ክብር የሚገኙበት ጸሎት ነው ስለዚህ ስናስቀድስ ብዙ በረከት እናገኝበታለን።
በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ መሥዋዕቶች ምን ምን ናቸው?
አምስቱ የስሜት ሕዋሳት በፀሎተ ቅዳሴ ጊዜ ያስቀድሳሉ፤ በቅዳሴ ጊዜ 5ቱ ምሥዋዕቶች ተሟልተው ይገኙበታል። እዚህንም 5ቱን መሥዋዕቶች ማንኛውም ክርስተያን ለፈጣሪው የሚያቀርበው ነው፡፡
1. የቁርባን መስዋዕት፡-
በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ መለኮት ወይኑ ተለውጦ ደመ መለኮት የሚሆነው በቅዳሴው ጸሎት ነው። ሳናስቀድስ አንቆርብምና የቁርባን መስዋዕት የሚፈጸመው በሥርዓተ ቅዳሴ ብቻ ነው፡፡ መስዋዕቱም በቤተልሔም ይዘጋጃል፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ በቤተ-መቅደስ ውስጥ ደግሞ ይቀርባል ወይም ይታደላል፡፡ ጌታችን ሲወለደ በቤተልሔም ተወልዶ ቀራንዮ ለዓለም ሁሉ መስዋዕት ሆኗልና ቀራንዮ በተባለች በቤተክርስቲያን ቅዱሱ መስዋዕት ለሕዝብ ይታደላል።
2. የከንፈር መስዋዕት፡-
ካህኑ፣ ዲያቆኑና ሕዝቡ በመቀባበል በአንድነት ምስጋና ለፈጣሪያቸው የሚያቀርቡበት የከንፈራችን ፍሬ የሚሰዋበት የፀሎት ክፍል ፀሎተ ቅዳሴ ነው፡፡
3. የመብራት መስዋዕት፡-
በቅዳሴ ጊዜ የሚበራው ጧፍ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ የሚሠጥ የመብራት መስዋዕት ነው፡፡ ምሳሌነቱም የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው። ይህውም ጌታችን ጨለማ ለሆነ ዓለም ብርሃን ሆኖ ብርሃንን ሊያበራ ወደ ዓለም መቷልና ነው፡፡
4. የዕጣን መስዋዕት፡-
የዕጣን ጸሎት ካህኑ ብቻ የሚያጥነው ሲሆን ይህውም በማዕጠንቱ አማካኝነት ቅዱሱን እጣን በመንበሩ፣ በቅዱሳን ስዕላቱ፣ በሕዝቡ መካከል ያጥናል። ይህውም የሕዝቡን ፀሎት ወደላይ ወደ ሥላሴ መንበር ይዞ ይወጣል።
በሰማይም ያሉ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሥላሴን መንበር እንደሚያጥኑ ሁሉ በምድርም ያለው ካህን የሰማያዊው ምሳሌ ነውና በምድር ያለውን መንበር በማጠን ለእግዚአብሔር የዕጣን መስዋዕት ያቀርባል፡፡
5. የሰውነት መስዋዕትነት፡-
በቅዳሴ ጊዜ አብዛኛውን ሰዓት ሙሉውን ማለት ይቻላል በመቆም የሚፀለይ የፀሎት ክፍል ነው፡፡ በመሐል 2 ጊዜያት ብቻ የስገዱ ትዕዛዝ ሲተላለፍ ሕዝቡ ሁሉ ፊቱን ወደ ፈጣሪው አዞሮ እራሱን አዋርዶ ይሰግዳል። በእግዚአብሔር ፊት መቆምም ሆነ መስገድ ለእግዚአብሔር የሚሰጥ የሰውነት መሥዋዕት ነው፡፡
ይህ የጸሎት ክፍል (ቅዳሴ) በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል፦
1. የዝግጅት ክፍል
2. የንባብና የትምህርት ክፍል
3. ፍሬ ቅዳሴ፦ ፍሬ ቅዳሴያት እንደየበዓሉ ይለዋወጣተሉ ብዛታቸውም ፲፬ (14) ናቸው። እነዚህም፡-
3.1. ቅዳሴ ዘሐዋርያት
3.2. ቅዳሴ እግዚእ
3.3. ቅዳሴ ማርያም
3.4. ቅዳሴ ዘዮሐንስ ወልደ ነጓድጓድ
3.5. ቅዳሴ ዘሠለስቱ ምዕት
3.6. ቅዳሴ ዘአትናቴዎስ
3.7. ቅዳሴ ባስልዮስ
3.8. ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
3.9. ጎርጎርዮስ ካልእ
3.10. ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ
3.11. ቅዳሴ ዘዮሐንስ አፈወርቅ
3.12. ቅዳሴ ዘቄርሎስ
3.13. ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ
3.14. ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ
- የጌታችን በዓል ከሆነ (ቅዳሴ እግዚእ)
-የጌታችን ምጽአት፣ ጳጉሜ እሑድ ቀን ከዋለች ሰንበት (ቅዳሴ አትናቴዎስ)
-የእመቤታችን በዓል ከሆነ ቅዳሴ ማርያም (ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየ)
-የመላእክትና የሐዋርያት በዓል ከሆነ (ቅዳሴ ዘያዕቆብ ዘሥሩግ)
-ከዘመነ ልደት እስከ ዘመነ ግዝረት (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልዕ)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ፦ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ሐሜት
ብዙ ሰው ‹‹እኔ ሐሜት አልወድም፡፡ ግን ማማት የሚወዱ ጓደኞች አሉኝ›› ይላል፡፡ አሁን እርሱ ምን እያደረገ ነው? ‹‹ወዳጆቼ ሐሜተኞች ናቸው›› ሲል እያማቸው አይደለምን? ወይስ ለእርሱ ሲሆን ሐሜቱ ተለውጦ የመረጃ ቅብብል ይሆናል?!
የማንወደው ነገር ግን እየጠላንም ቢሆን የምናደርገው ኃጢአት ሐሜት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ሐሜተኛ ሆኖ የተጠቀሰው በእባብ ያደረው ሰይጣን ነው፡፡ በመጀመሪያ የታማው ደግሞ እግዚአብሔር ሲሆን፣ ሐሜቱን ሰምታ ሳትመረምር የተቀበለችውና ለስሕተት የቸኮለችው ሴት ደግሞ ሔዋን ነበረች፡፡ (ዘፍ 3፥1-5)
የሰይጣን ሐሜት እንዲህ በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ አንደኛ "አትሞቱም፤ እንደ እርሱ እንዳትሆኑ ነው የከለከላችሁ" በሚለው ንግግሩ "እግዚአብሔር ዋሽቷችኋል" እያለ ፍቅሩን እንድትጠራጠር አደረገ። ሁለተኛ ደግሞ ከዛፉ ብትበሉ እንደ እርሱ ትሆናላችሁ በማለት የእግዚአብሔር አምላክነት "የዛፍ ፍሬ" በመብላት የተገኘ መሆኑንና እርሱም እንደ እነርሱ የነበረበት ጊዜ እንዳለ እንድታስብ እየገፋፋት ነው። ታዲያ ከዚህ በላይ ስም ማጥፋት (Character assassination) ከየት ሊገኝ ይችላል?
ሰይጣን በነገር ሁሉ ፍጹም የሆነን አምላክ ጆሮን ጭው የሚያደርግ ሐሰት ፈጥሮ ለማማት ወደ ኋላ ካላለ፣ አንዳች ጉድለት የማያጣብን እኛማ ከሐሜቱ ጅራፍ ልናመልጥ እንደማንችል ሊታወቅ ይገባል፡፡ በተለይ በአሁን ጊዜ ሐሜት በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ ሥሩን ሰድዷል። እንደውም ባልንጀራን ማማት እንደ ምግብ ቢሆን ኖሮ ብዙዎቻችን በዚህች ደሃ አገር ከመጠን በላይ ወፍረን እንቸገር ነበር።
ማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን የሐሜት አውድማዎች ሆነዋል። በየገጾቻችን ከሽነን የምናቀርባቸው ጽሑፎች ጠረናቸው የሰው ሥጋ የሰው ሥጋ ይላሉ። ፊታችን በሐሜት ወይቦ ሁለት መልክ ካወጣን ቆየን። ይኸው ሳንባችን በማማት አየር ተመርዞ ሳሉ ከበረታብን ሰነባብተናል። ወዳጃችንን የማናማበት ብቸኛው ጊዜ ከእርሱ ጋር የምንሆንበት ሰዓት ነው። ያውም ደግሞ ያንኑ ጊዜ ሌላኛውን ሰው ለማማት ካልተጠቀምንበት ማለቴ ነው።
ሊቁ ዮሐንስ ካዝያን እንደሚናገረው "ሰው ከሚጠቅመው ቃለ እግዚአብሔር ይልቅ የማይጠቅመው ሐሜት ያጓጓዋል። የአምላክ ቃል ሲነገር እንቅልፍ እንቅልፍ የሚለው ሁሉ፣ የሐሜት ነገር ሲሆን ግን እንደ እርሱ ንቁ የሚሆን የለም። በጥፍሩ ቆሞ ይሰማል። ሌሊቱን ሁሉ ሳይተኛ ቢያድር ደስ ይለዋል።"
ለመሆኑ ባልንጀራችንን ስለ ምን በቀስታ እናማዋለን? የወዳጃችንንስ ውድቀት በማውራት በእኛ ላይ የምንጨምረው ምን በጎ ነገር አለ? በሰው ፊት መልካም እየመሰልን ከኋላው ግን ስለ እርሱ ውድቀት በማውራት የራሳችንን ደረጃ ከፍ ማድረግ አይቻልም። ስለ ሌሎች በማውራት የምናጠፋውን ሰዓት ራሳችንን ለማሳደግ ብንጠቀምበት ኖሮ መኖራችንን ትርጉም እንዲኖረው ማድረግ ይቻለን ነበር።
"ንጹሕ ወዳጅነት" ሐሜትና ማሾክሾክ የሌለባት የታማኞች ጌጥ ናት። የሐሜት ስለታቸውን ያልጣሉ ሰዎች "እውነተኛ ባልንጀርነት"ን አያውቋትም። አንተ በፍቅር ወዳጅ አድርገህ ከፊትህ ስታቀርባቸው እነርሱ ከኋላህ ሆነው የሚያሙህን አትጥላቸው፤ አትጣላቸው። ነገር ግን የሐሜቱ እርሾ እንዳያገኝህ ቶሎ ተለያቸው። ከፊትህም አድርገህ አታሰቃያቸው። የእነርሱ ቦታ ከኋላህ መሆን ነው።
ሐሜት የሰይጣን ነው። ሰውን የሚያማ በገዛ ፈቃዱ አንደበቱን ለሰይጣን አሳልፎ የሰጠ ነው። ማማት በቤተ ክርስቲያን መለያየትን ያመጣል፣ ቤተሰብ ይበትናል፣ ወንድሞችን ያጣላል። ብንችል ስለ ሰው የምናውቀውን ጥሩውን እናውራ። የምናወራው ጥሩነት ከሌለው ደግሞ ቢያንስ ምንም አንበል።
ሔዋን ልክ እንደ አዳም እባብን "ሂጅልኝ" ብላ ብታባራት ኖሮ እነርሱም ከፈጣሪ ባልተጣሉ ሐሜትም ወደ ዓለም ባልገባ ነበር። ሐሜትን ማጥፋት ከፈለግን ሐሜተኛን እሺ አንበል። ማር ይስሐቅም "ወዳጁን በፊትህ የሚያንኳስሰውን ሰው አፉን መዝጋት ባትችል እንኳን ቢያንስ ሐሜቱን ከመስማት ተቆጠብ" ይላል። ሐሜትን ደስ ብሎህ ካልሰማኸው ደስ ብሎት የሚያማን ሰው ልትፈጥር አትችልም።
"ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱ ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ" ገላ 5፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ብዙ ሰው ‹‹እኔ ሐሜት አልወድም፡፡ ግን ማማት የሚወዱ ጓደኞች አሉኝ›› ይላል፡፡ አሁን እርሱ ምን እያደረገ ነው? ‹‹ወዳጆቼ ሐሜተኞች ናቸው›› ሲል እያማቸው አይደለምን? ወይስ ለእርሱ ሲሆን ሐሜቱ ተለውጦ የመረጃ ቅብብል ይሆናል?!
የማንወደው ነገር ግን እየጠላንም ቢሆን የምናደርገው ኃጢአት ሐሜት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ለመጀመሪያ ጊዜ ሐሜተኛ ሆኖ የተጠቀሰው በእባብ ያደረው ሰይጣን ነው፡፡ በመጀመሪያ የታማው ደግሞ እግዚአብሔር ሲሆን፣ ሐሜቱን ሰምታ ሳትመረምር የተቀበለችውና ለስሕተት የቸኮለችው ሴት ደግሞ ሔዋን ነበረች፡፡ (ዘፍ 3፥1-5)
የሰይጣን ሐሜት እንዲህ በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ አንደኛ "አትሞቱም፤ እንደ እርሱ እንዳትሆኑ ነው የከለከላችሁ" በሚለው ንግግሩ "እግዚአብሔር ዋሽቷችኋል" እያለ ፍቅሩን እንድትጠራጠር አደረገ። ሁለተኛ ደግሞ ከዛፉ ብትበሉ እንደ እርሱ ትሆናላችሁ በማለት የእግዚአብሔር አምላክነት "የዛፍ ፍሬ" በመብላት የተገኘ መሆኑንና እርሱም እንደ እነርሱ የነበረበት ጊዜ እንዳለ እንድታስብ እየገፋፋት ነው። ታዲያ ከዚህ በላይ ስም ማጥፋት (Character assassination) ከየት ሊገኝ ይችላል?
ሰይጣን በነገር ሁሉ ፍጹም የሆነን አምላክ ጆሮን ጭው የሚያደርግ ሐሰት ፈጥሮ ለማማት ወደ ኋላ ካላለ፣ አንዳች ጉድለት የማያጣብን እኛማ ከሐሜቱ ጅራፍ ልናመልጥ እንደማንችል ሊታወቅ ይገባል፡፡ በተለይ በአሁን ጊዜ ሐሜት በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ ሥሩን ሰድዷል። እንደውም ባልንጀራን ማማት እንደ ምግብ ቢሆን ኖሮ ብዙዎቻችን በዚህች ደሃ አገር ከመጠን በላይ ወፍረን እንቸገር ነበር።
ማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን የሐሜት አውድማዎች ሆነዋል። በየገጾቻችን ከሽነን የምናቀርባቸው ጽሑፎች ጠረናቸው የሰው ሥጋ የሰው ሥጋ ይላሉ። ፊታችን በሐሜት ወይቦ ሁለት መልክ ካወጣን ቆየን። ይኸው ሳንባችን በማማት አየር ተመርዞ ሳሉ ከበረታብን ሰነባብተናል። ወዳጃችንን የማናማበት ብቸኛው ጊዜ ከእርሱ ጋር የምንሆንበት ሰዓት ነው። ያውም ደግሞ ያንኑ ጊዜ ሌላኛውን ሰው ለማማት ካልተጠቀምንበት ማለቴ ነው።
ሊቁ ዮሐንስ ካዝያን እንደሚናገረው "ሰው ከሚጠቅመው ቃለ እግዚአብሔር ይልቅ የማይጠቅመው ሐሜት ያጓጓዋል። የአምላክ ቃል ሲነገር እንቅልፍ እንቅልፍ የሚለው ሁሉ፣ የሐሜት ነገር ሲሆን ግን እንደ እርሱ ንቁ የሚሆን የለም። በጥፍሩ ቆሞ ይሰማል። ሌሊቱን ሁሉ ሳይተኛ ቢያድር ደስ ይለዋል።"
ለመሆኑ ባልንጀራችንን ስለ ምን በቀስታ እናማዋለን? የወዳጃችንንስ ውድቀት በማውራት በእኛ ላይ የምንጨምረው ምን በጎ ነገር አለ? በሰው ፊት መልካም እየመሰልን ከኋላው ግን ስለ እርሱ ውድቀት በማውራት የራሳችንን ደረጃ ከፍ ማድረግ አይቻልም። ስለ ሌሎች በማውራት የምናጠፋውን ሰዓት ራሳችንን ለማሳደግ ብንጠቀምበት ኖሮ መኖራችንን ትርጉም እንዲኖረው ማድረግ ይቻለን ነበር።
"ንጹሕ ወዳጅነት" ሐሜትና ማሾክሾክ የሌለባት የታማኞች ጌጥ ናት። የሐሜት ስለታቸውን ያልጣሉ ሰዎች "እውነተኛ ባልንጀርነት"ን አያውቋትም። አንተ በፍቅር ወዳጅ አድርገህ ከፊትህ ስታቀርባቸው እነርሱ ከኋላህ ሆነው የሚያሙህን አትጥላቸው፤ አትጣላቸው። ነገር ግን የሐሜቱ እርሾ እንዳያገኝህ ቶሎ ተለያቸው። ከፊትህም አድርገህ አታሰቃያቸው። የእነርሱ ቦታ ከኋላህ መሆን ነው።
ሐሜት የሰይጣን ነው። ሰውን የሚያማ በገዛ ፈቃዱ አንደበቱን ለሰይጣን አሳልፎ የሰጠ ነው። ማማት በቤተ ክርስቲያን መለያየትን ያመጣል፣ ቤተሰብ ይበትናል፣ ወንድሞችን ያጣላል። ብንችል ስለ ሰው የምናውቀውን ጥሩውን እናውራ። የምናወራው ጥሩነት ከሌለው ደግሞ ቢያንስ ምንም አንበል።
ሔዋን ልክ እንደ አዳም እባብን "ሂጅልኝ" ብላ ብታባራት ኖሮ እነርሱም ከፈጣሪ ባልተጣሉ ሐሜትም ወደ ዓለም ባልገባ ነበር። ሐሜትን ማጥፋት ከፈለግን ሐሜተኛን እሺ አንበል። ማር ይስሐቅም "ወዳጁን በፊትህ የሚያንኳስሰውን ሰው አፉን መዝጋት ባትችል እንኳን ቢያንስ ሐሜቱን ከመስማት ተቆጠብ" ይላል። ሐሜትን ደስ ብሎህ ካልሰማኸው ደስ ብሎት የሚያማን ሰው ልትፈጥር አትችልም።
"ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱ ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ" ገላ 5፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ"
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የመድኃኒት እናት ሆይ በመዓልትም በሌሊትም አማላጅ ትሆኝኝ ዘንድ እሰግድልሻለሁ። እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ከእርሱ የሚገኘውን ኃይልን ይሰጠኝ ዘንድ ከአንቺ ወደ ተወለደው ልጂሽ እንድትለምኝልኝ እማጸናለሁ። በመወለዱ ድኅነት የተገባሽ ሆነሻልና። በሔዋን ውድቀት ሆነ። አብ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ገብርኤል አማካኝነት ሰላምን የላከልሽ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ሰላምታን ሰጠሽ ሰገደልሽም። ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ሰላምታ ይገባሻል። እነሆ ትጸንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ፣ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ። የልዑል ኃይል ይጸልልሻል፤ ከአንቺ የሚወለደውም ቅዱስ ነው፤ እርሱም የልዑል ልጅ ይባላል አለሽ።
በተቀደሰው ስሙ ኅሊናዬን ልቡናዬን እንዲቀድስ ትለምኝው ዘንድ እማጸንሻለሁ። ንጽሕት ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። የሕይወት ቃል ከአንቺ ሰው ይሆን ዘንድ በሥጋ ከአንቺ ይወለድ ዘንድ የተገባሽ የመድኃኒት እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። ከአንቺ በመዋሐዱም እኛ ዳንን። እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። በእናታቸው ማሕፀን ሕፃናትን የሚስላቸው ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ሁሉን የፈጠረው በማሕፀንሽ የተቀረጸብሽ የብርሃን እናት ሆይ እሰግድልሻለሁ። ረቂቅ ድንቅ ምሥጢርን ዓለምንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣውን እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እለምንሻለሁ። በመንፈሳዊ ልደት ይወልደኝ ዘንድ ወደ እርሱ ዓለምና አዳኝ ወደ ሆነች ዕውቀት ከፍ ያደርገኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እለምንሻለሁ፣ አማጸንሻለሁ።
የሕይወት መገኛ የነገሥታት ንጉሥ የባለሥልጣናቱ ባለሥልጣን የአምላኮችን አምላክ በበረት ያስተኛሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ። አዳኝ ስለሆነው ስለስምሽ እንዲረዳኝ ትለምኝልኝ ዘንድም ወደ አንቺ እለምናለሁ፤ እማልዳለሁም። በማየቱ አዳምንና ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ነጻ ያወጣውን በክንድሽ የታቀፍሽው እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ።
በረቂቅ መመልከቱ እንዲመግበኝ ከሰይጣን መሰናክልም እንዲያድነኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ፤ እማጸንሽማለሁ። ዓለማትን ሁሉ ለሚመግበው ጡትሽን ያጠባሽው የመድኃኒት እናት እመቤቴ ድንግል ማርያም ሆይ እሰግድልሻለሁ፤ የሰማይ ኃይላት የሚመገቡትም ከእርሱ ነው። ነፍሴን በፈቃዱ ከጸጋው ይመግባት ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ።
እመቤቴ ድግል ማርያም ሆይ ተወዳጁ ልጅሽ እንደ ፍጹም ፈቃዱ እንዲመግበኝ በየጊዜው በየሰዐቱ አማላጅ ሁኚኝ። ይህችም ወደ እርሱ የምትለምኝውን ልመና የተመላች መጽሐፍ ናት ። የለመንሁትን ሁሉ እርሱ ያደርግልሻልና። ኃጢአቴን ይቅር ይለኝ ዘንድ ወደ እርሱ እንድትለምኝልኝ እማጸንሻለሁ። ሰላምን ስለሰጠሽ ስለ አብ ከአንቺ ስለተወለደው አንቺንም ስለተዋሐደው ከአንቺም ሰው ስለሆነው ስለወልድ ፣ ስለቀደሰሽ፣ ከሦስቱ ቅዱስ ለአንዱ ማደሪያ ለመሆን እስከሚገባሽ ድረስ ስላነጻሽ ስለመንፈስቅዱስም እለምንሻለሁ። አገልጋይሽን ተወዳጁ ልጅሽ እንዲመግበኝ ትለምኝልኝ ዘንድ እማጸንሻለሁ። ለዘለዓለሙ አሜን።
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ባስልዮስ ሆይ! ንገረኝ...
በዚህ ዓለም የሥራ መስክ ገበሬ መርከብ ለመንዳት የማይነሣው፣ ወይም ወታደሩ የግብርናን ሥራ የማይሠራው፣ ወይም ሙያው መርከብ ነጂ የኾነ ሰው ጦር እንዲመራ እልፍ ጊዜ ቢጎተትም እንኳ እሺ የማይለው ለምንድን ነው? እያንዳንዱ ያለችሎታው ቢሰማራ የሚከተለውን አደጋ አስቀድሞ ስለሚያይ አይደለምን? ታዲያ ጥፋቱ ቁሳቁስና ንብረት በሚኾንበት ኹኔታ አስቀድመን ብዙ የምናስብና ግፊትና ግዴታን የማንቀበል ኾነን ሳለ፥ ክህነትን እንዴት እንደሚይዙትና እንደሚያገለግሉበት ለማያውቁ ቅጣቱ ዘለዓለማዊ በኾነበት ኹኔታ ግን ያለብዙ ማሰብና ማሰላሰል እንዲሁ በዘፈቀደ ወደዚህ ዓይነት ታላቅ አደጋ ውስጥ ዘለን እንገባለንን? የሌሎች ሰዎች ግፊትስ ምክንያት ሊኾነን ይችላልን? አንድ ቀን ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ የኾነው እግዚአብሔር ይጠይቀናል፡፡ ይህ ሰበብም አያድነንም፡፡
ከምድራዊ ነገሮች ይልቅ በመንፈሳዊ ነገሮች ላይ ይበልጥ ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናልና፡፡ በትንንሽ ነገሮች ላይ ጠንቃቆች ስንኾን እንታያለንና፡፡ እስኪ ንገረኝ! አንድ ሰው የቤት ሥራ ሙያ ሳይኖረው ብትሠራልን ስንለው እሺ ብሎ ቢመጣና ከዚያ በኋላ ግን ዕንጨቱንና ድንጋዩን ቢያበላሽና የሠራው ነገር ወዲያውኑ ተበታትኖ ቢወድቅ በራሱ ፈልጎ አለመምጣቱና በሌሎች ግፊት ሥራውን መጀመሩ በቂ ምክንያት ሊኾነው ይችላልን? በጭራሽ! የሌሎችን ግፊትና ጥሪ አልቀበልም ማለት ነበረበትና በርግጥም ተጠያቂ ነው፡፡
ታዲያ እንዲህ እንጨትና ድንጋይ ለሚያበላሽ ሰው በጥፋቱ ከመጠየቅና ከመቀጣት ለመዳን ምንም ምክንያት ከሌለው፥ ነፍሳትን የሚያጠፋ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በግድየለሽነት የሚያንጽ ሰው’ማ እንዴት? የሌሎች ግፊትና ማስገደድ በቂ ምክንያት ይኾነኛል ብሎ ሊያስብ ይችላልን? እንዲህ ብሎ ማሰብስ ሞኝነት አይደለምን?
ፈቃደኛ ያልኾነን ሰው ማንም ሊያስገድደው እንደማይችል ለማሳየት ብዬ ሐተታ መስጠት አያስፈልገኝም፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት እንደ ተናገርኩት ይህ ፈቃደኛ ያልኾነ ሰው እጅግ ተጭነዉትና ግድ ብለዉት ሌሎች ብዙ መንገዶችንም ተጠቅመው ወደዚህ ኃላፊነት አመጡት እንበል፡፡ ታዲያ ይህ ከቅጣት ሊታደገው ይችላልን? እማልድሃለሁ፤ በፍጹም ራሳችንን አናታልል! ሕፃናት ሳይቀሩ በቀላሉ በሚያውቁት ነገር ላይ እንደማናውቅ ኾነን አናስመስል፡፡ እንደማናውቅ ማስመሰላችን በዚያች ዕለት ላይ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም አይጠቅመንምና፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በዚህ ዓለም የሥራ መስክ ገበሬ መርከብ ለመንዳት የማይነሣው፣ ወይም ወታደሩ የግብርናን ሥራ የማይሠራው፣ ወይም ሙያው መርከብ ነጂ የኾነ ሰው ጦር እንዲመራ እልፍ ጊዜ ቢጎተትም እንኳ እሺ የማይለው ለምንድን ነው? እያንዳንዱ ያለችሎታው ቢሰማራ የሚከተለውን አደጋ አስቀድሞ ስለሚያይ አይደለምን? ታዲያ ጥፋቱ ቁሳቁስና ንብረት በሚኾንበት ኹኔታ አስቀድመን ብዙ የምናስብና ግፊትና ግዴታን የማንቀበል ኾነን ሳለ፥ ክህነትን እንዴት እንደሚይዙትና እንደሚያገለግሉበት ለማያውቁ ቅጣቱ ዘለዓለማዊ በኾነበት ኹኔታ ግን ያለብዙ ማሰብና ማሰላሰል እንዲሁ በዘፈቀደ ወደዚህ ዓይነት ታላቅ አደጋ ውስጥ ዘለን እንገባለንን? የሌሎች ሰዎች ግፊትስ ምክንያት ሊኾነን ይችላልን? አንድ ቀን ፈታሒ በጽድቅ ኰናኒ በርትዕ የኾነው እግዚአብሔር ይጠይቀናል፡፡ ይህ ሰበብም አያድነንም፡፡
ከምድራዊ ነገሮች ይልቅ በመንፈሳዊ ነገሮች ላይ ይበልጥ ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናልና፡፡ በትንንሽ ነገሮች ላይ ጠንቃቆች ስንኾን እንታያለንና፡፡ እስኪ ንገረኝ! አንድ ሰው የቤት ሥራ ሙያ ሳይኖረው ብትሠራልን ስንለው እሺ ብሎ ቢመጣና ከዚያ በኋላ ግን ዕንጨቱንና ድንጋዩን ቢያበላሽና የሠራው ነገር ወዲያውኑ ተበታትኖ ቢወድቅ በራሱ ፈልጎ አለመምጣቱና በሌሎች ግፊት ሥራውን መጀመሩ በቂ ምክንያት ሊኾነው ይችላልን? በጭራሽ! የሌሎችን ግፊትና ጥሪ አልቀበልም ማለት ነበረበትና በርግጥም ተጠያቂ ነው፡፡
ታዲያ እንዲህ እንጨትና ድንጋይ ለሚያበላሽ ሰው በጥፋቱ ከመጠየቅና ከመቀጣት ለመዳን ምንም ምክንያት ከሌለው፥ ነፍሳትን የሚያጠፋ፣ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በግድየለሽነት የሚያንጽ ሰው’ማ እንዴት? የሌሎች ግፊትና ማስገደድ በቂ ምክንያት ይኾነኛል ብሎ ሊያስብ ይችላልን? እንዲህ ብሎ ማሰብስ ሞኝነት አይደለምን?
ፈቃደኛ ያልኾነን ሰው ማንም ሊያስገድደው እንደማይችል ለማሳየት ብዬ ሐተታ መስጠት አያስፈልገኝም፡፡ ነገር ግን ከዚህ በፊት እንደ ተናገርኩት ይህ ፈቃደኛ ያልኾነ ሰው እጅግ ተጭነዉትና ግድ ብለዉት ሌሎች ብዙ መንገዶችንም ተጠቅመው ወደዚህ ኃላፊነት አመጡት እንበል፡፡ ታዲያ ይህ ከቅጣት ሊታደገው ይችላልን? እማልድሃለሁ፤ በፍጹም ራሳችንን አናታልል! ሕፃናት ሳይቀሩ በቀላሉ በሚያውቁት ነገር ላይ እንደማናውቅ ኾነን አናስመስል፡፡ እንደማናውቅ ማስመሰላችን በዚያች ዕለት ላይ በእውነት ያለ ሐሰት ምንም አይጠቅመንምና፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የሰው ልጅ ከውድቀት በፊት
እግዚአብሔር የሰው ልጅን ሲፈጥረው እንደ መላእክት አድርጎ ነው። ቅዱስት መላእክት ለባውያን፡ ሥጋዊ መሻት የሌለባቸው ከኃጢአት የነጹ እንደ ኾኑ ሁሉ የሰው ልጅም ሲፈጠር ምንም እንኳን ሥጋን የለበሰ ቢኾንም እንዲህ ኾኖ ነበር። የሰው ልጅ ያልተለመደ ዓይነት መልአክ ኾኖ የተፈጠረ ነው። ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ አዳምንና ሔዋንን ኹለት መላእክት" የሚላቸውም ለዚህ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ጋር ኾኖ ከአምላክ ጋር አንድነት የነበረው፡
ዲያብሎስና እርሱን የተከተሉት መላእክት እንዲቀኑ ያደረጋቸው የሰው ልጅ ሕይወት ነበር። ምንም እንኳን ሥጋን የለበሰ ቢኾንም እንደ ረቂቃኑ” መላእክት መኖሩ፣ በአንድ ጊዜ ረቂቅና ግዙፍ ፍጥረት መኾኑ ነበር ያስቀናቸው::
ይህ ሰው ለሞት የተፈጠረ አልነበረም። ምንም እንኳን ካለ መኖር ወደ መኖር የተፈጠረ እንደ መኾኑ በባሕርዩ ሊሞት የሚችል ማለት ሞት የሚስማማው ገና የተፈጠረ ቢኾንም፥ ሕያው ባሕርይ በኾነው በራሱ በእግዚአብሔር አርአያ የተፈጠረ በመኾኑ ሕጉን በመጠበቅና ፈጣሪውን በማወቅ ይህንን አርአያ እግዚአብሔርን ቢጠብቅ ግን አይሞትም ነበር። እግዚአብሔር ሕያው የምታደርገውን ነፍስ የሰጠው ስለ ኾነ ብሩህ፡ ውብ፡ ለባዊ፡ መልካም ሥራዎችን ለመሥራት ዓቅም ያለው የተፈጠረ ነው፥ ይሀ በርግጥም ልዩ ክብር እንደ ነበረ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘቡል) ሲገልፀውም፡-
ከዚህ ክብር የሚበልጥ ምን ክብር አለ? ከዚህ ትምክሕት የሚበልጥ ምን
የሚያስመካ ነገር አለ?... ሰውን በእርሱ አምሳል እንደ ፈጠረው እንዲመሰክር ከመኾን የበለጠ የሚያስመካ ምን ነገር አለ?" ይላል ።"
ሙስና፡ ሞት፡ ሕማምና ድካም የመጡበት ከዚህ በኤደን ገነት ውስጥ ይኖርበት ከነበረው የንጽሕናና የድንግልና ሕይወት ፈቀቅ ሲል ነው። ሞት የሚስማማው ኾኖ የተፈጠረ ቢኾንም፥ በገዛ ፈቃዱ እንዳይሞት ማድረግ ይችል የነበረው የሰው ልጅ መዋቲ የኾነው ከበደለ በኋላ ነው።
ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተፈጠረ ቢኾንም፥ ክብሩ ግን ሰማያዊ ነበር። አፈርና ትቢያ የኾነው፡ እግዚአብሔር የነገረውን ባለ ማመን ብሎም ባለመታዘዝ ሲበድል ነው። ጥንቱን ከትቢያ የተፈጠረ ቢኾንም እስኪወድቅ ድረስ ክብሩ እፍ ተብላ ከተሰጠችው ነፍሱ የተነሣ ከፍ ያለ ነበር። ስለዚህም እንደ መላእክት ስለሚበላው፡ ስለሚጠጣው፣ ስለሚለብሰው፡ ስለ እንቅልፍ፣ ወጥቶ ወርዶ ስለ መሥራት፣ በአጠቃላይ ስለዚህ ዓለም ኑሮ የሚጨነቅ አልነበረም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ይህን ግልፅ አድርጎ ሲነግረንም እንዲህ ይላል፡-
ምንም እንኳን በዚህ ምድር ላይ ሥጋ ለብሶ ቢኖርም ፍትወተ ሥጋ ሳይኖርበት እንደ ሰማያውያን መላእክት ኾኖ ይኖር ነበር። በትረ መንግሥቱን ይዞ የንግሥና ዘውዱን ጭኖ፡ ሐምራዊ መጎናጸፍያውን አድርጎ እንዳጌጠ ንጉሥ በነጻነትና በፍጹም ደስታ ይኖር ነበር። አንድም ነገር ሳይጐድልበት እጅግ ባለጸጋ ኾኖ በገነት ይኖር ነበር።
"
ይበላ የነበረ ቢኾንም፤ በአንድ መልኩ ጥሮ ግሮ የሚበላ አልነበረም፡ በሌላ መልኩ ደግሞ አሁን የምናውቀው ዓይነት ረሃብና ጥም ስለ ነበረበት አይደለም። መላእክት እንደማይርባቸውና እንደማይጠማቸው ኹሉ፥ ሰውም እንደዚህ ነበር። ሰውስ ይቅርና ዛሬ ሥጋ በል የምንላቸው እንስሳትም ከውድቀት በፊት ምግባቸው ማር እንጂ ሥጋ እንዳልነበረ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ይነግረናል።'
በዚያን ጊዜ የሰው ልጅ ምንም እንኳን ሥጋ የለበሰ የነበረ ቢኾንም፥ በሥጋው ብቻ የታጠረ ግን አልነበረም። መላእክት ሥጋዊ ፍላጎት እንደ ሌለባቸው ኹሉ' ሰውም ይህ ኣልነበረበትም። መላእክት ልብስ እንደማያሻቸው ኹሉ' ሰውም ልብስ የሚያስፈልገው አልነበረም። ልብሱ፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ እንደሚነግረን የክብር ልብስ ነበር ይህን የክብር ልብስ ለብሶ እያለ' እስራኤላውያን ሊቀ ነቢያት ሙሴ ፊቱን ሳይሽፍን ማየት የማይቻላቸው እንደ ኾኑ፥ የምድር ፍጥረታትም አዳምንና ሔዋንን ማየት አይቻላቸውም ነበር። አዳም ለእንስሳቱ ስም ሲያወጣላቸውና በፊቱ ሲያልፉ እንኳን ቀና ብለው ማየት ሳይቻላቸው አጎንብሰው ነበር። አዳም ለብሶት የነበረውን የክብር ልብስ ማየት አይቻላቸውም ነበር።' እንስሳቱስ ይቅሩና ዲያብሎስ ይህን የአዳም ክብር በግልፅ ማየት አይቻለውም ነበር።" አዳም ይህን የክብር ልብስ ለብሶ ሲኖር ከግዙፍ ልብስ ዕራቁቱ እንደ ኾነ እንኳን አያውቅም ነበር። ስለዚህ አሁን የምናውቀው ዓይነት ልብስ ለሰው ልጅ የተሰጠው "ለዚያ አጊጠዉበት ለነበረው የብርሃን ልብስና ከሥጋ መሻቶች ነጻ ኾነው ለኖሩበት ሕይወት ያልተገቡ ኾነው በመገኘታቸው ነው።'' የቆዳ ልብስ የተሰጣቸው ለዚያ የክብር ልብስ ያልተገቡ ኾነው በመገኘታቸው ብቻ ሳይኾን ላለማመናቸውና ላለመታዘዛቸው ማዘከሪያ እንዲኾን ነው።
ዳግመኛም የሰው ልጅ በራሱ ላይ ብቻ ሳይኾን በሌሎች በሚታዩ ፍጥረታት ላይ ንጉሥ ኾኖ ይኖር የነበረ ነው። መጨረሻ ላይ መፈጠሩ፣ ሌሎቹ ፍጥረታት ኹሉ እርሱ እንዲጠቀምባቸው መዘጋጀታቸው በገነት ውስጥ ያለ ጣር መኖሩ፡ እንስሳቱ ኹሉ ስም እንዲያወጣላቸው ወደ እርሱ መምጣታቸውም ይህን ንግሥናውን በግልፅ የሚያስረዱ ናቸው። ፍርሐትና መንቀጥቀጥ የመጣበት ከበደለ በኋላ ነው፤ ሔዋን ከእባብ ጋር ያለ ፍርሐት መነጋገርዋ ይህን የሚያሳይ ነው።
የሰው ልጅ ከውድቀት በፊት እጅግ ዐዋቂና ጠቢብም ጭምር ነበር። ይህም ሳይሳሳትና ሳይደግም ለእንስሳቱ ስም በማውጣቱ ታውቆአል።
ነጻነትም ነበረው። ከመበደሉ በፊት የሚያሻውን በጎ ነገር ለማድረግ አያቅተውም ነበር። በጎ ማድረግን አስቦ ማድረግ ያቃተው ሲበድል ነው።
ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ባልንጀራ አፍ ለአፍ የሚነጋገር ነበር። አባት ለልጁ ኹሉን ነገር እንደሚያስተምረው፥ እግዚአብሔርም ለአዳም ኹሉን ነገር ያስተምረው ነበር። በኋላ ሲወድቅ መጽሐፍ ቅዱስ የሰጠውም የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ስለ ራቀ ነው። አጠገብ ላለ ወዳጅ ደብዳቤ አይጻፍምና።በጎውንና ክፉውን የሚያውቅ መለየት የሚችል ነበር። መለየት የማይችል ቢኾን ኖሮ ባልተጠየቀ ነበርና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
እግዚአብሔር የሰው ልጅን ሲፈጥረው እንደ መላእክት አድርጎ ነው። ቅዱስት መላእክት ለባውያን፡ ሥጋዊ መሻት የሌለባቸው ከኃጢአት የነጹ እንደ ኾኑ ሁሉ የሰው ልጅም ሲፈጠር ምንም እንኳን ሥጋን የለበሰ ቢኾንም እንዲህ ኾኖ ነበር። የሰው ልጅ ያልተለመደ ዓይነት መልአክ ኾኖ የተፈጠረ ነው። ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ አዳምንና ሔዋንን ኹለት መላእክት" የሚላቸውም ለዚህ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ጋር ኾኖ ከአምላክ ጋር አንድነት የነበረው፡
ዲያብሎስና እርሱን የተከተሉት መላእክት እንዲቀኑ ያደረጋቸው የሰው ልጅ ሕይወት ነበር። ምንም እንኳን ሥጋን የለበሰ ቢኾንም እንደ ረቂቃኑ” መላእክት መኖሩ፣ በአንድ ጊዜ ረቂቅና ግዙፍ ፍጥረት መኾኑ ነበር ያስቀናቸው::
ይህ ሰው ለሞት የተፈጠረ አልነበረም። ምንም እንኳን ካለ መኖር ወደ መኖር የተፈጠረ እንደ መኾኑ በባሕርዩ ሊሞት የሚችል ማለት ሞት የሚስማማው ገና የተፈጠረ ቢኾንም፥ ሕያው ባሕርይ በኾነው በራሱ በእግዚአብሔር አርአያ የተፈጠረ በመኾኑ ሕጉን በመጠበቅና ፈጣሪውን በማወቅ ይህንን አርአያ እግዚአብሔርን ቢጠብቅ ግን አይሞትም ነበር። እግዚአብሔር ሕያው የምታደርገውን ነፍስ የሰጠው ስለ ኾነ ብሩህ፡ ውብ፡ ለባዊ፡ መልካም ሥራዎችን ለመሥራት ዓቅም ያለው የተፈጠረ ነው፥ ይሀ በርግጥም ልዩ ክብር እንደ ነበረ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘቡል) ሲገልፀውም፡-
ከዚህ ክብር የሚበልጥ ምን ክብር አለ? ከዚህ ትምክሕት የሚበልጥ ምን
የሚያስመካ ነገር አለ?... ሰውን በእርሱ አምሳል እንደ ፈጠረው እንዲመሰክር ከመኾን የበለጠ የሚያስመካ ምን ነገር አለ?" ይላል ።"
ሙስና፡ ሞት፡ ሕማምና ድካም የመጡበት ከዚህ በኤደን ገነት ውስጥ ይኖርበት ከነበረው የንጽሕናና የድንግልና ሕይወት ፈቀቅ ሲል ነው። ሞት የሚስማማው ኾኖ የተፈጠረ ቢኾንም፥ በገዛ ፈቃዱ እንዳይሞት ማድረግ ይችል የነበረው የሰው ልጅ መዋቲ የኾነው ከበደለ በኋላ ነው።
ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋና ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ የተፈጠረ ቢኾንም፥ ክብሩ ግን ሰማያዊ ነበር። አፈርና ትቢያ የኾነው፡ እግዚአብሔር የነገረውን ባለ ማመን ብሎም ባለመታዘዝ ሲበድል ነው። ጥንቱን ከትቢያ የተፈጠረ ቢኾንም እስኪወድቅ ድረስ ክብሩ እፍ ተብላ ከተሰጠችው ነፍሱ የተነሣ ከፍ ያለ ነበር። ስለዚህም እንደ መላእክት ስለሚበላው፡ ስለሚጠጣው፣ ስለሚለብሰው፡ ስለ እንቅልፍ፣ ወጥቶ ወርዶ ስለ መሥራት፣ በአጠቃላይ ስለዚህ ዓለም ኑሮ የሚጨነቅ አልነበረም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ይህን ግልፅ አድርጎ ሲነግረንም እንዲህ ይላል፡-
ምንም እንኳን በዚህ ምድር ላይ ሥጋ ለብሶ ቢኖርም ፍትወተ ሥጋ ሳይኖርበት እንደ ሰማያውያን መላእክት ኾኖ ይኖር ነበር። በትረ መንግሥቱን ይዞ የንግሥና ዘውዱን ጭኖ፡ ሐምራዊ መጎናጸፍያውን አድርጎ እንዳጌጠ ንጉሥ በነጻነትና በፍጹም ደስታ ይኖር ነበር። አንድም ነገር ሳይጐድልበት እጅግ ባለጸጋ ኾኖ በገነት ይኖር ነበር።
"
ይበላ የነበረ ቢኾንም፤ በአንድ መልኩ ጥሮ ግሮ የሚበላ አልነበረም፡ በሌላ መልኩ ደግሞ አሁን የምናውቀው ዓይነት ረሃብና ጥም ስለ ነበረበት አይደለም። መላእክት እንደማይርባቸውና እንደማይጠማቸው ኹሉ፥ ሰውም እንደዚህ ነበር። ሰውስ ይቅርና ዛሬ ሥጋ በል የምንላቸው እንስሳትም ከውድቀት በፊት ምግባቸው ማር እንጂ ሥጋ እንዳልነበረ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ይነግረናል።'
በዚያን ጊዜ የሰው ልጅ ምንም እንኳን ሥጋ የለበሰ የነበረ ቢኾንም፥ በሥጋው ብቻ የታጠረ ግን አልነበረም። መላእክት ሥጋዊ ፍላጎት እንደ ሌለባቸው ኹሉ' ሰውም ይህ ኣልነበረበትም። መላእክት ልብስ እንደማያሻቸው ኹሉ' ሰውም ልብስ የሚያስፈልገው አልነበረም። ልብሱ፣ ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ እንደሚነግረን የክብር ልብስ ነበር ይህን የክብር ልብስ ለብሶ እያለ' እስራኤላውያን ሊቀ ነቢያት ሙሴ ፊቱን ሳይሽፍን ማየት የማይቻላቸው እንደ ኾኑ፥ የምድር ፍጥረታትም አዳምንና ሔዋንን ማየት አይቻላቸውም ነበር። አዳም ለእንስሳቱ ስም ሲያወጣላቸውና በፊቱ ሲያልፉ እንኳን ቀና ብለው ማየት ሳይቻላቸው አጎንብሰው ነበር። አዳም ለብሶት የነበረውን የክብር ልብስ ማየት አይቻላቸውም ነበር።' እንስሳቱስ ይቅሩና ዲያብሎስ ይህን የአዳም ክብር በግልፅ ማየት አይቻለውም ነበር።" አዳም ይህን የክብር ልብስ ለብሶ ሲኖር ከግዙፍ ልብስ ዕራቁቱ እንደ ኾነ እንኳን አያውቅም ነበር። ስለዚህ አሁን የምናውቀው ዓይነት ልብስ ለሰው ልጅ የተሰጠው "ለዚያ አጊጠዉበት ለነበረው የብርሃን ልብስና ከሥጋ መሻቶች ነጻ ኾነው ለኖሩበት ሕይወት ያልተገቡ ኾነው በመገኘታቸው ነው።'' የቆዳ ልብስ የተሰጣቸው ለዚያ የክብር ልብስ ያልተገቡ ኾነው በመገኘታቸው ብቻ ሳይኾን ላለማመናቸውና ላለመታዘዛቸው ማዘከሪያ እንዲኾን ነው።
ዳግመኛም የሰው ልጅ በራሱ ላይ ብቻ ሳይኾን በሌሎች በሚታዩ ፍጥረታት ላይ ንጉሥ ኾኖ ይኖር የነበረ ነው። መጨረሻ ላይ መፈጠሩ፣ ሌሎቹ ፍጥረታት ኹሉ እርሱ እንዲጠቀምባቸው መዘጋጀታቸው በገነት ውስጥ ያለ ጣር መኖሩ፡ እንስሳቱ ኹሉ ስም እንዲያወጣላቸው ወደ እርሱ መምጣታቸውም ይህን ንግሥናውን በግልፅ የሚያስረዱ ናቸው። ፍርሐትና መንቀጥቀጥ የመጣበት ከበደለ በኋላ ነው፤ ሔዋን ከእባብ ጋር ያለ ፍርሐት መነጋገርዋ ይህን የሚያሳይ ነው።
የሰው ልጅ ከውድቀት በፊት እጅግ ዐዋቂና ጠቢብም ጭምር ነበር። ይህም ሳይሳሳትና ሳይደግም ለእንስሳቱ ስም በማውጣቱ ታውቆአል።
ነጻነትም ነበረው። ከመበደሉ በፊት የሚያሻውን በጎ ነገር ለማድረግ አያቅተውም ነበር። በጎ ማድረግን አስቦ ማድረግ ያቃተው ሲበድል ነው።
ከእግዚአብሔር ጋር እንደ ባልንጀራ አፍ ለአፍ የሚነጋገር ነበር። አባት ለልጁ ኹሉን ነገር እንደሚያስተምረው፥ እግዚአብሔርም ለአዳም ኹሉን ነገር ያስተምረው ነበር። በኋላ ሲወድቅ መጽሐፍ ቅዱስ የሰጠውም የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ስለ ራቀ ነው። አጠገብ ላለ ወዳጅ ደብዳቤ አይጻፍምና።በጎውንና ክፉውን የሚያውቅ መለየት የሚችል ነበር። መለየት የማይችል ቢኾን ኖሮ ባልተጠየቀ ነበርና።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#መንፈሳዊ_ብስለት
በሕይወታችን ውስጥ እግዚአብሔር የራቀ ፣ ሌላው ቀርቶ ከእኛ አጠገብ የማይገኝ የሚመስልበት ጊዜ አለ። እነዚህ ጊዜያት እምነታችን ደካማ የሚመስልበትና እግዚአብሔር ለእኛ በእውነት እንደሚያስብልን ለማመን የምንታገልበት ወይም ምናልባት እግዚአብሔር መኖሩን እንኳን መጠራጠር የምንጀምርበት ጊዜ ነው። በምዕራባዊው የክርስትና ባህል እነዚህ ጊዜያት ብዙውን ጊዜ የነፍስ ጨለማ ምሽት (The dark night of the soul) ብለው ይጠሩታል። እግዚአብሔር ከእኛ የራቀ ይመስላል እኛም ከእምነታችን ጋር እንታገላለን።
በእንደዚህ ዓይነት ጊዜያት እግዚአብሔር ከራሳችን እስትንፋስ ይልቅ ወደ እኛ እንደሚቀርብ እና እኛ ብቻ ግን እሱ እንደሌለ እንደሚሰማን ማስታወሱ ጥሩ ነው። እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ እንድንሠራ ለማድረግ እንዲህ ያሉትን ወቅቶች በሕይወታችን ይጠቀማል። ስንታገል እንጠነክራለን። እግዚአብሔር ራሱን ያገለለ በሚመስልበት ጊዜ አንድ ህፃን በእግሩ ቆሞ እንዲሄድ ጥቂት ርቀት ላይ ሆኖ እንደሚጠብቅ ወላጅ አይነት ነው። ልጁ የመጀመሪያውን እርምጃውን ብቻውን እንዲራመድ ያበረታዋል። ወላጁም ህፃኑ ከወደቀበት ለመድረስ ዝግጁ ነው። ነገር ግን ህፃኑ የመጀመሪያውን እርምጃ እንዲራመድ ወላጅ መፍቀዱ ለልጁ እድገት አስፈላጊ ነው።
ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት የመጀመሪያውን ጉዞ ብቻችንን እንድንራመድ በተገደድን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ጸጋ ያንጸናል፣ ይህም በእምነት እንድንበስል ያስችለናል። እግዚአብሔር እንደሚያስፈልገን ካልተሰማን በቀር መንፈሳዊ እድገት ይመጣ ዘንድ አይቻልም። እግዚአብሔር በራሱ እኛን አያስገድደንም። ብቻ ግን አንድ እርምጃ እንኳ እንድንራመድ ይጠብቃል። በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት የምንገነዘበው በትጋትና በተጋድሎ ውስጥ ስንሆን ነው፣ እና የበኩላችንን እስካደረግን ድረስ፣ የእግዚአብሔር ጸጋ በብዛት ይፈስልናል።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በሕይወታችን ውስጥ እግዚአብሔር የራቀ ፣ ሌላው ቀርቶ ከእኛ አጠገብ የማይገኝ የሚመስልበት ጊዜ አለ። እነዚህ ጊዜያት እምነታችን ደካማ የሚመስልበትና እግዚአብሔር ለእኛ በእውነት እንደሚያስብልን ለማመን የምንታገልበት ወይም ምናልባት እግዚአብሔር መኖሩን እንኳን መጠራጠር የምንጀምርበት ጊዜ ነው። በምዕራባዊው የክርስትና ባህል እነዚህ ጊዜያት ብዙውን ጊዜ የነፍስ ጨለማ ምሽት (The dark night of the soul) ብለው ይጠሩታል። እግዚአብሔር ከእኛ የራቀ ይመስላል እኛም ከእምነታችን ጋር እንታገላለን።
በእንደዚህ ዓይነት ጊዜያት እግዚአብሔር ከራሳችን እስትንፋስ ይልቅ ወደ እኛ እንደሚቀርብ እና እኛ ብቻ ግን እሱ እንደሌለ እንደሚሰማን ማስታወሱ ጥሩ ነው። እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ባለን ግንኙነት ውስጥ እንድንሠራ ለማድረግ እንዲህ ያሉትን ወቅቶች በሕይወታችን ይጠቀማል። ስንታገል እንጠነክራለን። እግዚአብሔር ራሱን ያገለለ በሚመስልበት ጊዜ አንድ ህፃን በእግሩ ቆሞ እንዲሄድ ጥቂት ርቀት ላይ ሆኖ እንደሚጠብቅ ወላጅ አይነት ነው። ልጁ የመጀመሪያውን እርምጃውን ብቻውን እንዲራመድ ያበረታዋል። ወላጁም ህፃኑ ከወደቀበት ለመድረስ ዝግጁ ነው። ነገር ግን ህፃኑ የመጀመሪያውን እርምጃ እንዲራመድ ወላጅ መፍቀዱ ለልጁ እድገት አስፈላጊ ነው።
ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት የመጀመሪያውን ጉዞ ብቻችንን እንድንራመድ በተገደድን ቁጥር፣ የእግዚአብሔር ጸጋ ያንጸናል፣ ይህም በእምነት እንድንበስል ያስችለናል። እግዚአብሔር እንደሚያስፈልገን ካልተሰማን በቀር መንፈሳዊ እድገት ይመጣ ዘንድ አይቻልም። እግዚአብሔር በራሱ እኛን አያስገድደንም። ብቻ ግን አንድ እርምጃ እንኳ እንድንራመድ ይጠብቃል። በሕይወታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት የምንገነዘበው በትጋትና በተጋድሎ ውስጥ ስንሆን ነው፣ እና የበኩላችንን እስካደረግን ድረስ፣ የእግዚአብሔር ጸጋ በብዛት ይፈስልናል።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የሰው ልጅ ከውድቀት በኋላ
የሰው ልጅ ፍጹም የተለወጠው በእግዚአብሔር ላይ ሲያምፅ ነው። ያን ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ተለየው፤ ያን ጊዜ የክብር ልብሱ ተወሰደበት፤ ያን ጊዜ ሐፍረትና ውርደት አገኘው፤ ያን ጊዜ ከመላእክት ሕይወት ወርዶ የዚህ ዓለም ጭንቀት የሚገዛው ፣ ጥሮ ግሮ የሚበላ፣ ልብሱ ከእንስሳት የተገኘ ቆዳ፣ እጅግ ብርቱ የኾኑ ፍትወታትና ሥጋዊ መሻቶች የሚጸኑበት፣ የሚርበው፣ የሚጠማው፣ የሚደክምና የሚሞት ኾነ።
እግዚአብሔርን መስሎ የሚያድግበት አቅም በውስጡ የነበረ ቢኾንም፥ የሰይጣንን ምክር ሰምቶ በአቋራጭ ያልተገባ ክብርን በመሻቱ ምክንያት፥ ያን ጊዜ የማያድግ ይልቁንስ ቁልቁል የሚወርድ ኾነ። እንደ እንስሳት የሚኖር አላዋቂ ኾነ። እንደ እንስሳት መኖርም የሰው ልጅ የመጨረሻ የውርደት መገለጫ ነበር።
የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሮ ሳለ እንደ እንስሳት ሲኖር ማየት በእውነት ጥንቱን እንስሳ ኾኖ በተፈጠረ በተሻለው ነበር የሚያስብል ኾነ። ከጌታ በታች ገዢ ሲኾን ይህን ባለማወቁና ከዕፀ በለስ ሰርቆ በመብላቱ በፍቃዱ ራሱን አዋርዷልና፥ ባሪያ ኾኖ ጌቶች ያልኾኑት የሚገዙት ኾኗልና እጅግ አሳዛኝ ፍጥረት ኾነ። በኃጢአት ብዛት ጠቁሮ በሰማያውያን አምሳል መኖር ተሳነው።
ቅዱስ ኤፍሬምም ይህንን ሲያይ፡-
"አዳም ከንግሥና ወርዶ ከእንስሳት መኖሪያ ሲያየው እንዴት እንደ ወደቀ እያሰበ ዳዊት አለቀሰለት (መዝ.48፡13)። ሸሽቶ ከዱር እንደ ተደበቀ የዱር እንስሳትን መሰለ። ከወደቀበት መርገም የተነሣም ከእንስሳት ጋር ሣርና ሥራሥር በላ፤ ጓደኛቸው ኾኖም እንደ እነርሱ ሞተ አለ።
ስለዚህም እውነተኛ ሰው መኾን ተሳነው። ሰውን ሰው የሚያስብለው የሰው መልክ ዓይን፣ አፍንጫ፣ አፍ ስላለው አይደለምና። እነዚህ የሰውነት ብልቶች ናቸውና። ሰው ብለን ልንጠራው የሚገባን የሰው ልጅን ጠባይ መገለጫ ገንዘብ አድርጎ ሲገኝ ነውና፤ እርሱም ማሰብ መቻሉና በዚያ መሠረት የቅድስና ሕይወትን መያዝ ነው።
ቀድሞ ይገዛቸው ይነዳቸው የነበሩት ብዙ እንስሳት በእርሱ ላይ የሚነሣሡበት ኾኑ። ምንም እንኳን ቀድሞ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ የተገኘ ኾኖ ሳለ እንደ መላእክት ይኖር የነበረ ቢኾንም፥ ሲወድቅ ግን ወደ እርሱ የሚመለስ ኾነ። መንፈስ ቅዱስ የማይመራው የማይነዳው ኾነ። ቀድሞ የነበረው እጅግ አስደናቂ ዐዋቂነትን አጥቶ በድንግዝግዝ የሚጓዝ ኾነ። ሞት ሙስና፣ ክፋት የአዳም አዲሶቹ መገለጫዎቹ ኾኑ።
ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ፥ አዳም ከእግዚአብሔር ጋር አፍ ለአፍ የማይነጋገር ኾነ። በእርሱና በእግዚአብሔር መካከል ኃጢአት እንደ ግድግዳ ኾኖ ቆመ። በዚህ ኹኔታ ውስጥ ላየውም ከላይ እንደ ተገለፀው አዳም እጅግ የሚያሳዝን ፍጥረት ኾነ። ሰውነቱ በኃጢአት ለመጠቃት እጅግ ተጋለጠ። ሞት ከተፈረደበት በኋላ ፍትወታት ወደ ባሕርዩ ዘልቀው ስለ ገቡ ደግ ሥራን ለመሥራት ከባድ ኾነበት። ልጓም የሌላት ፈረስ እንዲሁ እንደምትላተምና እንደምትወድቅ፥ ሰውም እንደዚህ ኾነ። ከምንም በላይ ደግሞ የአዳምና የሔዋን አንድነት ወደ መፍረስ ተቃረበ። በዲያብሎስ ምክር ምክንያት አዳምና ሔዋን እየተካሰሱና አንዳቸው በአንዳቸው ላይ እያመካኙ ወደ መለያየት የተቃረቡ ኾኑ።
ሲወድቅ የሚጠቅሙት (መንሻ የሚኾኑት)፥ ግን ደግሞ የውድቀቱ ማሳያ የኾኑ መገለጫዎች ወደ ባሕርዩ ዘልቀው ገቡ። ምክንያቱም ፍርሐት ሲመጣበት ስለ ኃጢአት፣ ኀዘን ሲመጣበት ስለ ኃጢአት፡ ሞት ሲመጣበት ስለ ኃጢአት እንዲያስብ እንጂ እርሱን ለመጉዳት የመጡ አይደሉምና። እግዚአብሔር እነዚህን ኹሉ የሰጠው በበደል ላይ በደል እየጨመረ እንዳይጠፋ ነው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
የሰው ልጅ ፍጹም የተለወጠው በእግዚአብሔር ላይ ሲያምፅ ነው። ያን ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ተለየው፤ ያን ጊዜ የክብር ልብሱ ተወሰደበት፤ ያን ጊዜ ሐፍረትና ውርደት አገኘው፤ ያን ጊዜ ከመላእክት ሕይወት ወርዶ የዚህ ዓለም ጭንቀት የሚገዛው ፣ ጥሮ ግሮ የሚበላ፣ ልብሱ ከእንስሳት የተገኘ ቆዳ፣ እጅግ ብርቱ የኾኑ ፍትወታትና ሥጋዊ መሻቶች የሚጸኑበት፣ የሚርበው፣ የሚጠማው፣ የሚደክምና የሚሞት ኾነ።
እግዚአብሔርን መስሎ የሚያድግበት አቅም በውስጡ የነበረ ቢኾንም፥ የሰይጣንን ምክር ሰምቶ በአቋራጭ ያልተገባ ክብርን በመሻቱ ምክንያት፥ ያን ጊዜ የማያድግ ይልቁንስ ቁልቁል የሚወርድ ኾነ። እንደ እንስሳት የሚኖር አላዋቂ ኾነ። እንደ እንስሳት መኖርም የሰው ልጅ የመጨረሻ የውርደት መገለጫ ነበር።
የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጥሮ ሳለ እንደ እንስሳት ሲኖር ማየት በእውነት ጥንቱን እንስሳ ኾኖ በተፈጠረ በተሻለው ነበር የሚያስብል ኾነ። ከጌታ በታች ገዢ ሲኾን ይህን ባለማወቁና ከዕፀ በለስ ሰርቆ በመብላቱ በፍቃዱ ራሱን አዋርዷልና፥ ባሪያ ኾኖ ጌቶች ያልኾኑት የሚገዙት ኾኗልና እጅግ አሳዛኝ ፍጥረት ኾነ። በኃጢአት ብዛት ጠቁሮ በሰማያውያን አምሳል መኖር ተሳነው።
ቅዱስ ኤፍሬምም ይህንን ሲያይ፡-
"አዳም ከንግሥና ወርዶ ከእንስሳት መኖሪያ ሲያየው እንዴት እንደ ወደቀ እያሰበ ዳዊት አለቀሰለት (መዝ.48፡13)። ሸሽቶ ከዱር እንደ ተደበቀ የዱር እንስሳትን መሰለ። ከወደቀበት መርገም የተነሣም ከእንስሳት ጋር ሣርና ሥራሥር በላ፤ ጓደኛቸው ኾኖም እንደ እነርሱ ሞተ አለ።
ስለዚህም እውነተኛ ሰው መኾን ተሳነው። ሰውን ሰው የሚያስብለው የሰው መልክ ዓይን፣ አፍንጫ፣ አፍ ስላለው አይደለምና። እነዚህ የሰውነት ብልቶች ናቸውና። ሰው ብለን ልንጠራው የሚገባን የሰው ልጅን ጠባይ መገለጫ ገንዘብ አድርጎ ሲገኝ ነውና፤ እርሱም ማሰብ መቻሉና በዚያ መሠረት የቅድስና ሕይወትን መያዝ ነው።
ቀድሞ ይገዛቸው ይነዳቸው የነበሩት ብዙ እንስሳት በእርሱ ላይ የሚነሣሡበት ኾኑ። ምንም እንኳን ቀድሞ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ የተገኘ ኾኖ ሳለ እንደ መላእክት ይኖር የነበረ ቢኾንም፥ ሲወድቅ ግን ወደ እርሱ የሚመለስ ኾነ። መንፈስ ቅዱስ የማይመራው የማይነዳው ኾነ። ቀድሞ የነበረው እጅግ አስደናቂ ዐዋቂነትን አጥቶ በድንግዝግዝ የሚጓዝ ኾነ። ሞት ሙስና፣ ክፋት የአዳም አዲሶቹ መገለጫዎቹ ኾኑ።
ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ፥ አዳም ከእግዚአብሔር ጋር አፍ ለአፍ የማይነጋገር ኾነ። በእርሱና በእግዚአብሔር መካከል ኃጢአት እንደ ግድግዳ ኾኖ ቆመ። በዚህ ኹኔታ ውስጥ ላየውም ከላይ እንደ ተገለፀው አዳም እጅግ የሚያሳዝን ፍጥረት ኾነ። ሰውነቱ በኃጢአት ለመጠቃት እጅግ ተጋለጠ። ሞት ከተፈረደበት በኋላ ፍትወታት ወደ ባሕርዩ ዘልቀው ስለ ገቡ ደግ ሥራን ለመሥራት ከባድ ኾነበት። ልጓም የሌላት ፈረስ እንዲሁ እንደምትላተምና እንደምትወድቅ፥ ሰውም እንደዚህ ኾነ። ከምንም በላይ ደግሞ የአዳምና የሔዋን አንድነት ወደ መፍረስ ተቃረበ። በዲያብሎስ ምክር ምክንያት አዳምና ሔዋን እየተካሰሱና አንዳቸው በአንዳቸው ላይ እያመካኙ ወደ መለያየት የተቃረቡ ኾኑ።
ሲወድቅ የሚጠቅሙት (መንሻ የሚኾኑት)፥ ግን ደግሞ የውድቀቱ ማሳያ የኾኑ መገለጫዎች ወደ ባሕርዩ ዘልቀው ገቡ። ምክንያቱም ፍርሐት ሲመጣበት ስለ ኃጢአት፣ ኀዘን ሲመጣበት ስለ ኃጢአት፡ ሞት ሲመጣበት ስለ ኃጢአት እንዲያስብ እንጂ እርሱን ለመጉዳት የመጡ አይደሉምና። እግዚአብሔር እነዚህን ኹሉ የሰጠው በበደል ላይ በደል እየጨመረ እንዳይጠፋ ነው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ጥቅምት 27 "በዓለ ስቅለት"
ጥቅምት 27 በዚህች ዕለት የአምላካችን የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው።
መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለኹላችን ድኅነት ሲል ራሱን ወድዶ ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። በቅዱስ ወንጌልም እርሱም መድኃኒታችን " ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም" ብሎ ነግሮናል። እውነት ነው፣ ራስን ነፍስን ስለጠላት ነፍስ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ?
ቸሩ አምላካችንን የአስቆሮቱ ይሁዳ ሊያስይዘው የሊቃነ ካህናቱን አገልጋዮች እየመራ አመጣቸው። እነርሱንም ማንን ትፈልጋላችሁ ሲላቸው የናዝሬቱ ኢየሱስን አሉት፣ እኔ ነኝ ቢላቸው የቸሩን አምላክ ድምጽ ሰምቶ አይደለም መቆም በሕይወት መጽናት የሚቻለው የለምና ወደ ኋላቸው ተስፈንጥረው ወደቁ። ደጋግሞም እንዲህ ኾነ። በኋላ ግን እኔ ነኝ ብሎ በፈቃዱ ይሁዳ ስሞ አሳልፎ ሰጣቸው።
ከያዙት በኋላ እያዳፉና እየጎተቱ በሰንሰለት አስረው ወደ ቀያፋና ሐና ግቢ ወሰዱት፣ እስከ ሦስት ሰዓትም አላሳረፉትም ሲያሰቃዩት አድረዋል፣ በራሱም ላይ ሰባ ሦስት ስቊረት ያለው ወደ ሦስት መቶ እሾኾችን የያዘ የእሾህ አክሊል ጎንጉነው ቢያደርጉበት የራስ ቅሉን ቀዶ ገብቶ እስከ ልቡ ዘልቋል። እንደምን ጭንቅ ነው? እንዲህም አድርገው ደግሞ እያፌዙ ርኲስ ምራቃቸውን ይተፉበትና በዘንግም ደጋግመው ይመቱት ነበር። እየተፈራረቁ ያለ ምንም ርኅራኄ ቸሩን አምላክ ሥጋው እየተቆረጠ እስኪወድቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጽኑዕ ግርፋትን ገርፈውታል። የገረፉበትም ጅራፍ በላዩ ላይ ሥጋን እየጎመደ የሚጥል፣ ሕመሙ አንጀት ሰርሥሮ የሚገባ በስለት የተያያዘበት ነበር።
በኋላም አላሳረፉትም እንዲህ አድርገውትም በሊቶስጥራ አደባባይ ያንን ዕርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት። እርሱ ግን ይህን ኹሉ ግፍ ሲያደርሱበት አንድም አልተናገረም ነበር። በቀራንዮም በአምስት ጽኑዕ ቅንዋት (ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ እና ሮዳስ) ቸንክረው ዕርቃኑን ሰቀሉት።
በዚህች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተሰበረ መጽናናትንም አልፈለገች ነበር፤ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ እናቱንም እናት ትሆነው ዘንድ በእግረ መስቀሉ አደራን ተቀበለ። ቅዱሳት አንስት በፍጹም ሀዘንና በዋይታ ዋሉ። በስልጣኑም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። ሰባት ድንቅ የኾኑ ተአምራትንም አድርጎ አምላክ መኾኑን ገለጠ። ይህም ጽኑዕ የኾነ ለሰማይ ለምድር የከበደ ነገር ሲከሰት ፀሐይ አምላኬን ዕርቃኑ እንዴት አያለሁ ብላ ጨለመች። ጨረቃ ደም ኾነች፣ ከዋክብቱም ረገፉ፣ ንዑዳን ክቡራን ንጹሐን መላእክትም ትዕግስቱን እያደነቁ በጽኑዕ ሐዘንና መደነቅ ከቅዱስ ዕፀ መስቀሉ ፊት እንደሻሽ ተነጠፉ።
አስራ አንድ ሰዓት በሆነም ጊዜ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር ቅድስት ሥጋውን ከመስቀሉ አውርደው በክብር ገንዘው በአዲስ መቃብር ቀበሩት። በሦስተኛውም ቀን እንደተናገረ ተነሳ።
በዛሬዋ ቀን ቤተ ክርስቲያን የመድኃኔለምን የስቅለት በዓል በደማቁ ታከብራለች፤ ይህም የለውጥ በዓል ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ስጋውን የቆረሰው መጋቢት 27 ቀን ነው፤ ይህ በዓል ግን በዐቢይ ጾም ስለሚውል በዐቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለና በዓል ማክበር ስለማይፈቀድ፤ ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ሰርታልናለች፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይክፈለን
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ጥቅምት 27 በዚህች ዕለት የአምላካችን የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው።
መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለኹላችን ድኅነት ሲል ራሱን ወድዶ ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። በቅዱስ ወንጌልም እርሱም መድኃኒታችን " ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም" ብሎ ነግሮናል። እውነት ነው፣ ራስን ነፍስን ስለጠላት ነፍስ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ?
ቸሩ አምላካችንን የአስቆሮቱ ይሁዳ ሊያስይዘው የሊቃነ ካህናቱን አገልጋዮች እየመራ አመጣቸው። እነርሱንም ማንን ትፈልጋላችሁ ሲላቸው የናዝሬቱ ኢየሱስን አሉት፣ እኔ ነኝ ቢላቸው የቸሩን አምላክ ድምጽ ሰምቶ አይደለም መቆም በሕይወት መጽናት የሚቻለው የለምና ወደ ኋላቸው ተስፈንጥረው ወደቁ። ደጋግሞም እንዲህ ኾነ። በኋላ ግን እኔ ነኝ ብሎ በፈቃዱ ይሁዳ ስሞ አሳልፎ ሰጣቸው።
ከያዙት በኋላ እያዳፉና እየጎተቱ በሰንሰለት አስረው ወደ ቀያፋና ሐና ግቢ ወሰዱት፣ እስከ ሦስት ሰዓትም አላሳረፉትም ሲያሰቃዩት አድረዋል፣ በራሱም ላይ ሰባ ሦስት ስቊረት ያለው ወደ ሦስት መቶ እሾኾችን የያዘ የእሾህ አክሊል ጎንጉነው ቢያደርጉበት የራስ ቅሉን ቀዶ ገብቶ እስከ ልቡ ዘልቋል። እንደምን ጭንቅ ነው? እንዲህም አድርገው ደግሞ እያፌዙ ርኲስ ምራቃቸውን ይተፉበትና በዘንግም ደጋግመው ይመቱት ነበር። እየተፈራረቁ ያለ ምንም ርኅራኄ ቸሩን አምላክ ሥጋው እየተቆረጠ እስኪወድቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጽኑዕ ግርፋትን ገርፈውታል። የገረፉበትም ጅራፍ በላዩ ላይ ሥጋን እየጎመደ የሚጥል፣ ሕመሙ አንጀት ሰርሥሮ የሚገባ በስለት የተያያዘበት ነበር።
በኋላም አላሳረፉትም እንዲህ አድርገውትም በሊቶስጥራ አደባባይ ያንን ዕርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት። እርሱ ግን ይህን ኹሉ ግፍ ሲያደርሱበት አንድም አልተናገረም ነበር። በቀራንዮም በአምስት ጽኑዕ ቅንዋት (ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ እና ሮዳስ) ቸንክረው ዕርቃኑን ሰቀሉት።
በዚህች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተሰበረ መጽናናትንም አልፈለገች ነበር፤ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ እናቱንም እናት ትሆነው ዘንድ በእግረ መስቀሉ አደራን ተቀበለ። ቅዱሳት አንስት በፍጹም ሀዘንና በዋይታ ዋሉ። በስልጣኑም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። ሰባት ድንቅ የኾኑ ተአምራትንም አድርጎ አምላክ መኾኑን ገለጠ። ይህም ጽኑዕ የኾነ ለሰማይ ለምድር የከበደ ነገር ሲከሰት ፀሐይ አምላኬን ዕርቃኑ እንዴት አያለሁ ብላ ጨለመች። ጨረቃ ደም ኾነች፣ ከዋክብቱም ረገፉ፣ ንዑዳን ክቡራን ንጹሐን መላእክትም ትዕግስቱን እያደነቁ በጽኑዕ ሐዘንና መደነቅ ከቅዱስ ዕፀ መስቀሉ ፊት እንደሻሽ ተነጠፉ።
አስራ አንድ ሰዓት በሆነም ጊዜ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር ቅድስት ሥጋውን ከመስቀሉ አውርደው በክብር ገንዘው በአዲስ መቃብር ቀበሩት። በሦስተኛውም ቀን እንደተናገረ ተነሳ።
በዛሬዋ ቀን ቤተ ክርስቲያን የመድኃኔለምን የስቅለት በዓል በደማቁ ታከብራለች፤ ይህም የለውጥ በዓል ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ስጋውን የቆረሰው መጋቢት 27 ቀን ነው፤ ይህ በዓል ግን በዐቢይ ጾም ስለሚውል በዐቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለና በዓል ማክበር ስለማይፈቀድ፤ ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ሰርታልናለች፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ይክፈለን
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
++++++ጠባቧ_መንገድ++++++
"በተጨባጭ እውነታ ሰፊውንና ልቅ የኾነውን መንገድ ይዘን ሳለ ጠባቡንና የቀጠነውን መንገድ እየተከተልን እንደ ኾነ በማሰብ እንዳንታለል በራሳችን ላይ ቅርብ ትኲረት እናድርግ። ቀጥሎ የሰፈረው ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን እንደ ኾነ ያሳይሃል፦ ሆድን ማጎስቆል (ስስትን መግደል)፣ ትጋሃ ሌሊት (ሌሊቱን ሙሉ መቆም)፣ ጥቂት ውኃ መጠጣት፣ ቍራሽ ዳብ መብላት (ከፊለ ኅብስት)፣ በተዋርዶ ድርቅ መንጻት፣ መናቅ፣ ፌዝን መቀበል፣ መሰደብ፣ የገዛ ፈቃድን ቆርጦ መጣል፣ በሚያስቆጣ ነገር መታገሥ፣ ባለ ማጉረምረም ንቀትን መታገሥ፣ ስድቦችን ቸል ማለት፣ ያልተገባ ጠባይን ጸንቶ መታገሥ፤ ሲታሙ አለመቆጣት፣ ሲዋረዱ አለመቆጣት፣ ሲነቀፉ ትሑት መኾን ነው። የገለጽናቸውን ጎዳናዎች የሚከተሉ ብፁዓን ናቸው፣ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴ 5፡3-13።" እንዲል ዮሐንስ ዘሰዋስው። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 102)።
በዚህ አባት ጽሑፍ ውስጥ አንደኛ ራሳችንን መመርመር እንዳለብን ተገልጿል። ልቅ በኾነው ሰፊ መንገድ በተባለው የዓለማዊነት መንገድ ላይ መኾን አለመኾናችንን በትኩረት እንድናስተውል ምክረ ሐሳብ ቀርቧል። ኹል ጊዜም ቢኾን ትክክለኛ ወደ ኾነው መንገድ ለመግባት አስቀድሞ የቆምንበትን መንገድ እና በዚያ መንገድ እንድንጓዝ ያደረገንን ውስጣዊ ፍላጎት መረዳት ያስፈልጋል። ምን ያህልስ ጊዜ ልቅ በኾነው የኃጢአት መንገድ ተጉዘን ይኾን? ምን ያህልስ የዚያ መንገድ ጣዕም በውስጣችን ቀርቶ ይኾን? እንዴትስ ከዚያ መንገድ መውጣት እንችላለን። እያልን በእርጋታ ለራሳችን ጥያቄ እያቀረብን ራሳችንን እንመርምር።
ኹለተኛው መሠረታዊ ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ የተገለጸበት ነው። ጥቂት መመገብን ከመለማመድ ጀምሮ ማንኛውንም ክፉ የተባሉ ነገሮችን የሚያደርጉብንን መታገሥ ተገቢ መኾኑን ያስረዳል። መንገዱን ጠባብ ያሰኘውም፥ የተገለጹትን ነገሮች ለመተግበር እጅግ የሚከብዱ ስለ ኾነ ነው። ጽድቁንና መንግሥቱን እያሰብን የምንኖር ከኾነ ግን ከባድ ሊኾኑ አይችሉም። ጠባቡ መንገድ ጣዕመ መንግሥተ እግዚአብሔርን እያሰቡ ኃጢአትን መጥላትን ማዕከል ያደረገ ነውና። የሚንቁንን፣ የሚሰድቡንን፣ የሚያሙንን መታገሥ ለብዙዎቻችን አስቸጋሪ ነው። በእውነትም የሚጠሉንን ላለመጥላት እየታገልንን ኹሌ ራሳችንን ትዕግሥትን ብናለማምድ እግዚአብሔር ይረዳናል። ትዕግሥት በእኛ ጥረት ብቻ ሳይኾን ከእግዚአብሔርም ጸጋ ኾኖ የሚሰጥም ነገር ነውና። እኛ ከልባችን ክፉን በትዕግሥት ስንቀበል እግዚአብሔር ጽናቱን ይሰጠናል። የጠባቡ መንገድ መድረሻው መንግሥተ እግዚአብሔር መኾኑን በሕሊናችን ውስጥ አስቀምጠን፥ መንግሥቱን እያሰብን እንኑር። አንድ ሯጭ ትኲረቱን በሙሉ የሚያደርገው ቀድመውት ያሉ ተወዳዳሪዎች ላይ እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ትኲረታችንን ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር አቅጣጫ ካደረግን በእኛ ላይ የሚደረጉ ክፉ ነገሮችን ኹሉ ሳናያቸው ማለፍ እንችላለን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"በተጨባጭ እውነታ ሰፊውንና ልቅ የኾነውን መንገድ ይዘን ሳለ ጠባቡንና የቀጠነውን መንገድ እየተከተልን እንደ ኾነ በማሰብ እንዳንታለል በራሳችን ላይ ቅርብ ትኲረት እናድርግ። ቀጥሎ የሰፈረው ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን እንደ ኾነ ያሳይሃል፦ ሆድን ማጎስቆል (ስስትን መግደል)፣ ትጋሃ ሌሊት (ሌሊቱን ሙሉ መቆም)፣ ጥቂት ውኃ መጠጣት፣ ቍራሽ ዳብ መብላት (ከፊለ ኅብስት)፣ በተዋርዶ ድርቅ መንጻት፣ መናቅ፣ ፌዝን መቀበል፣ መሰደብ፣ የገዛ ፈቃድን ቆርጦ መጣል፣ በሚያስቆጣ ነገር መታገሥ፣ ባለ ማጉረምረም ንቀትን መታገሥ፣ ስድቦችን ቸል ማለት፣ ያልተገባ ጠባይን ጸንቶ መታገሥ፤ ሲታሙ አለመቆጣት፣ ሲዋረዱ አለመቆጣት፣ ሲነቀፉ ትሑት መኾን ነው። የገለጽናቸውን ጎዳናዎች የሚከተሉ ብፁዓን ናቸው፣ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴ 5፡3-13።" እንዲል ዮሐንስ ዘሰዋስው። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 102)።
በዚህ አባት ጽሑፍ ውስጥ አንደኛ ራሳችንን መመርመር እንዳለብን ተገልጿል። ልቅ በኾነው ሰፊ መንገድ በተባለው የዓለማዊነት መንገድ ላይ መኾን አለመኾናችንን በትኩረት እንድናስተውል ምክረ ሐሳብ ቀርቧል። ኹል ጊዜም ቢኾን ትክክለኛ ወደ ኾነው መንገድ ለመግባት አስቀድሞ የቆምንበትን መንገድ እና በዚያ መንገድ እንድንጓዝ ያደረገንን ውስጣዊ ፍላጎት መረዳት ያስፈልጋል። ምን ያህልስ ጊዜ ልቅ በኾነው የኃጢአት መንገድ ተጉዘን ይኾን? ምን ያህልስ የዚያ መንገድ ጣዕም በውስጣችን ቀርቶ ይኾን? እንዴትስ ከዚያ መንገድ መውጣት እንችላለን። እያልን በእርጋታ ለራሳችን ጥያቄ እያቀረብን ራሳችንን እንመርምር።
ኹለተኛው መሠረታዊ ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ የተገለጸበት ነው። ጥቂት መመገብን ከመለማመድ ጀምሮ ማንኛውንም ክፉ የተባሉ ነገሮችን የሚያደርጉብንን መታገሥ ተገቢ መኾኑን ያስረዳል። መንገዱን ጠባብ ያሰኘውም፥ የተገለጹትን ነገሮች ለመተግበር እጅግ የሚከብዱ ስለ ኾነ ነው። ጽድቁንና መንግሥቱን እያሰብን የምንኖር ከኾነ ግን ከባድ ሊኾኑ አይችሉም። ጠባቡ መንገድ ጣዕመ መንግሥተ እግዚአብሔርን እያሰቡ ኃጢአትን መጥላትን ማዕከል ያደረገ ነውና። የሚንቁንን፣ የሚሰድቡንን፣ የሚያሙንን መታገሥ ለብዙዎቻችን አስቸጋሪ ነው። በእውነትም የሚጠሉንን ላለመጥላት እየታገልንን ኹሌ ራሳችንን ትዕግሥትን ብናለማምድ እግዚአብሔር ይረዳናል። ትዕግሥት በእኛ ጥረት ብቻ ሳይኾን ከእግዚአብሔርም ጸጋ ኾኖ የሚሰጥም ነገር ነውና። እኛ ከልባችን ክፉን በትዕግሥት ስንቀበል እግዚአብሔር ጽናቱን ይሰጠናል። የጠባቡ መንገድ መድረሻው መንግሥተ እግዚአብሔር መኾኑን በሕሊናችን ውስጥ አስቀምጠን፥ መንግሥቱን እያሰብን እንኑር። አንድ ሯጭ ትኲረቱን በሙሉ የሚያደርገው ቀድመውት ያሉ ተወዳዳሪዎች ላይ እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ትኲረታችንን ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር አቅጣጫ ካደረግን በእኛ ላይ የሚደረጉ ክፉ ነገሮችን ኹሉ ሳናያቸው ማለፍ እንችላለን።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#አሥርቱ_ትዕዛዛት
ወዳጆቼ እስቲ ዛሬ ከአሥርቱ ትዕዛዛት ውስጥ የሚገርመኝን አንድ እውነታ ልንገራችሁ። አስተውላችሁ ከሆነ ሁሉም ትዕዛዛት የተነገሩት በነጠላ (ለአንድ ሰው) ብቻ ነው። 'አድርግ ወይም አታድርግ!" ተብለው።
ሙሴ ከተራራው ላይ አሥርቱን ትዕዛዛት ይዞ የወረደው በመቶ ሺ ለሚቆጠሩት እስራኤላውያን ቢሆንም ትእዛዙ ግን እንደብዛታቸው አታምልኩ ፣ አትስረቁ ፣ በሐሰት አትማሉ እያለ የሚናገር አልነበረም፡፡ አሥሩም አድርግና አታድርግ በሚሉ በነጠላ ትዕዛዝና ሕግ የተሞሉ ናቸው፡፡
ስለዚህ ልክ መስረቅ ሲያምርህ 'ሀገሩ ሁሉ እየሰረቀ ነው እኔ ብቻዬን ምን ለውጥ አመጣለሁ? ጊዜው የሌብነት ነው!' ብለህ አትጽናና እግዚአብሔር 'አትስረቅ' እንጂ አትስረቁ አላለም፡፡ ሀገሩ ሁሉ ይስረቅ አንተ ግን 'አትስረቅ' ተብለህ የታዘዝከው ለብቻህ ነው ፤ የሚጠይቅህም ለብቻህ ነው፡፡ ማመንዘር በእኔ አልተጀመረ የማያመነዝር ማን አለ? ብለህ ለኃጢአትህ መጽናኛዎችን አታፈላልግ፡፡ 'አታመንዝር' ያለው ለአንተ ለብቻህ ነው፡፡ በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር ያለውም ላንተ ነው፡፡ 'የሥራዬ ጸባይ ነው ሥራዬ መዋሸት ይጠይቃል' ብለህ ሐሰትህን የኑሮ መግፊያ ስልት አታድርገው ብዙዎች በሐሰት ቢመሰክሩም አንተ ግን አትመስክር፡፡ ሁሉም መስክሮ እኔ ብቀር ምን ለውጥ ያመጣል? ብለህ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ 'ብዙ ናቸው ብለህ ከክፉዎች ጋር አትተባበር' ፈጣሪህ ያዘዘህ ለብቻህ ነው ምክንያቱም የጋራ ኩነኔና የጋራ ጽድቅ የለም፡፡
ጌታችን እንዲህ ይላል ፦ 'እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ' /ራእ. 22÷12/
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ወዳጆቼ እስቲ ዛሬ ከአሥርቱ ትዕዛዛት ውስጥ የሚገርመኝን አንድ እውነታ ልንገራችሁ። አስተውላችሁ ከሆነ ሁሉም ትዕዛዛት የተነገሩት በነጠላ (ለአንድ ሰው) ብቻ ነው። 'አድርግ ወይም አታድርግ!" ተብለው።
ሙሴ ከተራራው ላይ አሥርቱን ትዕዛዛት ይዞ የወረደው በመቶ ሺ ለሚቆጠሩት እስራኤላውያን ቢሆንም ትእዛዙ ግን እንደብዛታቸው አታምልኩ ፣ አትስረቁ ፣ በሐሰት አትማሉ እያለ የሚናገር አልነበረም፡፡ አሥሩም አድርግና አታድርግ በሚሉ በነጠላ ትዕዛዝና ሕግ የተሞሉ ናቸው፡፡
ስለዚህ ልክ መስረቅ ሲያምርህ 'ሀገሩ ሁሉ እየሰረቀ ነው እኔ ብቻዬን ምን ለውጥ አመጣለሁ? ጊዜው የሌብነት ነው!' ብለህ አትጽናና እግዚአብሔር 'አትስረቅ' እንጂ አትስረቁ አላለም፡፡ ሀገሩ ሁሉ ይስረቅ አንተ ግን 'አትስረቅ' ተብለህ የታዘዝከው ለብቻህ ነው ፤ የሚጠይቅህም ለብቻህ ነው፡፡ ማመንዘር በእኔ አልተጀመረ የማያመነዝር ማን አለ? ብለህ ለኃጢአትህ መጽናኛዎችን አታፈላልግ፡፡ 'አታመንዝር' ያለው ለአንተ ለብቻህ ነው፡፡ በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር ያለውም ላንተ ነው፡፡ 'የሥራዬ ጸባይ ነው ሥራዬ መዋሸት ይጠይቃል' ብለህ ሐሰትህን የኑሮ መግፊያ ስልት አታድርገው ብዙዎች በሐሰት ቢመሰክሩም አንተ ግን አትመስክር፡፡ ሁሉም መስክሮ እኔ ብቀር ምን ለውጥ ያመጣል? ብለህ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ 'ብዙ ናቸው ብለህ ከክፉዎች ጋር አትተባበር' ፈጣሪህ ያዘዘህ ለብቻህ ነው ምክንያቱም የጋራ ኩነኔና የጋራ ጽድቅ የለም፡፡
ጌታችን እንዲህ ይላል ፦ 'እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ' /ራእ. 22÷12/
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
አህያና ግርዛት
አሁን ሐዲስ ኪዳን ነው:: መገረዝ ግዴታ አይደለም:: ዋናው ጥምቀት ነው:: ባንገረዝ ምንም አይጎድልብንም:: በዚህ ጉዳይ በመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ውዝግብ ተነሣ:: አሕዛብ ሳይገረዙ ኖረዋልና ጸረ ግዝረት ሆኑ:: አይሁድ ደግሞ እንዴት ግዝረት እንተዋለን አሉ::
ወደ ክርስትና የተጠሩት እነዚህ ሁለት ወገኖች ሁለቱም ከራሳቸው አመጣጥ አንጻር እውነት አላቸው:: አሕዛብ የማያውቁትን ነገር መቀበል ሊገደዱ አይችሉም:: ክርስትናም አላስገደዳቸውም:: አይሁድ ደግሞ የኖሩበትን መተው አይችሉም:: ክርስትናም ግዝረትን ባይጠይቅም አልከለከለም::
በመጨረሻ በብዙ ምክር የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አሕዛብንም ያላገለለ እስራኤልንም ያላቃለለ ውሳኔ ወሰነች:: ውሳኔውን በጥሩ ቃል በመልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ሲል ገልጾታል::
"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ። ... እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት እንደዚሁ ይኑር" 1 ቆሮንቶስ 7:18፣ 20
በዚህ መሠረት ኦሪትን ተቀብለው ተገርዘው ወደ ክርስትና የተጠሩት እስራኤል በመገረዛቸው ይቀጥሉ እንጂ ወደ አለመገረዝ አይመለሱ ተባለላቸው:: ሳይገረዙ የተጠሩት አሕዛብ ግን መገረዝ የእነርሱ ልማድ አልነበረምና አይገረዙ ተባለ:: ይህ ለእስራኤል የተወሰነ ውሳኔም እንደ ኢትዮጵያ ኦሪትን ተቀብላ ለኖረችና ተገርዛ ሳለ የተጠራች (ሐውልቶችዋ ሳይቀር የተገረዘ ወንድን የሚያሳዩባት) ሀገርም ላይ ይጸናል::
ይህ ውሳኔ ለሁሉም እንደ ግዝረት ያሉ ሕግጋት ይሠራል::
"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ"
"ማንም አህያ እየበላ ተጠርቶ እንደ ሆነ አህያ ወዳለመብላት አይመለስ ፤ ማንም አህያ ሳይበላ ተጠርቶ እንደሆነም አህያ አይብላ"
(የአህያን ስም በአሳማ በአይጥ በውሻ ወዘተ እየቀየሩ ዐረፍተ ነገር ይሥሩ:: ሃሳቡ ያው ነው) ግዝረትም የማይበሉ ምግቦችም ከ613 የአይሁድ ሕግጋት (The 613 Mitzvot) ውስጥ ናቸው::
እስራኤል በግዝረት ቀጥሉ ሲባሉ ደስ አላቸው አሕዛብም አትገረዙ ሲባል ደስ አላቸው:: ለእስራኤል ሔደህ የአሕዛብን ዜና ብትነግራቸው ምንም እንኩዋን ግዝረት ግድ ባይሆንም ቅር ይላቸዋል:: የአህያ መበላት ዜናም የሚያስደስተው አህያን እንዴት ልንተው እንችላለን ብለው ለተጨነቁ አሕዛብ ብቻ እንጂ ለእኛ ሆድ የሚበጠብጥ ዜና ነው::
ከዚያ ውጪ እንደ ክርስቲያን ብሉ ብለን ልንሰብከው የሚገባን የሕይወት እንጀራ ሥጋ ወደሙ ብቻ ነው::
እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት ይኑር!
"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" ኤፌሶን 4:29
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
አሁን ሐዲስ ኪዳን ነው:: መገረዝ ግዴታ አይደለም:: ዋናው ጥምቀት ነው:: ባንገረዝ ምንም አይጎድልብንም:: በዚህ ጉዳይ በመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ውዝግብ ተነሣ:: አሕዛብ ሳይገረዙ ኖረዋልና ጸረ ግዝረት ሆኑ:: አይሁድ ደግሞ እንዴት ግዝረት እንተዋለን አሉ::
ወደ ክርስትና የተጠሩት እነዚህ ሁለት ወገኖች ሁለቱም ከራሳቸው አመጣጥ አንጻር እውነት አላቸው:: አሕዛብ የማያውቁትን ነገር መቀበል ሊገደዱ አይችሉም:: ክርስትናም አላስገደዳቸውም:: አይሁድ ደግሞ የኖሩበትን መተው አይችሉም:: ክርስትናም ግዝረትን ባይጠይቅም አልከለከለም::
በመጨረሻ በብዙ ምክር የሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን አሕዛብንም ያላገለለ እስራኤልንም ያላቃለለ ውሳኔ ወሰነች:: ውሳኔውን በጥሩ ቃል በመልእክቱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ሲል ገልጾታል::
"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ። ... እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት እንደዚሁ ይኑር" 1 ቆሮንቶስ 7:18፣ 20
በዚህ መሠረት ኦሪትን ተቀብለው ተገርዘው ወደ ክርስትና የተጠሩት እስራኤል በመገረዛቸው ይቀጥሉ እንጂ ወደ አለመገረዝ አይመለሱ ተባለላቸው:: ሳይገረዙ የተጠሩት አሕዛብ ግን መገረዝ የእነርሱ ልማድ አልነበረምና አይገረዙ ተባለ:: ይህ ለእስራኤል የተወሰነ ውሳኔም እንደ ኢትዮጵያ ኦሪትን ተቀብላ ለኖረችና ተገርዛ ሳለ የተጠራች (ሐውልቶችዋ ሳይቀር የተገረዘ ወንድን የሚያሳዩባት) ሀገርም ላይ ይጸናል::
ይህ ውሳኔ ለሁሉም እንደ ግዝረት ያሉ ሕግጋት ይሠራል::
"ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ"
"ማንም አህያ እየበላ ተጠርቶ እንደ ሆነ አህያ ወዳለመብላት አይመለስ ፤ ማንም አህያ ሳይበላ ተጠርቶ እንደሆነም አህያ አይብላ"
(የአህያን ስም በአሳማ በአይጥ በውሻ ወዘተ እየቀየሩ ዐረፍተ ነገር ይሥሩ:: ሃሳቡ ያው ነው) ግዝረትም የማይበሉ ምግቦችም ከ613 የአይሁድ ሕግጋት (The 613 Mitzvot) ውስጥ ናቸው::
እስራኤል በግዝረት ቀጥሉ ሲባሉ ደስ አላቸው አሕዛብም አትገረዙ ሲባል ደስ አላቸው:: ለእስራኤል ሔደህ የአሕዛብን ዜና ብትነግራቸው ምንም እንኩዋን ግዝረት ግድ ባይሆንም ቅር ይላቸዋል:: የአህያ መበላት ዜናም የሚያስደስተው አህያን እንዴት ልንተው እንችላለን ብለው ለተጨነቁ አሕዛብ ብቻ እንጂ ለእኛ ሆድ የሚበጠብጥ ዜና ነው::
ከዚያ ውጪ እንደ ክርስቲያን ብሉ ብለን ልንሰብከው የሚገባን የሕይወት እንጀራ ሥጋ ወደሙ ብቻ ነው::
እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት ይኑር!
"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" ኤፌሶን 4:29
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ልጆቼ! በድህነቴ ላይ ቸርነትን አድርጉልኝ፡፡ በዚህስ አልችልም ካላችሁ እሺ በቁስሌ ላይ ዘይትን አፍስሱልኝ፡፡ አሁንም ይህን ማድረግ ካልቻላችሁ ወደ እኔ ጠጋ በሉና አናግሩኝ፡፡ እናንተን ማየት፣ ከእናንተ ጋር መጨዋወት ይናፍቀኛልና፡፡
በገዛ ደሜ የገዛኋችሁ ልጆቼ! ከባድ ነገር እኮ አልለመንኳችሁም፡፡ እኔ የምፈልገው ትንሽ ዳቦ፣ ጊዜአዊ ማደርያ፣ እንዲሁም የሚያጽናኑ ቃላትን ብቻ ነው፡፡ “ይህ ሁሉ ማድረጌ ምን ይጠቅመኛል?” ካላችሁ ስለ ምሰጣችሁን ርስት መንግሥተ ሰማያት ብላችሁ አድርጉት፡፡ አሁንም ልባችሁ አልተነካምን? ስለ መንግሥተ ሰማያት አታድርጉት፤ ግን ደግሞ ስለ ሰብአዊ ርኅራኄ ይህን አድርጉልኝ፡፡ የእኔን መራቆት የሚያሳዝናችሁ በቀራንዮ አደባባይ ስለ እናንተ ብዬ የተራቆትኩት ብቻ ነውን? ታድያ አሁንም ‘ኮ በደጃችሁ ላይ ተጥዬ ዕራቆቴን ነኝ፡፡ ለምን አላዘናችሁልኝም? የታሰርኩት በቀራንዮ ብቻ ነውን? አይደለም፡፡ ታድያ እንደምን አታዝኑልኝም?
የማፈቅራችሁ ልጆቼ! በመስቀል ላይ ተሰቅዬ ሳለሁ “ተጠማሁ” እንዳልኩ ዛሬስ ስለ እናንተ ብዬ ደጋግሜ ይህን ቃል አልተናገርኩምን? ጕሮሮዬ ደርቆ ስለምን ትንሽ እንኳ አላሳዝናችሁም? ስለምንስ ይህ ሁሉ ፍቅር ስለ እናንተ መሆኑን ትዘነጉብኛላችሁ? የምለምናችሁ እናንተን ባለጸጋ ለማድረግ አይደለምን? ይህችን ትንሽ ቸርነት ስላደረጋችሁልኝ በዐይን ያልታየች፣ በጀሮ ያልተሰማች፣ በሰውም አእምሮ ያልታሰበች ርስት መንግሥተ ሰማያት እንድታገኙ ብዬ አይደለምን? ስለ እናንተ ብዬ ደሀ የሆንኩት ያኔ በመዋዕለ ሥጋዌዬ ብቻ እንደሆነ አታስቡ ልጆቼ! ዛሬም ቢሆን በደጃችሁ የተጣልኩት ስለ እናንተ ጥቅም እንደሆነ ተረዱልኝ፡፡
ከባድ ነገር ‘ኮ አልለመንኳችሁም፡፡ እስር ቤት መጥታችሁ ጠይቁኝ እንጂ አስፈቱኝ አላልኳችሁም፡፡ ታምሜ ጠይቁኝ እንጂ ፈውሱኝ አላልኳችሁም፡፡ ከጠየቃችሁኝ ብቻ በቂዬ ነው፡፡ እስኪ ልጠይቃችሁና እናንተም መልሱልኝ! በዚያ በአስፈሪው ቀን ስመጣ “ኑ እናንተ የአባቴ ብሩካን” የሚለውን ቃለ ሕይወት መስማት አትፈልጉምን? ዛሬ የሰጣችሁኝ ሁሉ የምረሳ ይመስላችኋልን? ያኔ በክብር ስመጣ ከእልፍ ወለዱ ጋር እንድሰጣችሁ አትሹምን? የማፈቅራችሁ ልጆቼ! ከደጃችሁ ተጥዬ የምለምናችሁ፣ ከበራችሁ ላይ ቆሜ ማደርያን የምጠይቃችሁ፣ እጄን ዘርግቼ እናንተን እናንተን የማየው ያኔ ትሉ ወደማይጠፋው እሳቱ ወደማያንቀላፋው እሳት እንዳትሄዱብኝ ብዬ ነው፡፡ ታድያ ይህን ለምን አትረዱልኝ ልጆቼ? ስለምን እንዳስቸገርኳችሁ ታስባላችሁ? ለእናንተ ጥቅም እንደሆነ እንዳትረዱ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው? ከእናንተ ጋር ቁጭ ብዬ ልብላ ስላችሁ ስለምን ትገፈትሩኛለችሁ? ይህን ያህል ቸርነት አድርጌላችሁ ሳለሁስ ስለምን በግልምጫ አያችሁኝ? ይህን ያህል መውደድ ወድጃችሁ ሳለሁ ስለምን በቅጡ ልታነጋገግሩኝ አልወደዳችሁም? ከአዳም ጀምሮ ዓለም እስኪያልፍ ድረስ ያለው ሕዝብ ሁሉ በአንድ አደባባይ ላይ ቆሞ፣ እልፍ አእላፍ መላእክት በዙርያዬ ረበው “ይህ/ ይህቺ ልጅ ወዳጄ ነው/ ናት፤ በመሆኑም በታላቅ ክብርና ዕልልታ አጅባችሁ ወደ ዘለዓለም ደስታዋ አግቡት/ አግቧት” የሚለውን ፍርዴ አትናፍቁምን?
ልጆቼ! እኔን ላለማየት ስለምን ፊታችሁን ትሸፍናላችሁ? ስለምን፡ታፍራላችሁ? እኔ ሳላፍርባችሁ ስለምን እናንተ አፈራችሁ?
ልጆቼ! ልባችሁ እንደተነካ አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ስሜት ብቻ አይሁን፡፡ ከንፈራችሁን ብቻ አትምጠጡብኝ፡፡ ከእናንተ የምፈልገው አንዲት ነገር ብቻ ነው፡፡ ከላይ የጠየቅኳችሁን ነገሮች ወደ ተግባር ቀይሯቸው፡፡ ለማይጠቅማችሁ ነገር አብዝታችሁ እየሮጣችሁ ለሚጠቅማችሁ ነገር አትስነፉ፡፡ “እኔኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ ይህን እንደምን እችላለሁ?” አትበሉኝ፡፡ አውቃለሁ! ነገር ግን ፈቃዳችሁን ብቻ ስጡኝ እንጂ እኔ ራሴ አደርግላችኋለሁ፡፡ “ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም” ብዬ.ያስተማርኳችሁን ቃል ረሳችሁትን? /ዮሐ.15፡5/፡፡ እንግዲያውስ ከእናንተ የምፈልገው ፈቃዳችሁን ነው፡፡ አሁን ካላችሁበት ቦታ ተንቀሳቅሳችሁ ወጣ ስትሉ ታገኙኛላችሁ፡፡ አናግሩኝ! አፍቃሪያችሁ መድኃኔዓለም ነኝ፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በገዛ ደሜ የገዛኋችሁ ልጆቼ! ከባድ ነገር እኮ አልለመንኳችሁም፡፡ እኔ የምፈልገው ትንሽ ዳቦ፣ ጊዜአዊ ማደርያ፣ እንዲሁም የሚያጽናኑ ቃላትን ብቻ ነው፡፡ “ይህ ሁሉ ማድረጌ ምን ይጠቅመኛል?” ካላችሁ ስለ ምሰጣችሁን ርስት መንግሥተ ሰማያት ብላችሁ አድርጉት፡፡ አሁንም ልባችሁ አልተነካምን? ስለ መንግሥተ ሰማያት አታድርጉት፤ ግን ደግሞ ስለ ሰብአዊ ርኅራኄ ይህን አድርጉልኝ፡፡ የእኔን መራቆት የሚያሳዝናችሁ በቀራንዮ አደባባይ ስለ እናንተ ብዬ የተራቆትኩት ብቻ ነውን? ታድያ አሁንም ‘ኮ በደጃችሁ ላይ ተጥዬ ዕራቆቴን ነኝ፡፡ ለምን አላዘናችሁልኝም? የታሰርኩት በቀራንዮ ብቻ ነውን? አይደለም፡፡ ታድያ እንደምን አታዝኑልኝም?
የማፈቅራችሁ ልጆቼ! በመስቀል ላይ ተሰቅዬ ሳለሁ “ተጠማሁ” እንዳልኩ ዛሬስ ስለ እናንተ ብዬ ደጋግሜ ይህን ቃል አልተናገርኩምን? ጕሮሮዬ ደርቆ ስለምን ትንሽ እንኳ አላሳዝናችሁም? ስለምንስ ይህ ሁሉ ፍቅር ስለ እናንተ መሆኑን ትዘነጉብኛላችሁ? የምለምናችሁ እናንተን ባለጸጋ ለማድረግ አይደለምን? ይህችን ትንሽ ቸርነት ስላደረጋችሁልኝ በዐይን ያልታየች፣ በጀሮ ያልተሰማች፣ በሰውም አእምሮ ያልታሰበች ርስት መንግሥተ ሰማያት እንድታገኙ ብዬ አይደለምን? ስለ እናንተ ብዬ ደሀ የሆንኩት ያኔ በመዋዕለ ሥጋዌዬ ብቻ እንደሆነ አታስቡ ልጆቼ! ዛሬም ቢሆን በደጃችሁ የተጣልኩት ስለ እናንተ ጥቅም እንደሆነ ተረዱልኝ፡፡
ከባድ ነገር ‘ኮ አልለመንኳችሁም፡፡ እስር ቤት መጥታችሁ ጠይቁኝ እንጂ አስፈቱኝ አላልኳችሁም፡፡ ታምሜ ጠይቁኝ እንጂ ፈውሱኝ አላልኳችሁም፡፡ ከጠየቃችሁኝ ብቻ በቂዬ ነው፡፡ እስኪ ልጠይቃችሁና እናንተም መልሱልኝ! በዚያ በአስፈሪው ቀን ስመጣ “ኑ እናንተ የአባቴ ብሩካን” የሚለውን ቃለ ሕይወት መስማት አትፈልጉምን? ዛሬ የሰጣችሁኝ ሁሉ የምረሳ ይመስላችኋልን? ያኔ በክብር ስመጣ ከእልፍ ወለዱ ጋር እንድሰጣችሁ አትሹምን? የማፈቅራችሁ ልጆቼ! ከደጃችሁ ተጥዬ የምለምናችሁ፣ ከበራችሁ ላይ ቆሜ ማደርያን የምጠይቃችሁ፣ እጄን ዘርግቼ እናንተን እናንተን የማየው ያኔ ትሉ ወደማይጠፋው እሳቱ ወደማያንቀላፋው እሳት እንዳትሄዱብኝ ብዬ ነው፡፡ ታድያ ይህን ለምን አትረዱልኝ ልጆቼ? ስለምን እንዳስቸገርኳችሁ ታስባላችሁ? ለእናንተ ጥቅም እንደሆነ እንዳትረዱ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው? ከእናንተ ጋር ቁጭ ብዬ ልብላ ስላችሁ ስለምን ትገፈትሩኛለችሁ? ይህን ያህል ቸርነት አድርጌላችሁ ሳለሁስ ስለምን በግልምጫ አያችሁኝ? ይህን ያህል መውደድ ወድጃችሁ ሳለሁ ስለምን በቅጡ ልታነጋገግሩኝ አልወደዳችሁም? ከአዳም ጀምሮ ዓለም እስኪያልፍ ድረስ ያለው ሕዝብ ሁሉ በአንድ አደባባይ ላይ ቆሞ፣ እልፍ አእላፍ መላእክት በዙርያዬ ረበው “ይህ/ ይህቺ ልጅ ወዳጄ ነው/ ናት፤ በመሆኑም በታላቅ ክብርና ዕልልታ አጅባችሁ ወደ ዘለዓለም ደስታዋ አግቡት/ አግቧት” የሚለውን ፍርዴ አትናፍቁምን?
ልጆቼ! እኔን ላለማየት ስለምን ፊታችሁን ትሸፍናላችሁ? ስለምን፡ታፍራላችሁ? እኔ ሳላፍርባችሁ ስለምን እናንተ አፈራችሁ?
ልጆቼ! ልባችሁ እንደተነካ አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ስሜት ብቻ አይሁን፡፡ ከንፈራችሁን ብቻ አትምጠጡብኝ፡፡ ከእናንተ የምፈልገው አንዲት ነገር ብቻ ነው፡፡ ከላይ የጠየቅኳችሁን ነገሮች ወደ ተግባር ቀይሯቸው፡፡ ለማይጠቅማችሁ ነገር አብዝታችሁ እየሮጣችሁ ለሚጠቅማችሁ ነገር አትስነፉ፡፡ “እኔኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ ይህን እንደምን እችላለሁ?” አትበሉኝ፡፡ አውቃለሁ! ነገር ግን ፈቃዳችሁን ብቻ ስጡኝ እንጂ እኔ ራሴ አደርግላችኋለሁ፡፡ “ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም” ብዬ.ያስተማርኳችሁን ቃል ረሳችሁትን? /ዮሐ.15፡5/፡፡ እንግዲያውስ ከእናንተ የምፈልገው ፈቃዳችሁን ነው፡፡ አሁን ካላችሁበት ቦታ ተንቀሳቅሳችሁ ወጣ ስትሉ ታገኙኛላችሁ፡፡ አናግሩኝ! አፍቃሪያችሁ መድኃኔዓለም ነኝ፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#ዋናው_እኔ_ነኝ
ብዙ የበደሉህ ዋኖች ይኖራሉ እንደ እኔ ግን አልበደለሁም፣ አንተን ያስከፉህ ቢሰለፉ ከፊት የምገኘው እኔ ነኝ፣ በኃጢአት ባህር መዋኘት ድሎት የሆናቸው ብዙ አሉ ዋናው ግን እኔ ነኝ፣ ልክ ባልሆነው ጎዳና የሚራመዱ አሉ መሪያቸው ግን እኔ ነኝ፣ አንተን በመቅረብ ፈንታ ጀርባ የሰጡህ አሉ እኔ ግን እብሳለሁ፣ ጌታዬ መድሃኒቴ ኢየሱስ አንተን የምትል ነፍሴ በስጋ ድካም ውስጥ ሳለ አለሁሽ ያልካት አንተ ነህ።
እኔ መማርህ እንዴት ያለ ምህረት ነው። የምህረትህ ድልድልነት ለእያንዳንዱ መንገዴ መሸጋገሪያ ሆኖኛል። እኔን ለማዳን ወደዚች አለም የመጣ አስታዋሼ አንተ ነህ። ከነ ኃጢያቴ እንዳልጠፋ እኔ ባለሁበት ተገኝተህ ያገኘኸን ፈላጊዬ ነህ፣ በሞት ጥላ ውስጥ ያለሁትን በደምህ ድምጽ የጠራኸኝ ባለውለታዬ አንተ ነህ፣ በምድረበዳው ብቻዬን ስባዝን ና ወደ እኔ ያልከኝ አስጠጊዬ አንተ ነህ።
እኔ ብቻ እንኳን በኃጢያት የጠፋው ብሆን የራስህ ጉዳይ ብለህ ከነበደሌ የማትተወኝ ለእኔ ብቻ እንኳን ብለህ ልትሞትልኝ የምትመጣ አፍቃሪዬ ነህ። ለእኔ ስትል ሰው የሆንክ አምላኬ ክርስቶስ ሆይ ክበር ተመስገን። እኔን ዋናውን ለማዳን ስትል ከሰው ተርታ ተገኝተህ በሰው ልክ የተመላለስክ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ተመስገን።
ወደ ክብሬ ልትመልሰኝ ክብርህን እንደመቀመት ሳትቆጥር ከላይ ከሰማያት የመጣህልኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ። እኔን ከማርከኝማ እኔን ይቅር ካልከኝማ ማንም ትምራለህ። እኔን ዋናውን ከተቀበልክማ መዳፍህ ሰፊ ነው ሁሉን ይቀበላል።
ለእኔ ስለሆነው በጎነትህ ክብር ይሁንልህ። አሜን
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤” 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
ብዙ የበደሉህ ዋኖች ይኖራሉ እንደ እኔ ግን አልበደለሁም፣ አንተን ያስከፉህ ቢሰለፉ ከፊት የምገኘው እኔ ነኝ፣ በኃጢአት ባህር መዋኘት ድሎት የሆናቸው ብዙ አሉ ዋናው ግን እኔ ነኝ፣ ልክ ባልሆነው ጎዳና የሚራመዱ አሉ መሪያቸው ግን እኔ ነኝ፣ አንተን በመቅረብ ፈንታ ጀርባ የሰጡህ አሉ እኔ ግን እብሳለሁ፣ ጌታዬ መድሃኒቴ ኢየሱስ አንተን የምትል ነፍሴ በስጋ ድካም ውስጥ ሳለ አለሁሽ ያልካት አንተ ነህ።
እኔ መማርህ እንዴት ያለ ምህረት ነው። የምህረትህ ድልድልነት ለእያንዳንዱ መንገዴ መሸጋገሪያ ሆኖኛል። እኔን ለማዳን ወደዚች አለም የመጣ አስታዋሼ አንተ ነህ። ከነ ኃጢያቴ እንዳልጠፋ እኔ ባለሁበት ተገኝተህ ያገኘኸን ፈላጊዬ ነህ፣ በሞት ጥላ ውስጥ ያለሁትን በደምህ ድምጽ የጠራኸኝ ባለውለታዬ አንተ ነህ፣ በምድረበዳው ብቻዬን ስባዝን ና ወደ እኔ ያልከኝ አስጠጊዬ አንተ ነህ።
እኔ ብቻ እንኳን በኃጢያት የጠፋው ብሆን የራስህ ጉዳይ ብለህ ከነበደሌ የማትተወኝ ለእኔ ብቻ እንኳን ብለህ ልትሞትልኝ የምትመጣ አፍቃሪዬ ነህ። ለእኔ ስትል ሰው የሆንክ አምላኬ ክርስቶስ ሆይ ክበር ተመስገን። እኔን ዋናውን ለማዳን ስትል ከሰው ተርታ ተገኝተህ በሰው ልክ የተመላለስክ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ተመስገን።
ወደ ክብሬ ልትመልሰኝ ክብርህን እንደመቀመት ሳትቆጥር ከላይ ከሰማያት የመጣህልኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ። እኔን ከማርከኝማ እኔን ይቅር ካልከኝማ ማንም ትምራለህ። እኔን ዋናውን ከተቀበልክማ መዳፍህ ሰፊ ነው ሁሉን ይቀበላል።
ለእኔ ስለሆነው በጎነትህ ክብር ይሁንልህ። አሜን
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤” 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
#መጽሐፍ_ቅዱስ
በአንድ ተራራማ ስፍራ እርሻ በማረስ ከልጅ ልጁ ጋር የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበር፡፡ ይህ ሽማግሌ ዘወትር ፀሐይ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ያነባል፡፡ የልጅ ልጁ የአያቱን ተግባር ይከታተል ስለነበር እሱም ያያቱን ፈለግ በመከተል ጠዋት ጠዋት እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱን ማንበብ ጀመረ፡፡
አንደ ቀን ታድያ አያቱን “አባባ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ልረዳው አልቻልኩም ደግሞም አንብቤ እንደጨረስኩ ወዲያውኑ እረሳዋለሁ እናም እንድረዳውና እንዳልረሳው ምን ማደረግ አለብኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡
ሽማግሌው ምንም ድምጽ ሳያሰሙ “ከሰሉን ወደ ምድጃው ጨመሩና እንካ ይሄን የከሰል ቅርጫት ይዘህ ወንዝ ውረድና ውሃ ይዘህልኝ ተመለስ” አሉት፡፡ ልጁ ትዛዙን ለመፈጸም ወደወንዝ ወርዶ ውሃውን ይዞ ሊመለስ ቢመክርም ቅርጫቱ ውሃውን እያንጠባጠበ ቤት ከመድረሱ በፊት ፈሶ አለቀበት፡፡ ሽማግሌው የልጁን ሁኔታ እያስተዋሉ “አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይዘህ ስትመጣ ግን ፈጠን ፈጠን ብለህ ተመለስ ብለው” ድጋሜ ላኩት፡፡ አሁንም ልጁ እንደተነገረው በፍጥነት ውሃውን ቀድቶ ሊመለስ ቢሞክርም ቤቱ ሳይደርስ ውሃው ፈሶ አለቀበት፡፡ አያቱንም “በቅርጫት ውሃ ማምጣት ስለማይቻል ሌላ መያዥ ይስጡኝና ላምጣ” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌ አያቱም “እኔ የምፈልገው የቅርጫት ውሃ ነው፡፡ ጠንክረህ ባለመሞከርህ ነው ፈሶ ያለቀብህ” በማለት እንደገና ላኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ በቅርጫት ውሃን ማምጣት እንደማይቻል ቢያውቅም ለአያቱ ታዛዥነቱን ለማሳየት ከበፊቱ ፈጥኖ ለማምጣት ሲሞክር ውሃው ፈሶ ስላለቀበት ባዶውን ቅርጫት እያሳየ “ተመልከት አባባ! እዲሁ ነው የምደክመው እንጅ እኮ ጥቅም የለውም” አለ፡፡
ከዚህ ጊዜ ምልልስ በኋላ ሽማግሌው “እስኪ ቅርጫቱን ተመልከተው” አሉት፡፡ ልጁ ቅርጫቱን ሲመለከት ከዚህ በፊት የማያውቀው ቅርጫት ይመስል ቅርጫቱ የተለየ ሆነበት የከሰል መያዣ እያለ በጅጉ የቆሸሸ ነበር፡፡ አሁን ግን ሙልጭ ብሎ ጸድቷል፡፡ ውስጡን ሲመለከተው ከመንጻቱ የተነሳ የበፊቱ ቅርጫት አልመስለው አለ፡፡
ስለዚህ ልጄ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ የሚሆነው እደሱ ነው፡፡ ላትረዳው ትችል ይሆናል ወይም ደግሞ ያነበብከውን ሁሉንም ነገር ላታስታውሰው ትችል ይሆናል ዳሩ ግን ባነበብክ ቁጥር ለውጨኛው የሚተርፍ ውስጣዊ ንጽህና እያመጣህ መሆኑን አትዘንጋ የመንፈስ ሥራ እንደዚህ ነው በማለት አስተማሩት፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በአንድ ተራራማ ስፍራ እርሻ በማረስ ከልጅ ልጁ ጋር የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበር፡፡ ይህ ሽማግሌ ዘወትር ፀሐይ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ያነባል፡፡ የልጅ ልጁ የአያቱን ተግባር ይከታተል ስለነበር እሱም ያያቱን ፈለግ በመከተል ጠዋት ጠዋት እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱን ማንበብ ጀመረ፡፡
አንደ ቀን ታድያ አያቱን “አባባ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ልረዳው አልቻልኩም ደግሞም አንብቤ እንደጨረስኩ ወዲያውኑ እረሳዋለሁ እናም እንድረዳውና እንዳልረሳው ምን ማደረግ አለብኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡
ሽማግሌው ምንም ድምጽ ሳያሰሙ “ከሰሉን ወደ ምድጃው ጨመሩና እንካ ይሄን የከሰል ቅርጫት ይዘህ ወንዝ ውረድና ውሃ ይዘህልኝ ተመለስ” አሉት፡፡ ልጁ ትዛዙን ለመፈጸም ወደወንዝ ወርዶ ውሃውን ይዞ ሊመለስ ቢመክርም ቅርጫቱ ውሃውን እያንጠባጠበ ቤት ከመድረሱ በፊት ፈሶ አለቀበት፡፡ ሽማግሌው የልጁን ሁኔታ እያስተዋሉ “አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይዘህ ስትመጣ ግን ፈጠን ፈጠን ብለህ ተመለስ ብለው” ድጋሜ ላኩት፡፡ አሁንም ልጁ እንደተነገረው በፍጥነት ውሃውን ቀድቶ ሊመለስ ቢሞክርም ቤቱ ሳይደርስ ውሃው ፈሶ አለቀበት፡፡ አያቱንም “በቅርጫት ውሃ ማምጣት ስለማይቻል ሌላ መያዥ ይስጡኝና ላምጣ” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌ አያቱም “እኔ የምፈልገው የቅርጫት ውሃ ነው፡፡ ጠንክረህ ባለመሞከርህ ነው ፈሶ ያለቀብህ” በማለት እንደገና ላኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ በቅርጫት ውሃን ማምጣት እንደማይቻል ቢያውቅም ለአያቱ ታዛዥነቱን ለማሳየት ከበፊቱ ፈጥኖ ለማምጣት ሲሞክር ውሃው ፈሶ ስላለቀበት ባዶውን ቅርጫት እያሳየ “ተመልከት አባባ! እዲሁ ነው የምደክመው እንጅ እኮ ጥቅም የለውም” አለ፡፡
ከዚህ ጊዜ ምልልስ በኋላ ሽማግሌው “እስኪ ቅርጫቱን ተመልከተው” አሉት፡፡ ልጁ ቅርጫቱን ሲመለከት ከዚህ በፊት የማያውቀው ቅርጫት ይመስል ቅርጫቱ የተለየ ሆነበት የከሰል መያዣ እያለ በጅጉ የቆሸሸ ነበር፡፡ አሁን ግን ሙልጭ ብሎ ጸድቷል፡፡ ውስጡን ሲመለከተው ከመንጻቱ የተነሳ የበፊቱ ቅርጫት አልመስለው አለ፡፡
ስለዚህ ልጄ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ የሚሆነው እደሱ ነው፡፡ ላትረዳው ትችል ይሆናል ወይም ደግሞ ያነበብከውን ሁሉንም ነገር ላታስታውሰው ትችል ይሆናል ዳሩ ግን ባነበብክ ቁጥር ለውጨኛው የሚተርፍ ውስጣዊ ንጽህና እያመጣህ መሆኑን አትዘንጋ የመንፈስ ሥራ እንደዚህ ነው በማለት አስተማሩት፡፡
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
"ለወፎች ክንፍ የተሰጣቸው በወጥመድ እንዳይያዙ ነው። ሰዎችም የማሰቡ ኃይልን የተሰጣቸው ኃጢአትን እንዲያስወግዱ ነው። እንግዲህ እንዲህ የማሰብ ኃይል ተሰጥቶን ሳለ ይባስ ብለን ከምድር አራዊት በታች የማናስተውል ከኾንን ሊደረግልን የሚችል ምህረት ወይም ይቅርታ እንደምን ያለ ምሕረት እንደምንስ ያለ ይቅርታ ነው?
በወጥመድ ተይዛ የነበረች ወፍ ድንገት ከወጥመዱ ብታመልጥ፤ ወደ ወጥመድ ገብቶ የነበረ አጋዘን ወጥመዱን በጣጥሶ ቢሄድ ከእንግዲህ ወዲህ በተመሳሳይ ወጥመድ እነዚህን መያዝ ከባድ ነው። የሕይወት ተሞክሮ ለሁለቱም ጥንቃቄን አስተምሯቸዋልና። እኛ ግን ምንም እንኳ በተመሳሳይ ወጥመድ ብንያዝም ተመልሰን ወደዚያ ወጥመድ እንወድቃለን፣ ምንም እንኳን በለባዊነት የከበርን ብንኾንም አእምሮ እንደሌላቸው እንሰሳት እንኳን ቀድመን አናስብም፤ አንጠነቀቅም!
ሴትን በማየት እልፍ ጉዳቶችን ተቀብለን ወደ ቤታችን የተመለስነው፤ በዝሙት ተመኝተንም ስናበቃ ለአያሌ ቀናት ያዘንነው ስንቴ ነው? ነገር ግን ከዚያ በኋላም ቢሆን በዚሁ ጉዳይ ላይ ጠንቃቆች አልኾንም፤ አንዱን ቁስል ሳናገግም ወደዚያ ክፉ ጠባይ እንወድቃለን፣ በተመሳሳይ መንገድ እንያዛለን፤ እጅግ ጥቂት ለኾነች የደስታ ሽርፍራፊ ብለንም ረጅምና ተደጋጋሚ ሥቃይን እንቀበላለን።
ዘውትር "በወጥመዶች መካከል እንደምትኼድ በገደልም መካከል እንደምትመላለስ ዕወቅ" የሚለውን ኃይለ ቃል ደጋግመን ለራሳችን ብንነግረው ግን ከእነዚህ ጉዳቶች ኹሉ እንጠበቃለን። (ሲራክ 9፥13)"
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09
በወጥመድ ተይዛ የነበረች ወፍ ድንገት ከወጥመዱ ብታመልጥ፤ ወደ ወጥመድ ገብቶ የነበረ አጋዘን ወጥመዱን በጣጥሶ ቢሄድ ከእንግዲህ ወዲህ በተመሳሳይ ወጥመድ እነዚህን መያዝ ከባድ ነው። የሕይወት ተሞክሮ ለሁለቱም ጥንቃቄን አስተምሯቸዋልና። እኛ ግን ምንም እንኳ በተመሳሳይ ወጥመድ ብንያዝም ተመልሰን ወደዚያ ወጥመድ እንወድቃለን፣ ምንም እንኳን በለባዊነት የከበርን ብንኾንም አእምሮ እንደሌላቸው እንሰሳት እንኳን ቀድመን አናስብም፤ አንጠነቀቅም!
ሴትን በማየት እልፍ ጉዳቶችን ተቀብለን ወደ ቤታችን የተመለስነው፤ በዝሙት ተመኝተንም ስናበቃ ለአያሌ ቀናት ያዘንነው ስንቴ ነው? ነገር ግን ከዚያ በኋላም ቢሆን በዚሁ ጉዳይ ላይ ጠንቃቆች አልኾንም፤ አንዱን ቁስል ሳናገግም ወደዚያ ክፉ ጠባይ እንወድቃለን፣ በተመሳሳይ መንገድ እንያዛለን፤ እጅግ ጥቂት ለኾነች የደስታ ሽርፍራፊ ብለንም ረጅምና ተደጋጋሚ ሥቃይን እንቀበላለን።
ዘውትር "በወጥመዶች መካከል እንደምትኼድ በገደልም መካከል እንደምትመላለስ ዕወቅ" የሚለውን ኃይለ ቃል ደጋግመን ለራሳችን ብንነግረው ግን ከእነዚህ ጉዳቶች ኹሉ እንጠበቃለን። (ሲራክ 9፥13)"
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
🔸 @dr_zebene_lemma
🔸🔹🔸 @dr_zebene_lemma
🔸 @dr_zebene_lemma
✍️Comment @Channel_admin09