አንቺና ጨረቃ
=========
መብረቅ ብልጭ ብሎ
ምስልሽን ሲፈጥር፤
ፀሀይ ስትስቅ ነው
አንቺን የምትመስል፣
ኩልል ያለ ውሃ
ሲያይሽ ይጠራል፣
ከዋክብትን አይተሽ
ስንቴ አሽኮርምመሻል።
ጨረቃ ደግሞ አይታ፣
ካንቺ ካልተዋስኩኝ ብርሃንሽን ብላ፣
እንደዘብ ጠባቂ
አንቺን ተከትላ፣
ከአጼ ቤት ጎጆ
ገባች ሰተት ብላ።
አውቀሽ ነው ቢባልም
አሁን አምኛለሁ፣
አንቺን ለመፈለግ፤
አይደለም ጨረቃ እኔም ደክሜያለሁ።
ሰአሊ እንዳይስልሽ
ቀለምሽ አይገባም፣
ገጣሚ እንዳይገጥምሽ
ያለው ቃል አይበቃም።
ሆኖብኝ ነው እንጂ
እንደ አጼ ቤት ልጆች፣
መች እዋስ ነበረ
ዋንጫና ቁልፊቶች።
አውቃለሁኝ አዎ
በዚ ውስጥ አትቆዪም፣
በፍቅርሽ ተይዤ፤
በልቤ ብልቃጥ ውስጥ
አንቺን ባስቀምጥም፣
ሰበርሽው እሱንም፣
አንቺና ጨረቃ
ጭራሽ አትያዙም፣
ድንገት ብትያዙ፤
የያዛችሁን ነገር ከመስበር አትቀሩም፣
አንቺና ጨረቃ
መስበርን አተዉም፣
አንቺም ጨረቃም
ወደኋላ አትሉም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
=========
መብረቅ ብልጭ ብሎ
ምስልሽን ሲፈጥር፤
ፀሀይ ስትስቅ ነው
አንቺን የምትመስል፣
ኩልል ያለ ውሃ
ሲያይሽ ይጠራል፣
ከዋክብትን አይተሽ
ስንቴ አሽኮርምመሻል።
ጨረቃ ደግሞ አይታ፣
ካንቺ ካልተዋስኩኝ ብርሃንሽን ብላ፣
እንደዘብ ጠባቂ
አንቺን ተከትላ፣
ከአጼ ቤት ጎጆ
ገባች ሰተት ብላ።
አውቀሽ ነው ቢባልም
አሁን አምኛለሁ፣
አንቺን ለመፈለግ፤
አይደለም ጨረቃ እኔም ደክሜያለሁ።
ሰአሊ እንዳይስልሽ
ቀለምሽ አይገባም፣
ገጣሚ እንዳይገጥምሽ
ያለው ቃል አይበቃም።
ሆኖብኝ ነው እንጂ
እንደ አጼ ቤት ልጆች፣
መች እዋስ ነበረ
ዋንጫና ቁልፊቶች።
አውቃለሁኝ አዎ
በዚ ውስጥ አትቆዪም፣
በፍቅርሽ ተይዤ፤
በልቤ ብልቃጥ ውስጥ
አንቺን ባስቀምጥም፣
ሰበርሽው እሱንም፣
አንቺና ጨረቃ
ጭራሽ አትያዙም፣
ድንገት ብትያዙ፤
የያዛችሁን ነገር ከመስበር አትቀሩም፣
አንቺና ጨረቃ
መስበርን አተዉም፣
አንቺም ጨረቃም
ወደኋላ አትሉም።
@abela_black
@getem
@getem
@getem
( ሚስትህ የኔ እኮ ናት )
አገሬው ቢተቸኝ በገዛ ድግሴ ሳለሁ ተባርሬ ፤
ስቀህ ብታየኝም አንተ ተደስተህ ሳልፍ ተማርሬ ፤
አዎን ያንተው መውደድ የራስህ ያረካት ፤
ሳታገባት በፊት ለኔ ሚስቴ እኮ ናት ፤
የምሬን ስነግርህ......
አብልጬ ምወዳት ከራሴ ከሁሉ ፤
ሚስትህ ሚስቴ ደሆነች ባያውቅልኝ ሁሉ ፤
የሰው ሚስት ተመኘ ይለኛል ሰው ሁሉ ።
ግዴለም ይበሉኝ እነሱ ያሻቸውን ፤
ቆርጠው ይቀጥሉ ያለ የሌለውን ፤
አንተ ግን አደራ እንዳትዘብተኝ ፤
ደርሰህ በነሱ ፊት እንዳትቦጭቀኝ ፤
ወዳጅን መቀማት ፤
በለሆሳስ ማጥቃት ፤
ሳይቆፍሩ መቅበር ፤
ያውም ባንድ ጀንበር ፤
ሙሾም ሳይወረድ ፤
ምነው ሳይረገድ ።
ሰሚ ባይሰማልኝ ባላቆም ጠበቃ፤
ይኸን ሁሉ ነገር አርገህ ስታበቃ ፤
ሚስቴን ቀማኝ ብለህ ብትሄድ አቤቱታ ፤
ለወናፍ አፍ ሁሉ ብታቀርብ ስሞታ ፤
የምሬን ነው ምልህ ዳኛውም አይፈርድም ፤
እኔ አልከሰስም እኔ አልወቀስም ፤
ከቻልክ የሚስቴ ባል ምላስህን ሰብስብ ።
#ኢዮብ_አሰፋ
@yomin1_2
@getem
@getem
@getem
አገሬው ቢተቸኝ በገዛ ድግሴ ሳለሁ ተባርሬ ፤
ስቀህ ብታየኝም አንተ ተደስተህ ሳልፍ ተማርሬ ፤
አዎን ያንተው መውደድ የራስህ ያረካት ፤
ሳታገባት በፊት ለኔ ሚስቴ እኮ ናት ፤
የምሬን ስነግርህ......
አብልጬ ምወዳት ከራሴ ከሁሉ ፤
ሚስትህ ሚስቴ ደሆነች ባያውቅልኝ ሁሉ ፤
የሰው ሚስት ተመኘ ይለኛል ሰው ሁሉ ።
ግዴለም ይበሉኝ እነሱ ያሻቸውን ፤
ቆርጠው ይቀጥሉ ያለ የሌለውን ፤
አንተ ግን አደራ እንዳትዘብተኝ ፤
ደርሰህ በነሱ ፊት እንዳትቦጭቀኝ ፤
ወዳጅን መቀማት ፤
በለሆሳስ ማጥቃት ፤
ሳይቆፍሩ መቅበር ፤
ያውም ባንድ ጀንበር ፤
ሙሾም ሳይወረድ ፤
ምነው ሳይረገድ ።
ሰሚ ባይሰማልኝ ባላቆም ጠበቃ፤
ይኸን ሁሉ ነገር አርገህ ስታበቃ ፤
ሚስቴን ቀማኝ ብለህ ብትሄድ አቤቱታ ፤
ለወናፍ አፍ ሁሉ ብታቀርብ ስሞታ ፤
የምሬን ነው ምልህ ዳኛውም አይፈርድም ፤
እኔ አልከሰስም እኔ አልወቀስም ፤
ከቻልክ የሚስቴ ባል ምላስህን ሰብስብ ።
#ኢዮብ_አሰፋ
@yomin1_2
@getem
@getem
@getem
እናፍቅሽ ይሆን
~ ~ ~ ~ ~ ~
ስቀሽ ስትለይኝ ስትሄጅ ካጠገቤ
ስትሰናበቺ ከሚወጅሽ ልቤ
ያመጣሽ ጎዳና ሲመልስሽ ወስዶ
መፋቀርን ክዶ ነግርኝ ሲሄድ መርዶ
እናፍቅሽ ይሆን ?
ታውቂው የለም እንዴ 🤔
ሀዘኔን ልረሳው መፍራቴን ልደብቅ
አጥብቄ መያዜን የቀሚስሽን ጨርቅ
ገና ሳትቀልጂ በመምጣትሽ
ብቻ እንደምፍለቀለቅ ።
ትውስ ይልሽ ይሆን ?
እናፍቅሽ ይሆን ?
እንደምሳሳልሽ ትሳሽልኝ ይሆን ?
እኔማ .....
እወድሽማለሁ አፈቅርሽማለሁ
አስብሽማለሁ ናፍቅሽማለሁ
አንቺስ አንቺ ሆዬ እናፍቅሽ ይሆን ?
እናፍቅሻለሁ ?
By ኢዮብ_አሠፋ(@yomin1_2)
@getem
@getem
@getem
~ ~ ~ ~ ~ ~
ስቀሽ ስትለይኝ ስትሄጅ ካጠገቤ
ስትሰናበቺ ከሚወጅሽ ልቤ
ያመጣሽ ጎዳና ሲመልስሽ ወስዶ
መፋቀርን ክዶ ነግርኝ ሲሄድ መርዶ
እናፍቅሽ ይሆን ?
ታውቂው የለም እንዴ 🤔
ሀዘኔን ልረሳው መፍራቴን ልደብቅ
አጥብቄ መያዜን የቀሚስሽን ጨርቅ
ገና ሳትቀልጂ በመምጣትሽ
ብቻ እንደምፍለቀለቅ ።
ትውስ ይልሽ ይሆን ?
እናፍቅሽ ይሆን ?
እንደምሳሳልሽ ትሳሽልኝ ይሆን ?
እኔማ .....
እወድሽማለሁ አፈቅርሽማለሁ
አስብሽማለሁ ናፍቅሽማለሁ
አንቺስ አንቺ ሆዬ እናፍቅሽ ይሆን ?
እናፍቅሻለሁ ?
By ኢዮብ_አሠፋ(@yomin1_2)
@getem
@getem
@getem
የማይነቃ ውሸት
(ሳሙኤል አለሙ)
እንደ ተወዛዋዥ ግንባር
በየምሶሶው የለጠፍሽው
"አለ" የምትለው አድባር፤
ሰርክ...
መዳኑን ብቻ አስለምደሽው፤
ሰርክ...
መኖሩን ብቻ አሳይተሽው፤
ሰርክ...
ሲስቅ...ሲጫወት
ይረሳዋል!
እንደሚሞት ካልነገርሽው።
@Samuelalemuu
@getem
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
እንደ ተወዛዋዥ ግንባር
በየምሶሶው የለጠፍሽው
"አለ" የምትለው አድባር፤
ሰርክ...
መዳኑን ብቻ አስለምደሽው፤
ሰርክ...
መኖሩን ብቻ አሳይተሽው፤
ሰርክ...
ሲስቅ...ሲጫወት
ይረሳዋል!
እንደሚሞት ካልነገርሽው።
@Samuelalemuu
@getem
@getem
@getem
ቅጽርህ የእናት እቅፍ
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
ሸክምን የሚያራግፍ
አልተነፍስ ጸሎት አይወጣ ቃል ከአፌ
ይተናል ጭንቀቴ ስመለስ አርፌ
እመጣለሁ ደጅህ ሀሳብ አንጠልጥዬ
እገባለሁ ቅጽርህ አንገቴን ደፍቼ
መች ታዝንብኛለህ
መች ትወቅሰኛለህ በሽቅጬ ከርፍቼ
አይነድህ ድፍረቴ
አይቆጨኝ ስንፈቴ
አይበሽቅህ ስህተቴ
አይገደኝ ዝለቴ
በኦና ተግባሬ
ውድቀት አንከርፍፌ ስቆም ከነእድፌ
ምን አድርጌልህ ነው?
አክመህ ምትልከኝ በምህረት መርፌ
ከመቀመጥ በቀር
ኢምንት ታህል ድርጊት ፈጽሜ የማላውቅ
አንዲት ዘለላ እንባ
በጉንጬ ሳልሰድ እንዴት ደመቅኩ በሳቅ?
እንዴት ቻልኩ መፍገግ?
እንዴት ቻልኩ ማማር?
እሬት ህይወት ይዤ
አጣፍጥልኝ ሳልል ሳልጠይቅ የሀሴት ማር
ትዕቢት አይሉት ጥጋብ
ፍርሃት አይሉት ስጋት
ስም ያላገኘሁለት
አንዳች አሳሪ ኃይል ወርሮኝ እንደ ውጋት
አላልኩኝ እግዚኦታ አልቆምኩኝ ሰዓታት
ፈውስ አሰኝቶኝ አላደረስኩ ኪዳን
ስለረገጥኩ ብቻ
ስላረፍኩ በቤትህ ይገባኝ ነበር መዳን?
እንጃ!
ብቻ እመጣለሁ ሀሳብ አንጠልጥዬ
ደጅህ እገኛለሁ ማረኝ ቃልን ጥዬ
አርፋለሁ ካንዱ ጥግ አንገቴን ደፍቼ
መች ትቆጣኛለህ
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ከነእድፌ ተኝቼ
ቆይቼ
ቆይቼ
.
.
.
ቆይቼ ስነሳ
ተጋድሞ አየዋለሁ ሸክሜ እንደ ሬሳ
አልጸለየም ሳትል
አልለመነም ሳትል
አላነባም ሳትል
ይገርመኛል እኮ
ጊዮርጊስ አባቴ ጭንቀቴን ስትጥል
ይገርመኛል ቅጽርህ...
ልክ እንደ እናት እቅፍ
ደስታን 'ሚያሳቅፍ!
አባብሎ 'ሚያሳርፍ!
ሸክምን 'ሚያራግፍ!
.
.
.
እርፍ!
#ኤልዳን
@marda129
@getem
@getem
@getem
📢 NOTICE: Register Now for Xpert Training Institute’s Master Trading Program!
Are you ready to Master Trading with Experts? Xpert Training Institute, in collaboration with Jmad Capital Consultancy, presents a VIP & Mentorship Trading Program designed to equip you with essential and advanced Forex trading skills.
🔹 Programs Offered:
✅ VIP Class – Comprehensive training covering essential trading concepts.
✅ Mentorship Class (Online) – Advanced flexible learning with expert guidance from anywhere.
✅ Mentorship Class (Offline) – In-depth coaching with hands-on learning experience.
📅 Program Details:
📌 Duration: 6 Weeks
📌 Class Type: Online & Offline (Flexible Schedule)
📌 Batch Limit: Only 20 Students Per Batch
📍 Registration & Contact Information:
📞 Call Us:
📲 +251953888882
📲 +251116504000
📧 Email Us: [email protected]
🌐 Register Now: Click Here to Register
🚀 Secure your spot today and start your journey to financial success!
Join our Telegram channel
https://www.tg-me.com/xpert_et
Are you ready to Master Trading with Experts? Xpert Training Institute, in collaboration with Jmad Capital Consultancy, presents a VIP & Mentorship Trading Program designed to equip you with essential and advanced Forex trading skills.
🔹 Programs Offered:
✅ VIP Class – Comprehensive training covering essential trading concepts.
✅ Mentorship Class (Online) – Advanced flexible learning with expert guidance from anywhere.
✅ Mentorship Class (Offline) – In-depth coaching with hands-on learning experience.
📅 Program Details:
📌 Duration: 6 Weeks
📌 Class Type: Online & Offline (Flexible Schedule)
📌 Batch Limit: Only 20 Students Per Batch
📍 Registration & Contact Information:
📞 Call Us:
📲 +251953888882
📲 +251116504000
📧 Email Us: [email protected]
🌐 Register Now: Click Here to Register
🚀 Secure your spot today and start your journey to financial success!
Join our Telegram channel
https://www.tg-me.com/xpert_et
የመኖሬን ቅንጣት
በጥርሶችሽ ንጣት
ቀናውን እድሌን
በአይኖችሽ ብሌን
የነገዬን ድምቀት
በውበትሽ ስምረት
አየሁኝ ተስሎ
ነገ አንቺን መስሎ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
በጥርሶችሽ ንጣት
ቀናውን እድሌን
በአይኖችሽ ብሌን
የነገዬን ድምቀት
በውበትሽ ስምረት
አየሁኝ ተስሎ
ነገ አንቺን መስሎ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
ላይድን ቁስል፤
ጨዉ መነስነስ፤
ከድንጋይ ላይ፤
ዉሃ ማፍሰስ ፤
ለሟች ዘመድ ፤
ዳግም ማልቀስ፤
መኖር ካሉት፤
እንደዚህ ነው፤
ሳቅን ትቶ፤
መንሰቅሰቅ ነው።
By ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ጨዉ መነስነስ፤
ከድንጋይ ላይ፤
ዉሃ ማፍሰስ ፤
ለሟች ዘመድ ፤
ዳግም ማልቀስ፤
መኖር ካሉት፤
እንደዚህ ነው፤
ሳቅን ትቶ፤
መንሰቅሰቅ ነው።
By ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ሥዕል ማሳል ለምትፈልጉ በሙሉ
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ
@seiloch
@seiloch
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ
@seiloch
@seiloch
መኖር
በፍላጭ ሰከንዶች፤
በሽራፊ ሰዓት፤
በደቂቃ ቅንጣት፤
እለት እየገፉ፤
ወራት እያለፉ፤
እየጣሉ አመታት፤
በዘመን ምትሀት፤
በአንዲት የጊዜ ጋት፤
መኖር መሳብ አይደል፤
ወደሞት መጠጋት ?
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
በፍላጭ ሰከንዶች፤
በሽራፊ ሰዓት፤
በደቂቃ ቅንጣት፤
እለት እየገፉ፤
ወራት እያለፉ፤
እየጣሉ አመታት፤
በዘመን ምትሀት፤
በአንዲት የጊዜ ጋት፤
መኖር መሳብ አይደል፤
ወደሞት መጠጋት ?
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ
(ሳሙኤል አለሙ)
እንቁላሉን፣ስጋውን እንዳልበላሁ
ሰው ያውቃል፤
ወተቱን ፣ እርጎውን እንዳልጠጣሁ
ሰው ያውቃል፤
ላግኘው ብየ
ልያዘው ብየ
እንዳልወጣኝ ፥ ክፉ ቃል
ሰው ያውቃል፤
አውቃለሁ አያውቁም
አያውቁም አውቃለሁ ፤
ስብሰለሰል ግዜ
ስንገበገብ ግዜ
የከንፈሬን ስሷን ቆዳ
--ልጬው እየበላሁ
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem
(ሳሙኤል አለሙ)
እንቁላሉን፣ስጋውን እንዳልበላሁ
ሰው ያውቃል፤
ወተቱን ፣ እርጎውን እንዳልጠጣሁ
ሰው ያውቃል፤
ላግኘው ብየ
ልያዘው ብየ
እንዳልወጣኝ ፥ ክፉ ቃል
ሰው ያውቃል፤
አውቃለሁ አያውቁም
አያውቁም አውቃለሁ ፤
ስብሰለሰል ግዜ
ስንገበገብ ግዜ
የከንፈሬን ስሷን ቆዳ
--ልጬው እየበላሁ
ፆመ እባላለሁ ፥ ፆሜን እየፈታሁ።
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
@Getem