የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ኘሮግራሞች በአገራዊው የብቃት ስታንዳርድ ተመዝነው ጥራትና ተገቢነታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ።
----------------------------------------------
(ሰኔ 15/2017 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ኘሮግራሞችን ጥራትና ተገቢነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጄና (ዶ/ር) ገልፀዋል ።
ከነዚህ ተግባራት መካከል የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር (Outcome based) መርህን ተከትለው እንዲተገበሩ በትምህርትና ስልጠና ፓሊሲው ላይ በተመላከተው ድንጋጌ መሰረት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ሥርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፍቃድ ኃ/ማሪያም በበኩላቸው ለ37 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የውጤት ተኮር ብቃት መለኪያ (Competency) ተዘጋጅቶ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ከ23 ዪኒቨርሲቲዎች፣ ከኢንዱስትሪዎች፣ ከሙያ ማህበራት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የየመስኩ ባለሙያዎች በክለሳ ሥራው ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በመድረኩም የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃንን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል የሆነው ውጤት ተኮር (Outcome based) የትምህርት ሥርዓት ስኬታማ እንዲሆን በተለይ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለየ መልኩ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲወጡም ተጠይቋል።
----------------------------------------------
(ሰኔ 15/2017 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት የአካዳሚክ ኘሮግራሞችን ጥራትና ተገቢነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚ ኤባ ሚጄና (ዶ/ር) ገልፀዋል ።
ከነዚህ ተግባራት መካከል የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር (Outcome based) መርህን ተከትለው እንዲተገበሩ በትምህርትና ስልጠና ፓሊሲው ላይ በተመላከተው ድንጋጌ መሰረት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ሥርዓተ ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ በሱፍቃድ ኃ/ማሪያም በበኩላቸው ለ37 የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የውጤት ተኮር ብቃት መለኪያ (Competency) ተዘጋጅቶ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
በዚህም ከ23 ዪኒቨርሲቲዎች፣ ከኢንዱስትሪዎች፣ ከሙያ ማህበራት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ የየመስኩ ባለሙያዎች በክለሳ ሥራው ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በመድረኩም የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃንን ብቃትና ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል የሆነው ውጤት ተኮር (Outcome based) የትምህርት ሥርዓት ስኬታማ እንዲሆን በተለይ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለየ መልኩ የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲወጡም ተጠይቋል።
የመስማት ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች በመለየት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡
የመስማት አቅም መለካት የሚያስችል የኦዲዮ ሜትሪ /Audiometry/ መሳሪያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
------------------------------------------------------
(ሰኔ 16/2017 ዓ.ም) የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና ማሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሐንስ ወጋሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ወቅት እንደገለጹት የመስማት ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች በመለየት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡
ጉዳታቸውና ችግራቸው ሳይለይ ትምህርት ቤት ውስጥ እንደ ሰነፍ የሚቆጠሩ ተማሪዎች መኖራቸውን የጠቆሙት ዶ/ር ዩሐንስ ትምህርት ቤት እያሉ በመስማት ችግር የሚፈለገውን ክህሎትና እውቀት ያልጨበጡ ተማሪዎች ለመደገፍ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://www.facebook.com/share/p/1Ehnc5LdEw/
የመስማት አቅም መለካት የሚያስችል የኦዲዮ ሜትሪ /Audiometry/ መሳሪያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
------------------------------------------------------
(ሰኔ 16/2017 ዓ.ም) የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራትና ማሻሻል መሪ ስራ አስፈጻሚ ዩሐንስ ወጋሶ (ዶ/ር) በስልጠናው ወቅት እንደገለጹት የመስማት ችግር ያለባቸውን ተማሪዎች በመለየት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡
ጉዳታቸውና ችግራቸው ሳይለይ ትምህርት ቤት ውስጥ እንደ ሰነፍ የሚቆጠሩ ተማሪዎች መኖራቸውን የጠቆሙት ዶ/ር ዩሐንስ ትምህርት ቤት እያሉ በመስማት ችግር የሚፈለገውን ክህሎትና እውቀት ያልጨበጡ ተማሪዎች ለመደገፍ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://www.facebook.com/share/p/1Ehnc5LdEw/
በሐረሪ ክልል የትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት በዲስትሪክት ደረጃ ሲካሄድ የነበረው የ2017 የት/ቤቶች ስፖርት ሊግ ውድድር ተጠናቀቀ።
----------------------------------------------
(ሰኔ 16/2017 ዓ.ም) በ14 የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች መካከል ከሰኔ ሰባት ጀምሮ በድምቀት ሲካሄድ የነበረው የ2017 ስፖርት ሊግ ውድድር ማጠቃለያውን አግኝቷል።
በቅርጫት ኳስና ቮሊ ቦል የፍፃሜ ጨዋታ የተደረገ ሲሆን በቅርጫት ኳስ አው አብዳል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአባድር አቻውን 57 ለ 52 በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።
በቮሊቦል ፍፃሜ ጨዋታ አባድርና መዕሪፍ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ባደረጉት የዋንጫ ጨዋታ መዕሪፍ 2 ለ 0 በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችሏል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://www.facebook.com/share/p/1B2nsZMiAk/
----------------------------------------------
(ሰኔ 16/2017 ዓ.ም) በ14 የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች መካከል ከሰኔ ሰባት ጀምሮ በድምቀት ሲካሄድ የነበረው የ2017 ስፖርት ሊግ ውድድር ማጠቃለያውን አግኝቷል።
በቅርጫት ኳስና ቮሊ ቦል የፍፃሜ ጨዋታ የተደረገ ሲሆን በቅርጫት ኳስ አው አብዳል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የአባድር አቻውን 57 ለ 52 በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።
በቮሊቦል ፍፃሜ ጨዋታ አባድርና መዕሪፍ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ባደረጉት የዋንጫ ጨዋታ መዕሪፍ 2 ለ 0 በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችሏል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤ https://www.facebook.com/share/p/1B2nsZMiAk/
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገር-በቀል እውቀትን በመሰነድና በማበልጸግ ለማህበረሰብ ጥቅም ማዋል እንደሚጠበቅባቸው ተመላከተ፤ በሀገር-በቀል እውቀት ዙሪያ አውደጥናት ተካሂዷል።
--------------------------------------------------
(ሰኔ 18/2017 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተ/መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሃንዲሶ(ዶ/ር) በአውደ ጥናቱ ላይ እንደገለጹት አገር-በቀል እውቀት ለተሻለ አገር ግንባታና ለማህበረሰብ እድገት እንዲውል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገር-በቀል እውቀትን በመለየት፣መሰነድ፣ በየዘርፉ ማደራጀት፣ መመርመር፣ ማወቅ፣ መረዳት እና ማበልጸግ እንደሚገባቸውም ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አገር-በቀል እውቀትን በአደረጃጀት ፣ በአሰራርና በግብዓት በመደገፍ ዘርፉ ለማህበረሰብ ልማትና ለአገር እድገት ጥቅም ላይ እንዲውል እየሰራ መሆኑን መሪ ስራ አስፈጻሚው አመልክተዋል።
የማህበረሰብ ጉድኝት እና አገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላም አለሙ በበኩላቸው ሀገር-በቀል ዕውቀት፣ ለአከባቢ ጥበቃና ለዘላቂ ልማት ግቦች መሳካት ያለው አስተዋፅዖ እየጎላ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫም ማግኘት ትችላላችሁ፤
https://www.facebook.com/share/p/1DDcgZ1Bzw/
--------------------------------------------------
(ሰኔ 18/2017 ዓ.ም) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተ/መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሃንዲሶ(ዶ/ር) በአውደ ጥናቱ ላይ እንደገለጹት አገር-በቀል እውቀት ለተሻለ አገር ግንባታና ለማህበረሰብ እድገት እንዲውል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሀገር-በቀል እውቀትን በመለየት፣መሰነድ፣ በየዘርፉ ማደራጀት፣ መመርመር፣ ማወቅ፣ መረዳት እና ማበልጸግ እንደሚገባቸውም ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር አገር-በቀል እውቀትን በአደረጃጀት ፣ በአሰራርና በግብዓት በመደገፍ ዘርፉ ለማህበረሰብ ልማትና ለአገር እድገት ጥቅም ላይ እንዲውል እየሰራ መሆኑን መሪ ስራ አስፈጻሚው አመልክተዋል።
የማህበረሰብ ጉድኝት እና አገር በቀል እውቀት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላም አለሙ በበኩላቸው ሀገር-በቀል ዕውቀት፣ ለአከባቢ ጥበቃና ለዘላቂ ልማት ግቦች መሳካት ያለው አስተዋፅዖ እየጎላ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫም ማግኘት ትችላላችሁ፤
https://www.facebook.com/share/p/1DDcgZ1Bzw/
አገር አቀፍ የቅድመ ልጅነት ዕድገትና ትምህርት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ።
------------------------------------------------
(ሰኔ 17/2017 ዓ.ም) በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ባለፉት ሁለት አመታት በመንግስትና በማህበረሰቡ በተሰሩ ስራዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርትን በማስፋፋትና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገልጿል።
"ልጆቻችን ብሩህ ነገን እንዲፈጥሩ መሠረቱን ዛሬ እንጣል " በሚል በተከናወነው መርሃ ግብር ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የሌሎች ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ሊሠራበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን አሁን ላይ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የልማት አጋሮች ጋር በተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የትምህርት ጥራትን በማጐልበት የሀገርን ብልጽልግና በማረጋገጥና ዜጎች ከሚመዘገበው ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትምህርት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመግለጽ የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/1Fn8WFGMfh
------------------------------------------------
(ሰኔ 17/2017 ዓ.ም) በንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ባለፉት ሁለት አመታት በመንግስትና በማህበረሰቡ በተሰሩ ስራዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርትን በማስፋፋትና ተደራሽ በማድረግ ረገድ ስኬቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገልጿል።
"ልጆቻችን ብሩህ ነገን እንዲፈጥሩ መሠረቱን ዛሬ እንጣል " በሚል በተከናወነው መርሃ ግብር ላይ የትምህርት ሚኒስቴርና የሌሎች ባለድርሻ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት በመስጠት ሊሠራበት የሚገባው ጉዳይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን አሁን ላይ ከሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የልማት አጋሮች ጋር በተፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የትምህርት ጥራትን በማጐልበት የሀገርን ብልጽልግና በማረጋገጥና ዜጎች ከሚመዘገበው ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ትምህርት ቁልፍ ሚና ያለው መሆኑን በመግለጽ የቅድመ ልጅነት እድገትና ትምህርት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤
https://www.facebook.com/share/p/1Fn8WFGMfh