Telegram Web Link
ኢማም ሱፍያን አስ‐ሰውሪይ [ረሒመሁላህ] እንዲህ ብለዋል:‐
«በነፍሱ ላይ ሦስት ነገሮችን ያገኘ ሰው ስኬታማነትን ይፍረድላት:‐
❶ አሸናፊና ኃያል የሆነውን አላህ መፍራት፤
❷ የተመረጡትን ነቢይ ማክበር እና
❸ ምርጥና መልካም ሰዎችን ማፈር [ሐያእ ማድረግ]።»
📚 ዐጃኢቡል‐ቁርኣን፥ ኢማም ፈኽሩዲን ራዚ
👍1918
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል:‐
«ይህ [ሐላል] ገንዘብ ጣፋጭ ነው። [የአላህን] ደንብ ጠብቆ ለያዘው እና ደንቡን ጠብቆ በተገቢው ቦታ ላዋለው ሰው [ለአኺራ] እንዴት ያለ አጋዥ ነው!?»
:
ገንዘብ በራሱ እርኩስ አይደለም። በራሱም ፀጋ አይደለም። መልካም ተሰርቶበት አኺራ የሚሸመትበት ሲሆን ግን 'ዱንያው' ራሱ 'የአኺራው' ማዕረግ ይሆናል። በስሜት ከነጎዱ፣ በፍቅሩ ከተለከፉ እና ለማንበር ካከማቹት ግን ወደር የሌለው ጥፋት ነው!
እስኪ ሶላቱ #ዱሓ እንስገድ። ከ5‐10 ደቂቃ ቢወስድብን ነው! ባረከላሁፊኩም!
50👍7
Audio
📚አል‐አዝካር ሚን ከላሚ ሰይዲል‐አብራር
📗 ክፍል 13:‐ በሌሊት ነቅቶ ከቤት ሲወጣ የሚለው ዚክር — በሽንት ላይ ሆኖ ዚክርና ንግግር ስለመከልከሉ
📆 ጥቅምት 27/ 2018 ዓ. ል.
2
አዝካርን እየተከታተላችኋት ነው?
እንዴት አያችኋት?…
ጠቃሚ አስተያየትዎን ይጣሉልን!
ጀዛኩሙላሁ ኸይረን!
25👍4
ቀልበ‐ቁርኣን፣ ጠባየ‐ነቢይ፣ መፍቅሬ‐ሰብ የነበሩት አባታችን ሙፍቲ ዑመርን [አላህ ይዘንላቸው] አንጋፋ መሻይኾች በተገኙበት፣ በመድረሳ ተማሪዎቻችን ታጅበን በቁርኣን ኸትም፣ በሶለዋት እና በሶደቃ አስበናቸዋል። አልሐምዱሊላህ!

በቁርኣን ኖሮ፣ ቁርአንን አስተምሮ በቁርኣን መታወስ እጅግ የሚያስደስት የሕይወት መልክ አለው። ሐጂ ከ300 ጊዜ በላይ ቁርኣንን የፈሰሩ፣ በጣፋጭ አቀራረባቸው የቁርኣንን ፍቅር በልብ ውስጥ የሚያጭሩ፣ የቁርኣንን ግርማ በመንፈስ ውስጥ የሚያሰርፁ ታላቅ ዐሊም ነበሩ።

እድሜ ልካቸውን ያገለገሉት ቁርኣን ሸፈዐ ይሁናቸው። የቀራነውን፣ የሶደቅነውን፣ የዘከርነውን፣ ዱዓችንን አላህ ያድርስላቸው!
57😍1
2025/11/10 03:36:29
Back to Top
HTML Embed Code: