አታውቂም
(kerim
የተዋቡ አይኖችሽ ካልተፋብኝ እቶን
አፍሽ ካልጠራብኝ የርግማን መዓቱን
በዚህ ሁሉ መሀል
መዓዛሽን ካልማግኩት
ታድያ ምኑን ኖርኩት?
-
-
-
አለም ብትጠፋ
ካንቺ እጦት አይከፋ
አታውቂም
መኖርሽ እንደሚያኖረኝ
አታውቂም
ከሌላም አይቼሽ ደስታ እንደሚያሰክረኝ
ከኔ ደስታ ይልቅ ስለ አንቺ ደስታ
የልቤ መሻት ነው ስላንቺ አዬመታ
አላውቅም
ቅናት ይሉት ስሜት ወዴት ተሰወረ
ልቤስ ስለ እጦቱ ስለምን ታተረ?
(እንዳልኩሽ አላውቅም)
By @poem2513
@getem
@getem
@paappii
(kerim
የተዋቡ አይኖችሽ ካልተፋብኝ እቶን
አፍሽ ካልጠራብኝ የርግማን መዓቱን
በዚህ ሁሉ መሀል
መዓዛሽን ካልማግኩት
ታድያ ምኑን ኖርኩት?
-
-
-
አለም ብትጠፋ
ካንቺ እጦት አይከፋ
አታውቂም
መኖርሽ እንደሚያኖረኝ
አታውቂም
ከሌላም አይቼሽ ደስታ እንደሚያሰክረኝ
ከኔ ደስታ ይልቅ ስለ አንቺ ደስታ
የልቤ መሻት ነው ስላንቺ አዬመታ
አላውቅም
ቅናት ይሉት ስሜት ወዴት ተሰወረ
ልቤስ ስለ እጦቱ ስለምን ታተረ?
(እንዳልኩሽ አላውቅም)
By @poem2513
@getem
@getem
@paappii
❤31👍20👎1🔥1😢1
ድንገት ያገኘሁት የድሮ ግጥሜ
____
ጀምበር ገባች ፥ መሸ
ያጸዳሁት ቤቴም ፥ መልሶ ቆሸሸ
አልጠፋም መብራቱ
አልተበላም 'ራቱ
አሁንም ክፍት ነው በርና መስኮቱ ።
ለቁር ተጋለጠ ፥ ጓዳዬ እንደ ውጪው
መቼ ነው የምትመጪው ?
መጽሐፍ ገለጥኩና መልሼ ዘጋሁት
ልጽፍ አሰብኩና ብዕሬን ወረወርኩት
መቆም መንጎራደድ
መቆም መንጎራደድ
መቆዘም መተከዝ ፥ በሐሳብ መሰደድ
ደርሶ ብንን ብንን
ደሞ ቁጭ ብድግ
ካንቺ ውጭ አላውቅም ምን እንደምፈልግ ።
ምኞት ነው ያለኝ ፥ ዝም ብሎ ምኞት
ወይ የማያኖር ፥ ወይ የማያስሞት
ትመጫለሽ እያልኩ በጉጉት ከምኖር
ምናለ በሞትኩኝ ለአንድ ለስድስት ወር ።
@getem
@getem
@paappii
By Hab Hd
____
ጀምበር ገባች ፥ መሸ
ያጸዳሁት ቤቴም ፥ መልሶ ቆሸሸ
አልጠፋም መብራቱ
አልተበላም 'ራቱ
አሁንም ክፍት ነው በርና መስኮቱ ።
ለቁር ተጋለጠ ፥ ጓዳዬ እንደ ውጪው
መቼ ነው የምትመጪው ?
መጽሐፍ ገለጥኩና መልሼ ዘጋሁት
ልጽፍ አሰብኩና ብዕሬን ወረወርኩት
መቆም መንጎራደድ
መቆም መንጎራደድ
መቆዘም መተከዝ ፥ በሐሳብ መሰደድ
ደርሶ ብንን ብንን
ደሞ ቁጭ ብድግ
ካንቺ ውጭ አላውቅም ምን እንደምፈልግ ።
ምኞት ነው ያለኝ ፥ ዝም ብሎ ምኞት
ወይ የማያኖር ፥ ወይ የማያስሞት
ትመጫለሽ እያልኩ በጉጉት ከምኖር
ምናለ በሞትኩኝ ለአንድ ለስድስት ወር ።
@getem
@getem
@paappii
By Hab Hd
❤73👍34😁26🤩6😢4
............
ትከተይኛለሽ ብዬ ስለማስብ
በሄድኩበት ሁሉ እጅ እንድሰበስብ
መዞር እፈራለሁ
ዞሬ ያጣሁሽ እንደው
ብቻዬን መሆኔስ ምን ነጻነት አለው
ትከተይኛለሽ
በአለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማስብ
ትዝታ እንደ ገላ ይዳብሰኝና
አለሄደችም ብዬ
ልቤን አጽና..ና...ና
ጀርባዬን አምናለሁ
አንቺ ከነጠቀኝ
እውነት ምን ዋጋ አለው
ያልኖሩበት ነገ ተስፋው ምን ሊጠቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቀም
በሄድኩበት ሁሉ
በሳር በገደሉ
እረኛ ያጣ በሬ በኮቴው ሲያደቀው
አንቺን ነሽ በዬ ነው በተስፈ የምስቀው
ጠረንሽ ቢጠፋኝ
ሽቶ ያኮፈሳት ላባም ሴት ፈልጌ
በሴሰኛ ስሜት ጭኗን ተፋትጌ
ሲረካ መንፈሴ
አንቺ ነሽ ብሎ ነው
የሚስቀው ጥርሴ
መቼም ለመኮነን
መዞርም አያሻም ሀጥያት በዝቷል ከፊት
የከፋኝ ጊዜ ነው የማቀው ያንቺን ፊት
ትከተይኛለሽ
ባለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማምን
እንትን ተመኝቼ ጌታዬን ስለምን
የሷንም እላለው
ይሰማሽ እንደሆን
እንጃ ምን አውቃለሁ
መሄድ እንደቀላል
መንገዱን ሲያረዝመው
መድረስ አይናፍቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቅም
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
ትከተይኛለሽ ብዬ ስለማስብ
በሄድኩበት ሁሉ እጅ እንድሰበስብ
መዞር እፈራለሁ
ዞሬ ያጣሁሽ እንደው
ብቻዬን መሆኔስ ምን ነጻነት አለው
ትከተይኛለሽ
በአለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማስብ
ትዝታ እንደ ገላ ይዳብሰኝና
አለሄደችም ብዬ
ልቤን አጽና..ና...ና
ጀርባዬን አምናለሁ
አንቺ ከነጠቀኝ
እውነት ምን ዋጋ አለው
ያልኖሩበት ነገ ተስፋው ምን ሊጠቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቀም
በሄድኩበት ሁሉ
በሳር በገደሉ
እረኛ ያጣ በሬ በኮቴው ሲያደቀው
አንቺን ነሽ በዬ ነው በተስፈ የምስቀው
ጠረንሽ ቢጠፋኝ
ሽቶ ያኮፈሳት ላባም ሴት ፈልጌ
በሴሰኛ ስሜት ጭኗን ተፋትጌ
ሲረካ መንፈሴ
አንቺ ነሽ ብሎ ነው
የሚስቀው ጥርሴ
መቼም ለመኮነን
መዞርም አያሻም ሀጥያት በዝቷል ከፊት
የከፋኝ ጊዜ ነው የማቀው ያንቺን ፊት
ትከተይኛለሽ
ባለሁበት አለሽ
ብዬ ስለማምን
እንትን ተመኝቼ ጌታዬን ስለምን
የሷንም እላለው
ይሰማሽ እንደሆን
እንጃ ምን አውቃለሁ
መሄድ እንደቀላል
መንገዱን ሲያረዝመው
መድረስ አይናፍቅም
አለሽ ብዬ አምናለሁ
ዞሬ ግን አላቅም
By @mad12titan
@getem
@getem
@paappii
👍39❤24🔥4😢1
ስርአት!
(የሞገሤ ልጅ)
አንተ የእኔ ምትክ፣
የእራሴ መታያ የአብራኬ ክፋይ፣
እንኳንም ወለድኩህ፣
የፈጠረህ ፈቅዶ ዐይኔን በዐይኔ እንዳይ።
አንተ ግን ቸኩለህ፣
መልሰህ መሄድህ ወደመጣህበት፣
ምን ሰይጣን መክሮህ ነው፣
ያረከኝ በሃዘን እንድኮረማመት።
የውልህ ልንገርህ፣
ተወልዶ ማረፉ በሰላሳኛ ቀን፣
ላንተም ኪሳራ ነው፣
ለኔም የእድሜ ልክ ስብራት ሰቀቀን።
ያንተን ጉዳት ላርዳህ፣
ለገነት ከሆነ ሞትህ በዚህ እድሜ፣
እኔም አልገባሁም፣
ካንተ በላይ ኖሬ 55 ቀን ጾሜ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
(የሞገሤ ልጅ)
አንተ የእኔ ምትክ፣
የእራሴ መታያ የአብራኬ ክፋይ፣
እንኳንም ወለድኩህ፣
የፈጠረህ ፈቅዶ ዐይኔን በዐይኔ እንዳይ።
አንተ ግን ቸኩለህ፣
መልሰህ መሄድህ ወደመጣህበት፣
ምን ሰይጣን መክሮህ ነው፣
ያረከኝ በሃዘን እንድኮረማመት።
የውልህ ልንገርህ፣
ተወልዶ ማረፉ በሰላሳኛ ቀን፣
ላንተም ኪሳራ ነው፣
ለኔም የእድሜ ልክ ስብራት ሰቀቀን።
ያንተን ጉዳት ላርዳህ፣
ለገነት ከሆነ ሞትህ በዚህ እድሜ፣
እኔም አልገባሁም፣
ካንተ በላይ ኖሬ 55 ቀን ጾሜ።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@getem
😢31👍23❤8👎3😱2
..........
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የቸረች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በነጭና ጥቁር
በበዛበት ህይወት
ተፈጥሮን በረሳ ቀለም በናፈቀው
ጸሀይ አይደለችም
ገላሽን አቅፎ ነው ጓዳዬ የሞቀው
ቤቴ የደመቀው
ያልተጋሩት እቶን
የሚማገዱበት ልክ እንደ ዕሳት ዕራት
ሞቶ የመኖር ብስራት
በብርሀኗ ውስጥ በሚንቦገቦገው
ፍቅርን ልፈልገው
ስዳራሽ እያዩ
ሞቶ ነው እያሉ ህያዋን ሲለዩ
ለዚህ ነው የምልሽ
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የሰጠች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በሳት ላልተዳሩ
ላልተፋቀሩ!
ቅሉ አይገባቸውም የቀለም አደሱ
የፍቅራቸው ምሱ ?
ዕሳት ዕራት መሆን ጸጋ መች ታደለ
ከሚነድ ወላፈን ጠብታን ያከለ
ለዕሳት ነፍስ የዘራ ስጋውን ሰውቶ
ጸሀይ አይደለችም
ውበቷ ብቻ ነው የሚታየው ጎልቶ
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የቸረች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በነጭና ጥቁር
በበዛበት ህይወት
ተፈጥሮን በረሳ ቀለም በናፈቀው
ጸሀይ አይደለችም
ገላሽን አቅፎ ነው ጓዳዬ የሞቀው
ቤቴ የደመቀው
ያልተጋሩት እቶን
የሚማገዱበት ልክ እንደ ዕሳት ዕራት
ሞቶ የመኖር ብስራት
በብርሀኗ ውስጥ በሚንቦገቦገው
ፍቅርን ልፈልገው
ስዳራሽ እያዩ
ሞቶ ነው እያሉ ህያዋን ሲለዩ
ለዚህ ነው የምልሽ
ቀለም
ጸሀይ አይደለችም የሰጠች ተፈጥሮን
ውበቷ ነው እንጂ ጨለማን ሰውሮን
በሳት ላልተዳሩ
ላልተፋቀሩ!
ቅሉ አይገባቸውም የቀለም አደሱ
የፍቅራቸው ምሱ ?
ዕሳት ዕራት መሆን ጸጋ መች ታደለ
ከሚነድ ወላፈን ጠብታን ያከለ
ለዕሳት ነፍስ የዘራ ስጋውን ሰውቶ
ጸሀይ አይደለችም
ውበቷ ብቻ ነው የሚታየው ጎልቶ
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍27❤15🔥3
በየሰፈሩ ሰፍረን
በየአጥሩ ተንጠልጠለን
አድዋን ያህል
አድባር ጥለን
ካምና ርቀን
ዛሬን ንቀን
ነገን ናፍቀን
መራመዱ እየጨነቀን
በየጥጉ ተናንቀን
ቀኑን ማሰብ እስኪያስፈራው
የታለ ባለፈረሱ?
የታለ ባለ ባንዴራው?
የታል የትውልድ አደራው?
አድዋን ያህል ትልቅ ጥለት
አድዋን ያህል ህብር ቀለም
ክብሩ ገብቶን
ፍሬው ታይቶን
ሳንደምቅበት ተያይዘን
ሳንኮራበት ታሪክ መዘን
በጊዜ ፊት እንዲህ ፈዘን
ያከበረን ያስከበረን
ኩራት ሆኖ ያዘለቀን
አድዋ ያህል ዘ ላ ለ ም ቀን
ስሙን መጥራት
ድሉን ማሰብ ተናነቀን?!
By Thomas lemma
@getem
@getem
@paappii
በየአጥሩ ተንጠልጠለን
አድዋን ያህል
አድባር ጥለን
ካምና ርቀን
ዛሬን ንቀን
ነገን ናፍቀን
መራመዱ እየጨነቀን
በየጥጉ ተናንቀን
ቀኑን ማሰብ እስኪያስፈራው
የታለ ባለፈረሱ?
የታለ ባለ ባንዴራው?
የታል የትውልድ አደራው?
አድዋን ያህል ትልቅ ጥለት
አድዋን ያህል ህብር ቀለም
ክብሩ ገብቶን
ፍሬው ታይቶን
ሳንደምቅበት ተያይዘን
ሳንኮራበት ታሪክ መዘን
በጊዜ ፊት እንዲህ ፈዘን
ያከበረን ያስከበረን
ኩራት ሆኖ ያዘለቀን
አድዋ ያህል ዘ ላ ለ ም ቀን
ስሙን መጥራት
ድሉን ማሰብ ተናነቀን?!
By Thomas lemma
@getem
@getem
@paappii
👍39❤32🔥8😢3🤩1
"ድንቄም ቆራጭ"😁😁😁
"""""""""""""""""""""
ከልብ ተሠርንቆ ልውጣ አልውጣ እያለ፤
ያስገባንው ነገር ከአቅም ካየ"ለ።
ይውጣ ምናባቱ ልብን ከበሽተ ካላረገን ደህና፤
አንቅሮ መትፋት ነው ከሚያሳጣን ጤና።
ሰውም እንደዚህ ነው፥
የልባችን እሳት የልባችን ንዳድ ለሱ ከበረደው፤
የፍቅራችን ሙቀት ቀዝቅዞ ከታየው።
ምን ሊያረግ ይቀመጥ ሊሆነን ፈተና፤
ከተመቸው ይሂድ መንገዱ ያውና።
የልባችን መሻት መሻቱ ካልሆነ፤
የመውደድ ፍላቱ ከሱው ከተነነ።
ልቡ የሸፈተን አስረን ላናስቀረው፤
መንገዱ ያውና ይሂድ ከተመቸው።
ብዬ እፎክርና ዝቼ በሃሳቤ፤
አስሮ ያስቀመጠው ይሸነፋል ልቤ።
አድሮ ልመና...ተው ፍታኝ
የቃልህ እስረኛ ነኝ🥹
ምን ላርግ ከእኔ ዘንድ አልሰራም
✍ጦቢያ
ቀን 21
የካቲት፦2017-አርብ
@getem
@getem
@getem
"""""""""""""""""""""
ከልብ ተሠርንቆ ልውጣ አልውጣ እያለ፤
ያስገባንው ነገር ከአቅም ካየ"ለ።
ይውጣ ምናባቱ ልብን ከበሽተ ካላረገን ደህና፤
አንቅሮ መትፋት ነው ከሚያሳጣን ጤና።
ሰውም እንደዚህ ነው፥
የልባችን እሳት የልባችን ንዳድ ለሱ ከበረደው፤
የፍቅራችን ሙቀት ቀዝቅዞ ከታየው።
ምን ሊያረግ ይቀመጥ ሊሆነን ፈተና፤
ከተመቸው ይሂድ መንገዱ ያውና።
የልባችን መሻት መሻቱ ካልሆነ፤
የመውደድ ፍላቱ ከሱው ከተነነ።
ልቡ የሸፈተን አስረን ላናስቀረው፤
መንገዱ ያውና ይሂድ ከተመቸው።
ብዬ እፎክርና ዝቼ በሃሳቤ፤
አስሮ ያስቀመጠው ይሸነፋል ልቤ።
አድሮ ልመና...ተው ፍታኝ
የቃልህ እስረኛ ነኝ🥹
ምን ላርግ ከእኔ ዘንድ አልሰራም
✍ጦቢያ
ቀን 21
የካቲት፦2017-አርብ
@getem
@getem
@getem
👍44❤16
በግድ የፈለቀች
ጠብ አደረኩ እምባ
"በቃ ይፍቱኝ አባ"
ይሄ ነው ሀጥያቴ
ከእግሮ ስር ያራቀኝ
ምን ልስራ
ምን ላድርግ
አዚሙ እንዲለቀኝ?
አዩኝ ትክ ብለው
ቀረቡኝ
ቀረብኩኝ
መስቀል ተሳለምኩኝ
ከዛ ግን አላውቅም
ካልቾ .. ጥፊ .. ጨምቧ
".. ያማል እኮ አባ"
"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"
"አዎን አባ ይፍቱኝ"
አገላብጠው መቱኝ።
"ይኸው የኔ ጎበዝ
መንፈሰ ከርታታው
አንዲህ ነው ሚፈታው"
እስቲ ዝቅ
እስቲ ዝቅ
ከዛ አንዴ ድልቅ!
ወይኔ መድሃኒአለም
እጃቸው እንዴት ያማል፤
"የኔ ልጅ ይሰማል?"
በተዋጠ ልሳን
"አይሰማም አባ"
በድጋሚ ጨምቧ
የጠገበ ልጄን
ሳጠምቅ አልገኝም
እስቲ ከፍ ጨምቧ
ያንተማ አይጠፋኝም
እስቲ ከፍ ጥብስ
እስት ዝቅ ጨምቧ
"ይበቃኛል አባ!"
"ምኑ ነው ሚበቃህ?"
የኔን ትንሽ ዱላ
ከሳር የቀለለ ፤
ንፅህና የታለ?
ድንግልና የታለ?
ከፍ ዝቅ ክልትው
ሸሸሁኝ በዳዴ ፤
አባ ይቅር በሉኝ
ተሳሳትኩኝ አንዴ
"ሰው አይደለው እንዴ?"
እሱማ ሰው ነበርክ
በእግዜር የሚፀና
ክህነቱስ ግና?
ድቁናውስ ግና?
ቀና በል ያዝ ጧ!
አትወራጭ ፡ ድርግም!
"አይለምደኝም ዳግም"
እሱን ለግዜር በለው
ይኸው የኔ ፋንታ ፤
ከፍ ዝቅ ድርግም
"እባኮት የኔታ"
"ይቅር በሉ ይላል
ወንጌሉን አይርሱ
መመለሴን አይደል
ሚፈልገው እሱ?"
"እሱማ መተሃል
ዱላ ለወጉ ነው
ዳግም እንደማትሄድ
.. ለማረጋገጫ ፤
"ይሄ ሁሉ እርግጫ?"
"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"
"እሺ ይፍቱኝ አባ"
ቀና ሳብ ጨምቧ
ከዛን ተረጋጉ
አየር ሳብ አረጉ
"ይኸውልህ ልጄ
አድገህ አይደል በእጄ
አይንህ ልቤን ወጋው
ከእሳት ሳይህ ሰጋው
ለዛ ነው የተቆጣው
እስኪ እጅህን አምጣው"
"ይኸው" ብዬ አቀበልኩ
"ለበረከት እንጂ
አይሆኑም ለመርገም፤
እንካ ዳዊት ድገም
ይበቃል የስካሁን
አንተን ሳይ ፈራለው
.. ከእቶን ከእሳት፤
ከንግዲህ አትሳሳት"
ብለው አሳለሙኝ
ዝቅ ስል አመመኝ
ለንስሃ ያልወጣ
እምባዬ ቀደመኝ
ዱላ ያጀገነው
ልቤን ብሶት ገፋው
ስብርብር እያልኩኝ
ከእግራቸው ተደፋው
"አሳፈርኮት አባ
አሰደብኮት አባ
አስተምረው መና
አሳደገው መና
አልበሰልኩም ገና
አልበቃውም ገና
ይቅር በሉኝ አባ
አፉ በሉኝ አባ"
ብዬ ጥምጥም አልኩኝ
ጉልበታቸው ግርጌ
ጎትተው አነሱኝ
አቀፉኝ ሳብ አርገው፤
"ይሄን ልጅነት ነው
ጌታ ሚፈልገው"።
አሁን ለርሱ ስጋ
ባለበሰህ ፀጋ
ስለምትበድለው
ግፍን ስትሰበስብ ፤
እኔማ በእጄ ነህ
ለሞተልህ አስብ!።
አልቅስ እዘን እንጂ
ተስፋ ለማይቆርጠው
የምትድንበትን
ምክንያት ሲገጣጥም ፤
የጠገብክ እንደሆን
እናትህ ሆድ እንኳን
እኔን አታመልጥም!።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ጠብ አደረኩ እምባ
"በቃ ይፍቱኝ አባ"
ይሄ ነው ሀጥያቴ
ከእግሮ ስር ያራቀኝ
ምን ልስራ
ምን ላድርግ
አዚሙ እንዲለቀኝ?
አዩኝ ትክ ብለው
ቀረቡኝ
ቀረብኩኝ
መስቀል ተሳለምኩኝ
ከዛ ግን አላውቅም
ካልቾ .. ጥፊ .. ጨምቧ
".. ያማል እኮ አባ"
"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"
"አዎን አባ ይፍቱኝ"
አገላብጠው መቱኝ።
"ይኸው የኔ ጎበዝ
መንፈሰ ከርታታው
አንዲህ ነው ሚፈታው"
እስቲ ዝቅ
እስቲ ዝቅ
ከዛ አንዴ ድልቅ!
ወይኔ መድሃኒአለም
እጃቸው እንዴት ያማል፤
"የኔ ልጅ ይሰማል?"
በተዋጠ ልሳን
"አይሰማም አባ"
በድጋሚ ጨምቧ
የጠገበ ልጄን
ሳጠምቅ አልገኝም
እስቲ ከፍ ጨምቧ
ያንተማ አይጠፋኝም
እስቲ ከፍ ጥብስ
እስት ዝቅ ጨምቧ
"ይበቃኛል አባ!"
"ምኑ ነው ሚበቃህ?"
የኔን ትንሽ ዱላ
ከሳር የቀለለ ፤
ንፅህና የታለ?
ድንግልና የታለ?
ከፍ ዝቅ ክልትው
ሸሸሁኝ በዳዴ ፤
አባ ይቅር በሉኝ
ተሳሳትኩኝ አንዴ
"ሰው አይደለው እንዴ?"
እሱማ ሰው ነበርክ
በእግዜር የሚፀና
ክህነቱስ ግና?
ድቁናውስ ግና?
ቀና በል ያዝ ጧ!
አትወራጭ ፡ ድርግም!
"አይለምደኝም ዳግም"
እሱን ለግዜር በለው
ይኸው የኔ ፋንታ ፤
ከፍ ዝቅ ድርግም
"እባኮት የኔታ"
"ይቅር በሉ ይላል
ወንጌሉን አይርሱ
መመለሴን አይደል
ሚፈልገው እሱ?"
"እሱማ መተሃል
ዱላ ለወጉ ነው
ዳግም እንደማትሄድ
.. ለማረጋገጫ ፤
"ይሄ ሁሉ እርግጫ?"
"ዝምበል"
"አባ ይፍቱኝ በል"
"እሺ ይፍቱኝ አባ"
ቀና ሳብ ጨምቧ
ከዛን ተረጋጉ
አየር ሳብ አረጉ
"ይኸውልህ ልጄ
አድገህ አይደል በእጄ
አይንህ ልቤን ወጋው
ከእሳት ሳይህ ሰጋው
ለዛ ነው የተቆጣው
እስኪ እጅህን አምጣው"
"ይኸው" ብዬ አቀበልኩ
"ለበረከት እንጂ
አይሆኑም ለመርገም፤
እንካ ዳዊት ድገም
ይበቃል የስካሁን
አንተን ሳይ ፈራለው
.. ከእቶን ከእሳት፤
ከንግዲህ አትሳሳት"
ብለው አሳለሙኝ
ዝቅ ስል አመመኝ
ለንስሃ ያልወጣ
እምባዬ ቀደመኝ
ዱላ ያጀገነው
ልቤን ብሶት ገፋው
ስብርብር እያልኩኝ
ከእግራቸው ተደፋው
"አሳፈርኮት አባ
አሰደብኮት አባ
አስተምረው መና
አሳደገው መና
አልበሰልኩም ገና
አልበቃውም ገና
ይቅር በሉኝ አባ
አፉ በሉኝ አባ"
ብዬ ጥምጥም አልኩኝ
ጉልበታቸው ግርጌ
ጎትተው አነሱኝ
አቀፉኝ ሳብ አርገው፤
"ይሄን ልጅነት ነው
ጌታ ሚፈልገው"።
አሁን ለርሱ ስጋ
ባለበሰህ ፀጋ
ስለምትበድለው
ግፍን ስትሰበስብ ፤
እኔማ በእጄ ነህ
ለሞተልህ አስብ!።
አልቅስ እዘን እንጂ
ተስፋ ለማይቆርጠው
የምትድንበትን
ምክንያት ሲገጣጥም ፤
የጠገብክ እንደሆን
እናትህ ሆድ እንኳን
እኔን አታመልጥም!።
© @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
❤75👍56🤩7🔥6😁6😱1
ሩህሩ ነበር ልብሽ፣
የዋህ የጨው እቃ፣
የማይከብድ ቀንበር፣
ተመቺ ለጫንቃ፤
አቃፊ ደጋፊ፣
ፈገግታ መጋቢ፣
የምሕረት ገባር፣
ከእውነት አጋቢ፤
ተናፋቂ ውበት፣
ውስጣዊ ብርሓን፣
የማይጨልም ትጋት፣
የሚደነቅ ልሳን፣
አቆራኝቶ ይዞ፣
ሰውረሽ ይዘሽው፣
የመወደድ ፅዋን እንዳይጎል ሞላሽው።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@paappii
የዋህ የጨው እቃ፣
የማይከብድ ቀንበር፣
ተመቺ ለጫንቃ፤
አቃፊ ደጋፊ፣
ፈገግታ መጋቢ፣
የምሕረት ገባር፣
ከእውነት አጋቢ፤
ተናፋቂ ውበት፣
ውስጣዊ ብርሓን፣
የማይጨልም ትጋት፣
የሚደነቅ ልሳን፣
አቆራኝቶ ይዞ፣
ሰውረሽ ይዘሽው፣
የመወደድ ፅዋን እንዳይጎል ሞላሽው።
By @tafachgitm
@getem
@getem
@paappii
❤30👍24🔥3
ይች በሰማይ ላይ
የተሳለች ፀሐይ
በዓለም ሰልጥና መንበሯን ዘርግታ
መኖሯ ቀን ቢባል ማዘቅዘቁዋ ማታ
ለኔ ምን ሊፈይድ እኔን ምን ቸገረኝ
አትገዛኝም ፀሐይ የራሴ ዓለም አለኝ።
ፀሐይ ለዘላለም ሳቶጣም ብትቀር
የት አይቶኝ ጨለማ የት ደርሶ ከኔ በር
ባንች መምጣት መኼድ ነው ቀኔ ሚቆጠር።
በኔ ዓለም ውስጥ ያለሽ የኔ ፀሐይ አንች
ስትመጭ ይነጋል ይመሻል ስትኼጅ።
By @yonas_sileshi
@getem
@getem
@paappii
የተሳለች ፀሐይ
በዓለም ሰልጥና መንበሯን ዘርግታ
መኖሯ ቀን ቢባል ማዘቅዘቁዋ ማታ
ለኔ ምን ሊፈይድ እኔን ምን ቸገረኝ
አትገዛኝም ፀሐይ የራሴ ዓለም አለኝ።
ፀሐይ ለዘላለም ሳቶጣም ብትቀር
የት አይቶኝ ጨለማ የት ደርሶ ከኔ በር
ባንች መምጣት መኼድ ነው ቀኔ ሚቆጠር።
በኔ ዓለም ውስጥ ያለሽ የኔ ፀሐይ አንች
ስትመጭ ይነጋል ይመሻል ስትኼጅ።
By @yonas_sileshi
@getem
@getem
@paappii
❤28👍26🔥3😁2
[በሠላሳ ክረምት]
.
.
ከቦኛል ፍርሀት ከቦኛል እርጅና
የጉብዝናው ወራት
በወጉ በወጉ አላለፈምና።
ያወዛውዘኛል የአዝማናት ነፋስ
መደገፊያ ምርኩዝ ከማን ብርቱ ልዋስ?
እነሳ የነበርኩ ተስፈንጥሬ እንዳነር
እራመድ የነበርኩ በግሮቼ ጀግኜ
ክንፌን ቆርጬ ጣልኩ ከፍርሀት ወግኜ።
ሳዘግም
እግሮቼ ሲርዱ
ስተኛ ጭኖቼ ሲበርዱ
የገላዬ ሙቀት ሲሸሽ ቀን ጠብቆ
ቆፈን ሲዳበለኝ እንደስም ተጣብቆ
እትቱ ዘፈኔ
ፀደይ እንዳልወጣ በጋን እንዳልገፋ
ግንባሩ ላይ ይዟል የማለፍ ወረፋ።
በሰላሳ ክረምት በሰላሳ በጋ
ገሚሱ የርግማን ጥቂቱ የፀጋ
ተብዬ ብጠየቅ “ምን አደረክበት?”
መልሴ
እንደሞላለት ሰው ዝም ብዬ ኖርኩበት።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
.
.
ከቦኛል ፍርሀት ከቦኛል እርጅና
የጉብዝናው ወራት
በወጉ በወጉ አላለፈምና።
ያወዛውዘኛል የአዝማናት ነፋስ
መደገፊያ ምርኩዝ ከማን ብርቱ ልዋስ?
እነሳ የነበርኩ ተስፈንጥሬ እንዳነር
እራመድ የነበርኩ በግሮቼ ጀግኜ
ክንፌን ቆርጬ ጣልኩ ከፍርሀት ወግኜ።
ሳዘግም
እግሮቼ ሲርዱ
ስተኛ ጭኖቼ ሲበርዱ
የገላዬ ሙቀት ሲሸሽ ቀን ጠብቆ
ቆፈን ሲዳበለኝ እንደስም ተጣብቆ
እትቱ ዘፈኔ
ፀደይ እንዳልወጣ በጋን እንዳልገፋ
ግንባሩ ላይ ይዟል የማለፍ ወረፋ።
በሰላሳ ክረምት በሰላሳ በጋ
ገሚሱ የርግማን ጥቂቱ የፀጋ
ተብዬ ብጠየቅ “ምን አደረክበት?”
መልሴ
እንደሞላለት ሰው ዝም ብዬ ኖርኩበት።
By Yadel Tizazu
@getem
@getem
@paappii
❤40👍27😱3🔥2🎉1
.......
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኘናቸው
ስመን ጠቆምናቸው
በተዘጋ ጎጆ
በእንባ እየተራጨን
ከመገፋት ጽዋ
በቀል ተጎነጨን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ነን ብለን አመንን
ውበትን ለመንን
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኛናቸው
በእናባ ጸለይናቸው
ፍቅርን ተሳልን
በበቀል ቆሰልን
ሳሚ ያጣ ከንፈር
አቃፊ ያጣ ገላ
የወደድነው ሁላ
ጸጸት አስጎነጨን
ስቆ ለእንባ እያጨን
አሸሸ መዳፋን
ነፈገን እቅፋን
ጸደቁብን በቃል
ውበት ልብ ይበቃል
ብለው ልብን ሸሹ
ገፍተው አቆሸሹ
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራምም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ጉለት ሆንን ያምላካቸው
ያምላካችን
በመልካችን
ለወደድነው አነስን
ለአፈቀርነው እረከስን
ተጎነጨን መገፋትን
መተፋትን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኘናቸው
ስመን ጠቆምናቸው
በተዘጋ ጎጆ
በእንባ እየተራጨን
ከመገፋት ጽዋ
በቀል ተጎነጨን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ነን ብለን አመንን
ውበትን ለመንን
የሄዱትን ሁሉ
የገፋንን ሁሉ
ስቀን ሸኛናቸው
በእናባ ጸለይናቸው
ፍቅርን ተሳልን
በበቀል ቆሰልን
ሳሚ ያጣ ከንፈር
አቃፊ ያጣ ገላ
የወደድነው ሁላ
ጸጸት አስጎነጨን
ስቆ ለእንባ እያጨን
አሸሸ መዳፋን
ነፈገን እቅፋን
ጸደቁብን በቃል
ውበት ልብ ይበቃል
ብለው ልብን ሸሹ
ገፍተው አቆሸሹ
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
መልከጥፋ መልካም
ብጉራምም ቀፋፊ
ጎባጣ አንገት ደፊ
ጉለት ሆንን ያምላካቸው
ያምላካችን
በመልካችን
ለወደድነው አነስን
ለአፈቀርነው እረከስን
ተጎነጨን መገፋትን
መተፋትን
ጠላናት ተፈጥሮን
ከእይታ ሰውሮን
By @mad12titan
@getem
@getem
@getem
👍30❤10🔥9👎1
| በዚህ አለም፥ በዚህ ህይወት ፍቅር እስካ'ለ -
ለህልም፥ ለመሻት፥ ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ።
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊትም ብሩህ እለት አለ።
እውነቱን ስነግርሽ፦ ፈተና ነበረ በየዕለቱ፣
ሰኞ ተሰብሬ - ተነሳሁ በነጋታው በጠዋቱ።
ማክሰኞ በተስፋ እያለምኹ ዋልኹና
ረቡዕ ከሰርኹ - የእጄ ስራ ቀረ መና።
ሐሙስ ቆምኩኝ፥ ፍቅርሽን ጥበቃ
ለአማልክቱ ምስጋና ይግባቸውና -
አርብ ላይ ደረስኹ መንገዴ ነውና!
ቅዳሜን ነደድኹ ጨስኹ -
ፍቅሬን አንቺን እየጠበቅኹ፥
ሰንበትን ከመቅደሱ ቀረኹ!
ውዴ
የፍቅርሽን መንገድ እጓዛለኹ! እጓዛለኹ!
ሰንበት ሰንበት ሲሆን ቆሜ ጠብቃለኹ!
በመጠበቅም ቆሞ፥
|
በመፈለግም ሄዶ፥
|
እኔ አፈቅርሻለኹ!
•°•°•°•°•°•°••°°••°•°•°°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•
በዚህ ምድር፥ በዚህ ህይወት ፍቅር እስካለ
የሚረታኝ፥ የሚያቆመኝ፥ የሚይዘኝ ማን አለ?
በዚህ አለም በዚህ ህይወት ፍቅር እስካ'አለ
ለህልም ለመሻት ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊት ብሩህ እለት አለ
•°•°•°••°•°•°•°•°°••°•°•°•°•°•°•°•°°•°•°
By ናኹ
@getem
@getem
@paappii
ለህልም፥ ለመሻት፥ ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ።
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊትም ብሩህ እለት አለ።
እውነቱን ስነግርሽ፦ ፈተና ነበረ በየዕለቱ፣
ሰኞ ተሰብሬ - ተነሳሁ በነጋታው በጠዋቱ።
ማክሰኞ በተስፋ እያለምኹ ዋልኹና
ረቡዕ ከሰርኹ - የእጄ ስራ ቀረ መና።
ሐሙስ ቆምኩኝ፥ ፍቅርሽን ጥበቃ
ለአማልክቱ ምስጋና ይግባቸውና -
አርብ ላይ ደረስኹ መንገዴ ነውና!
ቅዳሜን ነደድኹ ጨስኹ -
ፍቅሬን አንቺን እየጠበቅኹ፥
ሰንበትን ከመቅደሱ ቀረኹ!
ውዴ
የፍቅርሽን መንገድ እጓዛለኹ! እጓዛለኹ!
ሰንበት ሰንበት ሲሆን ቆሜ ጠብቃለኹ!
በመጠበቅም ቆሞ፥
|
በመፈለግም ሄዶ፥
|
እኔ አፈቅርሻለኹ!
•°•°•°•°•°•°••°°••°•°•°°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•°•
በዚህ ምድር፥ በዚህ ህይወት ፍቅር እስካለ
የሚረታኝ፥ የሚያቆመኝ፥ የሚይዘኝ ማን አለ?
በዚህ አለም በዚህ ህይወት ፍቅር እስካ'አለ
ለህልም ለመሻት ለምኞት ሁሌ መንገድ አለ
ለእያንዳንዱ ድቅድቅ ለሊት ብሩህ እለት አለ
•°•°•°••°•°•°•°•°°••°•°•°•°•°•°•°•°°•°•°
By ናኹ
@getem
@getem
@paappii
👍30❤26