Telegram Web Link
በሁለንተናዊ አቅሙ የዳበረ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ  ተገለጸ

ሐምሌ ፳፫/፳፻፲፯ ዓ.ም

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሥልታዊ ዕቅዱ ትኩረት አድርጎ ከሚሠራባቸው አገልግሎቶች መካከል መንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት በመስጠት ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን የሚያጠናክሩ  ካህናትና ባለሙያዎችን አሠልጥኖ ማሰማራት አንዱ ሲሆን በዚህ  ከጌዲዮ፣ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ለተውጣጡ በቁጥር 24 ለሚሆኑ ካህናት፣መምህራንና የዘርፉ ባለሙያዎች በዲላ  ዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል፡፡

በሥልጠናው   ለምክክር አገልግሎት የሚረዱ ክብረ ክህነትና አበ ነፍስ፣ መንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት አሰጣጥ፣ ኦርቶዶክሳዊ ጋብቻና የልጆች አስተዳደግ፣ ሱስና መሰል ተግዳሮቶች እንዲሁም ምጣኔ  ሐብትና  ማኅበራዊ  ዕድገት ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡

በመርሐ ግብሩ  የተገኙት የጌዲዮ፣ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገሪማ ባስተላለፉት መልእክት ካህናትና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ኦርቶዶክሳዊ የመሪነት ጥበብን ከራሳቸው ቤተሰብ በመጀመር ለምእመናን አርአያ መሆን ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን አክለውም አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን የሉላዊነት አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቋቋም ከዘመኑ ጋር በመራመድ በሁለንተናዊ አቅሙ የዳበረ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ መገንባት ላይ ማተኮር እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡

በሥልጠናው ጥሩ ግንዛቤና ልምድ እንዳገኙበት የገለጹት ተሳታፊዎቹ  ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱ ምእመናን ያለባቸውን ዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ ቀውስ  እንዲቋቋሙ  ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል፡፡
2
ማኅበረ ቅዱሳን  ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን ለማጠናከር  የአመካካሪዎች ሥልጠና እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ ሥልጠናው ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች ለመስጠት እንዲቻል ምእመናን የተለመደ ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪውን ያቀርባል፡፡


ይህን የሥልጠና መርሐ ግብር በገንዘብ መደገፍ ለምትፈልጉም፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400 መጠቀም  የምትችሉ  መሆኑን እንገልጻለን።

👇👇👇👇👇👇👇
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://www.tg-me.com/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
            :- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905
ማስታወቂያ

እሑድ ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ሊደረግ የነበረው መደበኛው የማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል ወርኃዊ ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች አማካኝነት የማይደረግ መሆኑን እየገለጽን በቀጣይ የሚከናወንበትን ቀን እናሳውቃለን።
57 የደረጃ ሁለት የአፋን ኦሮሞ ተተኪ መምህራን መመረቃቸው ተገለጸ

ሐምሌ ፳፭/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን ከሚያስተምራቸው ከአገር ውስጥ ግቢ ጉባኤያት የተውጣጡ በመሐል ማእከላት አስተባባሪነት በአዳማ አቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ሲሠለጥኑ የቆዩ 57 የደረጃ ሁለት የአፋን ኦሮሞ ተተኪ መምህራን በአዳማ (ናዝሬት) ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስመርቋል።

የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ጌቱ በንግግራቸው ማኅበረ ቅዱሳን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባልደረሰችባቸው የተለያዩ ቦታዎች እና በግቢ ጉባኤያት እየሠጠ ባለው አገልግሎት አመስግነዋል፡፡

ምክትል ሥራ አስኪያጁ በገለጻቸው የሠለጠኑት አዳዲስ መምህራን ባለው የአገልግሎት ክፍተት በተለይ በቋንቋ ለትውልዱ በማዳረስ ረገድ ቅድሚያ ሰጥተው በመሥራት የሚጠበቅባቸውን ድርሻ  እንዲወጡ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ መጋቤ ጥበባት ጌቱን ጨምሮ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ተወካዮች፣የዋና ማእከል ተወካዮች፣የአዳማ ማእከል ሥራ አስፈጻሚና አባላት፣የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋዮች እና ምእመናን ተገኝተዋል።
4
አዲስ አበባ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤ እያከናወነ እንደሚገኝ ገለጸ


ሐምሌ ፳፮/፳፻፲፯ ዓ.ም


የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤው  ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም እያከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የማእከሉ ሰብሳቢ ዲያቆን ኀይለማርያም መድኅን መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን  በመልእክታቸውም የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል በዘርፈ ብዙ የሥራ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ አመላክተዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ  ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምህረት  ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን
በበኩላቸው "አብረን እንሥራ" የሚል አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የዋናዉ ማእከል ተወካይ አጠቃላይ የማኅበረ ቅዱሳን ሪፖርት ምን እንደሚመስል ያቀረቡ ሲሆን የአዲስ አበባ ማእከል ዋና ሰብሳቢ ዲያቆን ኅይለማርያም መድኅን የ፳፻፲፯ ዓ.ም የአዲስ አበባ ማእከል ያከናወናቸዉን ተግባራት አብራርተዋል ።


ለማእከሉ ጠቅላላ ጉባኤ በተዘጋጀው  ዕቅድ ክንውን ላይ የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር ፣ የአሠራር ሥርዓትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን የዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃትን ዓላማው ባደረገው በዚሁ ዕቅድ ክንውን ላይ፣ የዋና ዋና ተግባራት ከመፈጸም አኳያ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲያቆን ኀይለ ማርያም መድኅን አስረድተዋል።

የቤተክርስቲያን የአስተዳደርና የአሠራር ለውጥ (ዘመኑን የዋጀ ዕቅድ እና ተጠያቂነት ያለበት የሰው ሀብት፣ የፋይናንስ፣ የዕቅድ ግምገማ የቴክኖሎጂና መረጃ አስተዳደር እና የሥጋት አስተዳደር ሥርዓት ) ፍኖተ ካርታን ለማስፈጸም ስልትና ፕሮግራም ማዘጋጀት፤ ከጠቅላይ ቤተክህነት እስከ አጥቢያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተግባራዊ እንዲሆን የማስቻል ሥራዎች መከናወናቸውንም አብራርተዋል።
1
የቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ ለውጥ ፍኖተ ካርታ ሊያስፈጽሙ የሚችሉ የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም ተጽእኖ ፈጣሪነት ተግባራዊ የሚያደርጉ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናን የሚጠይቅ መሆኑን ሰብሳቢው ጠቁመዋል።

በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት ዓላማው ባደረገው በዚህ እንቅስቃሴ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮን አደረጃጀት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ድረስ በማጠናከር፤ ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂ፣ በሚዲያና በሌሎች ልዩ ልዩ መንገዶች በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የሚሆንበትን አሠራር ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ሰፋፊ ሥራዎች መሠራታቸውን ሰብሳቢው አስገንዝበዋል።

የቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ አደረጃጀትና አወቃቀር አካባቢያዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን ባገናዘበ መልኩ ማጥናት እና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የአቅም ግንባታ መርሐ ግብር መሪዎችን ማፍሪያ ማዕቀፍ በማዘጋጀትና በመተግበር ረገድም ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

የአገልጋይ ተገልጋዮችን ምጥጥን መሠረት በማድረግ ሰብከተ ወንጌልን በተለያዩ ቋንቋዎች የሚያገለግሉና ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ቀዳሚ ሚና የሚወጡ 8200 መምህራን ማፍራት እና ማሠማራት ተችሏል ሲሉ ገልጸዋል።

በደረጃ አንድ እና በደረጃ ሁለት የሰባኪያነ ወንጌል ሥልጠናን በመስጠት መምህራንን ማፍራት ተችሏል ብለዋል።


ጉባኤው እስከ ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል።
2
2025/09/21 06:20:54
Back to Top
HTML Embed Code: