#ሁለገብ_አገልግሎት| መምህር ጌታቸው ተክሉ
#hawassa| ፍቅራችንንም ክብራችንንም እነሆ
የሐዋሳ ትዝታ ተመስርቶ የመጀመሪያውን ጉብኝት በመ/ር ድጋፌ (ነብስ ይማር) ካደረግንበት ቀን ጀምሮ በሐሳብም በምክር ከኛጋር የነበሩ፣ በተለየ የማስታወስ ችሎታቸው የመረጃ ቋታችንም የክብር አባላችንም መሆናቸውን በቅድሚያ መግለፅ እንወዳለን!
መምህር ጌታቸው ተክሉ
መምህር ጌታቸው ተክሉ ባሳለፉት የስራ ዘመን ለሀገራቸው በብዙ የስራ ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡ እንዲያው እኔ በጽሁፍ ለመግለጽ እንዲያመቸኝ መምህር እንዲሁም በመሃል ደግሞ እንደልጅነቴ ጋሼ እያልኩ ጽሁፉን ባስነብባችሁ እሳቸውና አንባቢያኖቻችን ቅር እንደማትሰኙ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ወደ 5፡00 ሰዓት ገደማ በመኖሪያ ቤታቸው ደረስን፡፡ በብዙ ፈገግታ ተቀበሉን፡፡ በጠዋት ከቤት ወጣ ብለው እንደተመለሱ ነገሩን፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ የጤና ምርመራ አድርገው አንድ እግራቸውን ከሚያስነክሳቸው በስተቀር ጥሩ ጤንነት ላይ እንዳሉ ሀኪማቸው እንደነገሯቸው አጫወቱን፡፡ እኛም ቀበል አድርገን እግዚአብሔር ከጤና ጋር እድሜን እንዲሰጣቸው ተመኘን፡፡
የመጀመሪያ ጥያቄዬ የነበረው በሚያስተምሩበት ወቅት በጣም ተቆጪ እንደነበሩ ተማሪዎችዎ ነግረውኝ ነበር እርሶ ምን ይላሉ አልኳቸው፡፡ አዎ እቆጣ ነበር ጥፋት ስመለከትና ሳስተምር ሲረብሹኝ አይቼ ማለፍ አልችልም ልክ ናቸው እቆጣ ነበር አሉኝ፡፡ በግል ሕይወትዎና በቤትዎስ ይሄ ባህሪዎ ይንፀባረጋል? አዎ አጠገቤ ያሉ ሰዎች ያውቃሉ ጥፋት ሳይ ፊትለፊት ከመናገር ወደኋላ አልልም፤ ይሄ በቃ ባህሪዬ ነው ምንም ማድረግ እችላለሁ፡፡ አሁንስ ይሄ ባህሪዎ እንዳለ ነው? አይ አሁንማ አረጀሁ ብለው ፈገግ አስባሉን፡፡
መምህር ጌታቸው በ1937 ዓ.ም ጉራጌ ዞን በቡኢ ወረዳ (ከቡኢ 16 ኪ.ሜ ወደ ምድረ ከብድ አቦ በሚወስደው መንገድ) ጨላ በተባለው ቦታ ተወለዱ። የቄስ ትምህርት ቤት ፊደል ከቆጠሩ በኋላ ዳዊት ደግመዋል፣ አስር ዓመት ሲሞላቸው አዲስ አበባ በሚገኘው ልዑል መኮንን ት/ቤት (ያሁኑ አዲስ ከተማ ት/ቤት መርካቶ አወቶብስ ተራ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ በ1952 ዓ.ም) ተምረው በ1961 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀቁ።
በ1963 ዓ.ም መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ገብተው አንድ ዓመት ደብረዘይት ተናኜ ወርቅ ሃይስኩል የማስተማር ብሔራዊ አገልግሎት (National Service)፣ በ1965 ዓ.ም ሐምሌ ወር ከግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እጅ ዲፕሎማቸውን ወስደዋል።
ሲዳሞ ክ/ሀገር ነጌሌ ቦረና ሃይስኩል በእንግሊዝኛ መምህርነት ተመደቡ፡፡ ሁለት ዓመት ካስማሩ በኋላ ቦረና አውራጃ ዕርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ሲቋቋም ከትምህርት ሚኒስተር በውሰት ተወስደው የቦረና አውራጃ እርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የዕለት ደራሽ ኃላፊ ሆነው ለሁለት ዓመታት ሰርተዋል፣ በ1971 ዓ.ም ወደ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የማስተማር ሥራቸውን ተመልሰው እዚያው ቦረና አውራጃ ነጌሌ ሃይሰኩል አስተምረዋል።
#በ1972 ዓ.ም ወደ ሀዋሣ ታቦር ሃይስኩል ተዛወሩ፡፡ በሀዋሣ ታቦር ሃይስልኩል ወስጥ እሰከ 1977 ዓ.ም ካስተማሩ በኋላ መደበኛ ሥራቸውን እየሠሩ ሀዋሣ ማዘጋጃ ቤት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመደቡ፣ በ1978 ዓ.ም የሀዋሣ ከተማ ምክትል ሹም ከዚያም ዋና ሹም ሆነው እስከ 1981 ዓ ም ሚያዚያ ወር ድረስ አገለገሉ።
ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ከማዘጋጃ ቤቱ ሥራ ጎን ለጎን የክፍለሀገሩ የቁጥጥር ኮሚቴ አባል ሆነው አገልግለዋል። የሀዋሣ ወረዳ መምህራን ማህበር ተመራጭ ሆነው በገንዘብ ያዥነት ሠርተዋል።
ከ1981 ዓ.ም ጀምሮ ሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ቢሮ፣ የቦረና አስተዳደር አካባቢ ፀሐፊ (ሸንጎ ፀሐፊ) ሆነው ተሹመዋል። ቦረና አሰተዳደር አካባቢ እስከ 1983 ዓ.ም ከቆዩ በኋላ በ1984 ዓ.ም ወደ ታቦር ሃይሰኩል ተመልሰው ጡረታ እስከወጡበት እስከ 1994 ዓ.ም ድረስ አስተምረዋል።
ጋሽ ጌታቸው የጡረታ መብታቸውን ካስከበሩ በኋላ:-
1ኛ/አፍሪካ ቤዛ ኮሌጅ ሀዋሣ ቅርንጫፍ፣ በአስተዳደርና በተማሪዎች ጉዳይ ኃላፊነት ለሁለት ዓመት፣
2ኛ/ በደቡብ ኢትዮጵያ የግል ኮሌጅ በዲንነት፣ በአስተዳዳሪነት፣ በውስጥና በውጭ ግንኙነት፣ የኃላፊነት ቦታዎች ለ16 ዓመታት ሠርተዋል፣
3ኛ/የደቡብኢትዮጵያ ክልል የግል ኮሌጆች ማሕበር ጸሐፊ ሆነው ሠርተዋል።
እኝህ ሁለገብ የብቃት ማሳያ የሆኑት ብርቱ አባታችን ባሳዩት የስራ ትጋት በተለያዩ ጊዜያት ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል ከሽልማቶቹም መሐከል፡-
1ኛ/በትምህርት ቤት ደረጃ የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀት በ1976 ዓ.ም
2ኛ/በሲዳማ አውራጃ ት/ቤቶች ጸ/ቤት ደረጃ ካሉ መምህራንና ሠራተኞች መካከል ተመርጠው የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል (1975 ዓ.ም)
3ኛ/በሲዳሞ ክ/ሀገር ት/ቤቶች ደረጃ ካሉ መምህራንና ሠራተኞች መካከል ተመርጠው የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት አግኝተዋል።
መጥቀስ ይቻላል።
የትምህርትደረጃቸው፡-
1. ዲፕሎማ በእንግሊዝኛ ቋንቋ
2.በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሁፍ (አማርኛ) ቢ ኤ ዲግሪ (1976 ዓም)
3. Higher Diploma Licence a Certified Professional Teacher Educator (DiLLA UNIVERSITY) January 2007
ጋሽ ጌታቸው አሁን የ79 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ ባለትዳር እና የ6 ልጆች አባት ሲሆኑ 10 የልጅ ልጆቸን አይተዋል፡፡ ባሳለፉ የስራ ዘመናቸው ሀገርንና ህዝብን በታማኝነትና በቅንን እንዳገለገሉ ይናገራሉ፡፡ ለዚህም ደስተኛ ነኝ የቀረኝን ዕድሜ ፈጣሪን እያመሰገንኩ እኖራለሁ ብለውናል፡፡
እኛም ህዝባችንን ያገለገሉ ባለውለታዎችን ለመሸለም 30 ሰዎችን ስንመርጥ ከላይ የተጠቀሱትን ስራዎች ባሻገር “የሐዋሳ ትዝታ” ፔጅ እንዲቀጠል በመምክር፤ በማበረታታት፣ ልክ ያልሆኑ ጽሁፎችን ሲመለከቱ በዚህ ቢስተካከል በማለትና በመገሰጽ እሳቸው ካሉበት ዕውቀት ጋር አነፃፀረው ሳይንቁ ትችላላችሁ ጎበዞች በማለት በሀሳብ በመደገፍ እስከአሁኗ ጊዜ ድረስ አብረውን ስላሉ ምስጋናችንን ብቻ ሳይሆን ክብራችንንም ለመግለፅ እንወዳለን።
ጋሼ ክብረት ይስጥልን፡፡ በድጋሚ ረዥም ዕድሜን ከጤና ጋር ተመኘንልዎት፡፡
በሐና በቀለ
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
#hawassa| ፍቅራችንንም ክብራችንንም እነሆ
የሐዋሳ ትዝታ ተመስርቶ የመጀመሪያውን ጉብኝት በመ/ር ድጋፌ (ነብስ ይማር) ካደረግንበት ቀን ጀምሮ በሐሳብም በምክር ከኛጋር የነበሩ፣ በተለየ የማስታወስ ችሎታቸው የመረጃ ቋታችንም የክብር አባላችንም መሆናቸውን በቅድሚያ መግለፅ እንወዳለን!
መምህር ጌታቸው ተክሉ
መምህር ጌታቸው ተክሉ ባሳለፉት የስራ ዘመን ለሀገራቸው በብዙ የስራ ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡ እንዲያው እኔ በጽሁፍ ለመግለጽ እንዲያመቸኝ መምህር እንዲሁም በመሃል ደግሞ እንደልጅነቴ ጋሼ እያልኩ ጽሁፉን ባስነብባችሁ እሳቸውና አንባቢያኖቻችን ቅር እንደማትሰኙ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ወደ 5፡00 ሰዓት ገደማ በመኖሪያ ቤታቸው ደረስን፡፡ በብዙ ፈገግታ ተቀበሉን፡፡ በጠዋት ከቤት ወጣ ብለው እንደተመለሱ ነገሩን፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ የጤና ምርመራ አድርገው አንድ እግራቸውን ከሚያስነክሳቸው በስተቀር ጥሩ ጤንነት ላይ እንዳሉ ሀኪማቸው እንደነገሯቸው አጫወቱን፡፡ እኛም ቀበል አድርገን እግዚአብሔር ከጤና ጋር እድሜን እንዲሰጣቸው ተመኘን፡፡
የመጀመሪያ ጥያቄዬ የነበረው በሚያስተምሩበት ወቅት በጣም ተቆጪ እንደነበሩ ተማሪዎችዎ ነግረውኝ ነበር እርሶ ምን ይላሉ አልኳቸው፡፡ አዎ እቆጣ ነበር ጥፋት ስመለከትና ሳስተምር ሲረብሹኝ አይቼ ማለፍ አልችልም ልክ ናቸው እቆጣ ነበር አሉኝ፡፡ በግል ሕይወትዎና በቤትዎስ ይሄ ባህሪዎ ይንፀባረጋል? አዎ አጠገቤ ያሉ ሰዎች ያውቃሉ ጥፋት ሳይ ፊትለፊት ከመናገር ወደኋላ አልልም፤ ይሄ በቃ ባህሪዬ ነው ምንም ማድረግ እችላለሁ፡፡ አሁንስ ይሄ ባህሪዎ እንዳለ ነው? አይ አሁንማ አረጀሁ ብለው ፈገግ አስባሉን፡፡
መምህር ጌታቸው በ1937 ዓ.ም ጉራጌ ዞን በቡኢ ወረዳ (ከቡኢ 16 ኪ.ሜ ወደ ምድረ ከብድ አቦ በሚወስደው መንገድ) ጨላ በተባለው ቦታ ተወለዱ። የቄስ ትምህርት ቤት ፊደል ከቆጠሩ በኋላ ዳዊት ደግመዋል፣ አስር ዓመት ሲሞላቸው አዲስ አበባ በሚገኘው ልዑል መኮንን ት/ቤት (ያሁኑ አዲስ ከተማ ት/ቤት መርካቶ አወቶብስ ተራ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ በ1952 ዓ.ም) ተምረው በ1961 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀቁ።
በ1963 ዓ.ም መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ገብተው አንድ ዓመት ደብረዘይት ተናኜ ወርቅ ሃይስኩል የማስተማር ብሔራዊ አገልግሎት (National Service)፣ በ1965 ዓ.ም ሐምሌ ወር ከግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እጅ ዲፕሎማቸውን ወስደዋል።
ሲዳሞ ክ/ሀገር ነጌሌ ቦረና ሃይስኩል በእንግሊዝኛ መምህርነት ተመደቡ፡፡ ሁለት ዓመት ካስማሩ በኋላ ቦረና አውራጃ ዕርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ሲቋቋም ከትምህርት ሚኒስተር በውሰት ተወስደው የቦረና አውራጃ እርዳታ ማስተባበሪያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን ቅ/ጽ/ቤት የዕለት ደራሽ ኃላፊ ሆነው ለሁለት ዓመታት ሰርተዋል፣ በ1971 ዓ.ም ወደ ትምህርት ሚኒስቴር፣ የማስተማር ሥራቸውን ተመልሰው እዚያው ቦረና አውራጃ ነጌሌ ሃይሰኩል አስተምረዋል።
#በ1972 ዓ.ም ወደ ሀዋሣ ታቦር ሃይስኩል ተዛወሩ፡፡ በሀዋሣ ታቦር ሃይስልኩል ወስጥ እሰከ 1977 ዓ.ም ካስተማሩ በኋላ መደበኛ ሥራቸውን እየሠሩ ሀዋሣ ማዘጋጃ ቤት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመደቡ፣ በ1978 ዓ.ም የሀዋሣ ከተማ ምክትል ሹም ከዚያም ዋና ሹም ሆነው እስከ 1981 ዓ ም ሚያዚያ ወር ድረስ አገለገሉ።
ከ1977 ዓ.ም ጀምሮ ከማዘጋጃ ቤቱ ሥራ ጎን ለጎን የክፍለሀገሩ የቁጥጥር ኮሚቴ አባል ሆነው አገልግለዋል። የሀዋሣ ወረዳ መምህራን ማህበር ተመራጭ ሆነው በገንዘብ ያዥነት ሠርተዋል።
ከ1981 ዓ.ም ጀምሮ ሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት ቢሮ፣ የቦረና አስተዳደር አካባቢ ፀሐፊ (ሸንጎ ፀሐፊ) ሆነው ተሹመዋል። ቦረና አሰተዳደር አካባቢ እስከ 1983 ዓ.ም ከቆዩ በኋላ በ1984 ዓ.ም ወደ ታቦር ሃይሰኩል ተመልሰው ጡረታ እስከወጡበት እስከ 1994 ዓ.ም ድረስ አስተምረዋል።
ጋሽ ጌታቸው የጡረታ መብታቸውን ካስከበሩ በኋላ:-
1ኛ/አፍሪካ ቤዛ ኮሌጅ ሀዋሣ ቅርንጫፍ፣ በአስተዳደርና በተማሪዎች ጉዳይ ኃላፊነት ለሁለት ዓመት፣
2ኛ/ በደቡብ ኢትዮጵያ የግል ኮሌጅ በዲንነት፣ በአስተዳዳሪነት፣ በውስጥና በውጭ ግንኙነት፣ የኃላፊነት ቦታዎች ለ16 ዓመታት ሠርተዋል፣
3ኛ/የደቡብኢትዮጵያ ክልል የግል ኮሌጆች ማሕበር ጸሐፊ ሆነው ሠርተዋል።
እኝህ ሁለገብ የብቃት ማሳያ የሆኑት ብርቱ አባታችን ባሳዩት የስራ ትጋት በተለያዩ ጊዜያት ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል ከሽልማቶቹም መሐከል፡-
1ኛ/በትምህርት ቤት ደረጃ የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀት በ1976 ዓ.ም
2ኛ/በሲዳማ አውራጃ ት/ቤቶች ጸ/ቤት ደረጃ ካሉ መምህራንና ሠራተኞች መካከል ተመርጠው የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል (1975 ዓ.ም)
3ኛ/በሲዳሞ ክ/ሀገር ት/ቤቶች ደረጃ ካሉ መምህራንና ሠራተኞች መካከል ተመርጠው የምስጉን መምህርነት የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት አግኝተዋል።
መጥቀስ ይቻላል።
የትምህርትደረጃቸው፡-
1. ዲፕሎማ በእንግሊዝኛ ቋንቋ
2.በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሁፍ (አማርኛ) ቢ ኤ ዲግሪ (1976 ዓም)
3. Higher Diploma Licence a Certified Professional Teacher Educator (DiLLA UNIVERSITY) January 2007
ጋሽ ጌታቸው አሁን የ79 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ናቸው፡፡ ባለትዳር እና የ6 ልጆች አባት ሲሆኑ 10 የልጅ ልጆቸን አይተዋል፡፡ ባሳለፉ የስራ ዘመናቸው ሀገርንና ህዝብን በታማኝነትና በቅንን እንዳገለገሉ ይናገራሉ፡፡ ለዚህም ደስተኛ ነኝ የቀረኝን ዕድሜ ፈጣሪን እያመሰገንኩ እኖራለሁ ብለውናል፡፡
እኛም ህዝባችንን ያገለገሉ ባለውለታዎችን ለመሸለም 30 ሰዎችን ስንመርጥ ከላይ የተጠቀሱትን ስራዎች ባሻገር “የሐዋሳ ትዝታ” ፔጅ እንዲቀጠል በመምክር፤ በማበረታታት፣ ልክ ያልሆኑ ጽሁፎችን ሲመለከቱ በዚህ ቢስተካከል በማለትና በመገሰጽ እሳቸው ካሉበት ዕውቀት ጋር አነፃፀረው ሳይንቁ ትችላላችሁ ጎበዞች በማለት በሀሳብ በመደገፍ እስከአሁኗ ጊዜ ድረስ አብረውን ስላሉ ምስጋናችንን ብቻ ሳይሆን ክብራችንንም ለመግለፅ እንወዳለን።
ጋሼ ክብረት ይስጥልን፡፡ በድጋሚ ረዥም ዕድሜን ከጤና ጋር ተመኘንልዎት፡፡
በሐና በቀለ
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
1. ፋሲካ ደጀኔ በሰመረ በኩል 3000
2. ታዲዮስ ማስረሻ 5000
3. ቢኒያም ገነሞ 500
4. ክፍሌ ቦሌ 1000
5. አሰግድ ዲቃሶ 10,000
6. ፅጌ ግርማ 500
7.መቅደስ መኮንን 1000
2. ታዲዮስ ማስረሻ 5000
3. ቢኒያም ገነሞ 500
4. ክፍሌ ቦሌ 1000
5. አሰግድ ዲቃሶ 10,000
6. ፅጌ ግርማ 500
7.መቅደስ መኮንን 1000
#እናመሰግናለን| 7 ደጋጎች
#hawassa| 66,000 ብር
በአስከፊው የመኪና አደጋ ያጣናቸው 11 ወጣት የደራ ጤና ስፖርት ማህበር አባላት ቤተሰቦች ማቋቋሚያና በህክምና ላይ ለሚገኙት በህይወት ላሉ ማሳከሚያ የበኩሌን በማለት በኮሚቴው በተከፈተው አካውንት 1000610475667 ንግድ ባንክ
1. አሰበ ወልዴ (አዝጋርት ፑቲክ) 10,000
2.ደምሴ አበበ (ካራሶሪያ ጋራጅ) 15,000
3. በሐብቷ አስቻለው በሐብቷ የስፖርት ትጥቅ መሸጫ) 10,000
4. ቢኒያም ተሰማ (ቢኒ መድሐኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች አከፋፋይ) 5,000
5. ይዲዲያ ሰለሞን (አሜን መድሐኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች አከፋፋይ) 1,000
6. ተስፋፂዮን ዳንኤል (ሐዋራ ፋርማሴቲካል) 15,000
7. አድማሱ ደነቀ 10,000 ብር ድጋፍ አድርገዋል።
በወጣ ይተካ ክብረት ይስጥልን።
ልዑል አምላክ ከዚህ አይነት ክፉ አደጋ ሁላችንን እንዲጠብቀን እየተማፀንን ሁላችንም ተረባርበን የተቻለንን ድጋፍ እናደርግ ዘንድ ጥሪ እናስተላልፋለን። ቃል የገባችሁ ካላችሁ ከወዲሁ ብታስገቡ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
#hawassa| 66,000 ብር
በአስከፊው የመኪና አደጋ ያጣናቸው 11 ወጣት የደራ ጤና ስፖርት ማህበር አባላት ቤተሰቦች ማቋቋሚያና በህክምና ላይ ለሚገኙት በህይወት ላሉ ማሳከሚያ የበኩሌን በማለት በኮሚቴው በተከፈተው አካውንት 1000610475667 ንግድ ባንክ
1. አሰበ ወልዴ (አዝጋርት ፑቲክ) 10,000
2.ደምሴ አበበ (ካራሶሪያ ጋራጅ) 15,000
3. በሐብቷ አስቻለው በሐብቷ የስፖርት ትጥቅ መሸጫ) 10,000
4. ቢኒያም ተሰማ (ቢኒ መድሐኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች አከፋፋይ) 5,000
5. ይዲዲያ ሰለሞን (አሜን መድሐኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች አከፋፋይ) 1,000
6. ተስፋፂዮን ዳንኤል (ሐዋራ ፋርማሴቲካል) 15,000
7. አድማሱ ደነቀ 10,000 ብር ድጋፍ አድርገዋል።
በወጣ ይተካ ክብረት ይስጥልን።
ልዑል አምላክ ከዚህ አይነት ክፉ አደጋ ሁላችንን እንዲጠብቀን እየተማፀንን ሁላችንም ተረባርበን የተቻለንን ድጋፍ እናደርግ ዘንድ ጥሪ እናስተላልፋለን። ቃል የገባችሁ ካላችሁ ከወዲሁ ብታስገቡ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
#የተዋጣለት_መርከበኛው_ነጋዴ| ኃይለ ጋሼ
#Hawassa| በልጅ ወግ አክብረናል
ኃ/ሚካኤል ገ/ሚካኤል) - ቶታል ማደያ ባለቤት
ኅይለ ሚካኤል የቤታቸው ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ ስለዚህ ታናናሾቻቸው እንደሀገራቸው ባህል ስምን በማስቀደም ኃይሌ-ጋሼ ይሏቸው ነበር፡፡ይህ በጉራጌ ማህበረሰብ የቤቱ ታላቅ አጠራር ነው። ቢሆንም ኋይለሚካኤል ገብረሚካኤል የሚለው የመታወቂያ ስማቸው ተዘነጋና አብዛኛው ሰው በኃይለጋሼ ነው የሚያውቋቸው፡፡
የተወለዱት ሰባት ቤት ጉራጌ እዣ ወረዳ በ1939 ዓ.ም ሲሆን በ4 ዓመታቸው በ1943 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንደሄዱ ይናገራሉ፡፡
በ1947 ዓ.ም ሚኒሊክ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ከተማሩ በኋላ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ከ9 እስከ 12 ተምረው በኋላ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ስለነበራቸው ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲነሰ ተቀላቅለዋል።
ይሁን እንጅ ዶርም ገብተው የሚማሩ ልጆች ውስን ስለነበሩ ዶርም ያልደረሳቸው ደግሞ ዩኒቨርሲቲው በወር በሚሰጠው 20 ብር ቤት ተከራይተው እንዲማሩ ያመቻች ስለነበር እኔም ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ስለነበርኩ ይህንን ለአባቴ ነገርኩት፡፡ ነገር ግን አባቴ አልተስማማም፡፡ እሱ ይፈልግ የነበረው እዚያው ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ውስጥ ዶርም ይዤ እንድማር ነበር፡፡ ከ3 ወራት በላይ ትምህርቴን መቀጠል አልቻልኩም፡፡
በ1959 ዓ.ም የኢትዮጵያ የመርከብ ድርጅት ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ማስታወቂያ በመለጠፍ - “አለምን መዞር ሲያምራችሁ ካፒቴን ኢንጅነር ትሆናላችሁ” ይባል ነበር፡፡ ይህንን ማስታወቂያ አይተው ጓደኞቼ ሲነግሩኝ ለመመዝገብ ስሄድ የሚፈልጉት 15 ተማሪዎች ስለነበር እኔንና አንድ ተማሪን ተጠባባቂ አድርገውን እሮብ ተመለሱ አሉን፡፡ ባሉን ቀን ስንመለስ ሁለታችንን ተቀበሉን፡፡
ከዚያም እኔን የቀጠረኝ መስሪያ ቤት የንግደ ድርጅት ነው፡፡ ከዚያም ለትምህርት ምፅዋ ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ያሉት የባሕር ኃይል ነበር (የጦር መርከብ)፡፡ የንግድ መርከብ ትምህርት አልነበረም፡፡ ሆኖም ግድየለም እዚያው ተማሩ ተብለን ለ2 ዓመት እዚያው ተማርን፡፡ ከ2 ዓመት ቆይታ በኋላ ከእኛ በፊት የነበሩ የንግድ መርከብ ተማሪዎች እስከአሁን የተማርነው አስፈላጊ እንዳልሆነ ነግረውን እንደገና ወደ አዲስ አበባ ተመልሰን ጠየቅናቸው፡፡
የንግድ መርከብ ትምህርት ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ የለም፡፡ በወቅቱ የኢትዮጵያ መርከብን የሚሰሩት ሆላንዳዊያን ነበሩ፡፡ ስለዚህ ከሆላንድ መንግስት ጋር ተነጋግረው ለ2 ዓመት እዚያ ተምረን ተመለስን፡፡ እዚያ ከተማርን በኃላ ወደመርከብ ወጣሁ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ለ19 ዓመታት መርከብ ላይ ነበር የሰራሁት፡፡ "
የኃይለጋሼ ወላጅ አባት አቃቂ ቃሊቲ ነዳጅ ማደያና ሆቴል ነበራቸው እንዲሁም ሀዋሳ ቶታል ማደያ በ1960ዎቹ መጨረሻ የከፈቱት ሲሆን የኃይለጋሼ ታናሽ ወንድማቸው ያስተዳድሩት ነበር፡፡ በኋላ በ1970 ዓ.ም አባታቸው በመኪያ አደጋ ድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ወንድማቸው ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ኃይለጋሼ ሀዋሳ ነዳጅ ማደያ የመስራት እቅዱ ባይኖራቸውም የአባታቸው ድንገተኛ ሞት ወደሀዋሳ መጥተው ቶታል ማደያውን በ1971 ዓ.ም ጀምሮ ማስተዳደር እንደጀመሩና ሀዋሳ እስከዛሬዋ ጊዜ ድረስ እንደኖሩ ነው የነገሩኝ፡፡
ኃይለጋሼ የሐዋሳውን ማደያ ተረክበው በሚሰሩበት ወቅት ባለቤታቸው ወ/ሮ ወይኒቱ ታደሰ ደግሞ ከቶታሉ ጀርባ በቆርቆሮ የተከለለ ቤት ውስጥ ምግብ ቤት በመክፈት ይሸጡ ነበር፡፡ በዋናነት የሚሰራው ክትፎና ፍርፍር ሲሆን ደንበኞቻችን ክትፎና ፍርፍር ሲያዙ አንድ “ኮርኒስ” የሚል ስም አወጡለት ለምግብ፡፡
እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ የአቦካዶ ጁስ ወ/ሮ ወይኒቱ አዘጋጅታ ትሽጥ እንደነበር ኃይለጋሼ ነግረውኛል፡፡ ግን አንድ ምግብ ስንት ነበር? አልኳቸው፡፡ አንድ ምግብ በሁለት ብር ከሃምሣ ሳንቲም ነበር አሉኝ፡፡ ከዚያም አሉ ኃይለጋሼ በጣም ለመደልንና ስራውን በስፋት እየሰራን አጠገቡ መሬት ማዘጋጃ ሲሰጠን በ1981 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የንግድ ቤት ፎቅ መጀመሪያ የሆነውን በማስገንባት በ1983 ዓ.ም ስራውን በአዲስ መልክ ቀጠልን፡፡
በጊዜው ታዋቂ የሚባሉ ሆቴሎች እነማን ነበሩ? አልኳቸው፡፡ ዋቢሸበሌ፣ ያማረ ሆቴል፣ ብሔራዊ ሆቴል፣ ሸዋበር ሆቴል፣ ሰጎን ሆቴል፣ አንበሳ ሆቴል፣ ዋርካ አጠገብ አለማየሁ ሆቴል እና ሌሎችም ነበሩ፡፡
ከዚያም ከምግብ ቤቱ ቀጥሎ በ1987 ዓ.ም ቶታል ባንድ ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዋሳ ከተማ የተጀመረ ሲሆን በጊዜው የባንዱ አባል የነበሩት ሐይማኖት ግርማ፣ ቴድሮስ ቬንቼዚ፣ ዝናቡ ገ/ስላሴ፣ ሰብለ መዝሙር፣ ገረመው በቀለ፣ አሰግድና ሌሎችም ነበሩበት፡፡
ከባንዱ በተጨማሪ ከአዲስ አበባ አርቲስቶችን እንጋብዝ ነበር፡፡ ቴዲ አፍሮን ጨምሮ በብዛት አርቲስቶች ይመጡ ነበር አሉኝ ኃይለጋሼ፡፡
ኃይለጋሼና ወ/ሮ ወይኒቱ በትዳር የተጣመሩት በ1960ዎቹ መጨረሻ ነው። የኃይለጋሼ አባትና የወይንዬ አባት በጣም የልብ ወዳጆች ናቸው፡፡ አዲስ አበባ ካሳንቺስ መንደር አንድ ሰፈር ኖረዋል፡፡ ማህበርም አብረው ጠጥተዋል፡፡ ከአቀራረባቸው የተነሳ እንደቤተሰብ ነው የሚተያዩት፡፡ ሐዋሳ የወይንዬ አባት የመንገድ ትራንስፖርት የመጀመሪያ የመንጃ ፈቃድ ፈታኝ በነበሩበት ወቅት የኃይለጋሼ ታናሽ ወንድም የቶታል ማደያውን ሲያስተዳድሩ የወይንዬ አባት ቤት ሐዋሳ ይኖር ነበር፡፡ ይሄ ሂደታቸው ቤተሰባዊነቱን አጠናክሮላቸዋል፡፡ ይሁንና በዚህ መካከል ኃይለጋሼ እና ወይንዬ ተዋደዋል፡፡ ይሄ ደግሞ በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ቅሬታን ፈጥሮባቸዋል፡፡
የቤተሰቦቻቸው ምክንያት ደግሞ እኛ ቤተሰብ ነን ጋብቻችሁን አንፈቅድም የሚለው ሀሳብ በሁለቱም ቤተሰቦች ዘንድ ስለነበር፡፡ ጥንዶቹ ግን አሻፈረኝ አሉ፡፡ ተያይዘው መኮብለልን መረጡ፡፡ ከዚያም ወደሀዋሳ በመምጣት መኖር ከጀመሩ በኋላ ወደቤተሰቦቻቸው በመመለስ ይቅርታ ጠይቀው በመታረቅ በቅሬታ የቆየውን የቤተሰቦቻቸውን ፍቅር ዳግም በማደስ ሕይወታቸውን መምራት ጀመሩ፡፡
ባህር ኃይል በነበሩበት ወቅት የትኞቹን ሃገራት አዩ አልኳቸው፡፡ ባህር ያለበት አካባቢ በሙሉ አይቻለሁ፡፡ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ነርዌ፣ ሲውዲን፣ ስፔን፣ ኢታሊ፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካንና ሌሎችንም ኢሮፕ ሃገራት በስራው አጋጣሚ እንደሄዱ ነገሩኝ፡፡ በወሬያችን መካከል እንደው ካይዋት ሀገር እዚህች ሃገር ብቀር ያሉበት አጋጣሚ አልነበረም? አልኳቸው፡፡ በፍፁም አንድም ቀን ከሀገሬ ለመውጣት ተመኝቼ አላውቅም፡፡ እንደዚህ ስል ግን ሀገሬ ውስጥ ችግር የለም ማለቴ አይደለም፤ #ግን_ከነችግሩ_ሀገሬን_እወዳታለሁ አሉኝ፡፡ ኃይለጋሼ ከንግዱም ዓለም ባሻገር ጎበዝ ከሚባሉ ፎቶ አንሺዎች መካከልም ነበሩበት፡፡
በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሄድኩበት ወቅት ሀገሬ እንዲህ ተለውጣ ባይ ብዬ እመኝ ነበር፡፡ ነገር ግን በሂደት ሀዋሳ እንዲህ ተለውጣ እለት እለት ባየሁ ቁጥር ከሰራን እንደምንለወጥ ያመንኩበት ሁኔታ አለ፡፡ የእኛ ልጆች ደግሞ በትምህርትም ቢሆን በጣም ጎበዞች ናቸውና ወደፊት ከዚህ በላይ ሀገራችንን እንደሚለውጡ ተስፋ አለኝ ብለዋል፡፡
አሁን ኃይለጋሼ 78 ዓመታቸው ሲሆን ከወይንዬ ጋር ያፈሩት 6 ወንድ ልጆች እና 10 የልጅ ልጆችን አይተዋል፡፡
#Hawassa| በልጅ ወግ አክብረናል
ኃ/ሚካኤል ገ/ሚካኤል) - ቶታል ማደያ ባለቤት
ኅይለ ሚካኤል የቤታቸው ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ ስለዚህ ታናናሾቻቸው እንደሀገራቸው ባህል ስምን በማስቀደም ኃይሌ-ጋሼ ይሏቸው ነበር፡፡ይህ በጉራጌ ማህበረሰብ የቤቱ ታላቅ አጠራር ነው። ቢሆንም ኋይለሚካኤል ገብረሚካኤል የሚለው የመታወቂያ ስማቸው ተዘነጋና አብዛኛው ሰው በኃይለጋሼ ነው የሚያውቋቸው፡፡
የተወለዱት ሰባት ቤት ጉራጌ እዣ ወረዳ በ1939 ዓ.ም ሲሆን በ4 ዓመታቸው በ1943 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንደሄዱ ይናገራሉ፡፡
በ1947 ዓ.ም ሚኒሊክ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ 8ኛ ክፍል ከተማሩ በኋላ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ከ9 እስከ 12 ተምረው በኋላ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ስለነበራቸው ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲነሰ ተቀላቅለዋል።
ይሁን እንጅ ዶርም ገብተው የሚማሩ ልጆች ውስን ስለነበሩ ዶርም ያልደረሳቸው ደግሞ ዩኒቨርሲቲው በወር በሚሰጠው 20 ብር ቤት ተከራይተው እንዲማሩ ያመቻች ስለነበር እኔም ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል ስለነበርኩ ይህንን ለአባቴ ነገርኩት፡፡ ነገር ግን አባቴ አልተስማማም፡፡ እሱ ይፈልግ የነበረው እዚያው ዩኒቨርሲቲ ጊቢ ውስጥ ዶርም ይዤ እንድማር ነበር፡፡ ከ3 ወራት በላይ ትምህርቴን መቀጠል አልቻልኩም፡፡
በ1959 ዓ.ም የኢትዮጵያ የመርከብ ድርጅት ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ማስታወቂያ በመለጠፍ - “አለምን መዞር ሲያምራችሁ ካፒቴን ኢንጅነር ትሆናላችሁ” ይባል ነበር፡፡ ይህንን ማስታወቂያ አይተው ጓደኞቼ ሲነግሩኝ ለመመዝገብ ስሄድ የሚፈልጉት 15 ተማሪዎች ስለነበር እኔንና አንድ ተማሪን ተጠባባቂ አድርገውን እሮብ ተመለሱ አሉን፡፡ ባሉን ቀን ስንመለስ ሁለታችንን ተቀበሉን፡፡
ከዚያም እኔን የቀጠረኝ መስሪያ ቤት የንግደ ድርጅት ነው፡፡ ከዚያም ለትምህርት ምፅዋ ወሰዱን፡፡ እዚያ ስንደርስ ያሉት የባሕር ኃይል ነበር (የጦር መርከብ)፡፡ የንግድ መርከብ ትምህርት አልነበረም፡፡ ሆኖም ግድየለም እዚያው ተማሩ ተብለን ለ2 ዓመት እዚያው ተማርን፡፡ ከ2 ዓመት ቆይታ በኋላ ከእኛ በፊት የነበሩ የንግድ መርከብ ተማሪዎች እስከአሁን የተማርነው አስፈላጊ እንዳልሆነ ነግረውን እንደገና ወደ አዲስ አበባ ተመልሰን ጠየቅናቸው፡፡
የንግድ መርከብ ትምህርት ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ የለም፡፡ በወቅቱ የኢትዮጵያ መርከብን የሚሰሩት ሆላንዳዊያን ነበሩ፡፡ ስለዚህ ከሆላንድ መንግስት ጋር ተነጋግረው ለ2 ዓመት እዚያ ተምረን ተመለስን፡፡ እዚያ ከተማርን በኃላ ወደመርከብ ወጣሁ፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ለ19 ዓመታት መርከብ ላይ ነበር የሰራሁት፡፡ "
የኃይለጋሼ ወላጅ አባት አቃቂ ቃሊቲ ነዳጅ ማደያና ሆቴል ነበራቸው እንዲሁም ሀዋሳ ቶታል ማደያ በ1960ዎቹ መጨረሻ የከፈቱት ሲሆን የኃይለጋሼ ታናሽ ወንድማቸው ያስተዳድሩት ነበር፡፡ በኋላ በ1970 ዓ.ም አባታቸው በመኪያ አደጋ ድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ወንድማቸው ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ኃይለጋሼ ሀዋሳ ነዳጅ ማደያ የመስራት እቅዱ ባይኖራቸውም የአባታቸው ድንገተኛ ሞት ወደሀዋሳ መጥተው ቶታል ማደያውን በ1971 ዓ.ም ጀምሮ ማስተዳደር እንደጀመሩና ሀዋሳ እስከዛሬዋ ጊዜ ድረስ እንደኖሩ ነው የነገሩኝ፡፡
ኃይለጋሼ የሐዋሳውን ማደያ ተረክበው በሚሰሩበት ወቅት ባለቤታቸው ወ/ሮ ወይኒቱ ታደሰ ደግሞ ከቶታሉ ጀርባ በቆርቆሮ የተከለለ ቤት ውስጥ ምግብ ቤት በመክፈት ይሸጡ ነበር፡፡ በዋናነት የሚሰራው ክትፎና ፍርፍር ሲሆን ደንበኞቻችን ክትፎና ፍርፍር ሲያዙ አንድ “ኮርኒስ” የሚል ስም አወጡለት ለምግብ፡፡
እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ በሀዋሳ ከተማ የአቦካዶ ጁስ ወ/ሮ ወይኒቱ አዘጋጅታ ትሽጥ እንደነበር ኃይለጋሼ ነግረውኛል፡፡ ግን አንድ ምግብ ስንት ነበር? አልኳቸው፡፡ አንድ ምግብ በሁለት ብር ከሃምሣ ሳንቲም ነበር አሉኝ፡፡ ከዚያም አሉ ኃይለጋሼ በጣም ለመደልንና ስራውን በስፋት እየሰራን አጠገቡ መሬት ማዘጋጃ ሲሰጠን በ1981 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የንግድ ቤት ፎቅ መጀመሪያ የሆነውን በማስገንባት በ1983 ዓ.ም ስራውን በአዲስ መልክ ቀጠልን፡፡
በጊዜው ታዋቂ የሚባሉ ሆቴሎች እነማን ነበሩ? አልኳቸው፡፡ ዋቢሸበሌ፣ ያማረ ሆቴል፣ ብሔራዊ ሆቴል፣ ሸዋበር ሆቴል፣ ሰጎን ሆቴል፣ አንበሳ ሆቴል፣ ዋርካ አጠገብ አለማየሁ ሆቴል እና ሌሎችም ነበሩ፡፡
ከዚያም ከምግብ ቤቱ ቀጥሎ በ1987 ዓ.ም ቶታል ባንድ ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዋሳ ከተማ የተጀመረ ሲሆን በጊዜው የባንዱ አባል የነበሩት ሐይማኖት ግርማ፣ ቴድሮስ ቬንቼዚ፣ ዝናቡ ገ/ስላሴ፣ ሰብለ መዝሙር፣ ገረመው በቀለ፣ አሰግድና ሌሎችም ነበሩበት፡፡
ከባንዱ በተጨማሪ ከአዲስ አበባ አርቲስቶችን እንጋብዝ ነበር፡፡ ቴዲ አፍሮን ጨምሮ በብዛት አርቲስቶች ይመጡ ነበር አሉኝ ኃይለጋሼ፡፡
ኃይለጋሼና ወ/ሮ ወይኒቱ በትዳር የተጣመሩት በ1960ዎቹ መጨረሻ ነው። የኃይለጋሼ አባትና የወይንዬ አባት በጣም የልብ ወዳጆች ናቸው፡፡ አዲስ አበባ ካሳንቺስ መንደር አንድ ሰፈር ኖረዋል፡፡ ማህበርም አብረው ጠጥተዋል፡፡ ከአቀራረባቸው የተነሳ እንደቤተሰብ ነው የሚተያዩት፡፡ ሐዋሳ የወይንዬ አባት የመንገድ ትራንስፖርት የመጀመሪያ የመንጃ ፈቃድ ፈታኝ በነበሩበት ወቅት የኃይለጋሼ ታናሽ ወንድም የቶታል ማደያውን ሲያስተዳድሩ የወይንዬ አባት ቤት ሐዋሳ ይኖር ነበር፡፡ ይሄ ሂደታቸው ቤተሰባዊነቱን አጠናክሮላቸዋል፡፡ ይሁንና በዚህ መካከል ኃይለጋሼ እና ወይንዬ ተዋደዋል፡፡ ይሄ ደግሞ በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ቅሬታን ፈጥሮባቸዋል፡፡
የቤተሰቦቻቸው ምክንያት ደግሞ እኛ ቤተሰብ ነን ጋብቻችሁን አንፈቅድም የሚለው ሀሳብ በሁለቱም ቤተሰቦች ዘንድ ስለነበር፡፡ ጥንዶቹ ግን አሻፈረኝ አሉ፡፡ ተያይዘው መኮብለልን መረጡ፡፡ ከዚያም ወደሀዋሳ በመምጣት መኖር ከጀመሩ በኋላ ወደቤተሰቦቻቸው በመመለስ ይቅርታ ጠይቀው በመታረቅ በቅሬታ የቆየውን የቤተሰቦቻቸውን ፍቅር ዳግም በማደስ ሕይወታቸውን መምራት ጀመሩ፡፡
ባህር ኃይል በነበሩበት ወቅት የትኞቹን ሃገራት አዩ አልኳቸው፡፡ ባህር ያለበት አካባቢ በሙሉ አይቻለሁ፡፡ እንግሊዝ፣ ጀርመን፣ ነርዌ፣ ሲውዲን፣ ስፔን፣ ኢታሊ፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካንና ሌሎችንም ኢሮፕ ሃገራት በስራው አጋጣሚ እንደሄዱ ነገሩኝ፡፡ በወሬያችን መካከል እንደው ካይዋት ሀገር እዚህች ሃገር ብቀር ያሉበት አጋጣሚ አልነበረም? አልኳቸው፡፡ በፍፁም አንድም ቀን ከሀገሬ ለመውጣት ተመኝቼ አላውቅም፡፡ እንደዚህ ስል ግን ሀገሬ ውስጥ ችግር የለም ማለቴ አይደለም፤ #ግን_ከነችግሩ_ሀገሬን_እወዳታለሁ አሉኝ፡፡ ኃይለጋሼ ከንግዱም ዓለም ባሻገር ጎበዝ ከሚባሉ ፎቶ አንሺዎች መካከልም ነበሩበት፡፡
በተለያዩ የዓለም ሀገራት በሄድኩበት ወቅት ሀገሬ እንዲህ ተለውጣ ባይ ብዬ እመኝ ነበር፡፡ ነገር ግን በሂደት ሀዋሳ እንዲህ ተለውጣ እለት እለት ባየሁ ቁጥር ከሰራን እንደምንለወጥ ያመንኩበት ሁኔታ አለ፡፡ የእኛ ልጆች ደግሞ በትምህርትም ቢሆን በጣም ጎበዞች ናቸውና ወደፊት ከዚህ በላይ ሀገራችንን እንደሚለውጡ ተስፋ አለኝ ብለዋል፡፡
አሁን ኃይለጋሼ 78 ዓመታቸው ሲሆን ከወይንዬ ጋር ያፈሩት 6 ወንድ ልጆች እና 10 የልጅ ልጆችን አይተዋል፡፡
በመጨረሻም ከተማችንን ስላገለገሉ እናመሰግናለን አልናቸው፡፡ እርሳቸውም አይ ለራሴ ጥቅም ሰራሁ እንጂ ህዝብን መች አገለገልኩ ብለሽ ነው አሉኝ፡፡ ያኔ ትዝ ይለኛል በአብዛኛዎቻችን ቤት የቡታጋዝ ተጠቃሚ በነበርንበት ጊዜ ከ1 ሌትር ጀምሮ ነጭ ጋዝ ይሸጡ ነበር፡፡ እሳቸው በአቅራቢያው ለዝቅተኛው ማሕበረሰብ ባያቀርቡ ከየት እንጠቀም ነበር? ብቻ ብዙ የሰሩ ሰዎች ብዙ ማውራት አይፈልጉም፡፡ ለእሳቸውም ለሚወዷቸው ባለቤታቸው እዲሁም በአጠቃላይ ለቤተሰቦቻቸው መልካም ምኞታችንን ተመኝተን ከእሳቸውም ከወይንዬም ምርቃትን ተቀብለን ለቀጣይ ሳምንት ጋቢ ለምናለብሰው አባት ቤት መንገጃችንን አቀናን፡፡ መልካም ዕለተሰንበት!
ሊዲያ /የሚኬ ባለቤት/ ስለቅንነትሽና ስለመልካም ትብብርሽ ሳላመሰግንሽ ማለፍ ንፉግነት ነው፡፡ ነፍፍፍፍፍ አመት ኑሪልኝ እህቴ፡፡
ምስጋና፡ ለፍቅሩና ጓደኞቹ እንዲሁም ለዶ/ር ዘነበ (አልፋኬር መካከለኛ ክሊኒክ) Zenebe Mekonnen
በሐና በቀለ
*
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
ሊዲያ /የሚኬ ባለቤት/ ስለቅንነትሽና ስለመልካም ትብብርሽ ሳላመሰግንሽ ማለፍ ንፉግነት ነው፡፡ ነፍፍፍፍፍ አመት ኑሪልኝ እህቴ፡፡
ምስጋና፡ ለፍቅሩና ጓደኞቹ እንዲሁም ለዶ/ር ዘነበ (አልፋኬር መካከለኛ ክሊኒክ) Zenebe Mekonnen
በሐና በቀለ
*
የፍቅር የሰላምና የአንድነት አርበኞች!
#የዝክረ_ደራ| የመዝግያ መርሐግብር
#hawassa| ነገ በ10 ሰዓት በሴንትራል ሆቴል
በቅድሚያ ለዛሬው ቀን ላደረሰን ፈጣሪ ምስጋና እያቀረብን በዝክረ ደራ (በመኪና አደጋ ላጣናቸው ወንድሞቻችን ቤተሰቦች ማቋቋሚያና ቀላልና ከባድ ጉዳት ለደረሰባቸው ህክምና ወጭ በሐገር ውስጥና በውጭ ሐገር ኮሚቴ ተቋቁም የገቢ ማሰባሰብ ከፍተኛ እንቅስቃሴ መደረጉ ይታወቃል። በዚህም እናንተ ከማፅናናት ባለፈ ላሳያችሁን ቤተሰባዊ ፍቅርና ላደረጋችሁት የገንዘብ ድጋፍ አክብሮታችንን ለመግለፅ እንወዳለን። ለሟቾችም ነብስ ይማር ለቤተሰብ መፅናናትን፣ ለቆሰሉት መሻርን ያድልልን ዘንድ እንመኛለን።
በመሆኑም ዝክረ ደራ የገቢ አሰባሰብ ኮሚቴ ያከናወናቸውን ተግባራትና ሌሎች አጠቃላይ ሂደት ለናንተ ለማቅረብ የመዝጊያ ፕሮግራሙን የፊታችን አርብ በሴንትራል ሆቴል በ10:00 ሰዓት ያከናውናል። በእለቱ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የሐይማኖት መሪዎች፣ የሟች ቤተሰቦች፣ በፈጣሪ ፍቃድ ከአደጋው የተረፉ ወንድሞች፣ የደራ ዘይት ጤና ስፖርት አባላት፣ ወዳጅ ዘመድ በተገኘበት ይከናወናል።
ኮሚቴው ሁላችሁንም በሴንትራል ሆቴል በ10 ሰዓት እንድትገኙ ጥሪውን ያቀርባል።
የዝክረ ደራ አስተባባሪ ኮሚቴ
01/9/2016
ሐዋሳ
#hawassa| ነገ በ10 ሰዓት በሴንትራል ሆቴል
በቅድሚያ ለዛሬው ቀን ላደረሰን ፈጣሪ ምስጋና እያቀረብን በዝክረ ደራ (በመኪና አደጋ ላጣናቸው ወንድሞቻችን ቤተሰቦች ማቋቋሚያና ቀላልና ከባድ ጉዳት ለደረሰባቸው ህክምና ወጭ በሐገር ውስጥና በውጭ ሐገር ኮሚቴ ተቋቁም የገቢ ማሰባሰብ ከፍተኛ እንቅስቃሴ መደረጉ ይታወቃል። በዚህም እናንተ ከማፅናናት ባለፈ ላሳያችሁን ቤተሰባዊ ፍቅርና ላደረጋችሁት የገንዘብ ድጋፍ አክብሮታችንን ለመግለፅ እንወዳለን። ለሟቾችም ነብስ ይማር ለቤተሰብ መፅናናትን፣ ለቆሰሉት መሻርን ያድልልን ዘንድ እንመኛለን።
በመሆኑም ዝክረ ደራ የገቢ አሰባሰብ ኮሚቴ ያከናወናቸውን ተግባራትና ሌሎች አጠቃላይ ሂደት ለናንተ ለማቅረብ የመዝጊያ ፕሮግራሙን የፊታችን አርብ በሴንትራል ሆቴል በ10:00 ሰዓት ያከናውናል። በእለቱ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት የሐይማኖት መሪዎች፣ የሟች ቤተሰቦች፣ በፈጣሪ ፍቃድ ከአደጋው የተረፉ ወንድሞች፣ የደራ ዘይት ጤና ስፖርት አባላት፣ ወዳጅ ዘመድ በተገኘበት ይከናወናል።
ኮሚቴው ሁላችሁንም በሴንትራል ሆቴል በ10 ሰዓት እንድትገኙ ጥሪውን ያቀርባል።
የዝክረ ደራ አስተባባሪ ኮሚቴ
01/9/2016
ሐዋሳ