ጥርሷ ሰዋሪ
ሳቋ ነዳፊ ፤
ከንፈሯ ገዳይ
ዐይኗ ገራፊ ፤
ፀጉሯ ሐመልማል
ልብሷ ደመና ፤
ገላዋ አበባ
ቃናዋ ናና ፤
ልክ እንደ ሰንደል
ልክ እንደ ብርጉድ ፤
የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !
ከሰማይ በቀር
የምድር አፈር የማይመጥናት ፤
ከመለዓክ በቀር
በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት
አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤
የሚገድሉላት
የሚሞቱላት
ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ሲሻት በምድር
ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤
ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤
እንኳን ለአዘቦት
ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤
እንኳን በፀሐይ
ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
እንኳን ቁሞ ሃጅ
ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤
እንኳን የሰው ዘር
ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤
ከፍቅር በቀር
ሌላ አይችላትም ፤
ከራሷ በቀር
የቱም አበባ አይመጥናትም ፤
የምድር ዕንቁ ናት
የምድር አበባ ፤
እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤
እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤
በዐይኖቿ ብቻ
ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤
ለባህር ዛጎል
ለሰማይ ኮኮብ
ለምድር አደይ ናት ፤
እንኳንስ ቁሜ
ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት
ከአንድ እኔ በቀር
ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ።
by Tewodros Kassa
@getem
@getem
@paappii
ሳቋ ነዳፊ ፤
ከንፈሯ ገዳይ
ዐይኗ ገራፊ ፤
ፀጉሯ ሐመልማል
ልብሷ ደመና ፤
ገላዋ አበባ
ቃናዋ ናና ፤
ልክ እንደ ሰንደል
ልክ እንደ ብርጉድ ፤
የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ !
ከሰማይ በቀር
የምድር አፈር የማይመጥናት ፤
ከመለዓክ በቀር
በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት
አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤
የሚገድሉላት
የሚሞቱላት
ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
ሲሻት በምድር
ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤
ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤
እንኳን ለአዘቦት
ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤
እንኳን በፀሐይ
ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤
ልጅማ ልጅ ናት !
እንኳን ቁሞ ሃጅ
ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤
እንኳን የሰው ዘር
ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤
ከፍቅር በቀር
ሌላ አይችላትም ፤
ከራሷ በቀር
የቱም አበባ አይመጥናትም ፤
የምድር ዕንቁ ናት
የምድር አበባ ፤
እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤
እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤
በዐይኖቿ ብቻ
ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤
ለባህር ዛጎል
ለሰማይ ኮኮብ
ለምድር አደይ ናት ፤
እንኳንስ ቁሜ
ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤
ልጅማ ልጅ ናት
ከአንድ እኔ በቀር
ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ።
by Tewodros Kassa
@getem
@getem
@paappii
❤76👍16😁10🔥5👎2
Forwarded from የሕይወት ዛፍ......Tree Of Life (Yoseph Yid.)
ሰላም ወዳጆች ዛሬ 9:30 አራት ኪሎ በዋልያ ቡክስ አዳራሽ የወዳጄ የኪሩቤልን መፅሐፍ እናስመርቃለን።
የምትችሉ እዛው እንገናኝ።
ማስታወሻ የኔን ምስል እዚ ውስጥ ፈልጎ ላገኘ የመጀመሪያው ሰው መፅሐፉን እሸልማለሁ...😅🙏
የምትችሉ እዛው እንገናኝ።
ማስታወሻ የኔን ምስል እዚ ውስጥ ፈልጎ ላገኘ የመጀመሪያው ሰው መፅሐፉን እሸልማለሁ...😅🙏
❤21
የኔ ሳቅ
.
.
ሁሉም ለየብቻዉ
እንደተለያየ
የኔ ሳቅ ለብቻው
ከኔ ጋራ ቆየ
አየሁት ሰማሁት
ሁሉን ተረዳሁት
ሳቄን ለማርከሻ
ቢቸግር ጠጣሁት
ቢቸግር በላሁት
እንደ ጎሽ ጠላ
እንደ 'ባር ማሽላ
ሳቄን ለማርከሻ
ከነገዉ መድረሻ
መረጥኩት ጠላሁት
ይስቃል እንዲሉኝ
ጥርሴን ተነቀስኩት
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ሁሉም ለየብቻዉ
እንደተለያየ
የኔ ሳቅ ለብቻው
ከኔ ጋራ ቆየ
አየሁት ሰማሁት
ሁሉን ተረዳሁት
ሳቄን ለማርከሻ
ቢቸግር ጠጣሁት
ቢቸግር በላሁት
እንደ ጎሽ ጠላ
እንደ 'ባር ማሽላ
ሳቄን ለማርከሻ
ከነገዉ መድረሻ
መረጥኩት ጠላሁት
ይስቃል እንዲሉኝ
ጥርሴን ተነቀስኩት
@topazionnn
@getem
@getem
❤42🔥4😢4👍2😱1
[ #ለእሷ! ]
የመዋደዳችን አበቃ ምዕራፉ
የመገናኛችን ተዘጋ በራፉ
ለምለም ምኞታችን እንደ ጉም በነነ
ዘላለም ነው ያልነው ቅጽበታችን ሆነ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ያኔ
በመስታወት ጡቦች በታሰረ ብርሀን
ጎጆ'ችንን መልተን
ከገበታችን ላይ ፍቅርን ዘርግተን
መውደድ በትኩሱ የተቋደስንበት
ነፍሳችን ጥለን ህጻን የሆንበት
ዛሬ እንደ ትዝታ በምኞት ይገርፋል
አየሩ ንፋሱ "የለሽም" ብሎ ያልፋል ።
━・・・━ ★ ━・・・━
የለሽም የለሽም
የመስታወት ጡቡ ወድቆ ተሰበረ
ብርሀን ጸዳሉ ወዳንቺ በረረ
በስብርባሪ ውስጥ ጸጸት ብቻ ቀረ
በጊዜ ጠብታ ትዝታን ያዘለ. . .
✿
ይኀው እዛች'ጋ
የገጽሽ ሀመልማል ጽልመቱን ይቀዳል
ከሳቅ ከጭዋታሽ ብርሀን ይወለዳል
እንደ ጀንበር ውበት በማለዳው ይሄዳል።
ይኀው እዛች'ጋ
የዳናሽ ማህሌ' ሀዘኔን ሳያስረሳኝ
ኮልታፋ አንድበትሽ በፍቅር ሲያነሳኝ
ህይወት እንደ ምንጣፍ እየጠቀለለው
ከትዝታ መቅረዝ ሰብስቦ ሲጥለው ።
✿
ይኀው ወደ አንቺ ጋር
ዛሬም እንደ ትናንት ልቤ ይሰደዳል
ተስፋውን ሰንቆ ለምኞቱ ይሄዳል
ከንፋስ ከአየሩ ♡
ከዛፍ ከቅጠሉ ♡
የለሽም የለሽም
የሚል ኦና ቃላት በምጥ ይወለዳል!።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
የመዋደዳችን አበቃ ምዕራፉ
የመገናኛችን ተዘጋ በራፉ
ለምለም ምኞታችን እንደ ጉም በነነ
ዘላለም ነው ያልነው ቅጽበታችን ሆነ።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ያኔ
በመስታወት ጡቦች በታሰረ ብርሀን
ጎጆ'ችንን መልተን
ከገበታችን ላይ ፍቅርን ዘርግተን
መውደድ በትኩሱ የተቋደስንበት
ነፍሳችን ጥለን ህጻን የሆንበት
ዛሬ እንደ ትዝታ በምኞት ይገርፋል
አየሩ ንፋሱ "የለሽም" ብሎ ያልፋል ።
━・・・━ ★ ━・・・━
የለሽም የለሽም
የመስታወት ጡቡ ወድቆ ተሰበረ
ብርሀን ጸዳሉ ወዳንቺ በረረ
በስብርባሪ ውስጥ ጸጸት ብቻ ቀረ
በጊዜ ጠብታ ትዝታን ያዘለ. . .
✿
ይኀው እዛች'ጋ
የገጽሽ ሀመልማል ጽልመቱን ይቀዳል
ከሳቅ ከጭዋታሽ ብርሀን ይወለዳል
እንደ ጀንበር ውበት በማለዳው ይሄዳል።
ይኀው እዛች'ጋ
የዳናሽ ማህሌ' ሀዘኔን ሳያስረሳኝ
ኮልታፋ አንድበትሽ በፍቅር ሲያነሳኝ
ህይወት እንደ ምንጣፍ እየጠቀለለው
ከትዝታ መቅረዝ ሰብስቦ ሲጥለው ።
✿
ይኀው ወደ አንቺ ጋር
ዛሬም እንደ ትናንት ልቤ ይሰደዳል
ተስፋውን ሰንቆ ለምኞቱ ይሄዳል
ከንፋስ ከአየሩ ♡
ከዛፍ ከቅጠሉ ♡
የለሽም የለሽም
የሚል ኦና ቃላት በምጥ ይወለዳል!።
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤54👍7🔥5
ሥትገቢ ሥትወጪ-
ዐይኔ ተደሥቶ ልቤን የሚያሞቀው፣
ዝቅ በል ሥትይኝ፣
መውረዴ ተክቦ - ክብሬን የሚንቀው።
በመናኛ ቀልድሽ-
እንድያ የምሥቀው - ድዴ እሥኪሠበር፣
አሁን የማይገባኝ፣
ያን ሠሞን ግን ካንቺ - ምን ፈልጌ ነበር?
(የሞገሤ ልጅ)
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ዐይኔ ተደሥቶ ልቤን የሚያሞቀው፣
ዝቅ በል ሥትይኝ፣
መውረዴ ተክቦ - ክብሬን የሚንቀው።
በመናኛ ቀልድሽ-
እንድያ የምሥቀው - ድዴ እሥኪሠበር፣
አሁን የማይገባኝ፣
ያን ሠሞን ግን ካንቺ - ምን ፈልጌ ነበር?
(የሞገሤ ልጅ)
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤29😁23🔥5
ህይወት ግን ምንድ ነው?
ህይወት ግን ምንድ ነው
ከዉስብስቡ አለም ግንኙነት ያለው
እንደፈለገ የሚያስደስት የሚያሳዝነው
ህይወት ግን ምንድን ነው
ለብዙ ነገሮች ጥያቄ የሆነው
ከጥልቁ ባህር አጥልቆ ሚያስቀረው
ግን ህይወት ምንድን ነው???????
አልቅሶ አለመሳቅ አቶ አለማግኘት
አዝኖ አለመደሰት ነው አይደል? ህይወት 😊😊😊
Kal..... @pilopater
@getem
@getem
@getem
ህይወት ግን ምንድ ነው
ከዉስብስቡ አለም ግንኙነት ያለው
እንደፈለገ የሚያስደስት የሚያሳዝነው
ህይወት ግን ምንድን ነው
ለብዙ ነገሮች ጥያቄ የሆነው
ከጥልቁ ባህር አጥልቆ ሚያስቀረው
ግን ህይወት ምንድን ነው???????
አልቅሶ አለመሳቅ አቶ አለማግኘት
አዝኖ አለመደሰት ነው አይደል? ህይወት 😊😊😊
Kal..... @pilopater
@getem
@getem
@getem
❤35👎12👍7🔥1
ጷግሜ
.
.
'ያመት ማካታቻ የቀናት ጭማሪ፤
የተስፋን ፀዳል ንጋት አብሳሪ፤
በሩፋኤል ጠበል ከበራችን ወተን፤
የዝናቡ ወጨፎ ብርዱ ሳይበግረን፤
በጉጉት ስንጠብቅ እስኪደርስ ቀኑ፤
አደይዋ እስክትፈካ ሲለወጥ ዘመኑ፤
በአዲሱ ልብሳችን እጅጉን ተዉበን፤
አበባዮሽ ስንል የክቱን ለባብሰን፤
የልጅነት ጊዜ.....
በትዝታ አስጉዞ ሁሌም ይናፈቃል፤
እንደ እንቦሳ ጥጆች ዘወትር ያስቦርቃል።
.....................................
ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
'ያመት ማካታቻ የቀናት ጭማሪ፤
የተስፋን ፀዳል ንጋት አብሳሪ፤
በሩፋኤል ጠበል ከበራችን ወተን፤
የዝናቡ ወጨፎ ብርዱ ሳይበግረን፤
በጉጉት ስንጠብቅ እስኪደርስ ቀኑ፤
አደይዋ እስክትፈካ ሲለወጥ ዘመኑ፤
በአዲሱ ልብሳችን እጅጉን ተዉበን፤
አበባዮሽ ስንል የክቱን ለባብሰን፤
የልጅነት ጊዜ.....
በትዝታ አስጉዞ ሁሌም ይናፈቃል፤
እንደ እንቦሳ ጥጆች ዘወትር ያስቦርቃል።
.....................................
ዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤89🤩6👍2
ቄጠማ ሆነብኝ እግሬ| አቃተኝ ነፍሴን ማበርታት
በይግባኝ ሸንጎ ገጥሜህ
---በአርምሞህ ቃሌን በመርታት
ስታውቀው የዓለም መልኩን አጨኀኝ ለመከራ ቁር
ክፍት ነው ደጄን አትቆርቁር!።
°
°
ተመልክት የዓለም መልኩን
ተለምዷል ወድቆ መረሳት
ጎዳናው ዕንባ ጠገበ
ይፋጃል ዕግርን እንደ እሳት!!!
ስታውቀው የዓለም መልኩን አጨኀን ለመከራ ቁር
ክፍት ነው ደጄን አትቆርቁር!።
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
በይግባኝ ሸንጎ ገጥሜህ
---በአርምሞህ ቃሌን በመርታት
ስታውቀው የዓለም መልኩን አጨኀኝ ለመከራ ቁር
ክፍት ነው ደጄን አትቆርቁር!።
°
በል ግባ እንደ አብርሃም ቤት
ጓዳዬን ማጀቴን ቃኘው
ሰባራ ሸክላዬን ጥጄ
በምኞት ሆዴን ሳሞኘው
አረፍ በል ከሳር ፍራሼ
አይመች ለገላ አይመጥን
ሳለቅስ ሳነባ አድራለሁ
ውል አልባ ህልሜን ስወጥን
በል ባርካት ደሳሳ ዳሴን
በፍቅርህ መሰረት አጽናት
ካልሆነም ስጋን አፍርሰህ
የዛለች ነፍሴን አድናት!።
°
ተመልክት የዓለም መልኩን
ተለምዷል ወድቆ መረሳት
ጎዳናው ዕንባ ጠገበ
ይፋጃል ዕግርን እንደ እሳት!!!
ስታውቀው የዓለም መልኩን አጨኀን ለመከራ ቁር
ክፍት ነው ደጄን አትቆርቁር!።
#የአብስራ_ሳሙኤል
@YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤59😢8🔥7🎉3
ከጭፈራው መሐል
አበባዮሽ እያልን ስንዞር ከየቤቱ፣
ቄጠማ ተይዞ ተለብሶ የክቱ።
ጨዋታዉ ሲደራ የከበሮዉ ድልቂያ፣
የድምድምታዉ ጩኸት ሆኖ ፈንጠዝያ።
ከጭፈራዉ መሐል ስትወርድ በእስክስታ፣
መቀነት ታጥቄ ሳይህ በስርቅታ።
በነፋስ ሽዉታ አይናችን ተጋጭቶ፣
በሴኮንድ እይታ ልባችን አዉግቶ።
ፀሐይ ስታበስር የድል ብስራት ዜማ፣
እስክስታዉ ሰደደን ወደ ፍቅር ማማ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
አበባዮሽ እያልን ስንዞር ከየቤቱ፣
ቄጠማ ተይዞ ተለብሶ የክቱ።
ጨዋታዉ ሲደራ የከበሮዉ ድልቂያ፣
የድምድምታዉ ጩኸት ሆኖ ፈንጠዝያ።
ከጭፈራዉ መሐል ስትወርድ በእስክስታ፣
መቀነት ታጥቄ ሳይህ በስርቅታ።
በነፋስ ሽዉታ አይናችን ተጋጭቶ፣
በሴኮንድ እይታ ልባችን አዉግቶ።
ፀሐይ ስታበስር የድል ብስራት ዜማ፣
እስክስታዉ ሰደደን ወደ ፍቅር ማማ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
❤48🔥5😁3👎2
በማያልቅ ሩጫ
በማይበርድ ፍጥጫ
መርጋት በሌለበት
መዋተት.....
ሁልጊዜ መጣደፍ
በቁስአለም መክነፍ
እፍፍፍፍ......
በጎዶሎ ፅዋ
በሰባራ ፎሌ
ደጋግሞ መጨለፍ
መንጠፍ........
መኖር እንዲ ሆኖ
ያለረፍት መክነፍ
መሞት ሆኗል ማረፍ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
በማይበርድ ፍጥጫ
መርጋት በሌለበት
መዋተት.....
ሁልጊዜ መጣደፍ
በቁስአለም መክነፍ
እፍፍፍፍ......
በጎዶሎ ፅዋ
በሰባራ ፎሌ
ደጋግሞ መጨለፍ
መንጠፍ........
መኖር እንዲ ሆኖ
ያለረፍት መክነፍ
መሞት ሆኗል ማረፍ።
By @poetkidus
@getem
@getem
@getem
❤50👍16🔥3🤩1
ጭር እንዳለ ቀን
ዝም እንዳለ ሌት
በጥባጭ ህጻን ልጅ
እንደሌለው ቤት
ቆሌ እንደራቀው አዚማም ሀሙስ
እንደ ጫት ድባብ
እንደ ቡና ሱስ
ቅር ቅር አልሽኝ...
ማተብ እንዳጣ ራቁት አንገት
እንደ ዋዜማ እንደ አዲስአመት
( ሆቴል እንደተከበረ አውዳመት... )
ቅር ቅር አልሽኝ...
ውዱዕ ሳያደርግ እንደሰገደ
እያመነታ እንደፈረደ
ሳይሰናበት ርቆ እንደ ሄደ ።
ቅር ቅር አልሽኝ...
እንደ መሰልጠን
በትዝታ ላይ እንደመጨከን
እንደ ሩቅ ሀገር
የማይለመድ እንግዳ ነገር
ቅር ቅር አልሽኝ...
ጨርሰው እንዳልቆረጧት ጥፍር
እንዳላፈረጧት ትንሽዬ ብጉር
በጥርስ መሐከል እንደ ገባች ስጋ
እየናፈቅሽኝ
እያጓጓሽኝ
አልዋጥ አልሽኝ ።
ቅር ቅር አልሽኝ ...
by Hab HD
@getem
@getem
@paappii
ዝም እንዳለ ሌት
በጥባጭ ህጻን ልጅ
እንደሌለው ቤት
ቆሌ እንደራቀው አዚማም ሀሙስ
እንደ ጫት ድባብ
እንደ ቡና ሱስ
ቅር ቅር አልሽኝ...
ማተብ እንዳጣ ራቁት አንገት
እንደ ዋዜማ እንደ አዲስአመት
( ሆቴል እንደተከበረ አውዳመት... )
ቅር ቅር አልሽኝ...
ውዱዕ ሳያደርግ እንደሰገደ
እያመነታ እንደፈረደ
ሳይሰናበት ርቆ እንደ ሄደ ።
ቅር ቅር አልሽኝ...
እንደ መሰልጠን
በትዝታ ላይ እንደመጨከን
እንደ ሩቅ ሀገር
የማይለመድ እንግዳ ነገር
ቅር ቅር አልሽኝ...
ጨርሰው እንዳልቆረጧት ጥፍር
እንዳላፈረጧት ትንሽዬ ብጉር
በጥርስ መሐከል እንደ ገባች ስጋ
እየናፈቅሽኝ
እያጓጓሽኝ
አልዋጥ አልሽኝ ።
ቅር ቅር አልሽኝ ...
by Hab HD
@getem
@getem
@paappii
❤72👍17🔥3😁3🎉2😱1