Telegram Web Link
አለቀለት ያሉት
(በእውቀቱ ስዩም)

ከጅረት አጠገብ ፥ቆሞ የኖረ ዛፍ
መብረቅ ገነደሰው
አሁን ድልድይ ሁኖ፥ ያሸጋግራል ሰው ::

“አለቀለት” ያሉት፤ ተልኮው መች አልቆ
ቆሞ የጠቀመ፥ መላ አያጣም ወድቆ፤

@getem
@getem
@paappii
80👍11🔥8
ለምን ትመጫለሽ?

ወና መሆን ለምዷል
ባይተዋር ነው ሆዴ
ትራስ አቅፎ ማደር
ለምዶበታል ክንዴ።

ገላዬ ቀዝቅዟል
ልቤ ተሰቅዟል
እንስት ላለማመን
ዜሮ ነኝ ስተመን
ብትመጭም ከንቱ ነው
መመለስሽ ምንም
ስታወሪ አልስቅም
በእንባሽ አልቆዝምም
በድን ነኝ አልድንም ።

ለምን ትመጫለሽ?

የለሁም በድሮ
ሌላ ነኝ ዘንድሮ
ግዴ አይደለም ነገ
አትገርመኝም ጀንበር
ብራና ክረምቱ …
ቢዛወር ዓመቱ
ጨፍሬ አልደክርም
አልመታም አታሞ
ዓመት አንድ ቀን ነው
ለከሸፈ ታሞ ።

ለምን ትመጫለሽ ?

መምጣትሽ እንደ ቧልት
መመለስሽ ምንም ...


ይህንን እያልኩኝ
ብናገር ብገጥምም
ስትመጪ ስዳበስ
በጣት በመዳፍሽ
ያልኩትን ዘንግቼ
አዲስ ሰው ሆንኩልሽ።

አትሄጂም አይደለ ?🙄

By (ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@paappii
28😁5👍4🔥2🤩1
ካላንተ አልኖርም፤
ብኖርም አልደምቅም፤

እያልኩኝ ዘርዝሬ፤
ቃላትን መንጥሬ፤
አልሸነግልህም።

በጣም እንዲገርምህ፤
እንደዉም ልንገርህ፤

ከተራራቅን ወዲህ...

ካገኘሁት ጋራ፤
ካገኘሁት ስፍራ፤

ካገናኘኝ መንገድ፤
እንባዬ እስኪወርድ፤

ፈገግታ አበዛለሁ፤
ናፈቅኸኝ መሰለኝ...
አብዝቼ እስቃለሁ።

በዔደን ታደሰ
@ediwub
@getem
@getem
👍159🔥6😢2
2025/10/24 18:11:00
Back to Top
HTML Embed Code: