ቤተ ክርስቲያን አርባ አራት ጥንዶች ልትሞሽር ነው
| ጃንደረባው ሚድያ | ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም.|
በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ጃን ቃና ዘገሊላ የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ያስተማራቸው 44 ጥንዶችን ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊድር እንደሆነ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ካሉ የውስጥ አባላት መካከል 47 የሚሆኑት በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን የፈጸሙ መሆናቸውን የኢጃት የሰው ኃይል ክፍል ኃላፊው ዲያቆን በረከተ ሥላሴ እሸቱ የገለጹ ሲሆን በጃን ቃና ዘገሊላ ሥር ደግሞ ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም በታሪክ የመጀመሪያው በሆነው የብዙኃን ጋብቻ መርሐግብር 23 ጥንዶች መዳራቸውን የጃን ቃና ዘገሊላ አስተባባሪ ወ/ት መቅደስ ጌታሁን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጃን ቃና ዘገሊላ ፕሮጀክት በወርኃ መጋቢት 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ለአንድ ወር ያህል ለ4ኛ ዙር ያዘጋጀውን የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለ350 ወጣቶች የሰጠ ሲሆን ትምህርቱን ከወሰዱ 44 የሚሆኑት ጥንዶች የብዙኃን ጋብቻ በተሰኘው ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በኅብረት በምትድርበት ልዩ መርሐግብር ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡
የብዙኃን ጋብቻ የዝግጅት ሂደትንና የጋብቻ ሥርዓቱ ስለሚፈጸምበት ሁኔታ ተብራርቶ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ይህ የብዙኃን ጋብቻ መርሐግብር አላማ ያደረገው ወጣቶች በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን እንዲፈጽሙ ለማድረግ፣ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በኅብረት የምትድርበትን ቀን ለመፍጠርና በሠርግ ምክንያት አድርጎ የሚሰባሰብ ትልቅ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብና ማኅበረሰብን ለመገንባት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በዚህ መሠረት እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ 44 ጥንዶች ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በደማቅ ስነ ሥርዓት ጋብቻቸውን የሚፈጽሙ ይሆናል፡፡
በመግለጫው ምዕመናን በዚሁ ቀን በካቴድራሉ ተገኝተው የደስታቸው ተካፋይ እንዲሆኑ ሙሽሮቹንም በጸሎት እንዲያስቡ ጥሪ ቀርቧል፡፡ በቀጣይ ዓመት ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ውጪ ጋብቻቸውን የፈጸሙ ምዕመናን ቃል ኪዳነቸውን የሚያድሱበት በጋራ ስጋወ ደሙን የሚቀበሉበት መርሐግብር እንደሚዘጋጅም ወ/ት መቅደስ አሳውቀዋል፡፡
ጃን ቃና ዘገሊላ የብዙኃን ጋብቻ የሚያደርገው በደጋግ ክርስቲያኖች የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ሲሆን አላማው ገብቷቸው የቤተ ክርስቲያንን አደራ ተቀብለው ይህ ታሪካዊ መርሐግብር እንዲሳካ የበኩላቸውን ጥረት ላደረጉ አጋር ተቋማትና ግለሰቦች በመግለጫው ምስጋና ቀርቧል፡፡
የጋዜጣዊ መግለጫውን ሙሉ ይዘት 12:00 ሰዓት ላይ በጃንደረባው ሚዲያ ዩቲዩብ ገጽ የሚለቀቅ ይሆናል፡፡
ጋብቻዬን በሥርዓተ ቤተ ክርሰቲያን እንዳልፈጽም የሚከለክለኝ ምንድን ነው?
| ጃንደረባው ሚድያ | ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም.|
በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ጃን ቃና ዘገሊላ የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ያስተማራቸው 44 ጥንዶችን ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊድር እንደሆነ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በማኅበሩ አገልግሎት ላይ ካሉ የውስጥ አባላት መካከል 47 የሚሆኑት በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን የፈጸሙ መሆናቸውን የኢጃት የሰው ኃይል ክፍል ኃላፊው ዲያቆን በረከተ ሥላሴ እሸቱ የገለጹ ሲሆን በጃን ቃና ዘገሊላ ሥር ደግሞ ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም በታሪክ የመጀመሪያው በሆነው የብዙኃን ጋብቻ መርሐግብር 23 ጥንዶች መዳራቸውን የጃን ቃና ዘገሊላ አስተባባሪ ወ/ት መቅደስ ጌታሁን ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ጃን ቃና ዘገሊላ ፕሮጀክት በወርኃ መጋቢት 2017 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ለአንድ ወር ያህል ለ4ኛ ዙር ያዘጋጀውን የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለ350 ወጣቶች የሰጠ ሲሆን ትምህርቱን ከወሰዱ 44 የሚሆኑት ጥንዶች የብዙኃን ጋብቻ በተሰኘው ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በኅብረት በምትድርበት ልዩ መርሐግብር ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡
የብዙኃን ጋብቻ የዝግጅት ሂደትንና የጋብቻ ሥርዓቱ ስለሚፈጸምበት ሁኔታ ተብራርቶ የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ይህ የብዙኃን ጋብቻ መርሐግብር አላማ ያደረገው ወጣቶች በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን እንዲፈጽሙ ለማድረግ፣ ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በኅብረት የምትድርበትን ቀን ለመፍጠርና በሠርግ ምክንያት አድርጎ የሚሰባሰብ ትልቅ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብና ማኅበረሰብን ለመገንባት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በዚህ መሠረት እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ 44 ጥንዶች ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በደማቅ ስነ ሥርዓት ጋብቻቸውን የሚፈጽሙ ይሆናል፡፡
በመግለጫው ምዕመናን በዚሁ ቀን በካቴድራሉ ተገኝተው የደስታቸው ተካፋይ እንዲሆኑ ሙሽሮቹንም በጸሎት እንዲያስቡ ጥሪ ቀርቧል፡፡ በቀጣይ ዓመት ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ውጪ ጋብቻቸውን የፈጸሙ ምዕመናን ቃል ኪዳነቸውን የሚያድሱበት በጋራ ስጋወ ደሙን የሚቀበሉበት መርሐግብር እንደሚዘጋጅም ወ/ት መቅደስ አሳውቀዋል፡፡
ጃን ቃና ዘገሊላ የብዙኃን ጋብቻ የሚያደርገው በደጋግ ክርስቲያኖች የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ሲሆን አላማው ገብቷቸው የቤተ ክርስቲያንን አደራ ተቀብለው ይህ ታሪካዊ መርሐግብር እንዲሳካ የበኩላቸውን ጥረት ላደረጉ አጋር ተቋማትና ግለሰቦች በመግለጫው ምስጋና ቀርቧል፡፡
የጋዜጣዊ መግለጫውን ሙሉ ይዘት 12:00 ሰዓት ላይ በጃንደረባው ሚዲያ ዩቲዩብ ገጽ የሚለቀቅ ይሆናል፡፡
ጋብቻዬን በሥርዓተ ቤተ ክርሰቲያን እንዳልፈጽም የሚከለክለኝ ምንድን ነው?
44ቱ ሙሽሮች ለታራሚዎች ድጋፍ አደረጉ
ጃንደረባው ሚዲያ | ግንቦት 17 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በማኅበራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጃን ጳውሎስና ሲላስ ከጃን ቃና ዘገሊላ ጋር በመሆን 44ቱን ሙሽሮች በማስተባበር በልደታ ክ/ከተማ በሚገኘው በወንጀል ነክ ነገር ውስጥ ገብተው የተገኙ ሕፃናት ማቆያና ተሐድሶ ተቋም ተገኝተው የአልባሳት፣ የንፅህና መጠበቂያ ቁሶች ድጋፍና የምሳ ግብዣ አድርገዋል፡፡
ይህ መርሐግብር በዋናነት የተዘጋጀው ጃን ጳውሎስ ሲላስ አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን (SPOT church) የተበረከተለትን 10 ሻንጣ ልብስ ለዚህ ተቋም ለማስረከብና ጃን ቃና ዘገሊላ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሚያዘጋጀው 2ኛው ብዙኃን ጋብቻ የሚሞሸሩት 44 ጥንዶች ከሰርጋቸው በፊት የታሰሩትን በመጠየቅ የጽድቅ ሥራ ላይ እንዲሳተፉ ለማድረግ፤ የትዳር ሕይወታቸውንም በተመሳሳይ የበጎ ምግባራት እንዲያሳልፉ ለማነሳሳት ነው ያሉት የጃን ቃና ዘገሊላ ተወካይ ዲያቆን በረከት ወርቁ ናቸው፡፡
ከሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን የተበረከተውን 10 ሻንጣ ልብስ እንዲሁም 44ቱ ሙሽሮች የለገሱትን የንፅሕና መጠበቂያ ቁሶች ለተቋሙ ተጠሪ ኃላፊ አቶ ጭምዴሣ ነገሣ ያስረከቡት የኢጃት ቦርድ አባል ወ/ት ማስረሻ ምትኩ ሲሆኑ ታዳጊዎቹ የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ እንደ 44ቱ ሙሽሮች ትምህርታቸውን ጨርሰውና ራሳቸውን ችለው የወጣትነት ጊዜያቸውን በመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያሳልፉ ምክር ሰጥተዋል፡፡
በመርሐግብሩ ታዳጊዎቹ ለ44ቱ ሙሽሮች መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሙሽሮቹም በተግባር ለሕጻናቱ አርአያ በመሆን የሰርጋቸውን ዋዜማ መልካም የሆነ ክርስቲያናዊ ተግባርን በመፈጸም ጀምረዋል፡፡ ጃን ጳውሎስና ሲላስ ለሕግ ታራሚዎች የጥየቃ መርሐ ግብር ፣ መንፈሳዊ የምክር አገልግሎትና የመጻሕፍት ልገሳም ላይ ከዚህ ቀደም ሲሠራ እንደቆየ ይታወሳል::
ጃንደረባው ሚዲያ | ግንቦት 17 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ በማኅበራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጃን ጳውሎስና ሲላስ ከጃን ቃና ዘገሊላ ጋር በመሆን 44ቱን ሙሽሮች በማስተባበር በልደታ ክ/ከተማ በሚገኘው በወንጀል ነክ ነገር ውስጥ ገብተው የተገኙ ሕፃናት ማቆያና ተሐድሶ ተቋም ተገኝተው የአልባሳት፣ የንፅህና መጠበቂያ ቁሶች ድጋፍና የምሳ ግብዣ አድርገዋል፡፡
ይህ መርሐግብር በዋናነት የተዘጋጀው ጃን ጳውሎስ ሲላስ አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው የሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን (SPOT church) የተበረከተለትን 10 ሻንጣ ልብስ ለዚህ ተቋም ለማስረከብና ጃን ቃና ዘገሊላ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በሚያዘጋጀው 2ኛው ብዙኃን ጋብቻ የሚሞሸሩት 44 ጥንዶች ከሰርጋቸው በፊት የታሰሩትን በመጠየቅ የጽድቅ ሥራ ላይ እንዲሳተፉ ለማድረግ፤ የትዳር ሕይወታቸውንም በተመሳሳይ የበጎ ምግባራት እንዲያሳልፉ ለማነሳሳት ነው ያሉት የጃን ቃና ዘገሊላ ተወካይ ዲያቆን በረከት ወርቁ ናቸው፡፡
ከሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን የተበረከተውን 10 ሻንጣ ልብስ እንዲሁም 44ቱ ሙሽሮች የለገሱትን የንፅሕና መጠበቂያ ቁሶች ለተቋሙ ተጠሪ ኃላፊ አቶ ጭምዴሣ ነገሣ ያስረከቡት የኢጃት ቦርድ አባል ወ/ት ማስረሻ ምትኩ ሲሆኑ ታዳጊዎቹ የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ሲወጡ እንደ 44ቱ ሙሽሮች ትምህርታቸውን ጨርሰውና ራሳቸውን ችለው የወጣትነት ጊዜያቸውን በመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲያሳልፉ ምክር ሰጥተዋል፡፡
በመርሐግብሩ ታዳጊዎቹ ለ44ቱ ሙሽሮች መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሙሽሮቹም በተግባር ለሕጻናቱ አርአያ በመሆን የሰርጋቸውን ዋዜማ መልካም የሆነ ክርስቲያናዊ ተግባርን በመፈጸም ጀምረዋል፡፡ ጃን ጳውሎስና ሲላስ ለሕግ ታራሚዎች የጥየቃ መርሐ ግብር ፣ መንፈሳዊ የምክር አገልግሎትና የመጻሕፍት ልገሳም ላይ ከዚህ ቀደም ሲሠራ እንደቆየ ይታወሳል::