የባከነ ሌሊት!!!!
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@gGetem
@gGetem
@leoyri
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@gGetem
@gGetem
@leoyri
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
#"የምፃተኛው_ኑዛዜ"
(በእውቀቱ ስዩም)
ካ’ገር ጫፍ እስከጫፍ በጥላህ ከልለህ
ተራራው የኔ ነው ለምን ትለኛለህ?
ወንዙ ድርሻዬ ነው ለምን ትለኛለህ?
እንኳንስ መሬቱ አንተም ያ’ንተ አይደለህ።
እኔ መጻተኛ አንተ ኗሪ ነኝ ባይ
እኔ እግሬን ስከተል ርስትህን ስታይ
ስቀርብህ ገፋኸኝ ስትገፋኝ ቦታ አጣሁ
ድንኳን ብትተክል፣ ነፋስ ሆኜ መጣሁ።
ያ’ባትህ ያ’ባቴ
ጠበኛ ስማቸው
ጠበኛ ሕልማቸው
በሕይወት ተጣሉ፣ ታረቁ ባፅማቸው
ባፈር ተቃቃሩ፣ አፈር አስማማቸው
በዙሪያቸው በቅሎ ከቧቸው ሞት ደኑ
መተቃቃፍ መርጠው ማማና ወይን ሆኑ።
ይችላል ይሉሃል ፍልሚያ ማዘጋጀት
ያ’ባት አጥንት ወስዶ ስሎ ጦር ማበጀት
አንተው ጦር ወርውረህ አንተው ቀድመህ ወድቀኽ
አካሌ ደረቴ መኾንኽን መች አወቅኽ ??? !!!
@gGetem
@gGetem
@gGetem
@leoyri
(በእውቀቱ ስዩም)
ካ’ገር ጫፍ እስከጫፍ በጥላህ ከልለህ
ተራራው የኔ ነው ለምን ትለኛለህ?
ወንዙ ድርሻዬ ነው ለምን ትለኛለህ?
እንኳንስ መሬቱ አንተም ያ’ንተ አይደለህ።
እኔ መጻተኛ አንተ ኗሪ ነኝ ባይ
እኔ እግሬን ስከተል ርስትህን ስታይ
ስቀርብህ ገፋኸኝ ስትገፋኝ ቦታ አጣሁ
ድንኳን ብትተክል፣ ነፋስ ሆኜ መጣሁ።
ያ’ባትህ ያ’ባቴ
ጠበኛ ስማቸው
ጠበኛ ሕልማቸው
በሕይወት ተጣሉ፣ ታረቁ ባፅማቸው
ባፈር ተቃቃሩ፣ አፈር አስማማቸው
በዙሪያቸው በቅሎ ከቧቸው ሞት ደኑ
መተቃቃፍ መርጠው ማማና ወይን ሆኑ።
ይችላል ይሉሃል ፍልሚያ ማዘጋጀት
ያ’ባት አጥንት ወስዶ ስሎ ጦር ማበጀት
አንተው ጦር ወርውረህ አንተው ቀድመህ ወድቀኽ
አካሌ ደረቴ መኾንኽን መች አወቅኽ ??? !!!
@gGetem
@gGetem
@gGetem
@leoyri
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
👫ግጣም አልባው ገጣሚ📖📚
☔️☂ #ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር🦋🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@leoyri
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👁💚💛❤️
#ተፃፈ_12_06_2012_ዓ_ም
💯 quality 😍🥰
Plc share
☔️☂ #ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር🦋🦋🦋🦋
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@leoyri
@gGetem
@gGetem
@gGetem
👁💚💛❤️
#ተፃፈ_12_06_2012_ዓ_ም
💯 quality 😍🥰
Plc share
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
#ጎዳና_ሰብ
#የነብስያዬ_ቁስል 😢
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@leoyri
@gGetem
@gGetem
✨✨✨✨✨✨✨✨
🦷✍30/09/2013ዓ.ም
✨ #የሕይወትን_ሕማም_ያየሁበት
👀SHARE &JOIN PLC
#የነብስያዬ_ቁስል 😢
#ገጣሚ_ሊዮ_ማክ
የሆሄያት ህብር
#የጥበብ_ማዕድ
@leoyri
@leoyri
@gGetem
@gGetem
✨✨✨✨✨✨✨✨
🦷✍30/09/2013ዓ.ም
✨ #የሕይወትን_ሕማም_ያየሁበት
👀SHARE &JOIN PLC
እየሔዱ መጠበቅ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኃላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
**********
@leoyri
@gGetem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
‹‹እየሄድክ ጠብቀኝ›› - ስትይኝ ሄጃለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ….
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ…
አክሱምን እንዳየሽ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ጠራቢው እኔ ነኝ!
ያለፍኩት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ሰማይ ጠቀስ ሐውልት - የተፈለፈለ፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
አክሱም ሐውልት ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ጥበብ አለ!!
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ላሊበላን አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
ፈልፋዩ እኔ ነኝ፤…
ያለፍሁት በዚያ ነው - ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ካንድ ውቅር ድንጋይ፤
ህንፃ ቤተ-መቅደስ ፤ የተፈለፈለ፡፡
ታምር የሚመስል - ታሪክም ያይደለ፤
በላሊበላ ውስጥ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ፅናት አለ፡፡
ቃልሽን አክብሪ - ቃሌን አከብራለሁ፤
መንገዴ እንዳይጠፋሽ..
በየደረስሁበት፤
ድንቅ ምልክትን - አኖርልሻለሁ፤
አንቺ ላትደርሺብኝ..
እኔ ግን እየሄድሁ - እጠብቅሻለሁ፡፡
*
*
እናምልሽ ውዴ - ትክል ድንጋይ አይተሸ፤
ታምር እና ታሪክ - ፈፅሞ እንዳይመስልሽ፤
የኔው መቃብር ነው!
ውድቀቴም እዛው ነው! ምልክት ይሁንሽ፡፡
አጋጥሞሽ እንደሆን…
ባባራ ዘመኑ፤
የራሱን መቃብር - ለመትከል የቻለ፤
መኖር የሚመስል - መሞትም ያይደለ፤
በጢያ ድንጋይ ላይ…
አንቺን የሚጠብቅ - የኔ ውድቀት አለ፡፡
ከውድቀቴ ኃላ - ባይንሽ የምታዪው፤
ታምር የሚመስል - ታሪክ የምትይው፤
ምልክት የሚሆን - መንገድ ስላልተውኩኝ፤
ከመሞቴ በፊት..
ውድቀቴን፤
ሽንፈቴን፤
ከመቃብሬ ላይ - እንዲህ ብዬ ፃፍሁኝ፡፡
ሩጫዬን ጨረስኩ፤
ሰው ነኝ - ተሸነፍኩ!!!
እናምልሽ ውዴ….
‹‹እየሔድህ ጠብቀኝ›› - ያልሽው ቃል ስህተት
ነው፤
ቃሉም ገብቶሽ እንደው…
መራመድ መሄድ ነው፤
መሮጥም መሄድ ነው፤
መብረርም መሄድ ነው፤
አንቺ እንድትደርሺብኝ …
እኔ እየሞትሁ - እጠብቅሻለው!!!
**********
@leoyri
@gGetem
Forwarded from የሆሄያት ህብር📝📝 (Sirake peterøs ☞Ye Yerijo)
ብልጭታ
እንደኖረ ሞተ ቢሆን የሰው ሚዛን
ከ'ዚ እርከን ለማለፋ ስንት አንደበት ደቃን።
የስኬትን ቅኔ በእድሜ ልክ ውዥንብር
ፍቺ ባይኖረውም ያለ ልክ መታተር
እርምጃዬ ሁሉ በእሾህ ቢገታ
የመንገዴ ብርሃን አይሆንም ብልጭታ።
.
.
.
.
ብቻ
.
.
.
ሚመሸው ቀን ከቀን ነውና ለመንጋት
የችግሬን ቋጥኝ አልቆጥርም እንደቅጣት።
✍ሊዮ ማክ
🚫ሰው ባስፈለገኝ ጊዜ ከጎኔ በተለያየ ሁኔታ እና አጋጣሚ ከጎኔ ለነበራቹ እና አሁንምም ላላቹ በሙሉ ከልቤ❤አመሰግናለሁ!።
👏👏👏👏👏👏👏
🙏🙏🙏🙏🙏
www.tg-me.com/gGetem
www.tg-me.com/leoyri
እንደኖረ ሞተ ቢሆን የሰው ሚዛን
ከ'ዚ እርከን ለማለፋ ስንት አንደበት ደቃን።
የስኬትን ቅኔ በእድሜ ልክ ውዥንብር
ፍቺ ባይኖረውም ያለ ልክ መታተር
እርምጃዬ ሁሉ በእሾህ ቢገታ
የመንገዴ ብርሃን አይሆንም ብልጭታ።
.
.
.
.
ብቻ
.
.
.
ሚመሸው ቀን ከቀን ነውና ለመንጋት
የችግሬን ቋጥኝ አልቆጥርም እንደቅጣት።
✍ሊዮ ማክ
🚫ሰው ባስፈለገኝ ጊዜ ከጎኔ በተለያየ ሁኔታ እና አጋጣሚ ከጎኔ ለነበራቹ እና አሁንምም ላላቹ በሙሉ ከልቤ❤አመሰግናለሁ!።
👏👏👏👏👏👏👏
🙏🙏🙏🙏🙏
www.tg-me.com/gGetem
www.tg-me.com/leoyri
Telegram
የሆሄያት ህብር📝📝
ውድ የሆሄያት ህብር ቻናል ቤተሰቦች ስለተቀላቀሉን እናመሰግናለን።👍👍
ቻናላችን፦
👉በግጥም 📔📰📼📼
👉በድርሰት📚📚
👉በትረካ📀🎼
👉በስዕል🃏🃏
👉ወጎች📜📜
👉በአጫጭር ልብ ወለዶች ወደ እናንተ እንደርሳለን።
ለሀሳብ እና አስተያየት
፦ሊዮ ማክ፦ @Leoyri
፦ዮሲ ማን፦ @yosikeman
፦የሪ፦ @yerijo
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል 👉 @gGetem
ቻናላችን፦
👉በግጥም 📔📰📼📼
👉በድርሰት📚📚
👉በትረካ📀🎼
👉በስዕል🃏🃏
👉ወጎች📜📜
👉በአጫጭር ልብ ወለዶች ወደ እናንተ እንደርሳለን።
ለሀሳብ እና አስተያየት
፦ሊዮ ማክ፦ @Leoyri
፦ዮሲ ማን፦ @yosikeman
፦የሪ፦ @yerijo
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል 👉 @gGetem
ክፍል ሁለት(፪)
ከባለፈው የቀጠለ....
👉🏾 የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን ፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።
:
👉🏾👉🏾 ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
👉🏾👉🏾 መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
👉🏾👉🏾 ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
👉🏾👉🏾 ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ ።
:
👉🏾👉🏾 ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።
:
👉🏾👉🏾 ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
👉🏾👉🏾 የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
👉🏾👉🏾 ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
👉🏾👉🏾 ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
:
👉🏾 ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል ።
:
👉🏾 እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ ።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
‼️ለጓደኛዎ #share ማድረጎን አይርሱ።
🔘 የተመቻችሁ 👍
✅ Join us;👉🏼 @gGetem
ከባለፈው የቀጠለ....
👉🏾 የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን ፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።
:
👉🏾👉🏾 ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
👉🏾👉🏾 መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
👉🏾👉🏾 ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
👉🏾👉🏾 ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ ።
:
👉🏾👉🏾 ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።
:
👉🏾👉🏾 ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
👉🏾👉🏾 የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
👉🏾👉🏾 ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
👉🏾👉🏾 ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
:
👉🏾 ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል ።
:
👉🏾 እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ ።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
‼️ለጓደኛዎ #share ማድረጎን አይርሱ።
🔘 የተመቻችሁ 👍
✅ Join us;👉🏼 @gGetem
#ትወደዋለች...
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እወደዋለሁ ብላኛለች
ፍቅሯን ነግራኛለች።
አምናታለሁ !
ደግሞም አላምናትም
ብትወደውማ
ከሌላ ወንድ ጋር አብራ አትወድቅም!
እሷ እንደምትለው
ውልደትና እድገቷ ጠባሳው ብዙ ነው
የማጣት ቀንበሩ ሸክሙ ከባድ ነው ...
ያምራታል መታየት
አምሮባት መገኘት
እኩል ለመሆን ነው ከጓደኞቿ ጋር
ነፍሷን የምታነደው በቁስ ጥቅም ስካር
ለአንድ አልቦ ለአንድ አንባር
አንድ አዳር ግድ ነው ከአንዱ ወንድ ጋር።
እሷ እንደምትለው.. .
ልቧ ታምኖለታል ገላዋ ቢክድም
እንደዛም ሆኖ ግን
በሱ ስፍር ልኬት ወንዱን አትመዝንም።
ይሄንን አውቃለሁ !
አዎን አምናታለሁ
አፍቃሪው ናት ብዬ
ከእውነታው ኮብልዬ
እሷ እንዳለችው.. .
ትውልድና እድገቷ ጠባሳው ብዙ ነው
የማጣት ቀንበሩ ሸክሙ ከባድ ነው
ገንዘብ ላጣ ድሀ
አምሮበት እንዲታይ መፍትሄው ምንድነው?
ከወንድ ጋር ማደር ከአንገት በላይ መሳቅ
በማስመሰል ስላቅ
መጫወት መደነስ
መብነሽነሽ መኩነስነስ
ሀጥያት ነው ብዬ ሳልደርስ ለወቀሳ
የማዝን መሰለኝ
ከጓደኞቿ ዘንድ ብትታይ ተናንሳ ።
አይ አይ አትወደውም !
እላለሁ ለጥቄ
ከእውነት ተናንቄ ...
የላትም ብትባል ቢንቋት ቢተዋት
ገላዋን ከማርከስ የለም የሚከብዳት ።
አይ .. አይ.. አትወደውም !
ብትወደውማ ...
ከእምነቱ ሰርቃ
ለሌላ ወንድ ወድቃ ...
ከሌላ ወንድ ጉያ ውስጡ ተወሽቃ
አንድ አዳር አይደለም
ለሰከንድ አትቆይም ...
እንዲህ ያለ ክህደት ፍቅር አይባልም።
ብዬ ከማለቴ ...
ስለሱ ሳወራ ከአንዴም ሁለቴ
የእንባ ውርጅብኝ ጉንጮቿ ላይ ዘርታ
ነጉዳ በትዝታ ...
በአፍቃሪ ሰው ሲቃ ጠርታዋለች ስሙን
አትወደውም ብዬ
ይሄን ቃል ባወጣ ... ይሆናል ወይ እሙን ?
አይሆንም!
አይሆንም !
መውደድማ ትወደዋለች
ለፍቅሩ ወድቃለች.. .
ሽንፈቱን ደብቃ
ሽንፈቷን ደብቃ ...
እሷ ጓደኞች ዘንድ
አልቦ ገዝቶልኛል ብላ አውርታለች
ሽቶ ገዝቶልኛል ብላ ተናግራለች ።
እላለሁ በልቤ
በሰው ቁስል እንጨት እንዳልሰድ አስቤ
አይ አይ አትወደውም ደግሞ ይለኛል ቀልቤ
እንደዚህ ሆኜ ነው እሷን የምሰማት
እንደዚህ ሆኜ ነው እሷን የምቀርባት
ለዚህ መንታ ሀሳቤ
ቁስ ንዋዩ ኖራት
ምናለ ባየኋት ?!... ምናል በመዘንኳት?
ብዬም ደግሞ አውቃለው
ማጣት ያሸነፈው ፍቅር ግን ምንድነው?
አይ አይ... አትወደውም
አይ አይ ...ትወደዋለች
ብቻ እንጃ.. .
ብቻ እንጃ.. .
ይህች ሴት ቅኔ ነች !
@gGetem
@gGetem
@gGetem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
እወደዋለሁ ብላኛለች
ፍቅሯን ነግራኛለች።
አምናታለሁ !
ደግሞም አላምናትም
ብትወደውማ
ከሌላ ወንድ ጋር አብራ አትወድቅም!
እሷ እንደምትለው
ውልደትና እድገቷ ጠባሳው ብዙ ነው
የማጣት ቀንበሩ ሸክሙ ከባድ ነው ...
ያምራታል መታየት
አምሮባት መገኘት
እኩል ለመሆን ነው ከጓደኞቿ ጋር
ነፍሷን የምታነደው በቁስ ጥቅም ስካር
ለአንድ አልቦ ለአንድ አንባር
አንድ አዳር ግድ ነው ከአንዱ ወንድ ጋር።
እሷ እንደምትለው.. .
ልቧ ታምኖለታል ገላዋ ቢክድም
እንደዛም ሆኖ ግን
በሱ ስፍር ልኬት ወንዱን አትመዝንም።
ይሄንን አውቃለሁ !
አዎን አምናታለሁ
አፍቃሪው ናት ብዬ
ከእውነታው ኮብልዬ
እሷ እንዳለችው.. .
ትውልድና እድገቷ ጠባሳው ብዙ ነው
የማጣት ቀንበሩ ሸክሙ ከባድ ነው
ገንዘብ ላጣ ድሀ
አምሮበት እንዲታይ መፍትሄው ምንድነው?
ከወንድ ጋር ማደር ከአንገት በላይ መሳቅ
በማስመሰል ስላቅ
መጫወት መደነስ
መብነሽነሽ መኩነስነስ
ሀጥያት ነው ብዬ ሳልደርስ ለወቀሳ
የማዝን መሰለኝ
ከጓደኞቿ ዘንድ ብትታይ ተናንሳ ።
አይ አይ አትወደውም !
እላለሁ ለጥቄ
ከእውነት ተናንቄ ...
የላትም ብትባል ቢንቋት ቢተዋት
ገላዋን ከማርከስ የለም የሚከብዳት ።
አይ .. አይ.. አትወደውም !
ብትወደውማ ...
ከእምነቱ ሰርቃ
ለሌላ ወንድ ወድቃ ...
ከሌላ ወንድ ጉያ ውስጡ ተወሽቃ
አንድ አዳር አይደለም
ለሰከንድ አትቆይም ...
እንዲህ ያለ ክህደት ፍቅር አይባልም።
ብዬ ከማለቴ ...
ስለሱ ሳወራ ከአንዴም ሁለቴ
የእንባ ውርጅብኝ ጉንጮቿ ላይ ዘርታ
ነጉዳ በትዝታ ...
በአፍቃሪ ሰው ሲቃ ጠርታዋለች ስሙን
አትወደውም ብዬ
ይሄን ቃል ባወጣ ... ይሆናል ወይ እሙን ?
አይሆንም!
አይሆንም !
መውደድማ ትወደዋለች
ለፍቅሩ ወድቃለች.. .
ሽንፈቱን ደብቃ
ሽንፈቷን ደብቃ ...
እሷ ጓደኞች ዘንድ
አልቦ ገዝቶልኛል ብላ አውርታለች
ሽቶ ገዝቶልኛል ብላ ተናግራለች ።
እላለሁ በልቤ
በሰው ቁስል እንጨት እንዳልሰድ አስቤ
አይ አይ አትወደውም ደግሞ ይለኛል ቀልቤ
እንደዚህ ሆኜ ነው እሷን የምሰማት
እንደዚህ ሆኜ ነው እሷን የምቀርባት
ለዚህ መንታ ሀሳቤ
ቁስ ንዋዩ ኖራት
ምናለ ባየኋት ?!... ምናል በመዘንኳት?
ብዬም ደግሞ አውቃለው
ማጣት ያሸነፈው ፍቅር ግን ምንድነው?
አይ አይ... አትወደውም
አይ አይ ...ትወደዋለች
ብቻ እንጃ.. .
ብቻ እንጃ.. .
ይህች ሴት ቅኔ ነች !
@gGetem
@gGetem
@gGetem
🐺 ቀበሮ ለዶሮ «የአባትህ ድምፅ በጣም ደስ ይለኝ ነበር» አለው።
🐓 ዶሮም «የኔም ድምፅ እኮ እንደ አባቴ ነው» በማለት መለሰ።
🐺 ቀበሮውም «እንደዛ ከሆነማ እባክህ ልታሰማኝ ትችላለህ ??» በማለት ተማጸነው።
🐓 ዶሮው «ምን ችግር አለው !» በማለት ጩኸቱን ለማሰማት ዓይኑን ሲጨፍን ቀበሮው ይዞት አፈተለከ።
ውሾች ሁሉ ዶሮውን ከቀበሮው አፍ ለማስጣል እየጮኹ እግር በእግር ተከታተሉት።
🐓 ዶሮው ለቀበሮው «ከውሾቹ ለመዳን ከፈለግክ ዶሮው የእናንተ ሰፈር አይደለም !!» በላቸው አለው። ቀበሮውም የተባለውን ለመናገር ሲሞክር ዶሮው ከአፉ አመለጠው።
🐺 ቀበሮውም በፀፀት ተውጦ «ዝም ማለት ሲገባው የተናገረ አፉ ይረገም ፤ ይኮነን» አለ።
🐓 ዶሮም በበኩሉ «መንቃት ሲገባው የተጨፈነ አይን ፤ ይኮነን» አለ። ይባላል
የምንነቃበት ቀን ይሁንልን!
@gGetem
@leoyri
🐓 ዶሮም «የኔም ድምፅ እኮ እንደ አባቴ ነው» በማለት መለሰ።
🐺 ቀበሮውም «እንደዛ ከሆነማ እባክህ ልታሰማኝ ትችላለህ ??» በማለት ተማጸነው።
🐓 ዶሮው «ምን ችግር አለው !» በማለት ጩኸቱን ለማሰማት ዓይኑን ሲጨፍን ቀበሮው ይዞት አፈተለከ።
ውሾች ሁሉ ዶሮውን ከቀበሮው አፍ ለማስጣል እየጮኹ እግር በእግር ተከታተሉት።
🐓 ዶሮው ለቀበሮው «ከውሾቹ ለመዳን ከፈለግክ ዶሮው የእናንተ ሰፈር አይደለም !!» በላቸው አለው። ቀበሮውም የተባለውን ለመናገር ሲሞክር ዶሮው ከአፉ አመለጠው።
🐺 ቀበሮውም በፀፀት ተውጦ «ዝም ማለት ሲገባው የተናገረ አፉ ይረገም ፤ ይኮነን» አለ።
🐓 ዶሮም በበኩሉ «መንቃት ሲገባው የተጨፈነ አይን ፤ ይኮነን» አለ። ይባላል
የምንነቃበት ቀን ይሁንልን!
@gGetem
@leoyri
ዘመን ተወጥሯል
በዜናና ስላቅ
ቀን መሽቶ ይነጋል
ስራችንን ሳና'ቅ።
ወትሮ ድሮ ፣ ድሮ
ሰውን አሳርሮ...
ተናጥቆ ና ሰርቆ...
ከሴት ገላ ወድቆ...
ውሎውን ያበቃ !
እንደ ሰብል ክምር
አዳሩን ሲወቃ…
ሲኮነን ሲረገም
በህሊናው ክሶች
ውሎው ሲገመገም
አድሮ ያነጋጋል
ነገን ለመታረም።
አሁን ይሄ ድሮ
ዛሬ ተቀይሮ
አንዴ በጦር ዜና
አንደዜ በነዋይ
ስጋውን ወጥሮ
ሰውን አሳርሮ
ተናጥቆ ና ሰርቆ
በሴስ ገላ ወድቆ
ነፍሱን የበደለ …
(ራሱን ሳይጠይቅ
እንዴት እንደዋለ)
አቀርቅሮ ይስቃል
በስልኩ ድራማ...
:
ለመጸጸት እንኳን
አያደርሰውማ!
(ሚካኤል አ)
@gGetem
@leoyri
በዜናና ስላቅ
ቀን መሽቶ ይነጋል
ስራችንን ሳና'ቅ።
ወትሮ ድሮ ፣ ድሮ
ሰውን አሳርሮ...
ተናጥቆ ና ሰርቆ...
ከሴት ገላ ወድቆ...
ውሎውን ያበቃ !
እንደ ሰብል ክምር
አዳሩን ሲወቃ…
ሲኮነን ሲረገም
በህሊናው ክሶች
ውሎው ሲገመገም
አድሮ ያነጋጋል
ነገን ለመታረም።
አሁን ይሄ ድሮ
ዛሬ ተቀይሮ
አንዴ በጦር ዜና
አንደዜ በነዋይ
ስጋውን ወጥሮ
ሰውን አሳርሮ
ተናጥቆ ና ሰርቆ
በሴስ ገላ ወድቆ
ነፍሱን የበደለ …
(ራሱን ሳይጠይቅ
እንዴት እንደዋለ)
አቀርቅሮ ይስቃል
በስልኩ ድራማ...
:
ለመጸጸት እንኳን
አያደርሰውማ!
(ሚካኤል አ)
@gGetem
@leoyri