ሆያ ሆዬ .....ሆ!
ሆያ ሆዬ.......ሆ!
°°°°°•••••°°°°°•••••
ተቀሰቀሰብኝ ቡሄ ትዝታዬ
ልቤ ስትፈነጥዝ ስትሰክር በፌሽታ
ከእኩዮቼ ጋራ በቡሄ ጨዋታ
በዛ ላይ ነፃነት አይቆጡም ጌታ፡፡
ገመድ እየገመድኩ ጅራፍ ስሰራ
በጩኸቱ ሳበስር ወጥቼ ከጋራ
በሆያሆዬ ዜማ በሞቀው ጭፈራ
ደሞ ይመሽና ችቦዬን ሳበራ
በልጅነት ፍቅር ወረት በማያውቀው
በጭፈራ ወጀብ ልብን በሚያሞቀው
የጌቶችን በር አፍ ሚያበስረው ደርሶ
ባባቶች ምርቃት ሙልሙል ፍቅር ቆርሶ
በእናቶች ስጦታ ከመቀነታቸው
በታቦሩ ብርሃን ሞልቶ ሰላማቸው
አስታቅፈውን ሙልሙል ሲፈስስ ፈገግታቸው
አይ ልጅነት ደጉ ምን አለ ከዚህ በላይ
ችቦ ተለኩሶ ፍቅር በርቶ ሲታይ፡፡
እንኳን አደረሰን!
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
ሆያ ሆዬ.......ሆ!
°°°°°•••••°°°°°•••••
ተቀሰቀሰብኝ ቡሄ ትዝታዬ
ልቤ ስትፈነጥዝ ስትሰክር በፌሽታ
ከእኩዮቼ ጋራ በቡሄ ጨዋታ
በዛ ላይ ነፃነት አይቆጡም ጌታ፡፡
ገመድ እየገመድኩ ጅራፍ ስሰራ
በጩኸቱ ሳበስር ወጥቼ ከጋራ
በሆያሆዬ ዜማ በሞቀው ጭፈራ
ደሞ ይመሽና ችቦዬን ሳበራ
በልጅነት ፍቅር ወረት በማያውቀው
በጭፈራ ወጀብ ልብን በሚያሞቀው
የጌቶችን በር አፍ ሚያበስረው ደርሶ
ባባቶች ምርቃት ሙልሙል ፍቅር ቆርሶ
በእናቶች ስጦታ ከመቀነታቸው
በታቦሩ ብርሃን ሞልቶ ሰላማቸው
አስታቅፈውን ሙልሙል ሲፈስስ ፈገግታቸው
አይ ልጅነት ደጉ ምን አለ ከዚህ በላይ
ችቦ ተለኩሶ ፍቅር በርቶ ሲታይ፡፡
እንኳን አደረሰን!
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤21👍14🎉1
እግረ-መንገድ
_ _ _ _ _ _ _ _
ጡሩንባውን ሰምተኸ፤
እንደ አጋጣሚ...
ከድንኳኑ ዘልቀኸ፤
ከሟች ፎቶግራፍ
ፊትለፊት ተቀምጠኸ፤
በጨዋታ መሐል
ድንገት ቀና ብለኸ፤
ያየኸው እንደሆን፤
ከሳሎን ያኖርከው
ያንተ ፎቶግራፍ
ትዝ ብሎ ይሆን?!
ያ... የልደትኸ ፎቶ
ያ... የምርቃትኸ ፎቶ
ያ... የሠርግኸ ፎቶ፤
የቤትኸን ግርግም
ግድግዳውን ሞልቶ፤
ዙ..ሪ..ያ..ው..ን ያለው፤
አለ'ለት ቀራኒዮ
ከድንኳኑ የሚሰቅለው።
ሳሙኤል አለሙ
@yeketemawmenagn
@getem
@getem
@getem
_ _ _ _ _ _ _ _
ጡሩንባውን ሰምተኸ፤
እንደ አጋጣሚ...
ከድንኳኑ ዘልቀኸ፤
ከሟች ፎቶግራፍ
ፊትለፊት ተቀምጠኸ፤
በጨዋታ መሐል
ድንገት ቀና ብለኸ፤
ያየኸው እንደሆን፤
ከሳሎን ያኖርከው
ያንተ ፎቶግራፍ
ትዝ ብሎ ይሆን?!
ያ... የልደትኸ ፎቶ
ያ... የምርቃትኸ ፎቶ
ያ... የሠርግኸ ፎቶ፤
የቤትኸን ግርግም
ግድግዳውን ሞልቶ፤
ዙ..ሪ..ያ..ው..ን ያለው፤
አለ'ለት ቀራኒዮ
ከድንኳኑ የሚሰቅለው።
ሳሙኤል አለሙ
@yeketemawmenagn
@getem
@getem
@getem
👍14❤13
◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌
by የአብስራ_ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
በል እንግዲህ እግዜር
መዝገብህን ክፈት| ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ| ስጋና አጥንት ሚሰረስር
፩
❛❛እዚህ እታች ሰፈር
ማዳበሪውን እንዳነገተ
ሀይላድ ሲለቅም
መኪና ገጭቶት| አንድ ህጻን ሞተ
ይሙት ግድ የለም
"ነበር አልን እንጂ"
የኖረው ህይወት| ህይወት አይደለም
ትራፊ እንጀራ ለዕልፍ አዕላፍ ያራቀራመተ
ባርከው እያለህ
ሳትባርክለት እርቦት የሞተ
ቀብሮት ወንድሙን
ከአይኑ አብሶ የእንባ ደሙኑ
ኑሮን ሊጋፋ
ለሀይላንድ ልቃሚ አንገት ቢደፋ
ያው እንደወጣ አልተመለሰም
እንደ ጥያቄው እንደ ምኞቱ
የሱን አልን እንጂ
ታሪኩ እራሱ ታሪክ ነው የስንቱ❜❜
በል እንግዲ እግዜር
መዝገብክን ክፈት| ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ| ስጋና አጥንት የሚሰረስር
፪
ደሞም አንዲት ሴት
የቀሚስ ቅዷ የጭኗ ቁስል
የአርብ ዕለት ጌጥክን ግርፋት ምስል
እንደከተበ
አይኗ በምሬት
የራሄል እንባ እያዘነበ
ስታልጎመጉም እንዲ ትል ነበር
❛❛የጫንክብኝን የህይወት ቀንበር
ችዬ ስጋፋው
ስለምን ወንዱን ስሜት አስከፋው
የገፋ ባሌን
ዝሙት ሀጥያቱን ገና ሳለምደው
ከሞት መራራ
ብልቱ መርቶ የሚያራምደው
በእናቱ እንጀራ
በሰባ እጆቹ ጨፍልቆ ይዞ
የሴት ገላዬን በቁም ገንዞ
በድን ሲያስቀረኝ
ቂም እንዳይመስልህ
በእንባ ዘለላ የሚያናግረኝ
ይልቅ መዳፍክን
የአንገት ማህተቤን| ወሰድ ከህይወቴ
አንቆ ሲደፍረኝ
ምስለ ስዕልህ ገዝፎ ከቤቴ
ተስፋ እንዳይሆነኝ ?
ስንቅ እንዳይሆነኝ ?
ኖረህ ዝምታ እያስደፈረኝ
ሆድ ይፍጀው እንጂ
ችዬ ያልነገርኩህ ብዙ ነበረኝ።❜❜
በል እንግዲህ እግዜር
መዝገብህን ክፈት| ጆሮህን ቀስር
ብሶት ልንገርህ| ስጋና አጥንት የሚሰረስር
፫
ደግሞ'ም ትዝ አለኝ
አንዱ ፈላስፋ የተናገረው
ከትቦ ያኖረው
❛❛የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
ውርቂያኖስ በእንባ እንደመለካት
ተጠማው ያለን በሀሞት ማርካት
እየቀበሩ
ማማረር ሀጥያት ብሎ መመካት
ነድያን አልፎ
ዲያቆን ፍለጋ መቅድስ ማንኳኳት❜❜
ደሞም ትዝ አለኝ
ትዝ አለኝ ብዙ. . . .
በሀረግ በስንኝ እንዴት ይቋጠር ?
ጋን ተሸክሞል ሰው እንደጠጠር!
ይልቅ ዝም ነው !
ሁሌም ዝም . . . .ዝም
የዚህ አለም ቁስል የዚህ አለም ብሶት
የትኛው ጠቢብ| ደራሲ ደርሶት ?
የትኛው አምላክ| እንባን አብሶት ?
ይልቅ ዝም ነው!
ሁሌም ዝም..... ዝም
ሰሚ ሳይኖረን አንናዘዝም!።
፬
እናም በል እግዜር
መዝገብህን ዝጋው| ጆሮ ዳባ አልብስ
የሰማ ሳይሆን
ስሙኝ ያለ ነው የሚያደባብስ
!. . .by የአብስራ_ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
Telegram
Yeabisra Samuel 📓🖋️
#ስነ_ግጥም
❤47😢7👍6😁2
◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌◌
@getem
@getem
@getem
ያው እንደምታውቂው
ሀገርሽ ሀገሬው እንቆቅልሽ ለምዶ
ሀገር ልስጥሽ ይላል ለመልሱ ተሰዶ
ውል አልባ ጥያቄ
ምላሽ አልባ ምኞት እንደ አደይ ይፈልቃል
መፈለጉን እንጂ ማግኘቱን ማን ያውቃል?
°
ያው እንደምታውቂው
አንቺም እንቆቅልሽ ለጉድ ትወጃለሽ
እንቆቅልህ . . . ምን አውቅልሽ?
፩ (ጥያቄ)
ከለምለም ሰርዶ ከጤዛው
ተማሪ እረኛ ተኝቷል
የአይኖቹን መክደን ጠብቆም
ተኩላውም በጎቹን በልቷል
የኔታም ከዋርካው ግርጌ
ይሄንን እያጣመሩ
እንዲህ የሚል ቅኔ አስተማሩ:
፪(መልሱ)
በጉም! እረኛ አለኝ ብሎ ጠባቂን አመነ
የተኩላ እራት ሆነ
(እናም ተማሪ ሆይ)
ጠባቂ አለኝ ብለህ
አዳኝ አለኝ ብለህ ከእሳት አታመልጥም
ይልቅስ ለትግሉ
ሰይፍህን አዘጋጅ ክንድህን አፈርጥም!
@getem
@getem
@getem
❤19👍5
, ( ደጅሽ ፀናሁ )
ለለመነ ሁሉ ለጠዬቀ ሁሉ
ይሰጣል ስለሚል የክርስቶስ ቃሉ
በርሽን አንኳኳሁ መጣሁ ልለምንሽ
ዳግም ደጅሽ ፀናሁ ቆምኩና ከጎንሽ
እኔማ ወዳጅሽን እኔንማ አፍቃሪሽ
ጭንቅና ህመሜን ቀርበሽ ብታይልይ
ድንገት እግዚሔር ፈቅዶ ልብሽ ቢራራልይ
ሱባኤ ገብቼ
አርባ ቀን አርባ ሌት በስምሽ ላፀልይ
አወ እገባለሁ አወ እፀልያለሁ
ብትመጭም ባትመጭም እውነት እልሻለሁ
በስምሽ ደግሼ ገና እዘክራለሁ
ይልቅ አቡዬና ስላሴን በሩን ተሳልመሽ
ጧፍና ሻማሽን መዕባሽን ሰተሽ
ዳግም ለእመብርሃን ጧፍን ተስለሽ
ከፍቅራችን ፅዋ መተሽ ተቋደሽ
By Habtamu dama
@getem
@getem
@getem
ለለመነ ሁሉ ለጠዬቀ ሁሉ
ይሰጣል ስለሚል የክርስቶስ ቃሉ
በርሽን አንኳኳሁ መጣሁ ልለምንሽ
ዳግም ደጅሽ ፀናሁ ቆምኩና ከጎንሽ
እኔማ ወዳጅሽን እኔንማ አፍቃሪሽ
ጭንቅና ህመሜን ቀርበሽ ብታይልይ
ድንገት እግዚሔር ፈቅዶ ልብሽ ቢራራልይ
ሱባኤ ገብቼ
አርባ ቀን አርባ ሌት በስምሽ ላፀልይ
አወ እገባለሁ አወ እፀልያለሁ
ብትመጭም ባትመጭም እውነት እልሻለሁ
በስምሽ ደግሼ ገና እዘክራለሁ
ይልቅ አቡዬና ስላሴን በሩን ተሳልመሽ
ጧፍና ሻማሽን መዕባሽን ሰተሽ
ዳግም ለእመብርሃን ጧፍን ተስለሽ
ከፍቅራችን ፅዋ መተሽ ተቋደሽ
By Habtamu dama
@getem
@getem
@getem
❤43👍7🔥4😁3
ናተይ ኩሉ
መዋደዳችንን እስካመነው ድረስ
ነይ ኪዳን እንሰር በቃል እንታነፅ
እቲ ዓውዲ ስድራቤት ዘይኮነስ አንዳችም ጥም
ፍቅር ካለ ሀገር አለ በኢትዮጵያ ተስፋ አንቆርጥም
ድሕሪ ሓደ ቦታ ኣብ ኣቦ ዕዳ
በደማችን እርቅ ይወርዳል መዓልቲ ሞት ግንባር ሓዳ
ናተይ ከሉ
እንዋደድ የለ....እንፋቀር የለ
ልክ እንዳምናው እንደበስቲያ ትላንትና
ዘይንጡፍ ኣይኮነን: ዝተፈላለየ ፍቕሪ አሉንና
አንቺን ከኔ ቢያርቁሽም ቢነጥሉሽ ከብሌኔ
ተስፋ አትቁረጪ ፍቅሬ
ተስፋ አልቆርጥም እኔ
ነገንም እንኑር ዛሬም አለንና
ሐደ እንሁንና
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
መዋደዳችንን እስካመነው ድረስ
ነይ ኪዳን እንሰር በቃል እንታነፅ
እቲ ዓውዲ ስድራቤት ዘይኮነስ አንዳችም ጥም
ፍቅር ካለ ሀገር አለ በኢትዮጵያ ተስፋ አንቆርጥም
ድሕሪ ሓደ ቦታ ኣብ ኣቦ ዕዳ
በደማችን እርቅ ይወርዳል መዓልቲ ሞት ግንባር ሓዳ
ናተይ ከሉ
እንዋደድ የለ....እንፋቀር የለ
ልክ እንዳምናው እንደበስቲያ ትላንትና
ዘይንጡፍ ኣይኮነን: ዝተፈላለየ ፍቕሪ አሉንና
አንቺን ከኔ ቢያርቁሽም ቢነጥሉሽ ከብሌኔ
ተስፋ አትቁረጪ ፍቅሬ
ተስፋ አልቆርጥም እኔ
ነገንም እንኑር ዛሬም አለንና
ሐደ እንሁንና
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤28
▵∘∘∘∘∘▴∘⊙⊙⊙⊙⊙⊙⊙⊙⊙
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
ስንወቃቀስ እድሜያችን ሸሸ
ስንገፋፋ ቀናችን መሸ
በመውደድ አጥቢያ በቦረቅንበት
የመለያየት ሰርዶ በቀለ
ፍቅራችን በቂም እየጠለሸ
¹
(በርግጥ...)
ሄጃለው ካልሺኝ አትመለሺም
እኔም እንዳምናው አልጠብቅሽም
ማነው ባለበት ያልተቀየረ ?
ከጊዜ ጋራ ውሎ እያደረ!
መዋደድ ማለት
ትናንት መምስል ፍጹም አይደለም!
ዛሬ ላይ ሆነም ትናንትን ማለም
ከህይወት ጋር ሰርክ እያደሩ
ለጋ ህልሞቼ ደጅሽ ነበሩ
²
(እናም...)
ያመነው እውነት ከሚነጥለን
በመለያየት ከምንከፋ
ህይወት አንዴ ናት
ጨበጥናት ስንል የምትጠፋ
ተይው ክስሽን አናሸንፍም ድል አንረታ
ከልቡ በላይ ዳኛ የለውም ወዶ የተረታ
³
(ደግሞም...)
ካለኔ በዕንባ መኖርሽን
አልፎ ሄጅ ንፋስ ነገረኝ
አውቃለሁ እንደምትወጂኝ
ጥላቻሽ እንደማይሽረኝ
ከኔም ዘንድ መተይሽ ባየሽው
የመኖር ምኞቴ ረግፏል
ሄጃለሁ ካልሺኝ ጀመሮ
ክንፎቼ ላባ ተገፏል
አድባሩም አውዱም አስጠላኝ
ወዳጆች ካልኳቸው ሸሸሁ
ዋልሽበት ባሉኝ እየዋልኩ
በራፍሽን ስከል አመሸሁ
⁴
(እናም...)
በመሸ ቀን በሌት ጀንበር
ስንካስስ ባስረፈድነው
በሰከነ ህያው ፍቅር
ስንራራቅ ባበረድነው…
የቀረንን ነጣላ እድሜ
እንኑራት በፈገግታ
አረፍ ብዬ ልጠብቅሽ
ከትናንቱ ከአምናው ቦታ
!#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤48👍3
እናቴ 🥰
.
.
.
ቢጨላልም ንጋት ቀኗ፤
ሲደካክም ወገብ ጎኗ፤
ማጀት ቤቷ ቢጎድልባት፤
ስቃይ ችግር ቢደቁሳት፤
በሀዘን ጊዜ በደስታዋ፤
አይከደን ሁሌም ጥርስዋ፤
ብትከፋ ምን ቢያደማት፤
ፈገግታ ነዉ የሚቀድማት።
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
.
ቢጨላልም ንጋት ቀኗ፤
ሲደካክም ወገብ ጎኗ፤
ማጀት ቤቷ ቢጎድልባት፤
ስቃይ ችግር ቢደቁሳት፤
በሀዘን ጊዜ በደስታዋ፤
አይከደን ሁሌም ጥርስዋ፤
ብትከፋ ምን ቢያደማት፤
ፈገግታ ነዉ የሚቀድማት።
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤99😢9👍2
#Akka_Qossaatti
ባካል ግብር ሳንገናኝ
ያይንን ውሃ ሳንረዳ
ቴሌግራም አስተዋውቆን
ሳንተያይ እንደባዳ
እንዳፍለኞች ሳናወራ
ሳታቀብጠኝ ሳላቀብጣት
ድብርት ቢጤ እየጫራ
ሳላገኛት እሷን ማጣት
ውለን አድረን መጨቃጨቅ
መተራረብ ለፍቅር ቃል
ኢመንት ነው መተያየት
መቀራረብ ብዙ ያዘልቃል
ከጎኔ እንዳለች ሰው
ሳይሰማኝ ሩቅ ያለሽ
አጠገቤ እንዳለሽ
ተቃርበሺው ይህን ቀልቤን
Waggaan tokko akka qossaatti darbe
ሳይታወቀኝ ሳይታወቅሽ
ቀናት ወርን እየተደገፈ
እንደ ቀልድ
እንደ ዋዛ አንድ አመት አለፈ።
እንኳን አደረሰን🍾 ለኔና ላንቺ ብቻ😁
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ባካል ግብር ሳንገናኝ
ያይንን ውሃ ሳንረዳ
ቴሌግራም አስተዋውቆን
ሳንተያይ እንደባዳ
እንዳፍለኞች ሳናወራ
ሳታቀብጠኝ ሳላቀብጣት
ድብርት ቢጤ እየጫራ
ሳላገኛት እሷን ማጣት
ውለን አድረን መጨቃጨቅ
መተራረብ ለፍቅር ቃል
ኢመንት ነው መተያየት
መቀራረብ ብዙ ያዘልቃል
ከጎኔ እንዳለች ሰው
ሳይሰማኝ ሩቅ ያለሽ
አጠገቤ እንዳለሽ
ተቃርበሺው ይህን ቀልቤን
Waggaan tokko akka qossaatti darbe
ሳይታወቀኝ ሳይታወቅሽ
ቀናት ወርን እየተደገፈ
እንደ ቀልድ
እንደ ዋዛ አንድ አመት አለፈ።
እንኳን አደረሰን🍾 ለኔና ላንቺ ብቻ😁
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤43👍5😁3🎉2
ቅዳጅ ሃሳቦች
ለመድብል ያልጣፈው ቀርቶ ባጭር ጉዞ
አያለሁ ወረቀት ቅዳጅ ሃሳብ ይዞ፡፡
ለመድፋት ሲኳትን ጭራሽ ሲፈርስበት
ሃሳብ በምጥ ወልዶ በኖ ሲጠፋበት፤
ከግጥም ጥመኛው ከዛ ከአብሮ አደጌ
እልፍ ቅዳጅ አለ ከማረፊያው ግርጌ፡፡
የሀሳብ ቁርጥራጭ የወረቀት ቅዳጅ
ፍቅር የተራበ ያጣ ዘመድ ወዳጅ
የሚጮህ ዝምታ በእንባ የታጀበ
በጉንጭ ሸራ ላይ በዕድሜ የነተበ፤
እልፍ ሀሳብ ይዞ ጠጥቶ አዋራ
ሰሚ በሌለበት በጩኸት ሚጣራ
ከዛ ከሱሰኛው ከአብሮ አደጌ ጓዳ
ጉም መሳይ ህልሙ በራሱ የተቀዳ
አያለሁ ዘወትር ጭምድድ ወረቀቶች
በጅምር የቀሩ ቅንጥብጣብ ትንቢቶች፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
ለመድብል ያልጣፈው ቀርቶ ባጭር ጉዞ
አያለሁ ወረቀት ቅዳጅ ሃሳብ ይዞ፡፡
ለመድፋት ሲኳትን ጭራሽ ሲፈርስበት
ሃሳብ በምጥ ወልዶ በኖ ሲጠፋበት፤
ከግጥም ጥመኛው ከዛ ከአብሮ አደጌ
እልፍ ቅዳጅ አለ ከማረፊያው ግርጌ፡፡
የሀሳብ ቁርጥራጭ የወረቀት ቅዳጅ
ፍቅር የተራበ ያጣ ዘመድ ወዳጅ
የሚጮህ ዝምታ በእንባ የታጀበ
በጉንጭ ሸራ ላይ በዕድሜ የነተበ፤
እልፍ ሀሳብ ይዞ ጠጥቶ አዋራ
ሰሚ በሌለበት በጩኸት ሚጣራ
ከዛ ከሱሰኛው ከአብሮ አደጌ ጓዳ
ጉም መሳይ ህልሙ በራሱ የተቀዳ
አያለሁ ዘወትር ጭምድድ ወረቀቶች
በጅምር የቀሩ ቅንጥብጣብ ትንቢቶች፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤26👍6
ቦግ.....እልም
.
.
ጭላንጭል ብርሃን በጽልመት ተከባ፤
ቦግ...እልም ስትል ስትወጣ ስትገባ፤
አለች እንዳይሏት በርታ ትጠፋለች፤
ከሰመችም ሲሏት ከሩቅ ትታያለች፤
ቦግ.......እልም፤
ጭልም......ጭልምልም፤
ብልጭ.....ድርግም፤
የኔም ህይወት እንዲሁ......
አይሆንላት ተሸነፈች፤
አይሳካም ተሰበረች፤
አበቃላት ወድቃ ቀረች፤
ብለዉ ሲናገሩኝ..........
የሩቋ ወጋገን ጎልታ 'ምትታየኝ፤
በተነሳሁ ቁጥር ወደኔ 'ምትቀርበኝ፤
ጠፍታ የማትጠፋዉ ያቺ ብርሃን ነኝ።
..............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ጭላንጭል ብርሃን በጽልመት ተከባ፤
ቦግ...እልም ስትል ስትወጣ ስትገባ፤
አለች እንዳይሏት በርታ ትጠፋለች፤
ከሰመችም ሲሏት ከሩቅ ትታያለች፤
ቦግ.......እልም፤
ጭልም......ጭልምልም፤
ብልጭ.....ድርግም፤
የኔም ህይወት እንዲሁ......
አይሆንላት ተሸነፈች፤
አይሳካም ተሰበረች፤
አበቃላት ወድቃ ቀረች፤
ብለዉ ሲናገሩኝ..........
የሩቋ ወጋገን ጎልታ 'ምትታየኝ፤
በተነሳሁ ቁጥር ወደኔ 'ምትቀርበኝ፤
ጠፍታ የማትጠፋዉ ያቺ ብርሃን ነኝ።
..............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤46👍9🔥6
አልጋዬ የምኞት በሀር ወዝሽ የፈሰሰበት
ማጀቴ የፈኖስ ብርሀን ሳቅሽ የደመቀበት
የጂጂ የመውደድ ዜማ
ተቃቅፈን የደነስንበት
ጎዳናው የተጓዝንበት
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
¹
የታክሲው ጥግ ላይ ወንበር
ከፍተሽ የምተገቢው በር
የቡና የዕጣን አውዱ
የቤተስክያን አጸዱ
የጧፏ ደቂቅ ብልጭታ
ያስቀደስንበት ቦታ
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
²
የትኩስ መቃብር ሽታ የተቆፈረ አፈር
ድንኳን የተጣለበት ሰፈር
የአበባ እቅፎች መቃብር ግርጌ የረገፉ
የዕድር ጥሩንባዋች ሞት የሚለፍፉ
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
ማጀቴ የፈኖስ ብርሀን ሳቅሽ የደመቀበት
የጂጂ የመውደድ ዜማ
ተቃቅፈን የደነስንበት
ጎዳናው የተጓዝንበት
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
¹
የታክሲው ጥግ ላይ ወንበር
ከፍተሽ የምተገቢው በር
የቡና የዕጣን አውዱ
የቤተስክያን አጸዱ
የጧፏ ደቂቅ ብልጭታ
ያስቀደስንበት ቦታ
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
²
የትኩስ መቃብር ሽታ የተቆፈረ አፈር
ድንኳን የተጣለበት ሰፈር
የአበባ እቅፎች መቃብር ግርጌ የረገፉ
የዕድር ጥሩንባዋች ሞት የሚለፍፉ
#አንቺን_ያስታውሰኛል!
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤29😢1
ሁሉም ይለወጣል
በአበባ ይተካል
ሸክሙም ቀንበሩም፤
ዘንበል ይሉልኛል
ድንግዝግዝ ቀናቶች፡
ችክ እንዳሉ አይቀሩም።
አምናለሁኝ እኮ፡
በኔ ላይ ይሆናል
ፍፁም የማይሆነው! ፤
እኔን የጨነቀኝ፡
እንዴት አድርጌ ነው
የማመሰግነው ?።
By @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
በአበባ ይተካል
ሸክሙም ቀንበሩም፤
ዘንበል ይሉልኛል
ድንግዝግዝ ቀናቶች፡
ችክ እንዳሉ አይቀሩም።
አምናለሁኝ እኮ፡
በኔ ላይ ይሆናል
ፍፁም የማይሆነው! ፤
እኔን የጨነቀኝ፡
እንዴት አድርጌ ነው
የማመሰግነው ?።
By @mikiyas_feyisa
@getem
@getem
@paappii
❤66🎉1
ጥርሷ ሰዋሪ
ሳቋ ነዳፊ ፤
ከንፈሯ ገዳይ
ዐይኗ ገራፊ ፤
ፀጉሯ ሐመልማል
ልብሷ ደመና ፤
ገላዋ አበባ
ቃናዋ ናና ፤
ልክ እንደ ሰንደል
ልክ እንደ ብርጉድ ፤
የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !
ከሰማይ በቀር
የምድር አፈር የማይመጥናት ፤
ከመለዓክ በቀር
በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት
አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤
የሚገድሉላት
የሚሞቱላት
ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ሲሻት በምድር
ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤
ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤
እንኳን ለአዘቦት
ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤
እንኳን በፀሐይ
ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
እንኳን ቁሞ ሃጅ
ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤
እንኳን የሰው ዘር
ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤
ከፍቅር በቀር
ሌላ አይችላትም ፤
ከራሷ በቀር
የቱም አበባ አይመጥናትም ፤
የምድር ዕንቁ ናት
የምድር አበባ ፤
እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤
እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤
በዐይኖቿ ብቻ
ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤
ለባህር ዛጎል
ለሰማይ ኮኮብ
ለምድር አደይ ናት ፤
እንኳንስ ቁሜ
ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት
ከአንድ እኔ በቀር
ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ።
by Tewodros Kassa
@getem
@getem
@paappii
ሳቋ ነዳፊ ፤
ከንፈሯ ገዳይ
ዐይኗ ገራፊ ፤
ፀጉሯ ሐመልማል
ልብሷ ደመና ፤
ገላዋ አበባ
ቃናዋ ናና ፤
ልክ እንደ ሰንደል
ልክ እንደ ብርጉድ ፤
የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !
ከሰማይ በቀር
የምድር አፈር የማይመጥናት ፤
ከመለዓክ በቀር
በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት
አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤
የሚገድሉላት
የሚሞቱላት
ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ሲሻት በምድር
ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤
ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤
እንኳን ለአዘቦት
ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤
እንኳን በፀሐይ
ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
እንኳን ቁሞ ሃጅ
ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤
እንኳን የሰው ዘር
ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤
ከፍቅር በቀር
ሌላ አይችላትም ፤
ከራሷ በቀር
የቱም አበባ አይመጥናትም ፤
የምድር ዕንቁ ናት
የምድር አበባ ፤
እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤
እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤
በዐይኖቿ ብቻ
ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤
ለባህር ዛጎል
ለሰማይ ኮኮብ
ለምድር አደይ ናት ፤
እንኳንስ ቁሜ
ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት
ከአንድ እኔ በቀር
ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ።
by Tewodros Kassa
@getem
@getem
@paappii
❤77👍16😁10🔥5👎2
Forwarded from የሕይወት ዛፍ......Tree Of Life (Yoseph Yid.)
ሰላም ወዳጆች ዛሬ 9:30 አራት ኪሎ በዋልያ ቡክስ አዳራሽ የወዳጄ የኪሩቤልን መፅሐፍ እናስመርቃለን።
የምትችሉ እዛው እንገናኝ።
ማስታወሻ የኔን ምስል እዚ ውስጥ ፈልጎ ላገኘ የመጀመሪያው ሰው መፅሐፉን እሸልማለሁ...😅🙏
የምትችሉ እዛው እንገናኝ።
ማስታወሻ የኔን ምስል እዚ ውስጥ ፈልጎ ላገኘ የመጀመሪያው ሰው መፅሐፉን እሸልማለሁ...😅🙏
❤21