Telegram Web Link
‘’ይሄስ ቀን ባለፈ
ፅልመት በገፈፈ
ጥለሽኝ ብትሄጂ
በወጣሽ ከቤቴ
ጉዷ ባለቤቴ …
እህህ እያልኩኝ
እንዲህ እያማጥሁኝ
አደባባይ መኃል
የማልናገረው …
ብዙ ህመም ነበረ
ደሜን ያመረረው ።’’
በማለት የፃፈ
አንድ ባል ነበረ !
‘ምን ሆነህ ነው? ‘ ስለው
እየተማረረ …
'ላንተ ከተናገርኩ
ስንቱን እንደቻልሁት
ይሄን ግጥም ታድያ
ለምን ነው የፃፍኩት ? '

ብሎ መለሰልኝ !

(ፈርቷት ነው መሰለኝ🙄)

#ሚካኤል

@getem
@getem
@getem
29👍14😁12
Forwarded from Sami Alemu
ጣዕሙን የሚያውቀው
(ሳሙኤል አለሙ)

እንደ ሌላው
እንደ ሌላው፤
ሰርክ...
ጉንጭሽ ጋ አይደረስም
ረ------ጅም ነው ኬላው።

እያዩት...
ያስውላል።
ዕሮብ ለት
እያዩት...
ያፆማል።
አርብ ዕለት

እንደ እኛው
እንደ እኛው፤
አንቺ...
ከቶ አልተፈጠርሽም
በቀን ስድስተኛው።

ለምን...?
አይባልም።
አይጠየቅም።
እንዴት...?
አትለውም።
አትከራከርም።

ከአፈሩም ፣ ከውኃውም
ከእስትንፋሱም ፣ ሌላም
አለው... ሌላም...ሌላም
ሌላም አለው ያከለበት፤
ወተቱን እንዳ---
ፈሰሰ---
---በት
ጉንጭሽን የሳመው።
ጣዕሙን የሚያቀው።

ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu

@getem
@getem
👍3819🔥1🤩1
...........


ኢትዮጵያዬ ልጄን ውለጅ
አንደወጣ ቀረ ከደጅ
አፈር ምሶ የቀበረ
ውለጅ ይላል እያረረ
ከገጠሩ
     ከመንደሩ
          ከጎዳና ከድንበሩ
ለዘላለም ለማይደላው
ለምን ? ልጄን ልጅሽ በላው!


By @mad12titan

@getem
@getem
@getem
👍46😢2512🔥2
ህይወት ሞልታ አትሞላም
    ወይ ጎላ አትጎድል
ቁልፉ ስኬት ሲሆን
ውድቀት ዋነኛው ድል

ስቃይ እና ደስታ...ድሎት እና ችግር
       ምን ቢሆን ጣዕሙ
ሁሉም እርግፍ ይላል
       ባንቺ ከተሳሙ
"ደስታ ምንም ነው
ስቃይ አይታሰብም
ለእንደኔ እና እንዳንቺ
ብቻ ሳሚኝ አንቺ"

ብዬ ነበር ብዬ ነበር

ሆኖ አንገትሽ ሌላ ዘንዳ
እያየሁት ዛሬ ባይኔ
አትረሳህም እለዋለው
ለተጎዳው ባንቺ ጎኔ
የቀን ሳቄን ከሳቅሽ ጋር
እንዳልሳቅነው ተያይዘን
ሲመሽ ሲጠልቅ ሁሉም ነገር
ስንቱ ቀናት ደበዘዘን
አይኔ ይበቃል ለመረዳት
ባላወጣው የፍቅሬን ቃል
እንደወደድኩሽ ነው...
ድፍን ሐገር ያውቃል

ውድቀት ቢሆን ሲመሽ ጊዜው
ይበቃኛል ለቀኑ ዕድል
ህይወት እንደዚህ ነች
ወይ ሞልታ አትሞላም
ወይ ጎላ አትጎድል።

አሳየሽኝ ስቃይ ድሉን
ከዚም ከዛም እያጣቀሽ
ተኮሳትረሽ ያው ወርቅ ነሽ
ትገያለሽ ደግሞ ስቀሽ

አስረዳሁሽ በአይን ወሬ
ልብሽ ከቶ ምኑን ነቃ
አንቺም ሂጂ ይለይልኝ
እኔም ደግሞ ልርሳሽ በቃ።


ዮኒ
    ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍306😢3🤩2
የደስታ ሰማይ - በር መክፈቻ፣
ይገኛል መስሎሽ - በመብረር ብቻ፣

በተዋስሽው ክንፍ - ሽቅብ ስትመጥቂ፣
የደመና ሆድ ስትሰነጥቂ ፣
(ድንገት ከአየር ላይ)
በባለ ክንፉ - ስትነጠቂ፥

በማይገመት - በማይጠበቅ ፣
በእድል ጨፈቃ - በጊዜ ለበቅ፣
በጊዜ ለበቅ - በማይመከት፣
ስትገረፊ -
ደንግጠን ሽቅብ - ስንመለከት፣
ስንመለከት የማታ ማታ፥
ያዘልሽው ላባ -
የአንቺ እንዳልሆነ - ትዝ ያለሽ ለታ፥

ወዮ የዛን 'ለት - ለመንደራችን፤
ወዮ ለመሬት፥
ወዮ ለጆሮ - ወዮ ለዐይናችን፤

By Michael Minassie

@getem
@getem
@paappii
👍1918🔥2
..........


በመዳፌ ጠፈር ዳሳሽ
በኣይኖቼ ህዋን አሳሽ
አፈር ድንጋዩን መርማሪ
ፀሀይን በጥፊ ኣብራሪ
ጨረቃን በኩርኩም ቀባሪ
በውርቅያኖስ የምግሞጠሞጥ
ከንፋስ እጥፍ የምሮጥ
ጉም ዘጋኝ በመዳፌ
በኖህ መርከብ ቀዝፌ
ከጥፋት ውሀ ተርፌ
ቅንጥብ ዘንባባ ቀጥፌ
ኣዲስ ምዕራፍ የማበስር
ብኩርናዬን የማልሸጥ በምስር
በኮከብ ወደም ምጫወት
የማድር ከኣብርሀም ቤት
እንግዳ ያልሆንኩኝ እንግዳ
የሩቅ ዘመድ የቅርብ ባዳ
ከጲላጦስ ሸንጎ የምፋረድ
በደመና ይምራመድ
   ከሰባሰገሎች ኣንዱ
ወርቅ እጣን ከርቤ የገበረ
ንጉሱን ከበረት ኣይቶ እረኛውን ያከበረ
ከድንጋይ ከህጻናት ጋር
ሆሳእና ብሎ የዘመረ
እኔ ነኝ ብኩኑ ባሪያህ የጥበብህ ማሳያ
የሀዲስ ኪዳን ነብይ የኦሪት ሀዋርያ
   በሀሳቤ እሩቅ ተጎዝ
ባካሌ ከቅርብ የማድር
ቅንጣት እምነት የጎደለኝ
የሚነቅል የተራራን ስር
እንኳንስ በደመና ላይ
በጠፈር ሰማይ ምድሩ
ሸክም ሆኖ የከበደኝ
የኣካሌ ክፋይ ኣፈሩ
ጉም መጨበጥ የምመኝ
የእጄን መና ለቅቄ
በሀሳብ ከኣብርሀም ያደርኩ
ከመንገድ መሀል ወድቄ
በኮከብ ወደሙ ቀርቶ
ጠጠር ማንሳት ያቃተኝ
ፍቅር መስቀል ይመስል
በየቀን የሚያቃትተኝ
አንድ ቀን ጠግቦ ለማደር
ብኩርናዬን የምሰዋ
ባገሬ መኖር ያቃተኝ
እንኳን በጠፈር ህዋ
ኣንድ ጉንጭ ውሀ የምለምን
ውርቂያኖስ መሉ ተፍቼ
ከሰገባ የማድር
ከስልክ እንጨት ስር ተኝቼ
ከጥፋት ውሀ ታዳሚ
ወይ ኣልድን ወይ ሰጥሜ ኣልሞት
እስትንፋስ አልባ የሆነ
የምኖሮ ትርጉም ኣልባ ህይወት
የኖህም መርከብ የራቀኝ
ለምግብ ጥንብ ኣንሳ የነቀኝ
መሲህ ፍለጋ ወጥቼ
ነብይ ይዜ የተመለስኩ
ሰባሰገል ተብዬ
ከሄሮድስ ጭፍሮች ያበርኩ
እንኳንስ ፀሀይ በጥፊ
ውቧን ጨረቃ በኩርኩም
ዝንብ ሽ ማለት ያቃተኝ
ሀሳቤ ብናኝ እንደ ጉም
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
በህልሜ ሁሌ ከደጅህ
ስነቃ ከተራራው ስር
ደራሽ በሌለበት ምድር
በሲቃ ድምጽ የምጣራ
ከመብረቅም በሚያስፈራ
የቅንጣት እምነቴ ተራራ ኣነቅል ቢለኝ
ተራራ ያሸከመኝ
ከገነት ያላደርኩ ከሲኦል ያልገባው
መሲሁን ጠቋሚ ኣንድ ኮከብ ያጣው
ወይ ድኜ ኣልድን ከስሜ አልጠፋ
ከፈራጅ ችሎት ዳኛ የማስከፋ
እኔ ነኝ ብኩኑ ፍጡርህ
ወድቄ ያለው ከግርህ
ፍቅርህን የምሻ ልቤን ኣሽችቼ
ልክ እንደ ኣይሁድ ጎኑን ወግቼ
ከእቅፍህ ውስጥ ማደር የምመኝ
ብኩኑ ልጅህ
ባሪያህ እኔ ነኝ


   By  @Mad12titan

@getem
@getem
@getem
👍3116😱5🔥3
ድልድይ ቢሆን ልብህ
ወደ ህይወት መሄጃ
ሞቼ አለመቅረቴን
መነሳቴን እንጃ
ማሻገርህን ያየ
ቢመሰክርም ሰው
ትረፍ ለሌላ ሟች
እኔ እንደሁ ሳይህ ነው
የምትፈራርሰው

By ዘማርቆስ

@getem
@getem
@paappii
21👍16🔥2
የዚች አለም ችግር
     ሁሌም ወደኋላ
የተራበው ቀርቶ
     የጠገበው በላ
እንዲህ ነው ምሳሌው
ሲተነተን ፍቺው
አንቺም የሌላ ሰው
እኔም ደግሞ ያንቺው

አወይ የኔ ህይወት
አወይ የኔ ተድላ
የማፈቅርሽ እኔ
የሚበላሽ ሌላ

ዮኒ
     ኣታን @yonatoz

@getem
@getem
@getem
👍3811😁9🔥5😱1🤩1
👍54🔥2😱1
አቦ.. እግዜር ተወኝ
'
'
ለምንድነው የማትጠራኝ
ለምንድነው የጠፋሁት
ቅዳሴው ሲሰማኝ
ቢራ ቤት ነው የነበርኩት

ለምን ከፋኝ በጭስ መሃል
ሳየው ያንተን የአምላክ ምስል ፣
መከራም እንዲህ ነው
ባለበት እዳ ነው አምላኩን የሚስል ፣

በቢራው አራፋት
በጃምቦው ብርጭቆ
ሀዘንህ ሲታየኝ ፣
ጨልጬ ብጠጣው
የማላይህ መስሎኝ ፣

ባዶ እስኪቀር የስካሬ ሞራል ፣
በማላውቀው ታምር
በማውቀው ቤተስኪያን
ድምፅህ ልጄን ይላል ፣

ለምን

ለምን እኔን ጠራህ
አሉህ አይድል በአጥርህ ፈርጡ
እነሱን ያዛቸው እኔን እንደሆነ
የለሁ ካጥረ ገጡ ፣

ተወኝ ልጠጣበት
ተወኝ አታሰማኝ የእርጋታህን ቃል ፣
ሙዚቃ ስጨምር ጭፈራ ሳበዛ
ለሽንት እንደወጣሁ
ያንተ ድምፅ ይሰማል ፣

ለምን...?እኔ መረጥክ
ተወኝ እግዜር ባክህ
ተወኝ ተወኝ አቦ ፣
አንድ በግ ስትፈልግ
ጠፍተው እንዳይቀሩ
ያሉልህ በደቦ ፣

እንዲህ ስናገር በሲጃራው መሃል
በጭሴ ውስጥ ቅርፁ
ያንተን መልክ ያሳያል

በስካሬ መሃል ይታየኛል እኔ
የሰከረ አምላክ የሰከረ ምስል ፣
አምላክም እንዲህ ነው
ባለበት እዳ ነው ጠፊ ልጁን ሚስል ፣

'
ግዕዝ ሙላት 🦘
@geez_mulat

@getem
@getem
@getem
👍5319😢11🤩3👎2🔥2🎉1
በድቅድቅ ጨለማ ወንበሬን አውጥቼ

መሀል መሬት ላይ ጨረቃ እሞቃለው

ወፎች ሲዘምሩ ቁጭ ብዬ አደምጣለው

ወደ ላይ ቀና ስል...

የጨረቃ ብርሃን አይኔን ይወጋኛል

ሙቀቷ እሳት ሁኖ በላብ ያጠምቀኛል



           ''አ      ዎ!      አሁን ይበቃኛል''

          ''ከዚ በላይ ብቆይ ምቀልጥ ይመስለኛል''

          ብዬ አሰብኩና...



ጥላውን ፍለጋ ወደ ቤቴ ገባው

ከቆጡ አልጋዬ ለመተኛት ሳስብ...

የ አልጋው ዝቅታ ሰላም ስላልሰጠኝ

ከፍ ካለው ቁርበት ከላይ ተንጋለልኩኝ..



አይኖቼን ገልጬ ድብን ብዬ ተኛሁ

ሰዉን እየረበሽኩ በደንብ አንኮራፋሁ

እንቅልፌ ሲመጣ ...

እንቅልፌ ሲመጣ ከ ሰመመን ነቃሁ;




          ነግቷል መሰለኝ ሰማዩ ጨልሟል

          ኮከቦችም አሉ ደመናም ደምኗል

          ሊዘንብ ነው መሰል ልብሴን ቶሎ ላስጣ

          ዝናብ ዘንቦ ሳያልቅ ፀሀይዋ ሳትመጣ::



    ዘይድ ሁሴን
   ታህሳስ -15 -2017

@getem
@getem
@getem
60👍46😁27🤩9👎3🔥1
ሎጥ ነሽ
🦘

ቅጥልጥል ፥ብግንግን ፥እርር እምር  ፤
ዝምም፥ ልምም ፥እድር ፤
እፍን፥ እምቅ ፥ላጀብ ፥ብድር ፤
ለወዝ ላይላፋ ፥ለዳገቱ ስብር ፤
ተንስኢ ላስነግር ፥በዋጉ ሰው አንዲር ፤
እኛ...እ'ድር..እኔ ላብር ፥ለራስ ሳድር ፣
ላለም ደረት ንፍት፥ ለራስ አንገት ስብር

'
'
ላክል ፤
ባክል ፤

ላንስ ፤
ዳንስ ፤

አይሆን ላይሆን ፥
ላገር ስሪያ ማሰሪያ ፣
መች አምሳሏ ነበረ፥
ያከበረችው ጥያ ፣
ቀጥ ብላ ማንጋጠጥ፥
ሎጥነሽ ወይ ?ኢትዬጵያ....
'
'
ግዕዝ ሙላት 🦘
@geez_mulat

@getem
@getem
@getem
👍308🔥5😱3
“ስኬተኛ ማነው ?”
ብዬ ጠየቅኋቸው
ታዋቂ አመጡልኝ
ይሄ ነው መልሳቸው ።

አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …

አሳዩኝ ከበርቴ
ባለ ንብረት ፣ ነዋይ
እንደዚህ ያለውን
ቀና ብዬም አላይ።

አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …

አመጡልኝ ምሁር
ፊደል የቆጠረ
የተመራመረ
ይሄም አልሰመረ።

አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …

ጠሩ ባለ ጥበብ
በጥሁፍ በቅኔ
ያስገኘልን ረብ
(በርግጥ ጥሩ ነበር
እንደዚህ ሲታሰብ )
መልስ ግን አይደለም።

አልተዋጠልኝም !
አልተረቱልኝም …

አንድ አጩ ቀጥሎ
ጽድቁን አደላድሎ
ያናናቀ ሞቱን…
የቃል ጥሩር ለብሶ
ያስታጠቀ ነፍሱን…

አገኙብኝ መልሱን !

(ሚካኤል አ)

@getem
@getem
@getem
👍4530🤩3
ወዳንቺ እዘረጋለሁ!
ባድግ ብዬ
ባውቅ ብዬ
አንዳች ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ!

መቃብር ቤቴን ማሞቂያ
የሙት መንደሬን ማድመቂያ
ካለፉም ወዲያ መታወቂያ…
የምትሆን
አንድ ሀተታ
አንድ እውነታ
የህይወትን ምናልባት
የመኖርን እልባት
አውቃት ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ!

ከሰማይ በታች አዲስ ነገር
ከምድር ከፍ ብሎ የሚነገር
“የከንቱ ከንቱ” የምትባል
የአላዋቂን ፈላስፋ
በአፍጢሙ የምትደፋ
ስታቅፊ ዐለም እንደሚጠቀለል
ስትገፊም ሰውነት ከላባ እንደሚቀል
ስትስሚ ኢምንት እንዲሆን ጠፈሩ
ስትነክሺም ማንነት እንደሚበተን አፈሩ…

ይቺን ምስጢር ተረድቼ ባልፍ ብዬ
የህይወት መስመሬን ማንቂያ
ውሎ አዳሬን መደበቂያ
ተስፋ ህልሜን መታረቂያ
የምትሆን
አንዲት ሁነት
አንዲት ኪነት
የመክረምን ፍልስምና
ከንቱነት ላይ ውብ አድርጋ ሸምና
ታውቀኝ ነበር እንድልባት
ወዳንቺ እዘረጋለሁ ካልተረሳሁ ምናልባት።

By Yadel Tizazu

@getem
@getem
@paappii
👍3016
@getem
     @getem
          @getem
👍272
ለተለያዩ የማስታወቂያ፣ የዘፈን ክሊፕ እና ድራማዎች ስራዎች በአዲስ አበባ ውስጥ ብቻ የሚኖሩ ሰዎችን ካስት ማድረግ እንፈልጋለን። - እድሜያቸው ከ35-45 - ከ25-30 - ከ10-18 ያሉ ወንዶችን እና ሴቶችን በአስቸኳይ እንፈልጋለን። የሚከተሉትን በቴሌግራም ይላኩልን። - 1 ሙሉ ሰውነት የሚያሳይ ፎቶ - 1 ከወገብ በላይ - 1 ፈገግታ የሚያሳይ ፎቶዎችን - ስም ስልክ እና እድሜ በሚከተለው አድራሻ ይላኩልን። https://www.tg-me.com/Ribki30 ስልክ የሚደወልላቸው ለስራው ሲመረጡ ብቻ ስለሆነ በትዕግስት ይጠብቁ ዘንድ እንጠይቃለን።
👍193
ነበርሽ ፤…
የጠዋት ፀሐይ
በቀስታ ደም የምታሞቅ ።

ነበርሽ ፤…
የዓለት ስር አበባ
ድንጋይ ተደብቆ የሳቃት ።

ነበርሽ ፤…
ልሙጥ የሻይ ብርጭቆ
ወገብሽ የሚያቃጥል ፤

ቀስ አድርገው
አለሳልሰው
እፍፍ ብለው
ልካቸው ድረስ አብርደው
በከንፈርሽ የሚቀምሱሽ ፤

ነበርሽ ፤…
ለሕይወት ተኩል
ለሞት አምስት ጉዳይ ።

ቴዎድሮስ ካሳ

@getem
@getem
@getem
👍478👎3🤩3
ዕዳዋ የለብኝ~አበዳሪ አይደለች
ደም አልተቃባችኝ~ዘመድ አልገደለች
አላስቀየመችኝ~ተናግራ ክፉ ቃል
እንከን አጣሁ ተብሎ~ሰው እንዴት ይራቃል?
ወይ አይደለች ሻማ~ጨርሼ አላነዳት
አንዳች አልሰረቀች~እንዳላሳድዳት
እንዴት ብለከፍ ነው~ስትርቅ የምወዳት?

ዘማርቆስ
By @wogegnit

@getem
@getem
@getem
56👍26😢6
❝ ሣቅ ተከሽኖ ግጥም ተመጥኖ ❞ ታላቅ የመክፈቻ ፕሮግራም በግዮን ሆቴል !

  ዘሃ ኢቨንትስ ከግዮን ሆቴል ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው የኪነጥበብ ምሽት ፤ 4ተኛ መድረኩን አርብ ታህሣሥ 25 - 2017 ዓ.ም ምሽት ከ10 : 30 ጀምሮ ያቀርባል ።

ጋሽ አያልነህ ሙላት ፣ ሠዓሊ እሸቱ ጥሩነህና ኮሜዲያን ደረጄ ሀይሌ የክብር እንግዶቻችን ናቸው ።

  የምሽቱ ፈርጥ ልዩ የክብር እንግዳችን አርቲስት ዓለም ፀሀይ ወዳጆ ናት ።

ደራሲና ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም እና ሰለሞን ሳህለ ውብ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ።

  ኮሜዲያን ናሆም በየነ መድረኩ ላይ ይደምቃል ፤ የአብጸጋ ተመስገን የተከሸነች ወግ አዘጋጅቷል ፤ ፈገግታ ባንድ ጥዑም ሙዚቃዎቹን አሰናድቷል ፣ ሒስ ፣ አጭር ፊልም ፣ ስዕልና ሌሎች ብዙ ትርዒቶች ተዘጋጅተዋል ።

  ለበለጠ መረጃ በ 0935697143 ይደውሉ ።

የ YouTube ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ 👍

https://youtube.com/channel/UC9ItbVvxXMLV7QIT-rCJyTg?si=Mj5GlhjsE1ZvBtjM

@getem
@getem
👍20🤩32
አቀርቃሪ አሉኝ፣
ቀና ብሎ ማየት መራመድ ሲሸሸኝ፣
ሊያብድላት ነው አሉኝ፣
በቁሜም በሕልሜም ቅዠት ሲረብሸኝ።

ሊረታ ነው አሉኝ፣
ስንቀጠቀጥላት ስሟ ትዝ ሲለኝ፣
ትክክል ናቸው ወይ፣
እኔ ከምወስን እናንተ ንገሩኝ?

By @eyadermoges1

@getem
@getem
@getem
30👍17🤩7👎3😁2
2025/07/11 18:59:46
Back to Top
HTML Embed Code: