Telegram Web Link
በተለያዩ ክብረ በዓላት ሳምንቱን ሙሉ የተከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሰራተኞች ቀን በዛሬው ዕለት 18 ሺ የአየር መንገዱ ሠራተኞች በተጋበዙበት እንዲሁም የአየር መንገዱ የቦርድ ሰብሳቢ ሌ/ጄነራል ይልማ መርዳሳ እንዲሁም የቦርድ አባላት፣ የአየርመንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም ሌሎች የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ አመራሮች በታደሙበት ታላቅ ስነ ስርአት ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ በተሠራው የአየር መንገዱ የእግር ኳስ ሜዳ ተከብሮ ውሏል።

በዝግጅቱ ላይ ከአየር መንገዱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞች ከዋና ስራ አስፈፃሚው እና ከየክፍሎቻቸው ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እጅ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል። በዛሬው
ዕለት የተከናወነው ክብረ በዓል ለአንድ ሳምንት የቆየው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰራተኞች ቀን ክብረ በዓል የመዝጊያ ዝግጅት ሲሆን በሰራተኞች ዘንድ ያለውን ቅርርብ የሚያሳድግ ነው። #የኢትዮጵያአየርመንገድ #የሰራተኞችቀን2017
2025/06/27 20:35:14
Back to Top
HTML Embed Code: