Telegram Web Link
የ2017 ዓ.ም የማእከላት ጠቅላላ ጉባኤ በተሳካ ሀኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ

ነሐሴ ፱/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን ወደ 50 የሚሆኑ ማእከላት የ2017 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤያቸውን ማካሄዳቸው ተገልጿል።

በጠቅላላ ጉባኤያቸው ሊቃነ ዻዻሳት፣የየሀገረ ስብከታቸው የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የየማእከላቱ አባላት፣ባለድርሻ አካላት፣የየወረዳ ማእከላት ተወካዮችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶችና የግቢ ጉባኤያት ተወካዮች ተገኝተዋል።

በማኅበረ ቅዱሳን ማእከላት አገልግሎት ማስተባበሪያ የሀገር ውስጥ ማእከላት ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ኃላፊ ዲ/ን መንግሥት ሰጠው ጠቅላላ ጉባኤ ማኅበረ ቅዱሳን በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት መንፈሳዊ አገልግሎቱን በአግባቡ ለማከናወን እንዲያስችለው በተለያየ ጊዜ በተለያየ ቦታ ከዋናው ማእከል ጀምሮ እስከ ግቢ ጉባኤያት ድረስ የሚደረግ ጉባኤ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በዚህም ወደ 50 የሚጠጉ የሀገር ውስጥና የውጪ ማእከላት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም በመርሐ ግብራቱ የየማእከላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት፣ በዋናው ማእከል የተሠሩ ዋና ዋና ተግባራትና አጠቃላይ መልእክት፣ የየማእከላቱ የ2017 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ፣ የፋይናንስ ፣ የኦዲት አገልግሎት ሪፖርቶች፣ የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ቀርበውና ሐሳብ ተሰጥቶባቸው የማጽደቅና የተለያዩ የመወያያ አጀንዳዎች መነሳታቸውን ገልጸዋል።
7
የዘንድሮው ዓመት የማእከላት ጠቅላላ ጉባኤ ከባለፈው ዓመት ሲነጻጸር ከአሁናዊ ከሀገሪቱና ከቤተ ክርስቲያን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በተለይ ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ አገልግሎት ለመፈጸም አስቸጋሪ ቢሆንም ማእከላቱ ይህ ሁኔታ ሳይገድባቸው ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ዋጋ እየከፈሉ አፈጻጸማቸውን ከዕቅዳቸው አንጻር ያሻሻሉበትና ማኅበሩ ባስቀመጠው መመሪያ መሠረት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በተቀመጠላቸው ጊዜ ማከናወናቸው መልካም ነው ያሉት ዲ/ን መንግሥቱ ከአፈጻጸም ረገድም ለውጥ ታይቶባቸዋል ሲሉ አመላክተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://www.tg-me.com/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
:- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905
6👍2
በውጭ ማእከላት የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንን ቤተሰባዊ አቅም ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ

ነሐሴ ፲፪/፳፻፲፯ ዓ.ም

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሥልታዊ ዕቅዱ ትኩረት አድርጎ ከሚሠራባቸው አገልግሎቶች መካከል መንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት በመስጠት ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን የሚያጠናክሩ ካህናትና ባለሙያዎችን አሠልጥኖ ማሰማራት አንዱ ነው።

በሀገር ውስጥ በልዩ ልዩ አህጉረ ስብከቶች ሥልጠና ሲሰጥ የቆየው አገልግሎት ክፍሉ በውጭ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንንም የዕድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሠራ የሚገኝ ሲሆን በዚህም መሠረት በቅርብ ርቀት ከሚገኘው የኬኒያ ማእከል ጋር በመተባበር ለተመረጡ ካህናትና ባለሙያዎች በበይነ መረብ /ቨርችዋል/ የታገዘ የአሠልጣኞች ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

በሥልጠናው የምክክር አገልግሎትን በማጠናከር አርአያ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ለመፍጠር የሚረዱ ክብረ ክህነትና አበ ነፍስ፣ መንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት አሰጣጥ፣ ኦርቶዶክሳዊ ጋብቻና የልጆች አስተዳደግ፣ ሱስና አሁናዊ ተግዳሮቶች እንዲሁም ምጣኔ ሀብትና ማኅበራዊ ዕድገት ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡

በመርሐ ግብሩ ከሃያ ስድስት በላይ ሠልጣኞች የተሳተፉ ሲሆን ሥልጠናው መንፈሳዊውን አስተምህሮ ከሳይንሳዊው ጋር በማስተሳሰር ዘመኑን በዋጀ መልኩ መሰጠቱ ውጤታማ እንደሚያደርጋቸው ተናግረዋል፡፡

ሠልጣኞች አክለውም በሥልጠናው ጥሩ ግንዛቤና ልምድ እንዳገኙበት ገልጸው በተለይ ኬኒያና አካባቢው በስደት ኑሯቸውን የሚመሩ ኢትዮጵያውያን መቆያ እንደመሆኑ በሁለንተናዊ አቅማቸው ጎልብተው ለሀገራቸውና ለቤተ ክርስቲያን ሚናቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል፡፡
7
ማኅበረ ቅዱሳን ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን ለማጠናከር የአመካካሪዎች ሥልጠና እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ ዓመታትም ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ለዚህም የቤተ ክርስቲያን አካላት በዕውቀት፣ በገንዘብና ቁሳቁስ በመደገፍ በቅንጅት አብረው እንዲሠሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ይህን የሥልጠና መርሐ ግብር በገንዘብ መደገፍ ለምትፈልጉም፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400 መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
7
Forwarded from ማኅቶት Wave
❤️የተወለዱበትን ወር በመምረጥ የሚደርሶትን መንፈሳዊ ቻናል በመቀላቀል ዕውቀቶችን ያግኙ
                   መልካም ዕድል!!!
𝚆𝚊𝚟𝚎 👉 @Beni_tes

https://www.tg-me.com/addlist/S3XRDXNUCygxNGE8
https://www.tg-me.com/addlist/S3XRDXNUCygxNGE8
https://www.tg-me.com/addlist/S3XRDXNUCygxNGE8
10
የፍኖተ ትጉሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ለ8ኛ ዙር ያስተማራቸውን 32 ተተኪ ሰባኪያነ ወንጌል ማስመረቁን አስታወቀ

ነሐሴ ፲፭/፳፻፲፯ ዓ.ም

የላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የፍኖተ ትጉሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ከደብሩ ሰበካ ጉባኤና ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር በመተባበር ከደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት የተውጣጡ 32 ተተኪ ሰባኪያነ ወንጌል በማስተማር ነሐሴ13 ቀን 2017 ዓ.ም ማስመረቁን አስታውቋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ መልአከ ፀሐይ ተስፋ ማርያም ነጋሽ የላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ፣ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ አባል፣ ርእሰ ደብር ተስፋ ደጀኔ የደብሩ የስብከተ ወንጌል ኃላፊ፣ አቶ የኋላሸት ሽፈራው የደብሩ የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀ መንበር፣ የማኅበረ ቅዱሳን ተወካዮች፣ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ተወካዮች፣ ካህናትና ምእመናን ተገኝተዋል።

የፍኖተ ትጉሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ዳንኤል ደሳለኝ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የማኅበረ ቅዱሳንን ጥናት መነሻ በማድረግ አገልግሎቱን ጀምረው እያከናወኑ መሆኑን በመግለጽ አጠቃላይ የተሠሩ ሥራዎችን ሪፖርት አድርገዋል።

ዲያቆን ዳንኤል ደሳለኝ አክለውም በዘንድሮው ዓመትም ለ8ኛ ዙር ያሠለጠኗቸውን ተመራቂ ደቀ መዛሙርት እንኳን ደስ አላችሁ በማለት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን አያይዘውም ሠልጣኞች ወደ አካባቢያቸው ሲመለሱ በተማሩት ትምህርት ወንጌል ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች በቋንቋቸው እንዲያስተምሩና የእግዚአብሔርን ልጅነት እንዲያገኙ ለማድረግ በኃላፊነት እንዲያገለግሉ አደራ ብለዋል።

አያይዘውም ዋና ጸሐፊው በሥልጠናው ለተሳተፉ ባለድርሻ ፣ አጋር አካላትና ምእመናንን አመስግነዋል።
9
ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ አባል ማኅበሩ ያከናወናቸውን ተግባራት ሪፖርት በማቅረብ በሁለቱ ዞኖች የተወጣጡና በሰባት ማለትም በአራፍ፣ በዳሰነች፣ በበንኛ፣ በማሌኛ፣ በዲሜኛ፣ በኮንሶኛና በሐመርኛ ቋንቋዎች ለሐዋርያዊ ተልእኮ መሠማራት የሚችሉ 32 ተመራቂ ሰባኪያነ ወንጌልን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ሊቀ ትጉሃን አክለውም ሠልጣኞች በቋንቋቸው አካባቢያቸውንና ምእመናንን እንዲያገለግሉ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህ ሥልጠና መሳካት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላደረጉም ምስጋናን ችረዋል።

የላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ተስፋ ማርያም ነጋሽ በበኩላቸው በጠረፋማውና በገጠራማው አካባቢ የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት እንዲስፋፋ ለማድረግና የቤተ ክርስቲያኗን ተልእኮ ከግብ ለማድረስ እየተሠራ ያለው ተግባር የሚበረታታ ነው ያሉ ሲሆን ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመጨረሻም የደብሩ አስተዳዳሪ ደቀ መዛሙርቱ የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር እንዲቀይሩ ያሳሰቡ ሲሆን ይህን አገልግሎት ለመደገፍ የእምነቱ ተከታይ የሆነ በሙሉ ማኅበራት፣ ገዳማትና አድባራት እንዲሁም ምእመናን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ መወጣት እንዲችሉ አሳስበዋል።
15🙏1
2025/09/20 22:37:14
Back to Top
HTML Embed Code: