የመጨረሻው የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ
ኢትዮጵያ ‘የመጨረሻ’ የተባለውን አራተኛ ዙር የሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ማካሄዷን ተከትሎ ግብጽ ብስጭቷን ገለጸች።
የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ የግድቡን ሙሌት ያከናወነችው የታችኛው ተፋሰስ አገራት ፍላጎትን ቸል በማለት ነው ብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ትናንት ጵጉሜ 5/2015 ዓ.ም. በይፋዊ የኤክስ ገጻቸው ኢትዮጵያ “አራተኛውንን እና የመጨረሻውን ሙሌት በተሳካ ሁኔታ” ስለማካሄዷ ይፋ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግድቡን ለመገደብ በገንዘብ በዕውቀት፣ በጉልበት እና በጸሎት የተሳተፉትን አመስግነው፣ ኢትዮጵያ ከግድቡ ግንባታ ጋር በተያያዘ የውስጥ እና የውጭ ጫናዎች እንደነበሩባት ገልጸዋል።
“ብዙ ፈተና ነበረው፤ ወደኋላ እንድንመለስ ብዙ ተጎትተን ነበር። በውስጥ ፈተና በውጭ ጫና ነበረብን። ከፈጣሪ ጋር የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚህ ደርሰናል።” ብለዋል።
ኢትዮጵያ ይህ ግንባታው ከተጀመረ 12 ዓመታትን ያስቆጠረውን ግዙፍ ግድብን በውሃ መሙላት ከመጀመሯ በፊት አስገዳጅ ስምምነት ላይ መደረስ አለበት በማለት ግብጽ እና ሱዳን ሲወተውቱ ቆይተዋል።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ከአባይ ውሃ ፍትሐዊ የሆነ የድርሻዬን መጠቀም አለብኝ በማለት አሳሪው ስምምነት ሳይደረስ ግድቡ ውሃ እንዲይዝ ስታደርግ ቆይታለች።
ይህን ተከትሎ የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትናንት በፌስቡክ ገጹ ላይ ኢትዮጵያ የግድቡን ውሃ ሙሌት ያከናወነችው ግብጽ፣ ሱዳን እና ኢትዮጵያ እ.አ.አ 2015 (መጋቢት 14፣ 2007 ዓ/ም) ላይ የተፈራረሙት 'የስምምነት መርሆዎች' በሚጥስ ሁኔታ ነው ብላለች።
ግብጽ በተፈራረምነው የመርህዎች ስምምነት መሠረት በግድቡ አሞላል እና ኦፕሬሽን ላይ አስገዳጅ ስምምነት ሳይደረስ የውሃ ሙሌት ማድረግ የተከለከለ ነው ብላለች።
“የኢትዮጵያ የአንድ ወገን እርምጃ በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች የተረጋገጡትን የታችኛው ተፋሰስ አገራትን ጥቅምና መብት እንዲሁም የውሃ ደኅንነታቸውን ያላገናዘበ ነው” ብሏል የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር።
ግብጽ ይህን ትበል እንጂ በሥልጣን ሹኩቻ በርስ በርስ ግጭት ውስጥ የገባችው ሌላኛው የታችኛው ተፋሰስ አገር ሱዳን የ4ኛው ዙር የውሃ ሙሌትን በተመለከተ እስካሁን ያለችው ነገር የለም።

በኢትዮጵያ፣ በሱዳን እና በግብፅ የሕዳሴ ግድብ ውሃ አሞላል እና ኦፕሬሽንን በተመለከተ በአዲስ አበባ፣ ካይሮ እና ካርቱም ተደጋጋሚ ድርድሮችን ሲያደርጉ ቢቆዩም ሦስቱ አገራት እስካሁን ከስምምነት መድረስ ሳይችሉ ቆይተዋል።
በቅርቡም በሦስቱ አገራት መካከል ሲደረግ የነበረው እና ለሁለት ዓመት ያህል ተቋርጦ የቆየው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ድርድር በነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ በካይሮ ተካሂዶ ያለውጤት ተበትኗል።
ይህ ውይይት በመስከረም 2016 በኢትዮጵያ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የግድቡ ግንባታ 11ኛ ዓመት ላይ፣ ባለፈው ዓመት የካቲት 13፣ 2014 ዓ.ም የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ይታወሳል።
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶው መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፣ ከአምስት ሺህ ሜጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ለጎረቤት አገራት ኃይል ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ግድቡ የሚይዘውን 74 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ሙሉ በሙሉ ሲይዝም ውሃው የሚተኛበት ስፍራ ርዝመት 246 ኪሎ ሜትር እንደሚደርስ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ግብፃውያን ግድቡ አገራቸው ከአባይ ወንዝ የምታገኘውን የውሃ መጠንን በመቀነስ ጉዳት ያስከትልብናል የሚል መከራከርያ ያቀርባሉ።
ኢትዮጵያ ግን የአባይ ውሃን የመጠቀም ተፈጥሯዊ መብት እንዳለት በመግለጽ፣ ግድቡ የታችኛው ተፋሰስ አገራትን የውሃ አቅርቦት በማይጎዳ ሁኔታ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለማመንጨት እንደምታውለው ትገልጻለች።
ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ መጀመሯን ይፋ ማድረጓን ተከትሎ ከግብፅ እና ከሱዳን በኩል ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማት ሲሆን፣ የግድቡ ጉዳይም ከአፍሪካ ኅብረት ባሻገር በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥም መነጋገሪያ ሆኖ ነበር።
ሦስቱ አገራት በግድቡ ዙሪያ በተለያዩ ጊዜያት በአፍሪካ ኅብረት እና በአሜሪካ አደራዳሪነት ንግግር ቢያደርጉም ሁሉንም ከሚያግባባ ስምምነት ላይ ሳይደርሱ ቆይተዋል።
ተጠናቆ ሥራውን ሲጀምር በአፍሪካ ግዙፉ እንደሆነ የሚነገርለት ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አገሪቱ አምስት ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገንዘብ ከራሷ በማውጣት እያከናወነች ነው።
Forwarded from Bemnet
Forwarded from Bemnet
የብሔራዊ የደኅንነት ምክር ቤት ፤ በወቅታዊ ሀገራዊ የደህንነትና ፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ መምከሩን አሳውቋል።

ይህ ተከትሎ ዘለግ ያለ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህ መግለጫ ፦
- ስለ ሀገራዊ ምክክር
- ስለ ሽግግር ፍትሕ
- ከመንግሥት ውጭ ታጥቀው ስለሚንቀሳቀሱ ኃይሎች
- ስለ ተሃድሶ ኮሚሽን
- ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት
- ስለ ህወሓት ታጣቂዎች
- ስለ ተፈናቃዮች መመለስ

...ሌሎችም ጉዳዮች ተነስተውበታል።

ምክር ቤቱ፥ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ የሀገረዊ ምክክር ኮሚሽን በክልል ደረጃ የምክክር መድረኮችን ማካሄድ ይጀምራል ብሏል።

ሀገራዊው የምክክር ጉባኤ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚካሄድ ተስፋ ይደረጋል ሲል ገልጿል።

ም/ቤቱ፤ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ መፅደቁን አስታውሷል።

እንደ አግባብነቱ፦
° የወንጀል ምርመራ እና ክስ
° እውነት ማፈላለግ
° ዕርቅ
° በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሠረተ ምሕረት
° ማካካሻ እና ተቋማዊ ማሻሻያ እንደ ሽግግር ፍትሕ ስልቶች በሀገራችን ተግባራዊ ይደረጋሉ ብሏል።

" የመንግሥት አንዱ መብት በብቸኝነት ኃይልን መጠቀም " መሆኑን ገልጾ በሀገራችን በተወረሰ የፖለቲካ ስብራት የተነሣ የታጠቁ ኃይሎች ተፈጥረዋል ብሏል።

የሀገሪቱን ሰላም የጸና ለማድረግ፣ እነዚህ የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ ፈትተው፣ የተሐድሶ ሂደት ውስጥ መቀላቀል አለባቸው ብሏል። " የፖለቲካ ጥያቄዎቻቸውንም በሀገራዊ ምክክር ሂደት በመሳተፍ መፍታት ይችላሉ " ሲል ገልጿል።

ለዚህም የተሐድሶ ኮሚሽን ተቋቁሟል። ዓላማውም፦
° መሣሪያ ማስፈታት
° የትጥቅ ቡድኖችን ሰላማዊ ማድረግና ከማኅበረሰቡ ጋር መቀላቀል ነው ብሏል።

መንግሥት የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አተገባበር ከሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ጋር የተናበበና የሚመጋገብ እንዲሆን ኃላፊነቱን ይወጣል ብሏል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፤ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ጦርነትን በፖለቲካዊ መፍትሔ የመቋጨት ባህል አምጥቷል ሲል ገልጿል።

የሰላም ስምምነቱ ለትውልድ የአሸናፊ ተሸናፊ ትርክትን ከቂም ጋር ላለማውረስ የተደረገ ውሳኔ እንደሆነ ገልጿል።

የሰላም ስምምነቱ እስካሁን ብዙ ውጤት እና እፎይታ ቢያስገኝም ቀሪ ሥራዎችም አሉ ብሏል።

በተለይ በስምምነቱ መሠረት " የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው " ሲል ገልጿል።

የማንነትና የአስተዳደር ወሰን ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች ጉዳይ እልባት ለመስጠት እንዲቻል የተቀመጠው አቅጣጫ ተግባራዊ መደረግ አለበት ብሏል።

" ካለፈ ስሕተተ አለመማር የመጀመሪያውን ስሕተት ከመሥራት የባሰ ነው " ያለው ም/ቤቱ፤ ካለፈው ስሕተታቸው ሳይማሩ ዛሬም ተመሳሳይ ችግር ለመፍጠር የሚከጅሉ አሉ ሲል ጠቁሟል።

እነዚህን ሁሉም ተባብሮ አደብ ማስገዛት ይኖርበታል ብሏል።

" ከትዕግሥት በኋላ የሚከሠት ሕግ የማስከበር ሥራ የሚኖረውን አስከፊ ውጤት ከቅርቡ ታሪካችን ልንማር ይገባል" ሲል አሳስቧል።

ም/ቤቱ፤ መንግሥት በትግራይ ክልል ብዙ ርቄት ሄዶ ቁስልን ለመሻር የሚያስችል ሥራ እየሠራ እንደሆነ ገልጿል።

" ይሄ ግን መንግሥታዊ ኃላፊነት እንጂ ፍርሃት ተደርጎ መወሰድ የለበትም " ብሏል።

" በፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነትና በሕገ መንግሥቱ መሰረት እንደ ሀገር የሚኖረው አንድ የመከላከያ ሠራዊት ብቻ ነው ክልሎች በክልል ከፖሊስ እና ሚሊሺያ ያለፈ የታጠቀና የተደራጀ ሠራዊት ሊኖራቸው አይችልም፤ አይገባምም " ብሏል።

በዚህ መሠረት ትጥቅ መፍታትና ተያያዥ ሂደቶች በተሐድሶ ኮሚሽኑ ዕቅድ መሠረት በፍጥነት ሊተገበሩ እንደሚገባ አሳስቧል።

ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።


የብሔራዉ የደኅንነት ምክር ቤት በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ባጋጠመ ግጭት፤ እንዲሁም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ባጋጠሙ የጸጥታ ችግሮች የተነሣ የተፈናቀሉ ዜጎች እንዳሉ ገልጿል።

" እነዚህ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ እየሠራን ነው " ብሏል።

" የአማራ እና የኦሮሚያ ክልል አመራሮች በጋራ ሠርተው ብዙዎችን ከመጠለያ ጣቢያ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ተደርጓል " ሲልም ገልጿል።

" በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል፤ በራያ እና አላማጣ አካባቢ ከተፈናቀሉ ዜጎች መንግሥትን ሳይጠብቁ በማኅበረሰባዊ መተሳሰብ ብቻ በርካታዎች ወደ ቤታቸው እየገቡ ነው " ሲል አመልክቷል።

በዚህ ሂደት " የተፈናቃዮችን ጉዳይ እንደ ፖለቲካ አጀንዳ አድርገው ሊጠቀሙ የሚፈልጉ አካላት መኖራቸው ታይቷል " ብሏል።

ም/ቤቱ እነዚህ ኃይሎች እነማን እንደሆኑ በግልጽ በስም ጠርቶ ባይገልጽም " ተፈናቃዮቹ ወደ ቤታቸው እንዳይመለሱ ፕሮፖጋንዳና ማስፈራሪያ ይደረድራሉ " ብሏል።

" አንዳንዴም በኃይል ጭምር የተፈናቃዮችን መመለስ ለማሰናከል ይቃጣቸዋል። " ሲል ገልጿል።

" መንግሥት ካለበት የሞራል እና የሕግ ኃላፊነት የተነሣ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቤታቸውና ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ማድረጉን ይቀጥላል " ሲል አሳውቋል።
2024/05/16 20:19:59
Back to Top
HTML Embed Code: