ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ - ገላሽን ይንካና
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
❤70👎13🤩12👍10😁8🔥5😱5🎉2
ጥያቄ??
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤44👍7🔥4👎3😁1
መንገደኛው ልቤ ቅጽበት'ዓት ከአንቺ ያደረ
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤24👍15😱2
(በዕምዓዕላፍ)
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
👍38❤35🔥2😢2🎉1
የማርያም መንገድ
.
.
መንፈሴ ሲዝል ሰላሜ ጠፍቶ፤
ልቤ ሲታወክ ዉስጤ ተረትቶ፤
ቢጨንቀኝ ጊዜ........
አጥብቄ ለመንኩ የማርያም መንገድ፤
ካለሁበት ማጥ ያሻግረኝ ዘንድ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
መንፈሴ ሲዝል ሰላሜ ጠፍቶ፤
ልቤ ሲታወክ ዉስጤ ተረትቶ፤
ቢጨንቀኝ ጊዜ........
አጥብቄ ለመንኩ የማርያም መንገድ፤
ካለሁበት ማጥ ያሻግረኝ ዘንድ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤63🔥7👍6
ኤሊና ጥንቸል ተቀጣጠሩ
ማራቶን ሩጫ ሊወዳደሩ።
የውድድሩ ሲያበቃ ሩጫ
እስቲ ገምቱ የማነው ዋንጫ?
— አዝማሪው —
በብላቴና ዕድሜዬ ስለ ህይወት ሲቀኙልኝ
ኤሊም ሆኜ እንድ'ቀድም
ጥንቸሎቼን አስተኙልኝ
መኖር መልካም ቀና ጥበብ የምትሻ
አሁን ባይገባንም
ትርጉም አይታጣም በስተ'መጨረሻ
፩
አየሽ በዚህ ተረት መኖር እንዲህ ይቀኛል
ሸክም ያልከው ዛጎል ጌጥህ ነው ይለኛል
አልችልም ካልክበት
አበቃ ካልክበት
ደሞ በአዲስ ፈና መንገድህን ቀጥል
የናቁት ጠጠር ነው ግዙፉን የሚጥል
ያቅተኛል ብለህ
ይከብደኛል ብለህ
በፍጹም አትፍራ።
ነበልባል ህልምህን
በእንቅልፋም ልቧች ላይ
ጎጆ አድርገህ ስራ።
ልቦናው የበራለት ከትልም ይማራል
ባሪያ ብለው የናቁት በጊዜው ይከብራል
አትፍራ! ግድየለም!
ሰጋር እግሩን አይተህ
❛❛አልቀድመውም አትበል❜❜
የኑሮን ውርርድ ሳትታክት ተቀበል
#ህይወት ጥበበኛው
መልካም ቅኔ አያጣም
ላሸነፈው ዋንጫ
ለደከመው ደሞ እንቅልፍ አይታጣም።
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
ማራቶን ሩጫ ሊወዳደሩ።
የውድድሩ ሲያበቃ ሩጫ
እስቲ ገምቱ የማነው ዋንጫ?
— አዝማሪው —
በብላቴና ዕድሜዬ ስለ ህይወት ሲቀኙልኝ
ኤሊም ሆኜ እንድ'ቀድም
ጥንቸሎቼን አስተኙልኝ
መኖር መልካም ቀና ጥበብ የምትሻ
አሁን ባይገባንም
ትርጉም አይታጣም በስተ'መጨረሻ
፩
አየሽ በዚህ ተረት መኖር እንዲህ ይቀኛል
ሸክም ያልከው ዛጎል ጌጥህ ነው ይለኛል
አልችልም ካልክበት
አበቃ ካልክበት
ደሞ በአዲስ ፈና መንገድህን ቀጥል
የናቁት ጠጠር ነው ግዙፉን የሚጥል
ያቅተኛል ብለህ
ይከብደኛል ብለህ
በፍጹም አትፍራ።
ነበልባል ህልምህን
በእንቅልፋም ልቧች ላይ
ጎጆ አድርገህ ስራ።
ልቦናው የበራለት ከትልም ይማራል
ባሪያ ብለው የናቁት በጊዜው ይከብራል
አትፍራ! ግድየለም!
ሰጋር እግሩን አይተህ
❛❛አልቀድመውም አትበል❜❜
የኑሮን ውርርድ ሳትታክት ተቀበል
#ህይወት ጥበበኛው
መልካም ቅኔ አያጣም
ላሸነፈው ዋንጫ
ለደከመው ደሞ እንቅልፍ አይታጣም።
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤56👍11🔥3
አብሮ መጥፋት
በፍቅር ሰንሰለት እኔን ላንቺ ድሮ፣
ያለፈ ታሪክሽን
የኀጢአቴን ግርሻት ሊያጠፋ ቀን ቀጥሮ፤
"ወደ ኋላ መዞር ላ'ፍታ ሳትመኙ፣
ወደ ፊት ተጓዙ ነጋችሁን ቃኙ!
ለፍቅር ታመኑ ለፍቅር ተቀኙ!"
የሚል ትእዛዝ ሰጥቶን
ትናንትናችን ላይ እቶን እሳት ቢለቅ፣
ወላዋይ መንፈስሽ
ልክ እንደ ሎጥ ሚስት ታየ ሲፍረከረክ፡፡
የቀድሞ ፍቅረኛሽ…
ያ ሁሉ ትዝታ
መጥፋት አብከንክኖሽ በድንገት ስትዞሪ፣
የጨው ሐውልት ግግር
አድርጎ ቢያስቀርሽ የፍጥረት ፈጣሪ፤
ሎጥን ልምሰል ብዬ…
የፍቅርሽ እርምጃ
ከኋላዬ ሲቀር ወደ ፊት አልሄድም፣
አይቼሽ ለማልቀስ
አይቼሽ ለመድረቅ
ያ'ምላኬን ቃል ሽሬ መዞሬ አይቀርም፡፡
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
በፍቅር ሰንሰለት እኔን ላንቺ ድሮ፣
ያለፈ ታሪክሽን
የኀጢአቴን ግርሻት ሊያጠፋ ቀን ቀጥሮ፤
"ወደ ኋላ መዞር ላ'ፍታ ሳትመኙ፣
ወደ ፊት ተጓዙ ነጋችሁን ቃኙ!
ለፍቅር ታመኑ ለፍቅር ተቀኙ!"
የሚል ትእዛዝ ሰጥቶን
ትናንትናችን ላይ እቶን እሳት ቢለቅ፣
ወላዋይ መንፈስሽ
ልክ እንደ ሎጥ ሚስት ታየ ሲፍረከረክ፡፡
የቀድሞ ፍቅረኛሽ…
ያ ሁሉ ትዝታ
መጥፋት አብከንክኖሽ በድንገት ስትዞሪ፣
የጨው ሐውልት ግግር
አድርጎ ቢያስቀርሽ የፍጥረት ፈጣሪ፤
ሎጥን ልምሰል ብዬ…
የፍቅርሽ እርምጃ
ከኋላዬ ሲቀር ወደ ፊት አልሄድም፣
አይቼሽ ለማልቀስ
አይቼሽ ለመድረቅ
ያ'ምላኬን ቃል ሽሬ መዞሬ አይቀርም፡፡
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
❤42🔥5👍2🤩2
(የሞገሴ ልጅ)
ከእኔ ካልመጣ
ሂጂልኝ ማለትን - አፌ ካልተማረ፣
ካልሄድኩ ካለ ልብሽ፣
ብከለክለውስ - መቼ ትቶት ቀረ?
ኁሌ አትሂጂ ባይ
ኁሌ ልሂድ በሚል ረባሽ ከተገፋ፣
ሰይጣንን ያስቀናል፣
እንኳንስ በሌላው በራሱ ሲከፋ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ከእኔ ካልመጣ
ሂጂልኝ ማለትን - አፌ ካልተማረ፣
ካልሄድኩ ካለ ልብሽ፣
ብከለክለውስ - መቼ ትቶት ቀረ?
ኁሌ አትሂጂ ባይ
ኁሌ ልሂድ በሚል ረባሽ ከተገፋ፣
ሰይጣንን ያስቀናል፣
እንኳንስ በሌላው በራሱ ሲከፋ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤30🔥5👍2🤩1
እጠራጠራለሁ
ተቃርበሽ ተቃርበሽ ስጠፊ ስላየሁ
ደግሞም እቀናለሁ
እንደኔ ምትወጂው ይኖር ወይ እላለሁ
አልመስል አለኝ እውነት-የምትስሚኝ የምታቅፊኝ
ተቃርበሽ ልጠፊኝ?
ፍቅር ጣዕም አስለምደሽ ከአይን ልደበዝሽ
ለምንድነው የምትስሚኝ?
ለምንድነው የምስምሽ?
እጠራጠራለሁ
ስትርቂኝ ስላየሁ
ስትስሚኝ ስላየሁ
ካንቺ ፍቅር ውጥን ብርቅም ብሸሽም
እወድሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም
አፈቅርሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም።
ብቻ
አለሁ እንዳለነው
ስትቀርቢኝ እያየው
ስትርቂኝ እያየው
አለሁኝ እንዳለሁ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ተቃርበሽ ተቃርበሽ ስጠፊ ስላየሁ
ደግሞም እቀናለሁ
እንደኔ ምትወጂው ይኖር ወይ እላለሁ
አልመስል አለኝ እውነት-የምትስሚኝ የምታቅፊኝ
ተቃርበሽ ልጠፊኝ?
ፍቅር ጣዕም አስለምደሽ ከአይን ልደበዝሽ
ለምንድነው የምትስሚኝ?
ለምንድነው የምስምሽ?
እጠራጠራለሁ
ስትርቂኝ ስላየሁ
ስትስሚኝ ስላየሁ
ካንቺ ፍቅር ውጥን ብርቅም ብሸሽም
እወድሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም
አፈቅርሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም።
ብቻ
አለሁ እንዳለነው
ስትቀርቢኝ እያየው
ስትርቂኝ እያየው
አለሁኝ እንዳለሁ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤28👍20😢4
ወንድ አይደለሁ?
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤58🔥4👎2🎉2🤩2
ፍትህ ለቃላት
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤76👍22😁13🔥9👎4🤩4🎉3
( ፈቀቅ በል )
==========
ከቆይታህ ትዝላለህ
ከቆይታህ ይደክምሀል
ተስፋ ማጣት መጨላለም
የሀዘን እሾህ ይወጋሀል
ስትባክን እንደመሸ
ሌቱም እንዲያ .. ይነጋብሃል
ግዴለህም ' ፈቀቅ በል '
ብትሰማው ይሻልሀል !
ቸር መዳፉ .. ኋላ ደርሶ ለታመነ
ስንት ባርያ ዋስ ሲሆነው
የእረፍት ውሃ ሰላም ደስታን
ከደጃፉ ሲያዘግነው
አንተ ልጁ እስከመች ነው
በዓለም ጉያ ምትባክነው ??
(ጴጥሮስ ጓዴ)
እርሳ የቀን መከራህን
መረብህን ዳግም ጣለው
በባዶነት የሚሰራ
ቸር አምላክ ነው ፊትህ ያለው
'ፈቀቅ በል ' ጥቂት ስንዝር
ከትላንቱ ድካም ብክነት
የመከነ ተስፋህ ግቡ
በርሱ ቃል ነው ሚሰምርለት !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
==========
ከቆይታህ ትዝላለህ
ከቆይታህ ይደክምሀል
ተስፋ ማጣት መጨላለም
የሀዘን እሾህ ይወጋሀል
ስትባክን እንደመሸ
ሌቱም እንዲያ .. ይነጋብሃል
ግዴለህም ' ፈቀቅ በል '
ብትሰማው ይሻልሀል !
ቸር መዳፉ .. ኋላ ደርሶ ለታመነ
ስንት ባርያ ዋስ ሲሆነው
የእረፍት ውሃ ሰላም ደስታን
ከደጃፉ ሲያዘግነው
አንተ ልጁ እስከመች ነው
በዓለም ጉያ ምትባክነው ??
(ጴጥሮስ ጓዴ)
እርሳ የቀን መከራህን
መረብህን ዳግም ጣለው
በባዶነት የሚሰራ
ቸር አምላክ ነው ፊትህ ያለው
'ፈቀቅ በል ' ጥቂት ስንዝር
ከትላንቱ ድካም ብክነት
የመከነ ተስፋህ ግቡ
በርሱ ቃል ነው ሚሰምርለት !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
❤59👍11🔥3
"አማኝ ነን ባዬች"
ከአፍ ከክንድህ እየጠረቡ
በድንክ ህልማቸው
በዘር መትረው ሰውን ገነቡ
ከፈረሰ አምላክ
ፈጣሪ የሌለው ፍጡር ተሰራ
እንዳያምን ገፉት እንዳይሸሽህ ፈራ
°
°
እናም
. . . . .የዚህ ታሪክ ፍቺው ሲተነተን
ምድር አይገባም በዘር ለሚበተን
❛❛በብሄር ነው ቢባል
በቀለም ነው ቢባል
በሀገር ነው ቢባል ❜❜
በዘር መካፋፈል መንስኤ ምንነቱ
አንድ ላይ መሆን ነው የሰው ልዩነቱ
በሀገር ያጣመሩት በእምነት ይጣረሳል
በብሄር የገነቡት በቀለም ይፈርሳል
ልቡናው ያልቀናለት
ካፈርም ዘር መርጦ ከስጋው ይዋቀሳል
በማፍረስ አይጸናም
-------ኬላ 'ና ድንበር ስለ'ገረሰሱ
በመለያየት ነው አንድ የመሆን መልሱ
አንቺም ካለሽበት እኔም ካለሁበት
ባንድ ላይ ተጋርተን
የአንድ ዛፍ እስትንፋስ የአንድ ጸሀይ ጮራ
ገላሽም ገላዬን
ልብሽ ልቦናዬን ከሸሸ ከፈራ
ዘር በእንባ ቢወድም ሀገር ቢፈራርስ
ይቅርታ ብቻ ነው ፍቅርን የሚመልስ
በብሄር አይደለ
በቀለም አይደለ
በሀገር አይደለ የሰው ልዩነቱ
በፈረሰ እምነት ላይ ስለተገነባ
----------አይጸናም እውነቱ
አንዲት ጸሀይ ሞቀን
በአንዲት ጀንበር ደምቀን
ጦር የሚያማዝዘን
ሀገርም አይደለ ብሄርም አይደለ
ከልባችን ላይ ነው ኬላው የተሳለ!
By የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤47👍8🔥2🎉1🤩1