, ( ግዛትሽ ነኝ )
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
እንደ ሀይቅ ጠልቄ ከሃገር የሰፋሁ
አለሜን ስፈልግ ከአለም የጠፋሁ
በልብሽ መቅደስ ውስጥ አብሬ የተሰፋሁ
ሰፊ ግዛትሽ ነኝ
ወሰን ያልወጣልኝ ለክብሬ ዘብ ያጣሁ
ወሰንሽን ደፍረው ግዛትሽን ሳይወርሱት
በዳው መሬትሽን መንጥረው ሳያርሱት
ነይና ግዛትሽን አንቺው ዘብ ሁኝለት
መረቡን አስፊ እና ወሰን አብጂለት
ዳግምም አታገኝው ብትባክኝ በስለት
ችላ ያልሽው ግዛት ገዥ ሰው ያገኘ ዕለት
ውቢቷን ቀለሜን ውዲቷን ህይዎቴን
አለሜን ስፈልግ አለሜን ማጣቴን
ላንቺ እንዲህ መሆኔን አንቺ ግን አታውቂም
አንቺ ግን አንቺ ግን አንቺ ግን አታውቂም
እውነት እልሽ አለሁ ያለ እኔም አትደምቂም
By Habtish
@getem
@getem
@getem
❤28👍18
ሀቁን ሁሉም ሰው፡
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
ቢሸፍንም...
ሰው ካለም ክፋት ፡ እንዳይማር
በሴትነት ዘንድ የሚፈፀም
ትልቅ ወንጀል ነው፡
አለማማር!።
እንደ አምላክ በስም ባይመለክ
ባይሰዋለት ዘቢብ ፣ እጣን
ማንም ሸፋፍኖ የማይክደው
ውበት በሰው ላይ
አለው ስልጣን።
መልኳ ያልገነነ ምትደንቅ ሴት
ሀሳቧ አለሙን ቢያገናኝም
በቆንጆ ልጅ ሳቅ ይሸፈናል
ስባሪ ትኩረት ፡ አያገኝም፤
ምንም በህጉ ባይፀድቅ እንኳ
ቃል በቃል ሰፍሮ በትዕማር
ወደው እንዳረጉት የራስ ምርጫ
ትልቅ ወንጀል ነው ፡ አለማማር!።
by @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
👍23❤18😱7🔥3
ግዴታ ሆኖ — ብለ፟ይሽ
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
ባላይሽ — ዳግም ደግሜ....
የማይሞላን ባዶ ጊዜ....
(የቀረኝን ግንጥል ዕድሜ....)
በነፍስሽ ጠረን ትዝታ.....
በመንፈስሽ እኖራለሁ ፤
(አልጥልሽም አራግፌ..)
ተሸክሜሽ እዞራለሁ ።
•
ባ`ካሌ — በስሱ ገላ...
በፊቴ — ደግሞ በኋላ....
በጣቴ — ጫፎች አሻራ....
በራሴ — በፀጉሬ ስፍራ ....
(ይዤሽ ነው — ዘመን ምሻገር !)
በልቤ በደሜ — ማገር ፥
በሆንኩት — በቀረኝ ነገር ።
From: Charles Bokouski : “ Living on luck”¹
__
¹ =.......
ⁱᶠ ⁱ ⁿᵉᵛᵉʳ ˢᵉᵉ ʸᵒᵘ ᵃᵍᵃⁱⁿ
ⁱ ʷⁱˡˡ ᵃˡʷᵃʸˢ ᶜᵃʳʳʸ ʸᵒᵘ
ⁱⁿˢⁱᵈᵉ, ᵒᵘᵗ ˢⁱᵈᵉ
ᵒⁿ ᵐʸ ᶠⁱⁿᵍᵉʳ ᵗⁱᵖˢ
ᵃⁿᵈ ᵃᵗ ᵇʳᵃⁱⁿ ᵉᵈᵉᵍᵉˢ
ᵃⁿᵈ ⁱⁿ ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᶜᵉⁿᵗᵉʳˢ
ᵒᶠ ʷʰᵃᵗ ⁱ ᵃᵐ ᵒᶠ
ʷʰᵃᵗ ʳᵉᵐᵃⁱⁿˢ
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
👍36❤25🔥6🤩2😱1
ሰው ነበርኩኝ
ተወለድኩኝ
(ከመሀፀን ወደኩኝ )
አለቀስኩኝ
(ሀዘን ገባኝ ሰው ፈለኩኝ )
አፌን ከፈትኩ
(የሆድ ጥልቀት አወኩ )
በቃኝ አልኩ
( በእድሜ ሰከንኩ )
ጠረን ለየሁ
( ምቾት አየሁ )
ቋንቋ ለመድኩ
(በቆፈሩት ወረድኩ )
መልክ ለየሁ
(እኔን አወኩ አዲስ ካየሁ )
አንተ ግን ለቤቴ
( እንግዳ ላጥንቴ )
ሆነህ የሩቅ ሩቅ
(እንደ ዘመድ እንቅ )
ለምን አደረኩህ ....?
ሴት ነበርኩኝ
የተጣፈ እጣዬ
( ግልጥ ጎባጣዬ )
ሊያውም በእኛ መንደር
( እንቢ ነው መግደርደር )
እያለ ከሚረግጥ
( በዘመን ረመጥ )
በዘር ማን ዘር እሳት
(የምትቃጠል ሴት) !!!
ጨዋ እኮ ነበርኩኝ
አፈነገጥኩልህ
( እራሴን ተውኩልህ )
ወፍ ሆንኩልህ ጫጩት
(ሳይበር እንደ ቀጩት )
ረግጬ ህጌን
(ገላምጬ ወጌን)
ክር እኮ ነበረኝ
የገባሁት ኪዳን
( የመነንኩለት ሀቅ በነፃ ለመዳን )
የወሰዳት ነፍሴን
( ያሳረፈኝ ምናብ ቆርጦ ግሳንግሴን )
ጌታ እኮ ነበረኝ
የልቤ ጉልበቱ
(ሰርክ መስዋእቱ )
የምገብርለት
(ያደረገኝ ዐለት )
ብዙ ነኝ
የማላውቃት እኔ
( ተለየች ከጎኔ )
ወጣች አፈትልካ
( እኔን ላንተ ልካ )
እንደ ሰው ....
(ሞትን እንድቀምሰው)
እንደ ሴት
( እንዳምጥ በምሬት )
እንደ ጨዋ
( እንድፈተን እንድሰዋ )
እንደ አማኝ
(እንድቀበል ሳይቀማኝ )
እንደ ድኩም
( እንዲያነቃኝ ህማም ኩርኩም )
እንደ ብዙ
(አንድ እንድሆን ጠፎ ጓዙ )
ህግ አዝዬ
(ትምክት ልቤን እንዳይንጠኝ )
ተኝቼ እንድነቃ
(አንተን መርጦ ሰጠኝ)
(በእምነት )
@getem
@getem
@getem
ተወለድኩኝ
(ከመሀፀን ወደኩኝ )
አለቀስኩኝ
(ሀዘን ገባኝ ሰው ፈለኩኝ )
አፌን ከፈትኩ
(የሆድ ጥልቀት አወኩ )
በቃኝ አልኩ
( በእድሜ ሰከንኩ )
ጠረን ለየሁ
( ምቾት አየሁ )
ቋንቋ ለመድኩ
(በቆፈሩት ወረድኩ )
መልክ ለየሁ
(እኔን አወኩ አዲስ ካየሁ )
አንተ ግን ለቤቴ
( እንግዳ ላጥንቴ )
ሆነህ የሩቅ ሩቅ
(እንደ ዘመድ እንቅ )
ለምን አደረኩህ ....?
ሴት ነበርኩኝ
የተጣፈ እጣዬ
( ግልጥ ጎባጣዬ )
ሊያውም በእኛ መንደር
( እንቢ ነው መግደርደር )
እያለ ከሚረግጥ
( በዘመን ረመጥ )
በዘር ማን ዘር እሳት
(የምትቃጠል ሴት) !!!
ጨዋ እኮ ነበርኩኝ
አፈነገጥኩልህ
( እራሴን ተውኩልህ )
ወፍ ሆንኩልህ ጫጩት
(ሳይበር እንደ ቀጩት )
ረግጬ ህጌን
(ገላምጬ ወጌን)
ክር እኮ ነበረኝ
የገባሁት ኪዳን
( የመነንኩለት ሀቅ በነፃ ለመዳን )
የወሰዳት ነፍሴን
( ያሳረፈኝ ምናብ ቆርጦ ግሳንግሴን )
ጌታ እኮ ነበረኝ
የልቤ ጉልበቱ
(ሰርክ መስዋእቱ )
የምገብርለት
(ያደረገኝ ዐለት )
ብዙ ነኝ
የማላውቃት እኔ
( ተለየች ከጎኔ )
ወጣች አፈትልካ
( እኔን ላንተ ልካ )
እንደ ሰው ....
(ሞትን እንድቀምሰው)
እንደ ሴት
( እንዳምጥ በምሬት )
እንደ ጨዋ
( እንድፈተን እንድሰዋ )
እንደ አማኝ
(እንድቀበል ሳይቀማኝ )
እንደ ድኩም
( እንዲያነቃኝ ህማም ኩርኩም )
እንደ ብዙ
(አንድ እንድሆን ጠፎ ጓዙ )
ህግ አዝዬ
(ትምክት ልቤን እንዳይንጠኝ )
ተኝቼ እንድነቃ
(አንተን መርጦ ሰጠኝ)
(በእምነት )
@getem
@getem
@getem
❤42👍34🔥5
ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ ገላሽን ይንካና
ወዮለት ሰማዩ
ወዮለት ደመና ።
ወፍ አይዘምርልሽ
ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ ።
ደግሞ ይሄን እወቂ
ሆዴ እንደሚበላኝ ካለ እኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ
በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር
በእግዜር ስትመኪ ።
እኔ ነኝ ጠባቂሽ
እኔ ነኝ ደስታሽ
እኔ ነኝ ፈገግታሽ
ሁሉንም የምሆን
እግዜር አላህ ሰማይ
ንፋስ ውሃ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ
ያንቺ ብቻ ታጋይ ።
ክነፍ በዪኝ ልክነፍ
እረፍ በዪኝ ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ በእኔ በኩል ይለፍ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
ወዮለት ሰማዩ
ወዮለት ደመና ።
ወፍ አይዘምርልሽ
ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ ።
ደግሞ ይሄን እወቂ
ሆዴ እንደሚበላኝ ካለ እኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ
በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር
በእግዜር ስትመኪ ።
እኔ ነኝ ጠባቂሽ
እኔ ነኝ ደስታሽ
እኔ ነኝ ፈገግታሽ
ሁሉንም የምሆን
እግዜር አላህ ሰማይ
ንፋስ ውሃ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ
ያንቺ ብቻ ታጋይ ።
ክነፍ በዪኝ ልክነፍ
እረፍ በዪኝ ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ በእኔ በኩል ይለፍ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
❤68👍28👎19🔥9🤩9😁4🎉2
ቁራኛ
ዘመን ያላዳነኝ
ያልፈታኝ ርቀት
ተአምር ያላነጻኝ
ያልፈወሰኝ ጥምቀት
ከናፍቆት ሚነጥል
የታጣልኝ ዳኛ
እድሜ ይፍታህ ያሉት
የፍቅር ምርኮኛ
ሆንኩልሽ ቁራኛ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
ዘመን ያላዳነኝ
ያልፈታኝ ርቀት
ተአምር ያላነጻኝ
ያልፈወሰኝ ጥምቀት
ከናፍቆት ሚነጥል
የታጣልኝ ዳኛ
እድሜ ይፍታህ ያሉት
የፍቅር ምርኮኛ
ሆንኩልሽ ቁራኛ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@paappii
❤37👍19😁5👎2🔥2