የባከነ ሌሊት!!!!
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
By bewuketu seyoum
@getem
@getem
@paappii
❤80😁24🔥14👍7😢2
የአብስራ ሳሙኤል
ከቤትሽ በር ላይ
ትንሽ ዘምበል ብሎ ቅጠሉ የረገፈ
አንቺ ስትወጪ የተንዘፈዘፈ
በአራራይ ዜማ
ጎንበስ ቀና ብሎ ውዳሴ የሚያሰማ
ዛፍ ካየሽ.......እኔ ነኝ
ደሞ ጮራ ከቦሽ
የጸሀዪ ንዳድ ገላሽን አልቦሽ
ማረፊያ ፍለጋ የተቀመጥሽበት
ስራ የፈታ ድንጋይ የዱርዬ መንበር
የኔ ገላ ነበር
ወይም ባለፈው 'ለት
በዕለተ ሰንበት ልደታን ስትስሚ
የተሽኮረመምሽው ምርቃት ስትሰሚ
ምንም ሳትሰጪ ሳትመጸውቺ
ህይወት ህይወት ጸዳል ለምትሸቺው ላንቺ
አሜን ሳትይ እንኳ የመረቀሽ ለማኝ
እኔ ነኝ
እናልሽ መቅደሴ
ሴያሻሽ እንደ ታዛ ሲያሻሽ እንደ ወንበር
ደጀ ሰላም ወድቆ ሲመርቅ የነበር
ከጎጆሽ ባይመጥን ከልብሽ ባይሞላ
በሄድሽበት ሁሉ በአምሳል እያጠላ
እንደ ንፍቀ ክበብ ሲዞርሽ የሚገኝ
እኔ ነኝ
@getem
@getem
@paappii
ከቤትሽ በር ላይ
ትንሽ ዘምበል ብሎ ቅጠሉ የረገፈ
አንቺ ስትወጪ የተንዘፈዘፈ
በአራራይ ዜማ
ጎንበስ ቀና ብሎ ውዳሴ የሚያሰማ
ዛፍ ካየሽ.......እኔ ነኝ
ደሞ ጮራ ከቦሽ
የጸሀዪ ንዳድ ገላሽን አልቦሽ
ማረፊያ ፍለጋ የተቀመጥሽበት
ስራ የፈታ ድንጋይ የዱርዬ መንበር
የኔ ገላ ነበር
ወይም ባለፈው 'ለት
በዕለተ ሰንበት ልደታን ስትስሚ
የተሽኮረመምሽው ምርቃት ስትሰሚ
ምንም ሳትሰጪ ሳትመጸውቺ
ህይወት ህይወት ጸዳል ለምትሸቺው ላንቺ
አሜን ሳትይ እንኳ የመረቀሽ ለማኝ
እኔ ነኝ
እናልሽ መቅደሴ
ሴያሻሽ እንደ ታዛ ሲያሻሽ እንደ ወንበር
ደጀ ሰላም ወድቆ ሲመርቅ የነበር
ከጎጆሽ ባይመጥን ከልብሽ ባይሞላ
በሄድሽበት ሁሉ በአምሳል እያጠላ
እንደ ንፍቀ ክበብ ሲዞርሽ የሚገኝ
እኔ ነኝ
@getem
@getem
@paappii
❤48🔥5👍1
" በረከተ-መንግስት"
( ግዮናይ ነኝ)!፧
ምስኪን ያገሬ ሰው...
ቀኑን ሲሮጥ ውሎ ሌሊት ይሸሸጋል፣
ተፈጥሮ ነውና...
በወፎች ዝማሬ አይቀርም ይነጋል።
ይኸው ደሞ ነጋ...
መስከረም ይመስል መድፉ ተተኮሰ፣
ከምንሸሽበቱ...
እየተከተለን ውጊያው ተለኮሰ።
* * * * * * * * *
ይኸውና ሞርተር...
አዲሱን ቆርቆሮ ባንድ'ዜ ቀደደ፣
እናት ታለቅሳለች...
የዘመናት ወዟ ቤቷ እየነደደ።
ሰብአዊነት ጠፋ...
እንደ ውሻ ሆነ የህዝቤ ክቡር ደም፣
ለቀብራችን እንኳን...
በነጋሢ ቄሳር ለቅሶ አልተፈቀደም።
* * * * * * * * *
እርሻ የሄደ ሰው...
ቀንበር ተሸክሞ በወጣበት ሲቀር፣
ምን እናደርጋለን...
ለላይኛው ጌታ ከማዳኘት በቀር።
@getem
@getem
@getem
( ግዮናይ ነኝ)!፧
ምስኪን ያገሬ ሰው...
ቀኑን ሲሮጥ ውሎ ሌሊት ይሸሸጋል፣
ተፈጥሮ ነውና...
በወፎች ዝማሬ አይቀርም ይነጋል።
ይኸው ደሞ ነጋ...
መስከረም ይመስል መድፉ ተተኮሰ፣
ከምንሸሽበቱ...
እየተከተለን ውጊያው ተለኮሰ።
* * * * * * * * *
ይኸውና ሞርተር...
አዲሱን ቆርቆሮ ባንድ'ዜ ቀደደ፣
እናት ታለቅሳለች...
የዘመናት ወዟ ቤቷ እየነደደ።
ሰብአዊነት ጠፋ...
እንደ ውሻ ሆነ የህዝቤ ክቡር ደም፣
ለቀብራችን እንኳን...
በነጋሢ ቄሳር ለቅሶ አልተፈቀደም።
* * * * * * * * *
እርሻ የሄደ ሰው...
ቀንበር ተሸክሞ በወጣበት ሲቀር፣
ምን እናደርጋለን...
ለላይኛው ጌታ ከማዳኘት በቀር።
@getem
@getem
@getem
😢32❤28😱1
ምን አጥፍተን ይሆን
.
.
ዳገቱን ስንወጣ ወድቀን ተነስተናል፤
ከተራራው አናት አብረን ተጉዘናል፤
የጠዋቷን ፀሐይ በደስታ ሞቀናል፤
በዉቧ ጨረቃ በፍቅር ደምቀናል።
ግና ናፍቆቴዋ................
በዛች የቀን ምራጭ ሰይጣን ሹክ ቢልህ፤
ፈጥነህ ተቀበልከዉ እሺታህን ሰጥተህ።
ከእግዜር ተጣልቼ ቀኒቱን ጠላኋት፤
ባትፈጠር ብዬ አምርሬ ረገምኳት።
እናም አካላቴ ምን ተሰምቶህ ይሆን?
አትፈልጊኝ ስትል ሀዘን ገብቶህ ይሆን?
እኔማ ናፍቆቴ.................
ምክንያቱን ሳላዉቀዉ፤
አንተም ሳትረዳዉ።
እንለያይ ብለህ ከጎኔ ስትርቀኝ፤
በላዬ ተንዶ ምድር ተደፋብኝ፤
የማደርገዉ አጣሁ ቀኑ ጨለመብኝ፤
ብልሀቴ ጠፍቶ ማጣፊያው ራቀኝ።
ትናንት የቀኑብን ዛሬ እያሸሞሩ፤
ተለያዩ ብለዉ እንዲሰማ ሀገሩ፤
በቡና ሸፋፍነዉ ለፍፈዉ ነገሩ።
ሙጫ ነች እያሉ ፍርድ ይበይናሉ፤
ህመሜን ሳያዉቁ እንዲህ ነች ይላሉ።
ካንተ ጋ አብሮ ሄዷል ፈገግታና ስቄ፤
ዘወትር የምኖር ብሶቴን አምቄ።
ምን አጥፍተን ይሆን ?
እንዲህ የተቀጣን ?
እንደዉ በደፈናዉ በቃችሁ የተባልን፤
በናፍቆት ችንካራት የተቸነከርን።
መንገድህን መርጠህ ከእኔ ብትሸሽም፤
ተስቶህ ነው እንጂ በደልከኝ አልልም።
✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ዳገቱን ስንወጣ ወድቀን ተነስተናል፤
ከተራራው አናት አብረን ተጉዘናል፤
የጠዋቷን ፀሐይ በደስታ ሞቀናል፤
በዉቧ ጨረቃ በፍቅር ደምቀናል።
ግና ናፍቆቴዋ................
በዛች የቀን ምራጭ ሰይጣን ሹክ ቢልህ፤
ፈጥነህ ተቀበልከዉ እሺታህን ሰጥተህ።
ከእግዜር ተጣልቼ ቀኒቱን ጠላኋት፤
ባትፈጠር ብዬ አምርሬ ረገምኳት።
እናም አካላቴ ምን ተሰምቶህ ይሆን?
አትፈልጊኝ ስትል ሀዘን ገብቶህ ይሆን?
እኔማ ናፍቆቴ.................
ምክንያቱን ሳላዉቀዉ፤
አንተም ሳትረዳዉ።
እንለያይ ብለህ ከጎኔ ስትርቀኝ፤
በላዬ ተንዶ ምድር ተደፋብኝ፤
የማደርገዉ አጣሁ ቀኑ ጨለመብኝ፤
ብልሀቴ ጠፍቶ ማጣፊያው ራቀኝ።
ትናንት የቀኑብን ዛሬ እያሸሞሩ፤
ተለያዩ ብለዉ እንዲሰማ ሀገሩ፤
በቡና ሸፋፍነዉ ለፍፈዉ ነገሩ።
ሙጫ ነች እያሉ ፍርድ ይበይናሉ፤
ህመሜን ሳያዉቁ እንዲህ ነች ይላሉ።
ካንተ ጋ አብሮ ሄዷል ፈገግታና ስቄ፤
ዘወትር የምኖር ብሶቴን አምቄ።
ምን አጥፍተን ይሆን ?
እንዲህ የተቀጣን ?
እንደዉ በደፈናዉ በቃችሁ የተባልን፤
በናፍቆት ችንካራት የተቸነከርን።
መንገድህን መርጠህ ከእኔ ብትሸሽም፤
ተስቶህ ነው እንጂ በደልከኝ አልልም።
✍ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤46🔥4👍2
የአብስራ ሳሙኤል
፩.
ከቀጠራት ካፌ
የአባቧዋን ገላ እየቀነጠሰች
ጥሏት ከሄደበት
በሀሳብ ተከትላው በሀሳብ ተመለሰች
ያልጠጣውን ቡና እንፋሎት ታየለች
ጠረኑን ቀላቅሎ ብን'ብሎ ሲጠፋ
እንደ ጠዋት ጤዛ እንደ ቀቢጸ ተስፋ
የመሄዱን ዳና እያመሳሰለ
ከመኖር ጎደለ
―✦―
፪.
እንባ አቅርሯል አይኑ
ዞር ብሎም ለማየት አልቀናም ልቡናው
ያውቀዋል ህሊናው
ሰው አልመጠናትም
ያቀፈችው ሁሉ ትከሻው አልሞቃትም
አትገባም ለሱ
ሰው አልሆነም እሱ
ቢጽፍላት ቢቀኝላት
እልፍ ግጥም እልፍ ቅኔ
መልኳን ተሳልሞ መመለስ ነው
ቃል አያቅም የ'ሱ ወኔ
―✦―
፫.
እናም እሷም ካለችበት እሱም ከሄደበት
በቀስተ ደመና አድማስ የሚያጣምር
የማይኖሩት ፍቅር
ለምትኖረው ህይወት እስትንፋሱን ቸረ
ሄደ ያለችው ገላ ሲመራት ነበረ
―☾―
@getem
@getem
@getem
፩.
ከቀጠራት ካፌ
የአባቧዋን ገላ እየቀነጠሰች
ጥሏት ከሄደበት
በሀሳብ ተከትላው በሀሳብ ተመለሰች
ያልጠጣውን ቡና እንፋሎት ታየለች
ጠረኑን ቀላቅሎ ብን'ብሎ ሲጠፋ
እንደ ጠዋት ጤዛ እንደ ቀቢጸ ተስፋ
የመሄዱን ዳና እያመሳሰለ
ከመኖር ጎደለ
―✦―
፪.
እንባ አቅርሯል አይኑ
ዞር ብሎም ለማየት አልቀናም ልቡናው
ያውቀዋል ህሊናው
ሰው አልመጠናትም
ያቀፈችው ሁሉ ትከሻው አልሞቃትም
አትገባም ለሱ
ሰው አልሆነም እሱ
ቢጽፍላት ቢቀኝላት
እልፍ ግጥም እልፍ ቅኔ
መልኳን ተሳልሞ መመለስ ነው
ቃል አያቅም የ'ሱ ወኔ
―✦―
፫.
እናም እሷም ካለችበት እሱም ከሄደበት
በቀስተ ደመና አድማስ የሚያጣምር
የማይኖሩት ፍቅር
ለምትኖረው ህይወት እስትንፋሱን ቸረ
ሄደ ያለችው ገላ ሲመራት ነበረ
―☾―
@getem
@getem
@getem
❤40👍6🔥1
⁂
የአብስራ ሳሙኤል
⁂
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ
ማለፊያ ምግባር ምን ሰራህ
በኖርክባት ስንዝር እድሜ
ምን'ን ዘርተህ ምን አፈራህ
እንዴያው ሲያስበው ይጨንቀኛል
ነፍሴን እንዳል'ጥላት እፈራለሁ
ፈራሽ ገላ ተጫምቼ
ስንት ዘመን እኖራለሁ
የእንባ ብዕር ከሚጠቀስበት
መዝገብ እንዳላሰፍር
መሾ ከሚወርድበት
ክብሬን እንዳላሳፍር
ለመንግስትህ እጨኝ ባልልም
ከመከራው ጠብቀኝ
የኔ እውቀት አያድነኝም
መልካሙን አንተ አሳውቀኝ
ለማትሞላ ጎደሎ ምድር
ህልም ነው ወዳልከው ስትለፋ
ተስፋ ነው ወዳልከው ስትገፋ
ማረፍ አይቀርምና ታርፋለህ
መሞት አይቀርምና ትሞታለህ
ማለፊያ ምግባር የሚሆን
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ
የበገና ክር መወጠር
ለዜማው መጣም ነው'ና
ምስገና መባ እንዲሆን
የህይወትህ ጥኡም ቃና
ለመንግስትህ እጨን ባንልም
ከመከራው አንተ ጠብቀን
የ'ኛ እውቀት አያድነንም
መልካሙን አንተ አሳውቀን
⁂
ለነፍስህ ቅሪት ምን አለህ ?@getem
@getem
@getem
❤51🔥3🤩1
.
ከገነት ላለኸዉ
.
የ'ግር እሳት ሆኖ ቢገርፈኝ መለየት ፍም እሳቱ፤
ልቤን አቀጣጠላት የናፍቆትህ ስር ግለቱ፤
በዛች የቀን ጎዶሎ ጥቁር ሞት አንተን ሲጠራ፤
እኔንም ጠርቶኝ በነበር ብጓዝ ከፍቅሬ ጋራ፤
ካንተ መራቅ አይሆንልኝ፤
ሌጣ ሆኜ አያምርብኝ፤
ዘወትር..መቃብርህን አቅፌ ስስም 'ዉላለሁ፤
ነጋ ጠባ..ስምህን ስደጋግም አድራለሁ፤
ያዩኝ በሙሉ.........
አበደች እያሉ ሲያሸሙሩብኝ፤
ከመቃብር አድራ ተለከፈች ሲሉኝ፤
መች ጆሮ ሰጠሁኝ መች አዳመጥኳቸዉ፤
ሞቷል እርሽዉ ሲሉኝ ላይኔ ጠላኋቸዉ፤
አይገባቸዉማ..........
በድኔን አስቀርታኝ መከረኚት ልቤ፤
አብራህ እንደሄደች አያዉቁም አሳቤ፤
ነፍሴ ከነፍስህ ጋር እንደተሳሰረች፤
ዳግም ላትነጠል እንደተጋመደች፤
ከጎኔ ባለገኝህም አይዞሽ ባትለኝ አንዴ፤
ጠረንህ ቢናፍቀኝም ባታባብለኝ ዉዴ፤
መቼም ላይጠፋ ከእኔነቴ፤
ዛሬም ህያዉ ነው ፍቅርህ ናፍቆቴ።
በዔደን ታደሰ እንደተፃፈ
@topazionnn
@getem
@getem
❤26😢11🤩2👎1
መኖሬ ከሆነ
እግሬ እንዳይራመድ
ልቤ ሲያጠምድ ወጥመድ
ልርቅ ስል ከሁሉ
ሲቀርቡኝ በሙሉ
አሉልኝ ያልኩኝ ለት
ብትንትን ሲሉ
በቅፅበት ደስታ
ስረሳው ሀዘኔን
ትንሽ ፈገግ አልኩኝ
ላነባው ዘመኔን
ወይ አለምን ንቄ
አልመነንኩ ከደብሩ
ወይ አልተሳካልኝ
አልተመቸኝ ምድሩ
መኖሬ ከሆነ ይቅርብኝ
ግድየለም ውሰደኝ እግዜሩ ።
By ኢዮብ_ዮሚን
@getem
@getem
@paappii
እግሬ እንዳይራመድ
ልቤ ሲያጠምድ ወጥመድ
ልርቅ ስል ከሁሉ
ሲቀርቡኝ በሙሉ
አሉልኝ ያልኩኝ ለት
ብትንትን ሲሉ
በቅፅበት ደስታ
ስረሳው ሀዘኔን
ትንሽ ፈገግ አልኩኝ
ላነባው ዘመኔን
ወይ አለምን ንቄ
አልመነንኩ ከደብሩ
ወይ አልተሳካልኝ
አልተመቸኝ ምድሩ
መኖሬ ከሆነ ይቅርብኝ
ግድየለም ውሰደኝ እግዜሩ ።
By ኢዮብ_ዮሚን
@getem
@getem
@paappii
Telegram
✍ዮ_ሚን
ፈጠራዎችን እንደመምባቸዋለን ስለሀሳብ እንሰማለን፡፡ እናሰላስላለን፡፡ ሰክረን ሳይሆን ሰክነን፡፡ሀሳብን እናስበዋለን፡፡
ዘላለም የሚቆየው ሀሳብ ነው፡፡
@Yob_minn
ዘላለም የሚቆየው ሀሳብ ነው፡፡
@Yob_minn
❤52😢7🤩1
" አሜን"
( ግዮናይ ነኝ)!፧
አንቺ ጋር ለመኖር...
ሺ ቁልቁል ወርጄ ብዙ ዳገት ወጣሁ፣
ዳኛ ሳይፈርድብኝ...
እንደ ወንጀለኛ በኑሮ ተቀጣሁ፣
ያ'ርባ ቀን ዕድሌን እጣ ፈንቴን አጣሁ።
* * *
ህይወትን ተራብኩኝ...
እንጃ ስለ ፍቅር ጥላቻን ተጠማሁ፣
ይኸው ደሞ ዛሬ...
እንለያይ የሚል ካ'ንደበትሽ ሰማሁ።
አሜን ያደርግልኝ...
እዛ ማዶ ልጓዝ ፍቅርሽን አልፌ፣
(አልጋዬ የት ነበር?)...
እስኪ ጋደም ልበል ናፍቆኛል እንቅልፌ።
* * *
ሰውነቴ ሁሉ...
እንደ ብሉይ ኃጢያት ለምጻም ሰው መሰለ፣
ፈጣሪ ያውቀኛል...
ህይወቴ ላ'ንቺነት ብዙ እንደ ቆሰለ።
ልሽሽ ካለሽበት...
ምድር እስከምታልቅ በሌትና ቀትር፣
ባህር እንኳን ባገኝ...
ሙሴ ይሰጠኛል የመክፈያ በትር።
@getem
@getem
@paappii
( ግዮናይ ነኝ)!፧
አንቺ ጋር ለመኖር...
ሺ ቁልቁል ወርጄ ብዙ ዳገት ወጣሁ፣
ዳኛ ሳይፈርድብኝ...
እንደ ወንጀለኛ በኑሮ ተቀጣሁ፣
ያ'ርባ ቀን ዕድሌን እጣ ፈንቴን አጣሁ።
* * *
ህይወትን ተራብኩኝ...
እንጃ ስለ ፍቅር ጥላቻን ተጠማሁ፣
ይኸው ደሞ ዛሬ...
እንለያይ የሚል ካ'ንደበትሽ ሰማሁ።
አሜን ያደርግልኝ...
እዛ ማዶ ልጓዝ ፍቅርሽን አልፌ፣
(አልጋዬ የት ነበር?)...
እስኪ ጋደም ልበል ናፍቆኛል እንቅልፌ።
* * *
ሰውነቴ ሁሉ...
እንደ ብሉይ ኃጢያት ለምጻም ሰው መሰለ፣
ፈጣሪ ያውቀኛል...
ህይወቴ ላ'ንቺነት ብዙ እንደ ቆሰለ።
ልሽሽ ካለሽበት...
ምድር እስከምታልቅ በሌትና ቀትር፣
ባህር እንኳን ባገኝ...
ሙሴ ይሰጠኛል የመክፈያ በትር።
@getem
@getem
@paappii
❤33👍2🔥2🤩2
ድክም ብል በሂወት መንገድ
እግሬ ቢዝል ብሰናከል
ቆፈን ብለብስ ለገላዬ
ቁራሽ ዳቦ ብከለከል
ቀን ቢገፋኝ ካለሁበት
ከከፍታ ብወረወር
"አትመጥንም" ብባል በአፍ
ከአመት አመት በቀን በወር
አይኔ ደምን ሰርክ ቢያነባ
እቅድ ግቤ ቢፋለስም
ዳና ትግሌን አደብዝዘው
ያለ ስሜ ቢሰጡኝ ስም
አትጨናነቂ
ዝምብለሽ ሳቂ!
አታውቂምና ነው!
ቀን የገፋውን ሰው ቀን እንደሚያነሳው
ፈጣሪ ላልከዳው እሱ እንደማይረሳው
አታውቂምና ነው!
ዝቅ ያለ ሰው ሁሉ ከፍታ እንደሚያገኝ
ማርያም
ማርያም ላለ ፈጣሪ እንደሚገኝ
አታውቂምና ነው!
ሞን ያስለቅስሻል ለምን ትጨነቂ
ሁሉ በርሱ ይሆናል ዝም ብለሽ ሳቂ
ቀን ሳይገፋ አያልፍም ቀን
አልፈጠረብሽም ምንድነው ሰቀቀን
ለኔ ብለሽ አትድከሚ
አይብረድሽ ፍርሃት ቁር
ጊዜ አይፈጅም ለመልስማ
ካምላክ ሄጄ ብቆረቁር
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ተስፋ መቁረጥ አይነበብ ካካል ገፅሽ ከመልክሽ ላይ
ሀይል ብርታቴ ይጨምራል የፊትሽን ፈገግታ ሳይ።
አንዲት ቅንጣት እንባ እንዳላይ ተደርድሮ ከጉንጭሽ ስር
ቀን እንደሆን አመሏ ነው ልታነሳ ምትሰረስር።
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
እግሬ ቢዝል ብሰናከል
ቆፈን ብለብስ ለገላዬ
ቁራሽ ዳቦ ብከለከል
ቀን ቢገፋኝ ካለሁበት
ከከፍታ ብወረወር
"አትመጥንም" ብባል በአፍ
ከአመት አመት በቀን በወር
አይኔ ደምን ሰርክ ቢያነባ
እቅድ ግቤ ቢፋለስም
ዳና ትግሌን አደብዝዘው
ያለ ስሜ ቢሰጡኝ ስም
አትጨናነቂ
ዝምብለሽ ሳቂ!
አታውቂምና ነው!
ቀን የገፋውን ሰው ቀን እንደሚያነሳው
ፈጣሪ ላልከዳው እሱ እንደማይረሳው
አታውቂምና ነው!
ዝቅ ያለ ሰው ሁሉ ከፍታ እንደሚያገኝ
ማርያም
ማርያም ላለ ፈጣሪ እንደሚገኝ
አታውቂምና ነው!
ሞን ያስለቅስሻል ለምን ትጨነቂ
ሁሉ በርሱ ይሆናል ዝም ብለሽ ሳቂ
ቀን ሳይገፋ አያልፍም ቀን
አልፈጠረብሽም ምንድነው ሰቀቀን
ለኔ ብለሽ አትድከሚ
አይብረድሽ ፍርሃት ቁር
ጊዜ አይፈጅም ለመልስማ
ካምላክ ሄጄ ብቆረቁር
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ተስፋ መቁረጥ አይነበብ ካካል ገፅሽ ከመልክሽ ላይ
ሀይል ብርታቴ ይጨምራል የፊትሽን ፈገግታ ሳይ።
አንዲት ቅንጣት እንባ እንዳላይ ተደርድሮ ከጉንጭሽ ስር
ቀን እንደሆን አመሏ ነው ልታነሳ ምትሰረስር።
አትጨናነቂ
ዝም ብለሽ ሳቂ!
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤40👍5🔥1🎉1
በምድር ፍትህ የለም
.........................
ለእውነት የሚቆም ራሱን የካደ
ከራሱ አስበልጦ አምሳሉን የወደደ
የአዳም ዘር ሆኖ በምድር ስለሌለ
ፍትህ በቃል ብቻ ተመዝግቦ ዋለ::✍
፠፠፠፠
ባለንባት አለም የኔም ያንተም ጠባይ
ለምድር ይቅርና ያስፈራል ለሰማይ::
እናም!... .
ፍትህ ለእገሊት!
ፍትህ ለእገሌ!
ፍትህ.......ፍትህ......!
ፍትህ........!
እያሉ መጮህ አንዳችም አይሰራም
እንኳንስ ለሰው ልጅ
ምንኖርባት ምድር ለንጉስ አትራራም፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@paappii
.........................
ለእውነት የሚቆም ራሱን የካደ
ከራሱ አስበልጦ አምሳሉን የወደደ
የአዳም ዘር ሆኖ በምድር ስለሌለ
ፍትህ በቃል ብቻ ተመዝግቦ ዋለ::✍
፠፠፠፠
ባለንባት አለም የኔም ያንተም ጠባይ
ለምድር ይቅርና ያስፈራል ለሰማይ::
እናም!... .
ፍትህ ለእገሊት!
ፍትህ ለእገሌ!
ፍትህ.......ፍትህ......!
ፍትህ........!
እያሉ መጮህ አንዳችም አይሰራም
እንኳንስ ለሰው ልጅ
ምንኖርባት ምድር ለንጉስ አትራራም፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@paappii
❤46😢14👍4🔥4
ጨዋታዉ ፈረሰ
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
ቦጭቀን፤
ቦጫጭቀን፤
እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ልጅነቴ ልጅነትህን፤
ለጋነትህ ጮርቃነቴን፤
በትዝታ እየቃኘሁ፤
ሳቃችንን እየሰማሁ፤
በትዉስታ ምልሰት፤
በጥሞና ስመለከት።
በድንጋይ ከታትፈን፤
ማባያ ጨምረን፤
መረቁን ከልሰን፤
የሰራነዉ ጎመን።
ለሚመጣዉ ዘመን፤
የእቃቃ ሰርጋችን፤
ሚዜ ስናዘጋጅ ፤
መኖርን ስንዋጅ፤
ወረቀት ቀዳደን፤
ቦጭቀን፤
ቦጫጭቀን፤
እየጎዘጎዝን፤
ሰፈር ስናበላሽ፤
መንደር ስናቆሽሽ፤
ቡና አፍልተን፤
ቁርሱን በልተን፤
ደግሞ ስንጣላ፤
ይጠፋናል መላ፤
ኩርኩም ስንቃመስ፤
ጮኸን ስንዋቀስ፤
መተቃቀፍ በማግስቱ፤
መንከባለል በክረምቱ፤
ስንቱ አለፈ በጊዜያቱ።
የእቃቃ ቤታችን፤
ያለምነዉ ኑሯችን፤
ጨዋታዉ ፈረሰ፤
ዳቦዉ ተቆረሰ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤62🔥4👍3
•
[የውሃ ውርደቱ — የዥረት ቅሌቱ......
«መመለሱ ላይቀር ጎብጦ መደፋቱ ፤
"ፋውንቴን ነህ" ተብሎ ወደ ላይ መውጣቱ ።» ]
•
እኔ ገራም የምንጭ ውሃ .....
ኩልል ያልኩኝ ድምጽ አልባ “ማይ” ፤
ተራራ ላይ የቆምሽውን ክንፋም ውበት
በሩቅ የማይ ።
ክብርስ ለእኔ መውረድ ነው
መፍሰስ ቁልቁል በመሬት ፣
አንቺ ደግሞ ከከፍታው
በክንፍሽ አቅም መቆዬት ።
እንዳይሆን አርጎታል መቼም
ተፈጥሮ ነው እንቆቅልሽ ፤
እንዳንቺ ወደ ደመና
ከፍ ማለት ምን አውቅልሽ?!
ዥረት ነኝ እንዳ
•
መቼም ኗሪ ዝም አያውቅም ....
ይበልሽ ያሻውን ይፍረድ ፣
ዝቅ በይ “ውረጅ እንውረድ” ።
•
እንደዚህ ነግሬሽ እንጂ
መሪር ሀቁን አሳውቄ ፤
ውሃ ብሆን (እንዳ
ብሞክር እንኳን አልደርስም ፤
ተፈጥሮ ሕጉን አልጥስም ።
አንቺ ግን የመጣሽ እንደሁ.....
«ቤቷ ነበር ያ ደመና ....
ቤቷ ነበር ያ ተራራ ፣
እዩዋት ክንፍ እንደሌላት
በዥረት ጀርባ ተሳፍራ ፣
ወረደች! አይ ተዋረደች
አጃዒብ ፍቅር! » ይባላል
ማ`ናችን ብንቀል ይቀላል?
•
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
[የውሃ ውርደቱ — የዥረት ቅሌቱ......
«መመለሱ ላይቀር ጎብጦ መደፋቱ ፤
"ፋውንቴን ነህ" ተብሎ ወደ ላይ መውጣቱ ።» ]
•
እኔ ገራም የምንጭ ውሃ .....
ኩልል ያልኩኝ ድምጽ አልባ “ማይ” ፤
ተራራ ላይ የቆምሽውን ክንፋም ውበት
በሩቅ የማይ ።
ክብርስ ለእኔ መውረድ ነው
መፍሰስ ቁልቁል በመሬት ፣
አንቺ ደግሞ ከከፍታው
በክንፍሽ አቅም መቆዬት ።
እንዳይሆን አርጎታል መቼም
ተፈጥሮ ነው እንቆቅልሽ ፤
እንዳንቺ ወደ ደመና
ከፍ ማለት ምን አውቅልሽ?!
ዥረት ነኝ እንዳ
ኗኗሬ
"ውረጅ እንውረድ" ነው ምልሽ ።•
መቼም ኗሪ ዝም አያውቅም ....
ይበልሽ ያሻውን ይፍረድ ፣
ዝቅ በይ “ውረጅ እንውረድ” ።
•
እንደዚህ ነግሬሽ እንጂ
መሪር ሀቁን አሳውቄ ፤
ውሃ ብሆን (እንዳ
መሌ)
አልወስድሽም አሳስቄ ።
•
ውብዬ ...
(ወደድኩም ብዬ.....)
ወዳንቺ ሽቅብ ለመውጣት ብሞክር እንኳን አልደርስም ፤
ተፈጥሮ ሕጉን አልጥስም ።
አንቺ ግን የመጣሽ እንደሁ.....
«ቤቷ ነበር ያ ደመና ....
ቤቷ ነበር ያ ተራራ ፣
እዩዋት ክንፍ እንደሌላት
በዥረት ጀርባ ተሳፍራ ፣
ወረደች! አይ ተዋረደች
አጃዒብ ፍቅር! » ይባላል
ማ`ናችን ብንቀል ይቀላል?
•
By @Bekalushumye
@getem
@getem
@getem
❤30👍3
ጊዜው ተቀይሮ
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ
ብናኝ ትቢያ አክሎ
ሁሉ እንኳን ቢሆን ፥ የማይታመን
አንተ ግን እመን
አንተ ግን ታመን
አሁንም በግ ሁን ፥ በፍየል ዘመን ።
ግዴታ አይደለም
ወከባን መልመድ
ወቅትን መዛመድ
ከጊዜው እኩል ፥ አብሮ መራመድ
ስለዚህ ውረድ !
እምቢ በል ገግም
ቀስ ብለህ አዝግም ።
አጉል መሰልጠን አያስፈልግም ።
ክፋት የለውም
በወግ በወጉ
ለገዢ ሀሳብ ቦታ ቢለቁ
ያረጀን ነገር በአዲስ ቢተኩ
ግን ደሞ አሉ - የማይነኩ ።
በጊዜ ፍጥነት የማይለኩ ።
እስካሁን ከመጣው
ገናም ከሚያመጣው
ከቁስ ከማሽኑ
ዘመን የማይሽርህ ፥ አንተ ነህ ፋሽኑ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
ፍቅር ጥምቡን ጥሎ
ብናኝ ትቢያ አክሎ
ሁሉ እንኳን ቢሆን ፥ የማይታመን
አንተ ግን እመን
አንተ ግን ታመን
አሁንም በግ ሁን ፥ በፍየል ዘመን ።
ግዴታ አይደለም
ወከባን መልመድ
ወቅትን መዛመድ
ከጊዜው እኩል ፥ አብሮ መራመድ
ስለዚህ ውረድ !
እምቢ በል ገግም
ቀስ ብለህ አዝግም ።
አጉል መሰልጠን አያስፈልግም ።
ክፋት የለውም
በወግ በወጉ
ለገዢ ሀሳብ ቦታ ቢለቁ
ያረጀን ነገር በአዲስ ቢተኩ
ግን ደሞ አሉ - የማይነኩ ።
በጊዜ ፍጥነት የማይለኩ ።
እስካሁን ከመጣው
ገናም ከሚያመጣው
ከቁስ ከማሽኑ
ዘመን የማይሽርህ ፥ አንተ ነህ ፋሽኑ ።
By Hab Hd
@getem
@getem
@paappii
❤48🔥6😱4🎉1
ዝብርቅርቅ ባለዉ በህይወት አዙሪት፤
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤29👍4🔥2
