Telegram Web Link
አንዲት ምስኪን ሀገር
.
.
.
ሙሾ እያወረደች ነጠላ አዘቅዝቃ፤
ኩርማን ስትለምን ከማጀቷ ርቃ፤

መኖር ታክታ ክንዷ ዝሎ፤
በእንባ ብዛት ፊቷ ከስሎ፤

ሰላምን ተርባ ተሰብሮ መንፈሷ፤
በላይዋ አለቀ የዝን ጥቁር ልብሷ፤

ቀኝ ጎኗ ሲድን ግራዉ ይታመማል፤

መዳንን ስትሻ ሀኪሙ ይጠፋል፤
መድሀኒት ቀማሚ በሀገሩ ጠፍቶ፤

ቁስሏ ሲያመረቅዝ ህመሟ በርትቶ፤
ከቤቷ እየመጡ ይማርሽ ይሏታል፤
መድሀኒቷን ነፍገዉ ፈዉስ
ይመኙላታል።

በዔደን ታደሰ
@ediwub

@getem
@getem
" በረከተ-መንግስት"
                   ( ግዮናይ ነኝ)!፧
ምስኪን ያገሬ ሰው...
ቀኑን ሲሮጥ ውሎ  ሌሊት ይሸሸጋል፣
ተፈጥሮ ነውና...
በወፎች ዝማሬ   አይቀርም ይነጋል።
ይኸው ደሞ ነጋ...
መስከረም ይመስል  መድፉ ተተኮሰ፣
ከምንሸሽበቱ...
እየተከተለን   ውጊያው ተለኮሰ።
* * *         * * *         * * *
ይኸውና ሞርተር...
አዲሱን ቆርቆሮ  ባንድ'ዜ ቀደደ፣
እናት ታለቅሳለች...
የዘመናት ወዟ    ቤቷ እየነደደ።
ሰብአዊነት ጠፋ...
እንደ ውሻ ሆነ  የህዝቤ ክቡር ደም፣
ለቀብራችን እንኳን...
በነጋሢ ቄሳር  ለቅሶ አልተፈቀደም።
* * *         * * *         * * *
እርሻ የሄደ ሰው...
ቀንበር ተሸክሞ   በወጣበት ሲቀር፣
ምን እናደርጋለን...
ለላይኛው ጌታ   ከማዳኘት በቀር።

@getem
@getem
@getem
2025/06/27 16:33:25
Back to Top
HTML Embed Code: