{የቀይ ኮከብ ጥሪ የተቀነጨበ \ ከበዓሉ ግርማ}

የሰው ልጅ በጣም የሚወደው ንብረቱ ሕይወቱ ነው። ሕይወቱም የተሰጠው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ለባከኑ አመታት ምንም አይነት ጭንቀት ሳይሰማው የተሰጠውን ሂወት መኖር አለበት። ስላለፉ ጥቃቅን ነገሮች እያሰበ በሀፍረት የመሸማቀቁን ትርጉም በጭራሽ ሊያውቀው አይገባም...በሂወቴ ሙሉ ክፍል የተሰጠኝ ሙሉ ሀይል የተቸረኝ በአለም ላይ ምርጥ ለሆነ አላማ ነው።

@maninet1
@betsiroyal
ማንነት
ፍቅር በዚያ ወራት (ሚካኤል.አ) #ክፍል 3 ከንፈሮቹን ልጎርሳቸው ተጠጋሁት.. ወደ ከናፍሩ ስጠጋ የውብ ትንፋሹ መዓዛ አወደኝ ። የተቀባው ሽቶ በአፉ ከሚያላምጠው ሜንት ማስቲካ ጋር ሲዳበል የገነት መግቢያው የሱ መዓዛ ነው ቢሉኝ ውሸት ነው አልልም። ወድያው "አይዞሽ ውዴ! " የሚል ድምፅ ሰማሁ ። ሺት ! የፈራኋት ጣውንቴ መጣች ። የነጃት ጥላቻዬ አስራ አንድ በመቶ ሲያድግ ተሰማኝ (ፖለቲካ አይደለም…
ፍቅር በዚያ ወራት !
ክፍል 4
(ሚካኤል አ)
"አንተ ማነህ ?"
የደነገጥኩት ክፉኛ ነው ። ራሴን ለዶክተር ዛክ አሳልፌ ሰጥቻለሁ ብዬ ስለማስብ ብቻ ገላዬን ከሱ ነጥቄ ያረከስኩ ነው የመሰለኝ።
ንፁህ ረከሰች !
ያ ህሊናዬን የሚኮረኩመኝ ፀፀት አገረሸ።
"ማር ነሽ አለኝ " አጠገቤ ተንጋሎ የነበረው ጎረምሳ።
"እንዴ ዶክተር እዘዘ?"
በሳቅ ተንከተከተ ። የዶክተር ዛኪ ጓደኛ ...
"ከተማሪዬ ጋር በዚህ መልኩ ይነጋል ብዬ አላምንም "
እንዲህ ሲለኝ ደግሞ አለቀስኩ ... አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጬ አለቀስኩ ። እንባዬ ይቅርታ ነው ... ዛኪዬ ማረኝ ብሎ የሚግፈለፈል እንባ በልቤ ውስጥ ፈልቶ በጉንጬ ላይ ፈሷል። የፊት ጉንጬን ይለበልበኛል ።
እዘዝ ግንኙነታችን በኮንዶም መሆኑን አስረድቶ ሊያባብለኝ ሞከረ። ያሳሰበኝ የገላዬ ጤና አልነበረም...የልቤ...የህሊናዬን ህመም የአካል ጤንነቴ አያክመውም።
ብዙ እብዶች.. . የአካል ጤነኞች ነን። ህሊናችን ግን ስለሚያነክስ ታማሚዎች ነን።
ሰው ከውስጡ ካልታረቀ በስተቀር በሽተኛ ነው። ንዋይም...ቤተሰብም ... ሀሴትም እኔን ከህመሜ አይታደጉኝም። መንፃት የምፈልገው ለስሜ ክብር ለመስጠት ነው።
ለስሜ ክብር ስሰጥ ህሊናዬን እወለውለዋለሁ ። ህሊናዬ ሲነፃ ለዛኪ እገባዋለሁ የሚል የራስ መተማመን ይኖረኛል። ለዛኪ እስካልተገባሁት ድረስ ደግሞ ስንኩል ነኝ።
የዛሬው አጋጣሚ ደግሞ ሌላ የሽንፈቴ ገፅ ነው። ለእዘዝ ከብሬ ባገኘው እንኳ የቅርብ ጓደኛውን ባየሁት ቁጥር መርከሴ ይታሰበኛል ።
"ንፁህ ተረጋጊ..." እጆቹን አይኖቼ ላይ ሊያሳርፍ ሲሞክር ገፈተርኩት ።
እዘዝ ባለጌ ነህ ትለዋለች ነፍስያዬ ። የጓደኛህን ገላ አታለህ የቀማህ እርኩስ ነህ ይለዋል ውስጤ ።
እያየሁ ጠላሁት ... መርከስ መልክ ቢኖረው እዘዝ ነው ። መርከስ መልክ ቢኖረው ንፁህ ናት ።
ልብሴን ለባብሼ ክፍሉን ለቅቄ ወጣሁ ። ከሲኦል የማመልጥ ይመስለኛል። የሆቴሉ የመጀመርያ ኮሪደር ስደርስ እያመለጥኩ ነው።
ብንንንንንንንን.. ..
።።።።።።።።።።
ከዛች ቀን በኃላ ትምህርት ቤት አልሄድም። እንደ እርጎ የሰከነው ዛኪን ማየት ሌላ ፀፀት ነው ለኔ ።
የነጃትን አይኖች ማየት ለኔ ተጨማሪ አርጩሜ ነው ።
የፍቅር አምላክ የዛኪን ልቦና ወደ ነጃት አዙሮ ለሽልማት ሲያጫት አየሁ።
አፈርኩ ... ለአምስት ቀናት አፍሬ ከክፍል ቀረሁ ።
ከሰመመኔ ለቀናት አልነቃሁም።
የፀፀት በትር ገላዬን አድቅቆት ቆዘምኩ ...
ከዚህ መዛል ንቂ ሲለኝ ግን ሀሙስ የምትባል ቀን ሌላ ተዓምር ይዛ መጣች።
ሀሙስ የቀን ቅዱስ ። ማለዳውን በቅድስና አልያም የፀፀት ቤንዚኗን ለማርከፍከፍ በላዬ ላይ ተሰየመች ።
ጉዱ የስልክ ጥሪዬ ነው ።
እንደ ኤሊ እየተንቀራፈፍኩ በዳበሳ ስልኬን አገኘኋት ። አንድ አይኔን ሳልገልጥ ደዋዩን አየሁት ።
መንቃት ብቻ አይደለም ...
ከአልጋዬ ተስፈንጥሬ ቆምኩኝ። ደዋዩ ነፍሴን ሙሉ የሚያደርጋት ሀኪሜ ነው ።
Teacher zaki.. .
ስልኬ ከእጄ በምን ፍጥነት ወድቆ ወለሉ ላይ እንዳረፈ አልገባኝም።
በምን ተዓምር ዛክ እኔ ጋር ደወለ ?
ላንሳው ይሆን?
(ይቀጥላል.. . )

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ


📚ሁሉን ነገር መፈለግ፣ ሁሉን መሻት፣ ያለገደብ ለመኖር ማሰብ የዚህ ዓለም ጣጣ፣ የድካም ምንጭ ነው።

📚የምትጠቀምበትን ያክል ብቻ እወቅ፤ የሚያጠግብህን ያክል ብቻ ብላ፤ የሚያረካህን ያክል ብቻ ጠጣ፤ ሁሉን ነገር ማጣት ሰቀቀን ቢሆንም ሁሉን ነገር ማግኘትም ዕዳ ይሆናል፡፡

📚ምንም አለማወቅ ባዶነት ቢሆንም ሁሉን ማወቅ ደግሞ ሸክምም ይሆናል።''

<ዝጎራ>


ማጋራት መተሳሰብ ነው!

📚 @maninet1
ሰላም ቤተሰቦች ለሰሞኑን

የአለማየሁ ዋሴ እሸቴን መፅሐፍ ልለቅላችሁ አስቤያለው ከየትኛው ይጀመር @betsiroyal ላይ ምርጫችሁን ንገሩኝ

📚1.እመጓ
📚2.ዝጎራ
📚3.መርበብት
📚4.ሰበዝ
📚5.ሜተራሊዮን በቅርቡ የታተመ ስለሆነ በpdf ለም!
@betsiroyal

ማጋራት መተሳሰብ ነው!

📚 @maninet1
ፍቅር በዚያ ወራት !

(ክፍል 5)
ሚካኤል.አ

ለምን እንደሆነ ባላውቅም የዛኪን ስልክ አለማንሳት አልቻልኩም። ድምፁ ናፍቆኛል.. .

"ሄሎ "

"ሄሎ ንፁህ.. ."

ዝም አልኩት ። ረጋ ያለ ድምፅ!  ... 

ንፁህ ብሎ ሲጠራኝ እንባዬ ፈሰሰ ። አፍቃሪው ልቤ በክህደት ሰንሰለት ተተብትቦ በፀፀት አርጩሜ እየተወገረ ነው።

"ሄሎ " .. የድምፄን መጥፋት ሲረዳ ደግሞ ተናገረ ።

"ሄሎ ቲቸር "

"በሰላም ነው የጠፋሽው? ህመሙ አልተሻለሽም እንዴ?"

የተሻለኝ ህመም የለም። ጭራሽ የማይድን ሌላ የውስጥ ቁስል አመርቅዣለሁ ።

እወደዋለሁ.. .

የንሰሀዬ መንገድ የሱ ስክነት ነው። እሱ ቢያቅፈኝ...እሱ ቢያስብልኝ... እሱ መዳፉን አውሶ ቢዳብሰኝ እንደስሜ እነፃ ነበር ።

"ምንድነው ለቅሶ ነው የምሰማው ?" 

"አዎ ዛክ "

"ምን ሆነሻል ?" 

"እወ.. .."

ሰውን እወድሀለሁ ብሎ መናገር ለካ ይከብዳል ።

ቃላቶቼን ከምኔው እንደዋጥኳቸው አላቅም። ለሱ ፍቅሬን መግለፅ ስሜቱን የሚገድልብኝ ይመለኛል። ዛክ ከወንዶች ሁሉ ይለያል ብዬ ባስብም ሁሉም ወንዶች ደግሞ የሚያመሳስላቸው የጋራ ባህሪ እንዳላቸው አምናለሁ ። 

ሴት ልጅ ለወንድ ልጅ የውስጧን ስሜት በግልፅ ከነገረችው ለሷ ያለው አመለካከት ይወርዳል። ወንድ ልጅ ከአፍቃሪው ይልቅ በኩራት ገመድ ወጥራ ለምታሰቃየው ሴት የልቡ በራፍ ይከፈታል ።

ኩራት !

ወንዶች መለመን ይፈልጋሉ.. . እንደ ወርቅ ተደብቃ የማህደሯ ክርታስን ለመቆፈር የምታታግል ሴት የወንዶችን ልብ ቁልፍ በእጇ ይዛ ትዞራለች ።

"ምን አልሽ?"

"አወ...ቅማ ዶክተር እባክህ ትንሽ ህመሜ ስለጠነከረ ተጨማሪ ቀናትን ባልመጣ እንዳትቀየመኝ። "

"ለምን እቀየምሻለሁ?  ትምህርትም...ስራም.. .ከጤና በላይ አይሆኑም። ስትኖሪ ነው ሁሉ ነገር የሚኖረው።

በይ ፈጣሪ ይማርሽ ።"

"አሜን !" አልኩት ።

ይሄን ያልኩት ግን ለበሽታዬ ድህነት አይደለም። ፈጣሪ እኔ ላይ የሰራሽውን ሀጥያት ይቅር ብሎ ይማርሽ እንዳለኝ ነው የተረዳሁት የኔ ካህን ።

ስልኩ ሲቋረጥ ከንፈሬን ወደ ስክሪኑ ሰድጄ ሳምኩት ።

እኔ የሱ መቅደላዊት ማርያም ... 

በደሌ በፍቅሩ የሚነፃ ከሆነ ብዬ በእንባዬ ራስኩኝ።

....

በዛኑ ቀን ዶክተር እዘዝ ደወለ።

በሙት ስሜቴ ስልኩን አነሳሁት ። እድለ ቢሶች ከምንወደው ነገር ይልቅ የማንወደው ነገር ይከተለናል ። ዶክተር እዘዝ ን አልወደውም። በተለይ ከዛ ክስተት በኃላ የርኩሰቴ ቤንዚን ሆኖ ይሰማኛል።

"ጣፋጯ " አለኝ።

መራሩ ልበለው ይሆን?

"ይቅርታ ዶክተር ...እንደዚህ አትበለኝ "

" ምነው አንዴ የቀመሽውን ገላ መድገም አትወጅም መሰለኝ። ይሄ እኮ የሴቶች ሳይሆን የእኛ ባህሪ ነበር ለወትሮው ...

ቂ....ቂ...ቂ ..."

ሳቅ ይሄን ያህል ይቀፋል?

"ሁሉም ነገር ባጋጣሚ ነው የሆነው "

ቲቸር እዘዝ ቀፋፊ ሳቁን ቀጠለው ።

"ቂ....ቂ ...ቂ 

ለማንኛውም ተረጋጊ ...ጥሩ ጊዜ ነበረን። ጥሩም ሆነን ሴሚስተሩን እንጨርሳለን"

ይሄን ሲል እየዛተ ነው። ለኔ ጥሩ ካልሆንሽ ጥሩ ጊዜ አይኖረንም ሊለኝ እንደፈለገ ግልፅ ነው።

"እባክህ..."

አላስጨረሰኝም ። ስልኩ ከወዲያኛው አቅጣጫ የመዘጋት ድምፅ አሰማኝ። 

ካሁን በኃላ ትምህርት ቤቴ ገሀነሜ ነው። 

ዶክተር እዘዝ የሰይጣኑ ቁንጮ ሉሲፈሬ ነው።

ዛክን በድዬ ከሱ ጋር ያሳለፍኩትን የአልጋ ላይ ጨዋታ እንደማልደግመው አውቃለሁ።

ገላዬን ስነሳው ደግሞ ነጥብ እንደሚነሳኝ እሙን ነው ። 

የኔና የሱ ግንኙነትን ደግሞ ዛክዬ ከሰማ ሌላ የህይወት ፍላት ላስተናግድ ነው ።

ሁለት ፍላት በአንድ እስትንፋሴ የምሸከምበት አቅም ያለኝ አይመስለኝም።

አልጋዬ ማህፀን ገብቼ ተሸፋፍኜ ተኛሁ ።

የውሸት እንቅልፍ ነበር ...

ሰኞ ትምህርት ቤት ስሄድ ለሚገጥመኝ ጦርነት ልቦናዬን ማዘጋጀት ጀመርኩ ።

አሸናፊው ማን እንደሚሆን እናያለን! 

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal
አንዳንድ ትዝታ አለ
-ዝምታችን -ከዝምታ ገዝፎ በአርምሞ በተዘጋንበት ጊዜ :በዕዝነ ልቡናችን በኩል <<ኡኡ>> ብሎ የሚጮህ ፡፡ በለሆሳስ ÷በዝግታ ካሳለፍነዉ የእድሜ ዘመን፡ ቅፅበቶቻችንን ከሽርፍራፊ የልጅነት ምስላችን በልጦ ፡በልቦቻችን ጥጋጥግ ካንጠለጠልነዉ ፡ ተናፋቂ ትዝታወች መሀል ፡ ምናለ በደገምነዉ እያልን የምንመኘዉ፡፡
ከትላንት ትዝታወቻችን ጋር ፡ ባንቀላፋን ቁጥር ሳንሰለች ደጋግመን የምንኖረዉ፡፡ አንዳንድ ትዝታ አለ ፡ እንደወይን እያደር ጣዕሙ የሚጨምር ፡ በእምባ በተምሸርንበት ጊዜ እንኳ ÷ በሐዘን ወህኒ ተወርዉረን ፡ መረሳት ክፋ እድል ፊት ለፊታችን ሲጋረጥ፡ የመኖር ጣዕም ሲጎመዝዝ ÷በእቅፋ ሚያስጠልለን፡፡ አንዳንድ ትዝታ አለ በዘመን መጎስቆል ባረመምንበት ጊዜ እንደ አዲስ የሚወልደን ፡ የማያረጅ የእድሜያችን ሞቃት ምዕራፍ ፡፡ አነዳንድ ትዝታ አለ --- አየ ጉድ - ትዝ አለችኝ መሰል፡፡
አድፎ ቆርፍዶ እስኪረግፍ ወዜ
ነበር እስኪመስለኝ እስኪንደኝ ግዜ፣
ከኗሪ ባሻገር ከሰው ጥግ ቆሜ፣
በመጠበቅ ብቻ አስቆጠርኩኝ እድሜ።

@maninet1

#አዲብ
የዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ለፈተና ወደ ተመደቡበት ካምፖስ ጉዞ ሲያደርጉ መያዝ የተፈቀደላቸው፣ መያዝ የተከለከሉ እና የጊዜ ሰሌዳ እንደሚከተለው ሀመሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

መያዝ የተፈቀደው፦

• አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ፣ የማታ ልብስ፣ ደረቅ ምግብ፣ ልብስ፣ ቦርሳ፣ የመፈተኛ ካርድ፣ እርሳስ፣ ላጲስ፣ የማስታወሻ ደብተር፣ ባዶ ወረቀት፣ መፅሐፍ

መያዝ የተከለከሉ፦

• ማንኛውም ድምፅ የሚቀዳ፣ ቪዲዮ የሚቀዳ ወይም ፎቶግራፍ የሚያነሳ መሳሪያ፣ ካሜራ
• ማንኛውም ከቴሌ መስመርም ይሁን ከቴሌ ውጭ መልዕክት በዲጂታል ቴክኖሎጂ መቀበያ ወይም ማስተላለፊያ ውጤቶች (ታብሌት፣ ኮሚፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስልክ፣ አይፓድ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ፍላሽ)

የጊዜ ሠሌዳ፦

• ማህበራዊ ሳይንስ
➤ 26 እስከ 28/01/2015 ዩኒቨርሲቲ መግቢያ
➤ 29/01/2015 ኦሬንቴሽን
➤ 30/01/2015 እስከ 02/02/2015 ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ

• የተፈጥሮ ሳይንስ
➤ 05 እስከ 06/02/2015 ዩኒቨርሲቲ መግቢያ
➤ 07/02/2015 ኦሬንቴሽን
➤ 08/02/2015 እስከ 11/02/2015 ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ

ምንጭ
@tikvahuniversity
@maninet1
🔰 የትኛውን መጽሐፍ በPDF ይፈልጋሉ 🔰



▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

1. የጉለሌው ሰካራም
2. ዴርቶጋዳ
3. አለቃ ገብረሐና እና አስቂኝ ቀልዶቻቸው
4. ልጅነት
5. አልኬሚስቱ
6. የፍቅር ኬሚስትሪ
7. ማህሌት
8. ኦማሂሬ
9. ኦሮማይ
10. ዮቶር (ኮብላይ ካህን)
11. ራማቶሓራ
12. ዣንቶዣራ
13. ዮራቶራድ
14. ዮቶድ
15. አደፍርስ
16. ኢቫንጋዲ
17. ሌላ ሰው
18. እርካብና መንበር
19. ብርቅርቅታ
20. ፒያሳ - ማሕሙድ ጋ ጠብቂኝ
21. ዙቤይዳ
22. በቀለኛው ሰላይ
23. ከአድማስ ባሻገር
24. ቆንጆዎቹ
25. የእስር ቤቱ አበሳ

1. Atomic Habits
2. Time Management
3. How to win friends & Influence people
4. The Alchemist
5. Philosophy of mind
6. 100 great business ideas
7. Five ways to know yourself
8. Emotional Intelligence
9. Zero to one
10. Think and grow rich
11. Born a Crime
12. Be your own brand
13. Memory Manipulation
14. How to make anyone fall in love with you
15. The 5 second rule
16. Smart thinking skills
17. Start where you are
18. Rich dad poor dad
19. 100 ways to motivate yourself
20. From failure to success
21. How to write a business plan
22. Elon musk
23. Spoken English
24. 7 habits of highly effective teens
25. Boundaries
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █        🇯 🇴 🇮 🇳         █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
“ያለማሰብ ውሳኔ”

“እውነትን በራስህ አይኖች ማየትን ተማር፡፡ አንድ ሰው የነገረህን ነገር ብቻ እውነት አድርገህ በፍጹም አትቀበል”

በአሁን ሰዓት በአንድ አንተ በማታውቀው ቦታ ሁለት ሰዎች ተገናኝተው እጅግ በጣም ስሜታዊ በሆነ መልኩ ስለአንተ እየተነጋገሩ ነው እንበል፡፡ እነዚህ ሰዎች በሚነጋገሩበት ነገር ላይ ያለህን አመለካከት ወይም ስሜት ተናገር ብትባል ምን ትላለህ?

ምናልባት መልስህ፣ “ምንም አመለካከት ወይም ስሜት የለኝም” የሚል ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ምክንያቱም፣ ስለሁኔታው ምንም የምታውቀው ነገር ስለሌለህ ነው፡፡

ሰዎቹ ተገናኝተው ስለአንተ አወሩ እንጂ አንተ ጋር ምንም የደረሰ ነገር የለም፡፡ በተጨማሪም፣ ስለአንተ የሚለዋወጡት ጠንካራ ስሜትን ያዘለ ንግግር መልካም ይሁን ክፉ የምታውቀው ነገር የለህም፡፡ ስለሆነም፣ በሁኔታው ላይ ምንም አይነት አመለካከትም ሆነ ስሜት ሊኖርህ አይችልም፡፡

ከዚህ እውነታ ሁለት ነገሮችን መመልከት እንችላለን፡፡

አንደኛው፣ የምትሰማቸውንና የምታያቸውን አሉታዊ ነገሮች በቀነስክ ቁጥር ጠንካራ ስሜቶችና አመለካከቶችን ትቀንሳለህ፡፡ ስለሆነም፣ ለሕይወትህ ሕልውናና እድገት አስፈላጊ ከሆኑን ነገሮች ውጪ መስማትና ማየት የማይገቡህን ነገሮች ማጣራትና አላስፈላጊውን ማስወገድ ታላቅ ጥበብ ነው፡፡

በሁለተኛ ደረጃ ልታስብ የሚገባህ ጉዳይ፣ አንዳንድ ጊዜ ስለአንተ የሚባለውን ሁሉ ላለመስማት የማትችልበት ጊዜ እንዳለ ማስታወስ አለብህ፡፡ ስለዚህም፣ ልክ ከላይ እንደጠቀስነው ስለነገሮቹ ፈጽሞ በማትሰማበት ጊዜ የሚኖርህን አይነት ኃይልና አቅም እንዲኖርህ ከፈለግህ፣ በምትሰማውና በምታየው ነገር አንጻር የግድ ጠንካራ ስሜትና አመለካከት ልትይዝ እንማይገባህ ማሰብ ትችላለህ፡፡


ያም ሆነ ይህ የምታንሸራሽራቸው ስሜቶችና ለመግለጽ የምትፈልጋቸው አመለካከቶች በተበራከቱ ቁጥር ያንን ለማድረግ ለዋናው ዓላማህ ሊውል ከሚገባው ጉልበትና ጊዜ ላይ መቀናነስ እንደሚገባህ አትዘንጋ፡፡ በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ በአይኖችህ ካላየህና በማስረጃ ካላረጋጋጥክ በስተቀር መረጃን በጆሮህ ሰምተህ ብቻ ከማመን ተጠበቅ፡፡ በተጨማሪም፣ በአይኖችህ አይተህ ሙሉ ለሙሉ አረጋግጠህ ያላመንክበትን ነገር በአንደበትህ በመናገር ከማስተጋባትም ራስህን ጠብቅ፡፡

በተጨማሪም፣ በውስጥ በአይኖችህ አይተህ ሙሉ ለሙሉ ያላመንክበትን ነገር በአንደበትህ በመናገር ከማስተጋባትም ራስህን ጠብቅ፡፡

“የጥበብ መንገድ” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተቀነጨበ፡፡

https://www.tg-me.com/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/
አንድ ሚኒስትር፣ ሚኒስትር ዴኤታ እና ዳይሬክተር ቁጭ ብለው ስለወሲብ የጦፈ ክርክር እያደረጉ ነው።

ሚኒስትሩ ወሲብ 60% ልፋት፣ 40% ደግሞ መዝናናት ነው የሚል አቋም ይዟል። ሚኒስትር ዴኤታው ደግሞ የለም ወሲብ 75% ልፋት፣ 25% ደግሞ መዝናናት ነው ብሎ ተከራከረ። ዳይሬክተሩ በበኩሉ ወሲብ 90% ልፋት፣ 10% ደግሞ መዝናናት ነው ብሎ እንደሚያምን ገልፆ ተከራከረ።

ክርክራቸው በጦፈበት ደቂቃ አንድ የበታች ፈፃሚ ሰራተኛ ቢሮውን አንኳኩቶ ብቅ አለ። ይሄኔ ዳይሬክተሩ "እንደውም እሱ ይፍረደን!" አለና ክርክራቸውን ነገሩት። በደንብ ከሰማቸው በኋላ "ይቅርታ አድርጉልኝና ወሲብ ምንም ልፋት የሌለበት 100% መዝናናት ነው!" አላቸው።

አለቆቹ በመገረም "እንዴት እንደዚያ አልክ??" አሉት። ጀለስም ፀጉሩን እያሻሸ እንዲህ ሲል መለሰላቸው . . .

"በጣም ቀላል ነው! ወሲብ ምንም ዓይነት ልፋት ቢኖረው ኖሮ እንደተለመደው እኔ እንድፈፅምላችሁ ታዙኝ ነበረ!" 😁

By Gemechu Merara fana
ኒላ ዘ መንፈስ
(አሌክስ አብርሃም)

ፊደል አበደች! ያች የአገር ምልክት የነበረች ቆንጆ አበደች! ያች ድፍን የአገሩ ወንድ የሚመኛት ቆንጆ፣ እርሷ ካልሰራችበት ፊልም አናይም የተባለላት ውብ ወጣት ኢትዮጵያዊት ተዋናይ አበደች። መጀመሪያ ነገሩ እንደተራ ሐሜት ነበር የታየው፣ ቆይቶ ግን ብቻዋን ስታወራና ስትስቅ አንዳንዴም ልክ እጎኗ ሰው ያለ እስኪመስል እጇን እያወራጨች ስታወራ የሚያሳዩ በስልክ የተቀረፁ ቪዲዮዎች ሶሻል ሚዲያው ላይ በተደጋጋሚ ሲለቀቁ ህዝቡ ማበዷን አረጋገጠ አዘነም! በተለይ በአንዱ ቪዲዮ የልብስ መሸጫ ቡቲክ ውስጥ ገብታ አንድ ቀሚስ ይዛ የሆነች ሴት ጋር እያወራች ትታያለች «አንች ደግሞ ሁሉ ነገር አይጥምሽም ! እሽ አሁን ይሄ ምኑ ነው ያስጠላሽ ? ፈዘዘ? በቃ የግድ ቦግ ማለት አለበት?» እያለች! ባለሱቋ ግራ ተጋብታ ታያታለች፥ ምክንያቱም ማንም ሰው ከጎኗ አልነበረም።

አንዳንዶች ገንዘብ አሰባስበን ህክምና እናስገባት ሲሉ ሌሎች ፀበል ይሻላል የሚል አስተያየታቸውን ሰጡ። የሆነ ሆኖ ስመ ጥሯ ፣ቆንጆዋና ታዋቂዋ ተዋናይ ፊደል አድማሱ ማንም ምክንያቱን ባላወቀው ምክንያት አበደች።ይሄ ነገር የጀመራት «ሂውማን ሄር» የተባለውንና በዋና ገፀ ባህሪነት የተወነችበትን ፊልም ካስመረቀች ሁለት ቀን በኋላ መሆኑን ቤተሰቦቿ ሰይፉ ፋንታሁን ለተባለ የቴሌቪዥን ሾው አቅራቢ ተናግረዋል።

በስራዋ የቀኑ ሰዎች አስደግመውባት ነው የሚል ነገርም በሰፊው ይናፈሳል። እንደውም የአፍሪካ ፊልም ፌስቲቫል ላይ ለመሳተፍ በሚል ሰበብ በዚያ ሰሞን ናይጀሪያ ሄዳ የተመለሰችው ተዋናይት ሲፋን ግዛቸው ከዚህ ጉዳይ ጋር ተያይዞ ስሟ ተነስቷል። ስለምትቀናባት ፊደል ላይ የናይጀሪያ መተት አሰርታባታለች የሚሉ ውስጥ አዋቂዎች ተሰምተዋል። በእርግጥ ጥርጣሬውን ከፍ ያደረገው ሲፋን አብረዋት ወደናይጀሪያ የተጓዙ የፊልም ባለሙያዎች ከተመለሱ በኋላ ናይጀሪያ ለሶስት ቀናት ቆይታ መመለሷ ነበር። እርሷ ግን ታስተባብላለች« አንድ የናይጀሪኣ ልብስ አምራች መቀመጫሽ ስለሚያምር ልብስ አስተዋውቂልን ብሎኝ የስቱዲዮ ፎቶ ፕሮግራም ስለነበረኝ ነበር የቆየሁት » ስትል። ብዙዎች ታዲያ "ኡኡቴ ናይጀሪያ መቀመጫ ጠፍቶ? " እያሉ አሽሟጠጡ!

የሆነ ሆኖ ፊደል አበደች። በትክክል ምንድነው የሆነው? ከፊልም ምርቃቱ አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ ውድ የእራት ልብስ ከምትሰራላት ዲዛየነር ጋር በአንድ የፋሽን ስቱዲዮ ተገናኝተው በእለቱ ስለምትለብሰው ልብስ እያወሩ ነበር። የመረጠችው ልብስ ቆንጆና ውበቷን የሚያጎላ ቢሆንም ልብሱ ጋር አብሮ የሚሄድ ረዥም ፀጉር አንደሚያስፈልግ ዲዛየነሯ ነገረቻት። ፊደል በተፈጥሮ ፀጉሯ አጠር ያለና ከርዳዳ ነው። ብዙ ካወጡ ካወረዱ በኋላ ዲዛየነሯ ታዋቂ «ሂውማን ሄር» አቅራቢ ወደሆነ ደንበኛዋ ደውላ የምትፈልገውን ፀጉር አይነት ነገረችው። ደንበኛዋ እየሳቀ «አሁን ከህንድ የገባ አስገራሚ ፀጉር አለ፣ ልክ እንዳልሽው ነው» ብሎ አበሰራት! ወዲያው እንድታየው በሰው ልኮላት ፊደል ሞከረችው። በእርግጥም ፀጉሩ ሲያዩት ልብ የሚያስደነግጥ፣ እንደድቅድቅ ጨለማ የጠቆረ ግን ደግሞ ብርሃን ሲያርፍበት የሚያንፀባርቅ ውብ ሂውማን ሄር ነበር። ብዛቱና ርዝመቱ ከምንም በላይ ሲንቀሳቀስ መዘናፈሉ ፊደልንም ዲዛየነሯንም አስደሰታቸው። ዋጋው ከተለመደው ወደድ ቢልም ፊደል ብዙ አላስጨነቃትም።

እንደተለመደው የፊልሙ ምርቃን ዜና ሚዲያውን ሞላው። ብዙዎች ተውበው በአዳራሹ ተውረገረጉ ከምንም በላይ ግን የፊደል ውበት በእለቱ የለበሰችው ልብስና ፀጉሯ ለወንዶች ፈተና ለሴቶችም ቅናት ሁኖ ዋለ። በተለይ ፀጉሯ በብዙዎች ተደነቀ! ፊደል በቀጣዩ ቀን ከታዋቂው ባለሃብት ገስጥ ጥጋቡ ጋር የእራት ቀጠሮ ነበራቸው። ከዛም በፊት አንድ ሁለት ጊዜ አብረው ወጥተዋል። አሁን የምትይዘው መኪናም ግማሸ ወጩ የተሸፈነው በእርሱ ሲሆን ግማሹን ግን ለፍታ ደክማ ባገኘችው የራሷ ገንዘብ የተገዛ ነው። ብዙዎች እንደሚያስቡት ገስጥን የቀረበችው ለብሩ ብላ አልነበረም። ፊደል እንደዛ አይነት ሴት አልነበረችም። ገስጥ እንደአንዳንድ ባለሃብቶች «ገንዘብ ካላ በሰማይ መንገድ አለ» የሚል ትዕቢተኛ ሰው አልነበረም። አርፎ መሬት ለመሬት የሚሄድ ጨዋ ሰው ነው። በእርግጥ ስራውም መሬት ነክ ነው። ትራክተር እና የእርሻ ማሽነሪዎች አስመጭ። ሰሊጥና ቡና ላኪ። ምንም እንኳን ባለትዳርና የአራት ልጆች አባት ቢሆንም ፍቅራቸውን ግን ማቆም አልቻሉም ነበር። ግንኙነታቸው ሚስጥር ነው ማንም አያውቅም።

እና የዛን ቀን ምሽት ፊደልና ገስጥ በውድ ሆቴል ራት በልተው ወደክፍላቸው ገቡ። ገስጥ በቲቪ እያያት ክፉኛ ሲመኛት አድሮ ስለነበርና የቀማመሱት ዋይን ምኞቱን ስላባባሰው ገና ከመግባታቸው ልብሷን አወላልቆ ራቁቷን አስቀራት! እንዲህ ርቃኗን ቁማ ሲያያት ሊያመልካት ምንም አይቀረውም! በውበቷ በወጣትነቷ ፈዘዘ። ከምንም በላይ ወገቧ ላይ የሚዘናፈለው ጥቁር ፀጉር እንደእሳት የሚነድ ከመሰለው ቀይ ሰውነቷ ጋር ሲያየው ቀልቡን አሳተው። በፍጥነት ልብሱን አወላልቆ ፊቷ ቆመ! ትንፋሻቸው ናረ . . . ክፍሉ በአንዳች ሙቀትና ስሜት ሊፈነዳ የደረሰ መሰለ! እየተስገበገበ ጠጋ ብሎ አቀፋትና እጁን ፀጉሯ ላይ ሲያሳርፍ ...

«አንተ እከካም እጅህን አንሳ » የሚል የተቆጣ የሴት ድምፅ አምባረቀ። ሁለቱም በድንጋጤ ወደበሩ ዞሩ፥ ማንም የለም! ሁለቱ ብቻ ናቸው። ተያዩ ድምፁ የፊደል አልነበረም። ግራ እንደተጋቡ ያው ድምፅ ቀጠለ « ምን ይመስላል . . . ከቦርጩ ቂ..ምነቱ ወንድ ልጅ እንዲህ ሲዝበጠበጥ ደስ አይልም » ገስጥ ግራ ገብቶት ክፍሉን ቃኘ . . . ፍራሹን አንስቶ አልጋው ስር ተመለከተ ወዲያ ወዲህ ተራወጠ ።
«ወደዛ አታፈንድድብኝ፥ ልብስህን ልበስ ምን ይንዘላዘልብኛል እዚህ ! አስቀያሚ . . . ደግሞ ምንድነው ቂ. . ህ እንዲህ የጠቆረው? እየተንፏቀክ ነው እንዴ የምትሄደው? ከመጥቆሩ መዥጎርጎሩ! ሐብታም አይደለህ ቅባት ክሬም ምናምን አትጠቀምም? የቅባት እህል እየሸጥክ አንተ አፈር መስለሀል! ይሄ ሁሉ ሃብት ያላወዛው ፎከታም ሰውነት ሂሂሂሂሂሂ ፤ ደግሞ ችኮላህ ! ትራክተር ነገር ነህ ...ተንደርድረህ ልታርሳት ነው ? አንች ደግሞ ምን ሁነሻል? እኩያሽን አትፈልጊም ? ወይስ ደደብ ነገር ነሽ?

«ማነሽ አንች?» አንች አለች ፊደል በፍርሃት ዙሪያዋን እያየች
« ምናባሽ ያገባሻል ? አሁን ይሄን ፎከታም ወደዛች ጋንጩር ሚስቱ ላኪና ወደቤታችን እንሂድ ደክሞኛል»
«ወደቤታችን? ወደማን ቤት ? » መልስ የለም። ፊደል በድንጋጤ ልብሷን ለባበሰች ! ገስጥም እንደዚያው! ሁለቱም ደንግጠው እጃቸው ይንቀጠቀጥ ነበር። ከመታጠቢያ ቤት እስከቦርሳዋ ያልፈተሹት ነገር አልነበረም። ማንም አልነበረም ማንም! ሁለቱ ብቻ።

ገስጥ ፊደልን ወደቤቷ ሊያደርሳት በውድ መኪናው በዝምታ ተቀመጥው እየተጓዙ ነበር። ያ አስፈሪ የሴት ድምፅ «ምን ይዘጋችኋል ሙዚቃ የለም? ምኖቹ አዚማሞች ናቸው በቡድሃ !» አለ። ገስጥ በድንጋጤ ፍሬን ሲይዝ ከኃላቸው በፍጥነት የሚከተል መኪና ጋር ለትንሽ ከመላተም ተረፉ።
«አንተ ደንባራ በስርዓት አትነዳም እንዴ ? ይሄ እርሻ ቦታህ የምትነዳው ትራክተር አይደለም ይዘኸን እንዳትሞት»

«አንች የውሻ ልጅ ማነሽ ?» አለ በቁጣ
«አንተ ደደብ እኔን ነው የውሻ ልጅ የምትለው? እንዲች ነኝና ኒላ! » ብላ ፎከረች
«ኒላ?» አሉ ፊደልና ገስጥ በአንድ አፍ ?
ፊደል እቤቷ ደርሳ ከገስጥ መኪና ስትወርድ ሁለቱም ከፍርሃታቸው ብዛት ደህና እደር ደህና እደሪ እንኳን አልተባባሉም!

እቤቷ እንደገባች በሯን በፍጥነት ዘጋችና በፍርሃት እየተንቀጠቀጠች ዙሪያዋን ማየት ጀመረች! ድንገት ሳታስበው እንባዋ ተዘረገፈ!
«ምን ያነፋርቅሻል? ደግሞ እንዳለ ላብ ላብ ሸተሻል ተነሸና ሻዎር ውሰጅ?» አላት ያ የሴት ድምፅ !
«እንዴ ቆይ ማነሽ ?» አለች በድንጋጤ ግድጋዳውን በጀርባዋ ተደግፋ እየተንቀጠቀጠች!
«አትፈሪ ! አናላ እባላለሁ ! ነፍሴን ይማረውና ጓደኞቸ ኒላ ነበር የሚሉኝ . . . ኒላ ልትይኝ ትችያለሽ አንችም! »
«እሽ ኒላ ምንድነሽ? የት ነሽ? ምንድነው የምትፈልጊው ?. . .»
«ኦ እኔ ሰው ነበርኩ እንዳንች . . . በእርግጥ አሁን መንፈስ ነኝ . . . ከሁለት ዓመት በፊት ህንድ ውስጥ ነው የሞትኩት . . .ሁለቱን ዓመት የት እንደነበርኩ እኔም አላውቅም! ይሄ አናትሽ ላይ ያደረግሽው ፀጉር የእኔ ነው! ልክ ፀጉሩን ሰውነትሽ ጋር ሲነካካ አንች ውስጥ ሁኘ ነቃሁ!
«እ?» አለች ፊደል በበለጠ ፍርሃት ፀጉሯን እየነካካች!
«አዎ ! ፍቅረኛየ ጋር በባቡር ስንጓዝ ነበር ባቡሩ ሃዲዱን ስቶ ያለቅነው! ለመጨረሻ ጊዜ ከአደጋው በፊት ፍቅረኛየ ይሄን ፀጉሬን በእጁ እያበጠረ በጣም እንደሚወደው እየነገረኝ ነበር። እንድንከባከበውም አደራ ብሎኛል! ፀጉሬን አመልከው ነበር። በጓደኞቸ በዘመድ አዝማዱ ሁሉ የተደነቀልኝ ፀጉር! ምን ዋጋ አለው... አንች እንዲህ በማይረባ ቅባትና በዚህ አቧራ አገርሽ አጎሳቆልሽው እንጅ ውብ ነበር። የሆነ ሁኖ ከዚህ በኋላ መንፈሴ በፀጉሬ በኩል አንች ውስጥ ገብቷል። ሰውነትሽ የጋራችን ስለሆነ ለብቻሽ አትወስኝም ።

«ነገውኑ ፀጉርሽን እፈተዋለሁ» አለች እየፈራች!
ለውጥ የለውም! መንፈሴ ውስጥሽ ነው ያለው ! ፀጉሬን እንደመጓጓዣ ውሰጅው ! መንፈሴ ተጭኖበት የመጣ መጓጓዣ! አገልግሎቱን ጨርሷል። እና ከዚህ በኋላ የማንም ፎከታም ጋር አትሄጅም ፍቅረኛችንን አብረን እንመርጣለን ፣ ምግባችንን ፣ ልብሳችንን ፣ አብረን እንበላለን አብረን እንዘንጣለን ፣ እና ደስ የሚለን ፍቅረኛ ካገኘን አብረን እን. . . ሂሂሂሂ!

ይቀጥላል!

@maninet1
@betsiroyal
ኒላ ዘ መንፈስ 2
(አሌክስ አብርሃም)

በክፍል አንድ ትረካችን አናላ ወይም በቁልምጫ ስሟ ኒላ የምትባል ህንዳዊት ሴት ከፍቅረኛዋ ጋር ይጓዙበት የነበረ የመንገደኞች ባቡር ሐዲዱን በመሳቱ ትሞታለች። ይች ሴት በዘመድና ወዳጆቿ ዘንድ የምትታወቀው በውብ ጥቁር ፀጉሯ ሲሆን እርሷም ለፀጉሯ ያላት ፍቅር እና እንክብካቤ የማምለክ ያህል ነበር። ምን ያደርጋል ያ አደጋ ነፍሷን ነጠቃት። ሰው ሟች ነው! ቆንጆም ሴት ትሁን ጀግና ወንድ ማንም ከዚህ ህግ አያልፍም። ይሁንና ኒላ ለራሷም ባልገባት ሁኔታ ከሁለት ዓመት በኋላ እዚች ምድር ላይ ያውም ኢትዮጵያ ፣ ያውም ፊደል የተባለች ታዋቂ ኢትዯጵያዊ የፊልም ተዋናይት ውስጥ መንፈስ ሁና ተከሰተች። ኒላ ራሷ እንደምትለው ለሁለት አመት የት እንደነበረች ምን እንደነበረች አታውቅም! የምታውቀው ነገር ተዋናይቷ የገዛችው «ሂውማን ሄር» የኒላ እንደነበርና ተዋናይቷ ፀጉር ጋር ሲነካካ ለሁለት ዓመት ሙት የነበረ ፀጉሯ ህይዎት እንደዘራ፣ ወዲያው በፀጉሩ በኩል ሙሉ መንፈስ ሁና ሰውነቷ ውስጥ እንደገባች ነው። ቀጣዩን እነሆ . . .
* **

የዛን ቀን ምሽት ፊደል መተኛት አልቻለችም! በፍርሃት አልጋዋ ላይ ተቀምጣ ሳታቋርጥ ውስጧ ተቀምጣ የምታወራውን ኒላ ግራ በመጋባት ታዳምጣለች።
«ተነሽ ገላችንን እንታጠብ፤ በላብ ጠረን ገደልሽኝኮ » አለች ኒላ! ፊደል አሁንም እያላባት ቢሆንም ምን ትሁን ምን ትፈልግ የማታውቃት እንግዳ ፊት ልብሷን ማውለቅ ፈራች! በቀስታ «የእኔ እህት ለምን ወደምትሄጅበት አትሄጅልኝም ? ፀጉርሽንም ውሰጅው አልፈልግም በጣም እያስጨነቅሽኝ ነው!» አለቻት!

« አንች የማይገባሽ ደደብ ሴት ነሽ ልበል? ነፍስሽን ከስጋሽ «ተለይተሽ ሂጅ» ማለት ትችያለሽ? ራሴን እንዳጠፋ እየጠየቅሽኝ ነው? በቃ ይሄ የአንች ሰውነት የእኔም ነው! ፈልጌሽ አልመጣሁም! ደህና ያረፈ ነፍሴን አምጥተሽ የቀሰቀሽው አንች ነሽ! እንዴት እንደገባሁም እንዴት እንደምሄድም አላውቅም ! ያለን አማራጭ ተከባብረን አብረን መኖር አለበለዚያ ተያይዘን ወደመቃብር መውረድ ነው! ይብላኝ እንጅ ላንች፣ መሞት እንደሆነ ለእኔ ብርቄ አይደለም. . . ይልቅ ተነሽ እንታጠብ እንዴት ነው ላብ በላብ የሆነው በቡድሃ! ለሞላ ሰውነት እዚች ውስጥ ታስቀምጠኝ! » አለች በቁጣ!

ፊደል እየተንቀጠቀጠች ወደሻወር ሄደች! ልብሷን በፍርሃት . . . በቀስታ አወላለቀች! የሻወሩን ውሃ በቀስታ ከፍታ ሙቀቱን በእጇ «ቸክ » ካደረገች ኋላ በደንብ የሞቀ ውሃ እስኪወርድ ሰውነቷን በእጇ ከልላ ዳር ላይ ቆመች! ጠባቡ ሻዎር በእንፋሎት መታፈን ሲጀምር በቀስታ ወደሚወርደው ውሃ ራመድ አለች!
«እንዴ ፀጉርሽን ሳትሸፍኝው ልትገቢ ባልሆነ?» አለች ኒላ ! በጩኸት!
«እረስቸው ነበር » ብላ ሮዝ ቀለም ያለውን የፀጉር መሸፈኛ የፕላስቲክ ቆብ አጠለቀች ! እና የቀኝ ትከሻዋን አስቀድማ ወደውሃው ገባች! ውሃው የፀጉር መሸፈኛው ላይ ሲያርፍ ዝናብ የቆርቆሮ ጣራ ላይ የሚፈጥረው አይነት ድምፅ ይፈጥራል! ወይም እንደዛ ይመስላታል ፊደል።
«ኡኡኡኡ አንች የማትረቢ ሴት አብደሻል? ወደዛ ውጭ ! » ብላ ጮኸች ኒላ! ጩኸቷ ጎረቤት ሁሉ ይሰማ ነበር!
«እንዴ ምን ሁነሻል? ታጠቢ አላልሽኝም እንዴ?» ብላ ዘላ ወጣች!
«እና ታጠቢ ማለት ተቀቀይ ነው?እንደዚህ በተፍለከለከ ውሃ የምትቀቀይው ድንች ነሽ? ለነገሩ ከአንች ድንች ይሻላል ከንቱ! በዚህ አይነትማ ፀጉሬን ከጥቅም ውጭ ነው የምታደርጊው. . . ቆይ ቆይ ለመሆኑ ተምረሻል? ወይስ ይሄን መቀመጫሽን እያገማደልሸ ብር የሚያሳይሽ ማንም እከካም ቦርጫም ባለትዳር ጋር መተኛት ብቻ ነው እውቀትሽ?»

« ለምን ስትናገሪ ስርዓት አይኖርሽም ? እኔ ሴት አዳሪ አይደለሁም፣ የተከበርኩ የፊልም ባለሙያ ነኝ! ለከት ይኑርሽ ! መንፈስ ሁኝ ፀጉር የራስሽ ጉዳይ ነው! . . . » ብላ ቱግ አለች ፊደል! እንባ እየተናነቃት!

«ሂሂሂሂሂሂ ! የተከበርኩ? ማነው የሚያከብርሽ? ሂሂሂሂ ያች ጓዝ ሚስቱ ስትደብረው ነው አንች ጋር እየመጣ የሚዝናናው ትራክተር የሆነ ሰውየ ?! ወይስ ያ ካሜራ ፊት እንደበቀቀን የሚጮህ ዳይሬክተር ተብየ? ስሙንማ ይዞታል!የታባቱ ተምሮ ነው ዳይሬክተር የሆነው? የዩ ቲዮብ ምሩቅ ወይስ "ዳይሬክተር" የዳቦ ስም መሰለው እናቱ የምታወጣለት? አንችም "ዳይሬክተር አወጣኝ" እያልሽ ቀሚስሽን ትነሰንሻለሽ! ልብሽ እብጥ ብሏል!

"እንዴዴዴ"

"የምን እንዴ ነው! ያም ቦርጫም እከካም በገንዘቡ ነው የገዛሽ ፤እንደትራክተር! ትራክተር እንኳን ያርሳል፣ አንች በጀርባሽ ተነጥፈሽ የሰው ባል አምሮት መወጫ ከመሆን ውጭ ምን ጥቅም አለሽ? ፊልም ትላለች እንዴ ? ቦሊውድን ያላየ! ሁለተኛ እንደዚህ ትጮኺብኝና አሳብጀ ልብስሽን አስጥየ ነው መሳቂያ የማደርግሽ! ከንቱ! ሸር . . ጣ! አሁን ውሃውን አቀዝቅዥው ! ዘንቧጣ! ደግሞ ራቁትሽን ሲያዩሽ ምንድነው የምትመስይው? ልብስ ነው ሰው ያስመሰለሽ! ከአምስት ዓመት በኋላ ማንም ዙሮ የማያይሽ ቆዳ ፊት ነው የምትሆኝው! ያ ሰሊጣምና ትራክተራም ራሱ እንዳላየ ነው የሚያልፍሽ »

ፊደል ተሳቀቀች! ማንም በሰውነቷ እንዲህ ዝቅ አድርጓት አያውቅም! አይቷት የማይንሰፈሰፍ ወንድ የለም! ቢሆንም መመላለስ አልፈለገችም! ሲጀመር ምን ጋር ነው የምትመላለሰው? ይችን ጉድ ፈራቻት፤ ይችን አስቀያሚ ሴት ክፉኛ ፈራቻት! እናም በትህትና « እኔኮ ቀዝቃዛ ውሃ ስለማልወድ ነው» አለች! ፍርሃት በተቀላቀለበት ሳግ የሚተናነቀው ድምፅ ! ይችን ፍጥረት ትሁን ቅዠት ምኗም መጋጨቱ ...! እንደውም ወደፖሊስ ጣቢያ ሂዳ ኡኡ ልትል አማራት!እዛው አሳድሩኝ ልትል ፈለገች፤ ፈራች በጣም ፈራች!

«ወደድሽ አልወደድሽ ግድ አይሰጠኝም! ሰውነቱ የጋራችን መስሎኝ! በሙቅ ውሃ የተቀቀለ አስቀያሚ ሰውነት ውስጥ ተቀምጨ መኖር የሚያስደስተኝ ይመስልሻል? ወጣት ነኝ ሳልሞት በፊት ገና ሃያ አራት ዓመቴ ነበር ! ግን ደደብ አልነበርኩም! ስለሙቅ ውሃ በኃላ አስረዳሻለሁ! አሁን ሙቀቱን ቀንሽው በይ ! ምናይነቷ ውስጥ ነው ያስቀመጠኝ ? ቆንጆ ብቻ ! » ተነጫነጨች! ፊደል ቀዝቃዛ ውሃውን ጨመረችው እና «አሁንስ?» አለቻት የማትታይ የማትታወቅ ሴት በራሷ ፍላጎት ላይ ፈቃድ መጠየቋ ደግሞ አበሳጫት!
«በእጅሽ ሞክሪዋ እኔ መንፈስ ነኝ! እጅ የለኝ እግር ፤በአንች እጅ ነው የማውቀው !» ፊደል እጇን ዘርግታ የሚወርደውን ውሃ ሞከረችው
«አሁንም ትኩስ ነው በደንብ ቀንሽው » ቀነሰችው «አሁን ይሻላል! »

ፊደል በጣም ከመፍራቷ ብዛት ውሃ ውስጥ ሁና ሁሉ ያልባት ነበር። «ይልቅ የገላ ሳሙናሽ ሸታው ደስ ሲል» ፊደል አልመለሰችም! ኒላ ወሬዋን አላቆመችም! « ኡፍፍ ሻዎር ስወስድ. . . ፍቅረኛየ ሮሃንን ነው የማስታውሰው ! በጣም የሚያምር አስተማሪ ነበር . . .እንደዛ ሰሊጣም ሽማግሌሽ እንዳታስቢው! እዛ እከካም ዳይሬክተር ተብየ ጋርም እንዳታወዳድሪው ! ወንዳወንድ ነበር. . . ጅኒየስ! ብዙ ሐሳብ ነበረን!ብዙ! " ጮክ ብላ ማንጎራጎር ጀመረች

የህንድ ተራሮች ግዝፈት
ሞገስህን አይሸፍኑም
ሙቀት ያለህ ስሜት ያለህ
ተራራ ነህ ውብ ተራራ
በአለት ማንነትህ ውስጥ
ፍቅር የሚንተገተግ
እንደ እሳተ ገሞራ ...
ፊደል ድንገት «ግን አማርኛ እንዴት ቻልሽ ?» አለቻት! ከጠየቀቻት በኋላ በመጠየቋ ተሳቀቀች!እንደሰው እውቅና መስጠትና ማናገር አልፈለገችም ነበር።
«አማርኛ ምንድነው?»
«እንዴ ይሄ የምታወሪበት ቋንቋ ነዋ»
«እኔ የማወራው ሂንዲ ነው፤ አንችም የምታወሪው የሚሰማኝ ጥርት ባለ ሂኒዲ ቋንቋ ነው! ሲጀመር ደግሞ እኔ አላወራም! ለማውራት ከንፈር ምላስ ያስፈልጋል. . . መንፈስ ነኝ ከንፈርም ምላስም የለኝም ! እኔ የማስበውን የአንች ከንፈርና ምላስ ነው የሚያወራው ! አእምሮሽ አድርገሽ እይኝ! አእምሮ አያወራም ያስባል ወደከንፈር ትዕዛዝ ይልካል! በሌላ አባባል መስተዋት ፊት ቁመሽ ስናወራ ብትመለከች የእኔንም የአንችንም ወሬ የሚናገረው የአንችው አፍ ነው! »
«እ?» አለች ፊደል የበለጠ ጭንቀት ውስጥ ገብታ! ነገሩ ሁሉ ተገለባበጠባት! የሻወሩን የብረት ድጋፍ ይዛ እንደመቆም አለች።

«በይ አሁን እንውጣ . . . ተዘፍዝፈሽ ልታድሪ ነው እንዴ?»
«ግን ለምንድነው ስድብ የምትወጅው? »
« ስድብ ? ትንሽ ቁጡ ነኝ ! በተለይ ድድብናን አልታገስም. . . ለመሆኑ የስሜ ትርጉም ምን ማለት እንደሆነ ይገባሻል? አናላ ነው ስሜ . . .አናላ ማለት እሳት ማለት ነው! እሳት! እኔ ላይ እንደእንጨት አትድረቂ ትቃጠያለሽ !! ገለባ አትሁኝ ትቃጠያለሽ! ከገለባ ሰዎች ጋር አትጠጊ ውስጥሽ ያለሁት እሳት ነኝ እበላቸዋለሁ! በተለይ ፀጉሬን ማንም ካለእኔ ፈቃድ ከነካ እንደላስቲክ ነው የማቀልጠው! እኔ አናላ ነኝ ፤ አናላ ዘ መንፈስ! ከዚህ በኋላ ይሄ ሰው የሚያጨበጭብለት ከንቱ ሰውነትሽ እንደክብሪት ቀፎ ነው ! ውስጥሽ እሳት የሆንኩ እኔ አለሁ! አብረን አመድ መሆን አልያም የምለውን እያደረግሽ መኖር ነው ምርጫሽ!

ይቀጥላል!

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal
ኒላ ዘ መንፈስ 3
(አሌክስ አብርሃም)

የመጀመሪያዎቹ ሳምንታት አስፈሪ እና ግራ አጋቢ ነበሩ ለፊደል፤ ከባድ ሆነውባት አለፉ! እንቅልፍ ማጣት ግራ መጋባት ...በየቀኑ ፍርሃቷ ቀስ በቀስ እየለቀቃት ቢሄድም መልመድ ያልቻለችው አንድ ነገር መታዘዝን ነበር። ውስጧ ተደላድላ የተቀመጠችው የተረገመች ኒላ ደግሞ ማዘዝ ነፍሷ ነው። መታዘዝ ነፍስ ስጋና መንፈስን ለአዛዢ ማስገዛት ነው! ፊደል ከልጅነቷ በነፃነት ያደገች ልጅ ናት።ከፍ ስትል ከተማሪ እስከአስተማሪ፣ ከመንደር ጎረምሳ እስከሚጠጓት ወንዶች ለውበቷ ተንበርክከው ስትጠራቸው አቤት ስትልካቸው ወዴት ባይ አሽከሮቿ ነበሩ! አሞጋሿ ብዙ ነበር! ዞር ስትል የሚያሟት ፊት ለፊት ይሽቆጠቆጡላታል።

ሌሎችን በአይን እይታ ብቻ ቁጭ ብድግ የምታደርጋቸው ፊደል ዛሬ ምንነቷ ለማይታወቅ መንፈስ በእሷ አባባል«ገረድ» ሁናለች። ለምሳሌ ፊደል በተፈጥሮ ውበቷም ይሁን በሽቅርቅር ፋሽን ተከታይነቷ ሊነኳት እንኳን የምታስፈራ ንፁህና ቆንጆ ትሁን እንጅ ቤት ውስጥ ዝርክርክ ነበረች። የበላችበት ዕቃ ለቀናት ሊከመር ልብሷ እዚህና እዛ ተዝረክርኮ ለሳምንታት ሊቆይ ይችላል። ኒላ ደግሞ ፈፅሞ ከዚህ ተቃራኒ ናት። አይደለምና መዝረክረክ ፊደል በራሷ ቤት ከነጫማዋ ምንጣፍ ላይ ከወጣች ታብዳለች!
«አንች የማትረቢ ቆሻሻ . . .» ብላ ነው የምትጀምረው!

አንድ ቀን ጧት (ሌሊት ማለት ይቀላል ከጧቱ አስር ሰዓት ) ፊደል በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ እንዳለች በሚያስበረግግ ጩኸት «ተነሽ» አለቻት ኒላ !ጩኸቱ ፊደልን አስበርግጎ ቀኑን ሙሉ ለእራስ ምታት ዳረጋት ! ቢሆንም ፊቷን እንዳጨፈገገች ተነስታ አልጋዋ ጫፍ ላይ ተቀመጠች!
«ዛሬ ይሄን ቤት እናፀዳለን»
«እንዴ . . .»
«አፍሽን ዝጊ ! እንደዚህ የተግማማ ቤት ውስጥ ልኖር አልችም! ገና ለገና መንፈስ ነኝ ታይፎይድና ታይፈስ አይዘኝም ብየ ዝም ልል አልችልም! ድብርት ራሱ ከታይፎይድ እኩል ነው! ቆሻሻ አልወድም ነገርኩሽ! ቆይ ለመሆኑ የምትኖሪው ለእነዚህ ተጎልተው የአንችን የማይረባ ፎቶና አርቲ ቡርቲ ፊልም ለሚያዩ ድንዙዞች ነው ወይስ ለራስሽ? ውጭ አፈር አይንካኝ ትያለሽ ቤትሽ ግን በክቷል ለራስሽ ክብር የለሽም ? በዚህ ቤት ነው እንግዳ የምንጋብዘው? »
«የምን እንግዳ ነው ! እኔ ማንንም እቤቴ አልጋብዝም. .»
«እኔ እጋብዛለኋ»
«ምን. . .?»
«እ ን ግ ዳ እጋብዛለሁ!!
«የምን እንግዳ ነው በቤቴ የምትጋብዥው ? አልበዛም?»
« ቤ ታ ች ን በይ!»

«አልልም ቤቴ ነው! »

«ቤታችን ነው» ፊደል ደከማት ! መንፈስ ግን አይደክመውም ይሆን ስትል አሰበች! የዛን ቀን ለዓመታት ያልተፀዳ ቤቷን ለማፅዳት ስትፈጋ ዋለች!ከኪችን እስከሸንት ቤት ከበረንዳ እስከግቢው ወገቧ እስኪንቀጠቀጥ አፀዳች! ኒላ ዘና ብላ ታዛታለች! ትሰድባታለች ልክ የባሪያ አሳዳሪ ነበር የምትመስለው! » ራሷን እስክትስት ቢደክማትም ውጤቱ ለራሷ ገረማት።

በዚህ ሁኔታ አንዴ ሲጣሉ ሌላ ጊዜ ሲኮራረፉ ቀናት ነጎዱ! ይች ግራ የገባት መንፈስ እንደባሪያ ያዘዝኩሽን አድርጊ ስትላት ያለመደችው መታዘዝ ከእልህ ጋር እየተቀላቀለ ግራ የገባት ልጅ አደረጋት! ቢሆንም ይች ወፈፌ ከታዘዘቻት የማትቆጣ እንደውም ትሁትና የጓደኝነት መንፈስ ያላት ፍጥረት መሆኗን ተረድታለች። አንዳንዴ ለቀናት ድምፅዋን ስለምታጠፋ ትታት የሄደች ይመስላት ነበር። ይሁንና ስሟን ጠርታ አለሽ ወይ ማለት ትፈራለች!አብረው በቆዩበት ጊዜ አንዳንድ ባህሪዎቿን ማወቅ ችላለች። እና በፀባይ ልትይዛትና እስከወዲያኛው የምትሸኝባትን መንገድ ለመፈለግ ወሰነች!

አንድ ቀን እንዲሁ ሲነታረኩ ውለው እንደተኮራረፉ ፊደል ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሷን በስሟ ጠራቻት
«ኒላ »
«ምን ፈለግሽ?»
«ይቅርታ ስላስቀየምኩሽ . . . ግራ ገብቶኝ ነው » ኒላ ዝም አለች! «እንደምታይው አድናቂ እንጅ ጓደኛም ዘመድም የለኝም! ብቸኛ ነኝ! የሚመጡት ሁሉ ወይ እውቅናየን አልያም ሴትቴን ፈልገው የሚመጡ ናቸው ጥልቅ ብቸኝነት ውስጥ የምኖር ብቸኛ ሴት ነኝ! እባክሽ ተረጅኝ»

« የነገርሽኝ ነገር አያሳዝንም. . .እዛ ሂጅና አብራሽ የምታለቃቅስ ሴት ፈልጊ! ልፍስፍስ ሴት አልወድም!ኢትዯጵያዊያን ተያይዘን እንውጣ ከሚላችሁ ይልቅ ሙሾ የሚያወርድላችሁን አስለቃሽ ነው የምትወዱት! አንች ራስሽ ራስሽን የምታደንቂው መስተዋት ፊትኮ ነው! የራስሽ እንኳን ጓደኛ አይደለሽም! ማንም የሚገዛሽ ለገበያ ያቀረብሽውን ነው! መቀመጫሽን ያቀረብሽለት አለም አዕምሮሽን ሊመርጥ አይችልም! ምኔን አይተው ተጠጉኝ ከማለትሽ በፊት ምንሽን አሳየሻቸው? ታዋቂ ነሽ እንጅ አያውቁሽም! ራስን ሸፍኖ እወቁኝ እያሉ ማልቀስ አለ እንዴ? ኪንኪ ፀጉርሽን እንኳን በእኔ ፀጉር ነው የሸፈንሸው! አየሽ የቤት ኪራይ ባልከፍልም በፀጉሬ የመጣልሽን በረከት ተካፋይ ነኝ! ሸበላ ወንድም ከመጣ ተካፋይ ነኝ ሂሂሂሂሂሂሂ! በነፃ አይደለም አንች ውስጥ የምኖረው ሰው ለእናት አገሩ እጁን እግሩን አይንና ሌላ አካሉን እንደሚሰጥ ፀጉሬን ሰጥቸሻለሁ፤ ፀጉር አካል ነው! አፍንጫሽ ላይ ያለው ዲኤን ኤ ፀጉርሽም ውስጥ አለ! ስለዚህ ጡረታ የምወጣው አንች ውስጥ ነው» ፊደል በዝምታ ስትሰማት ቆየች!

ኒላ ቀጠለች «ለመሆኑ ሶሻል ሚዲያው ላይ ስንት ተከታይ አለሽ?»
«ወደአንድ ሚሊየን. . .»አለች ፊደል!
«ለዚህ ሁሉ ተከታይሽ ምን ሰጠሽው? ፎቶ ፎቶ አሁንም ፎቶ . . . ፎቶሽ ምንሽን ያሳያል ? ቂ . . .ሽን ፣ ጡትሽን ፣ እግርሽን ፣ ጥፍርሽን . . . ጥፍራም! ባለፈው ፊልምሽን ልታስመርቂ ስትዘጋጅ ፀጉር ቤት ስንት ሰዓት ቆየሽ . . . አምስት ሰዓት ፣ ማሳጅ ቤት ሶስት ሰዓት ልብስ ስትለኪ ስታወልቂ አራት ሰዓታት ! ቢያንስ በየሳምንቱ «ራስን መጠበቅ» በሚል ሰበብ እድሜሽን መስተዋት ፊት እንደሽንኩርት በመላጥ የምታጠፊውን ጊዜ አስቢ! በዚህ መሃበረሰብ ውስጥ የአንች ቂ . . . ጤና ጣቢያ ነው ትምህርት ቤት? ቁንጅና ጥሩ ነው ! ግን ትንሽ ክፍተት ትንሽ መስኮት ነገር ከቁንጅናሽ አልፈው ወደአንች ሊገቡ ለሚፈልጉ ተይላቸው!

ድፍን ቆንጆ ብቻ አትሁኝ!በርና መስኮት የሌለው ደረጃ የሌለው ውብ ህንፃ ጥቅሙ ከውጭ መታየትና ለዙሪያው አዳማቂ መሆን ብቻ ነው!ሰዎች እንዲያርፉብሽ ውስጥሽ ትንሽ ወንበሮች ይኑሩ! እንደዛ ስልሽ እንደመሰል ጓደኞችሽ ነጠላሽን አደግድገሽ ለበዓል ካሜራ ፊት ድሆችን አሰልፈሽ ብሉልኝ ጠጡልኝ የምትይውን የሚያቅለሸልሽ «በጎ ስራ» አይደም! እሱ በጎ ስራ ሳይሆን «በጎ አድናቆት» ነው ! ምግብ መፀወትሽ እውቅናና አድናቆት ተመፀወትሽ! የለማኝ ሰልፍ ውስጥ ነሽ! ተደነቅሽበት ተወደሽበት ግን ባዶ ነሽ! ለራስሽ ስምና ዝና የምትቃርሚበት በጎ ስራ የስም ሜካፕ ነው! ራስሽን ብቻ ነው የሚያሳምረው! አንድ ቀን ሲዘንብ ታጥቦ አስቀያሚነትሽ ያገጣል!

«እስኪ ስለራስሽ ንገሪኝ » አለች ፊደል ትንሽ ጨዋታውን ለማስቀየር! ትችት አትወድም!

«ወሬኛ አትሁኝ ! እድሜ ልክሽን ስለሌሎች ሰምተሻል ፤አሁን ቢመርም ስለራስሽ መስሚያሽ ነው!. . .ለምንድነው ግን ኢትዯጵያዊያን አብዝታችሁ ስለሌሎች መስማት የምትወዱት? ራሳችሁን ትፀየፋላችሁ ወይስ በራሳችሁ ታፍራላችሁ?» ፊደል ዝም አለች! «ከድህነታችሁ በላይ አስከፊው ባህሪያችሁ ከእራሳችሁ መራቃችሁ ነው! ዙሪያችሁ ገደል እና ሚስጥር ነው . . .
ትዳር ይሁን ስልጣን ሐይማኖት ይሁን ማህበር ከነሸክማችሁ ስለምትገቡ እጣ ፋንታችሁ የሌሎችን ሸክም ማቅለል ሳይሆን ራሳችሁም ሸክም መሆን ነው። ራሳችሁ እንኳን ወደራሳችሁ የምትቀርቡበት አንድ ቀጭን መንገድ አድናቆት ብቻ ነው! ሰው በዚህ ልክ እንዴት ከራሱ ጋር ይጣላል በቡድሃ?!

ይቀጥላል!

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal
ኒላ ዘ መንፈስ 4
(አሌክስ አብርሃም)

በክፍል ሶስት ትረካችን ኢትዮጵያዊቷ ፊደል እና በሂውማን ሄር ሰበብ በውስጧ የገባችው ኒላ የተባለች የሙት መንፈስ (የፀጉሩ ባለቤት ነኝ የምትል) ከብዙ ስድድብና አለመግባባት በኋላ ቀስ በቀስ እርስ በእርስ ማውራት እንደጀመሩ፤ ፊደል ነገሩ በቁጣና በሐይል የማይሆን ስለመሰላት በውስጧ ተቀምጣ እንደ አለቃ የምታዛትን ነጭናጫዋን ኒላን በፀባይ ለመያዝ እንደወሰነች አይተናል። ይባስ ብሎ ኒላ ገና በቀናት እድሜ ስለፊደልና መሰሎቿ ኢትዮጵያዊያን ባህሪ እየጠቀሰች ፊደልን መምከርና መውቀስ ጀምራለች! ቆሻሻ እንደማትወድ በመግለፅ የፊደልን ቤት አስፀድታታለች! ኒላ መንፈስ ናት፤ ከሁለት ዓመት በፊት ህንድ ውስጥ በ24 ዓመቷ በባቡር አደጋ የሞተች ሴት መንፈስ! ከሞቷ በፊት እጅግ የምትወደውና የምትሳሳለት ፀጉሯ «ሂውማን ሄር» ተብሎ ወደኢትዯጵያ ተላከ ! ፊደል የተባለች ታዋቂ ተዋናይት ገዝታ ተጠቀመችበት፤ በዛው ቅፅበት የኒላ መንፈስ በፀጉሩ በኩል የፊደልን ሰውነት ተጋርቶ መኖር ጀመረ! አሁን ፊደል ማለት አንዲት ሴት ግን በውስጧ ሁለተኛ መንፈስ የሚኖርባት ግራ የተጋባች ሴት ሆናለች! ቀጣዩን እነሆ!

* * ** *

«አንች ህንዳዊ ነሽ ፣ እንደነገርሽኝ ኢትዮጵያን ካወቅሻት ገና የተወሰኑ ቀናት ቢሆንሽ ነው! ግን ስለእኔም ይሁን ሌሎች ኢትዮጵያዊያን ልክ እዚህ ተወልዶ እንዳደገ ሰው ትናገሪያለሽ ! የምትይውን ነገር ሁሉ እንዴት አወቅሽው? » አለች ፊደል የኒላን ቁጣና ዘለፋ የተቀላቀለበት ምክር በዝምታ ስታዳምጥ ከቆየች በኋላ!

«ስለመንፈስ ምንም አታውቂም? ይሄ የሚበዛው ክፍሉ በማይረባ ዝባዝንኬ የተሞላ አዕምሮሽ ለእኔ እንደኮምፒውተር ወይም እንደስልክ ነው አሰራሩ! መንፈስ ሁኘ ውስጥሽ ስገባ ከህፃንነትሽ ጀምሮ እስከአሁን የተጠራቀመ ትዝታሽ ችሎታሽ ፣ባህሪሽ፣ ስሜትሽ ሁሉም ነገር አንች የምታውቂውና የምታስታውሸው ሁሉ እኔ «ሜሞሪ» ላይ ተጭኗል። ግን የምጠቀመው የምፈልገውን ሲሆን የምጠቀመውም በእኔ በራሴ መንገድ ብቻ ነው! የራሴ ህልውና አለኝ ፣የራሴ አስተሳሰብና ስሜት አለኝ፣ የራሴ ችሎታና አረዳድ አለኝ፣ የሌለኝ አካል ብቻ ነው!

አካሌ እዛ ህንድ ተቃጥሎ አመዱ ወንዝ ላይ ተበትኗል! ከእንግዲህ እነዛ ውብ የሰውነት ክፍሎቸ ዳግም አይመለሱም! ያ ውብ ፈገግታየ የለም ፣ ስለዚህ ፈገግታሽን እጋራለሁ፣ እነዛ ውብ እግሮቸ እና እጆቸ የሉም ስለዚህ የአንችን እግርና እጅ እጋራለሁ ፣ ከንፈሮቸ የሉም የአንችን ከንፈሮች እጋራለሁ. . . ለዛ ነው እንደአሳማ የሚያገሳና እንደውሻ የሚናከስ ትንፋሹ ጋን ጋን የሚሸት ወንድ እንዲስምሽ የማልፈልው! ሁለታችንም ያልተስማማንበት ወንድ አጠገብሽ አይደርስም! ምክንያቱም ሰውነትሽ ሰውነቴ ነው! ሂሂሂሂሂ ስንት ነገር አለ! የተረፈኝ ብቸኛ መታሰቢያ ይሄ አንች አናት ላይ የተቀመጠው ፀጉሬ ብቻ ነው! ይሄ ፀጉር ሁሉ ነገሬ ምድር ላይ የቀረኝ ብቸኛ መታሰቢያ ነው። ጓደኞቸ የምወዳቸው ቤተሰቦቸና ነፍሴን የምሰጥለት ፍቅረኛየ ሁሉም ተረት ናቸው አሁን!ለዘላለም አብረውኝ አይኖሩም! ህይዎት እንዴት አጭር ናት? " አለች ባዘነ ድምፅ!

«ፀጉርሽ እንዴት ተረፈ ግን?»

በቤተሰቦቸ እምነት ሴት ልጅ በህይዎት ዘመኗ ሁለት ጊዜ ፀጉሯን ለምናመልክበት ቤተ መቅደስ ትሰጣለች፣ ልክ እንደስዕለት ነው! አንድ ከማግባቷ በፊት፣ ትዳሯ እንዲባረክ (ይሄ በፍላጎት የሚደረግ ነው) ሁለተኛው በወጣትነቷ ከሞተች! እንደገና ስትፈጠር በመልካም ሰው ወይም እንስሳ እንድትፈጠር! እኔ ግን አንች ውስጥ ተፈጠርኩ ሂሂሂ!

ምናልባት ያኔ ፀጉሬን ስቆረጥ ቅር ስላለኝ አምላካችን አዝኖብኝ ይሆናል። ልክ እናተ አስራት መባ ስጦታ እንደምትሉት ነው! በበሃላችን ፀጉር የመጨረሻው የሴት ልጅ ክብር አንዲት ሴት ለምታመልከው ጣኦት ፀጉሯን መስጠቷ ክብሯን ኩራትና ፀጋዋን ሁሉ ለአምላኳ የመስጠት ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው! ወይም ከቸገራት ፀጉሯን ሸጣ ኑሮዋን ልትደጉም ትችላለች! ማንም ሴት ቸግሯት ፀጉሯን ስትሸጥ ደስ ብሏት አትሄድም ከእንባ ጋር ነው!

«ቤተመቅደሱ ፀጉሩ ምን ያደርግለታል?» አለች ፊደል

ቤተመቅደሱ ፀጉሩን ሰብስቦ ሂውማን ሄር ለሚያዘጋጁ ካምፓኒዎች ይሸጠዋል ! ካምፓኒዎቹ አዘጋጅተው ወደመላው ዓለም ይሸጡታል! የእኔም ፀጉር በዚሁ መንገድ ነው የሚመጣው! እኔ የመጀመሪያውን ፀጉሬን በሰጠሁበት ቀን ስድስት ሺ ሴቶች ሰጥተዋል። ወደሁለት ቶን ፀጉር ማለት ነው! ሁለት መቶ ኩንታል ማለት ነው! ይሄ አንዲት ትንሽ ከተማ ላይ ብቻ ነው፤ በመላው ህንድደግሞ ብዙ ሚሊየን ኩንታል ይሆናል! አሁን የገረመኝ ከዛ ሁሉ ጉድ ፀጉር ስንት አገር እያለ እንዲህ አይነት ከአመት አመት ፀሐይና አቧራ የማይለየው፣ ዜጎቹም ግራ የተጋቡበት አገር መንቃቴ ! ይባስ ብሎ እንደአንች አይነት በዚህ ዕድሜዋ እንደ 11 ዓመት ልጅ የምታስብ ሴት ውስጥ መኖሬ . . .» አለች። ፊደል ፈገግ አለችና

«ግንኮ በዕድሜ እበልጥሻለሁ ለምን አታከብሪኝም ኒላ?»

«እሱማ አገራችሁም በዕድሜ ስንቱን አገር ትቀድማለች ? ግን አሁንም ገና ትላንት እንደተመሰረተ አገር እንደተወዛገበች እንደተደናበረች ነው! ጉራ ብቻ! ገና ጡጦ ላይ እኮናችሁ! የሶስት ሽ ዓመት ሚሚ ! » ፊደል ዝም አለች! አገር ጅኒ ጃንካ ይደክማታል።

ፊደል ቀኑን ሙሉ ከተማ ወጥታ ልብስና አስቤዛ ስትገዛ ውላ ተመለሰች! ኒላ ልብስ ታመራርጣት ነበር። በአንዳንድ ምርጫቸው ስለማይጋቡ መጨቃጨቃቸው አልቀረም! ፊደልን ከሩቅ የሚያይዋት ሰዎች «ለየላት» ይላሉ! በተቻላት መጠን ዝም ለማለት ብትሞክርም የኒላ ጭቅጭቅ ዝም የሚኣስብል አልነበረም። እንደውም በአንድ ቀሚስ ከለር ምርጫ ስላልተግባቡ ወደቤት ሲመለሱ ተኮራርፈው ነበር።


ፊደል ሻዎር ወስዳ ራት በልታ ወደምኝታዋ ስትሄድ ኒላ ድንገት ወሬ ጀመረች «እኔ የምልሽ ፊደል . . .ለምን የፌስ ቡክ አካውንት አትከፍችም ?»
"አለኝ ምን ያደርግልኛል! "

ለአንች ማን አለሽ ?

እና ለማን ነው ?

ለእኔ !

እንዴ ጭራሽ ?

ምን ችግር አለው? በስሜ ክፈችልኝ ጓደኞቸን አገሬን ቤተሰቦቸን ማየት እፈልጋለሁ! የድሮ አካውንቴን ባስብ ባስብ ማስታወስ አልቻልኩም! ይመስለኛል የእኔን ሜሞሪ ፕሮሰስ የሚያደርገው የአንች አዕምሮ ማስታወስ ላይ ትንሽ ደከም ያለ ነው መሰል ሂሂሂ !

እና ፌስቡክ አካውንት ያለው መንፈስ ልትሆኝ? አለች ፊደል ነቆራዋን እንዳልሰማ አልፋ! በነገሩ ግርምት ተፈጥሮባት ነበር።

አዎ! ክፈችልኝ! በዛውም የፍቅረኛየን የእኔን የድሮ የጓደኞቸን ፎቶ አሳይሻለሁ!

ፊደል ጉጉትና ፍርሃት ተቀላቀለባት ! ግን ጉጉቷ አሸነፋት! ይች ከሁለት አመት በፊት ሞትኩ የምትል ሴት ምን ትመስል ይሆን? እውነት ናት አንደሰው ምድር ላይ ኑራ ነበር? ጓጓች ! «ከፈለግሽ ምን ቸገረኝ» አለችና ወደማንበቢያ ጠረጴዛዋ ሄደች! ውስጧ ግን የሆነ የጅል ስራ እንደምትሰራ እየነገራት ነበር። ላፕቶፗን ከፈተችና «እሽ በምን ስም ልክፈትልሽ? »

ኒላ N I L A ፊደል ስሙን አስገባች ! ድንገት ግን ኒላ በሳቅ ፍርስ አለች ! ሂሂሂሂሂ ሂሂሂሂሂሂ ካካካካካኣ

ምን ያስቅሻል?
«ታይፕ አደራረግሽ ነዋ! ፊደሎቹን እያፈላለግሽ ነው የምትጫኝያቸው… አያቴ ነበር እንደዚህ የሚፅፈው . . . ይገርማልኮ አሁን አንች የተማርሽ ዘመናዊ ታዋቂ የፊልም ተዋናይ ነሽ! ታይፕ ማድረግ እንኳን በወጉ አትችይም! ይመስለኛል ታይፕ አደራረግ ወደፊት ማስተማር ሳይኖርብኝ አይቀርም!

ፊደል በስጨት አለች « አሁን የጀመርነውን እንጨርስ ወይስ ልተኛ ?» አለቻት በቁጣ !

«አትቆጭ ፊደል! ኢትዯጵያዊያን አለመቻላችሁ ሳይሆን አትችሉም መባላችሁ ያበሳጫችኋል! ቀኑን ሙሉ ስልክና ኮምፒውተር ላይ አቀርቅረሽ እየዋልሽ ታይፕ ማድረግ እንኳን በስርዓት አለመቻልሽ ሊያስቆጭሽ ነበርኮ የሚገባው!

ትልቅ እውቀት መሆኑ ነው? አለች ፊደል

ነውና! እኔ በአስራሁለት ዓመቴ ነው ጥንቅቅ አድርጌ ኪቦርድ አጠቃቀም የቻልኩት

«የራስሽ ጉዳይ ወሬ አለብሽ. . . በነገራችን ላይ እየረዳሁሽ መሆኑን አትርሽ »

«ሂሂሂሂሂ ሂጅ ካሜራ ማኖችሽን ጥሪና "ኒላን እየረዳኋት" ብለሽ ነገ ለአድናቂዎችሽ እዩልኝ በይ! . . . እሽ እያሳደድሽ የአባቴን ስም ፃፊ!

እንዲህ እያሉ ለኒላ አዲስ አካውንት ከፈቱ! በመጨረሻም ኒላ በምትነግራት መሰረት የኒላን ቤተሰቦች አካውንት ከፈቱ ! ኒላ መጀመሪያ ያየችው የወንድሟን አካውንት ነበር . . . እንደነፍሷ የምትወደውን ወንድሟን ! ፕሮፋይሉ ላይ «ውቧ እህቴን ካጣኋት ሁለት ዓመት ሆነ እንወድሻለን» ከሚል የእንግሊዝኛ ፅሁፍ ስር እጅግ ውብ የሆነች ሴት ፎቶ ይታያል!

ፊደል ልቧ ስንጥቅ አለ! ካሰበቻት በላይ ቆንጆ ሴት ነበረች ! ፀጉሯ በቀኝ ትከሸዋ በኩል አልፎ ፊት ለፊት እየተዘናፈለ ይወርድና ተፋዋ አካባቢ ድረስ ቁልቁል ወርዷል! ፈገግታዋ ሲበዛ ውብ ፊቷን የበለጠ አስውቦታል! የለበሰችው ደማቅ ቀይ የህንድ ባህላዊ ልብስ ድምቀቷን አጉልቶት ፎቶ ሳይሆን ህያው ስጋና ደም ያላት ፍጥረት አስመስሏታል!
«አንች ነሽ ? » አለች ፊደል ! ኒላ ግን ማልቀስ ጀምራ ነበር!
ፊደል በዝምታ ቆየች! ኒላ ለቅሶዋን አቁማ ሌላ ስም ነገረቻት! ፊደል ስሙን አስገብታ ስትከፍተው አንድ መልከመልካም ወጣት ከአንዲት ሴት ጋር በባህላዊ የሰርግ ልብስ አምሮ የሚታይበት የሰርግ ፎቶ ስክሪኑን ሞላው! ከጎኑ ቆንጆ ሚስቱ በፈገግታ ቁማለች!

ኒላ « ይሄ ቀልድ ወይም ህልም መሆን አለበት » አለች በቀስታ ! ከዚያም ድንገት «ውሻ የውሻ ልጅ » ብላ ጮኸች በጩኸቱ የፊደል ሰውነት ተናወጠ!
«ምንድነው ኒላ ?» አለች በፍርሃት ! «ፍቅረኛየ፣ ባቡር ላይ አብረን ሞትን ያልኩሽ ፍቅረኛየ ! ገና ከሞትኩ በሁለት ዓመቴ ጓደኛየን አግብቶ ነዋ! ይሄው አይታይሽም ይች ውሻ ጓደኛየ ናት . . . ጓደኛየ ! የራሴ ጓደኛ »

ፊደል ግራ ገባት « ቆይ ባቡሩ ላይ ሞተ አላልሽኝመረ . . .? »

«እኔጃ እኔ ስለሞትኩ የሞተ ነው የመሰለኝ ! አላውቅም . . . ምናልባትም ውሻ ቶሎ አይሞትም » ኒላ ዝም አለች ! ረዥም ዝምታ !

ኒላ አለች ፊደል የምታደረገው ግራ ገብቷት መልስ የለም . . . ኒላ ትሰሚኛለሽ ? ዝምታ ! በቀስታ ላፕቶፑን ዘግታ ወደምኝተዋ ሄደች! ዝምታው ያስፈራ ነበር።
ይቀጥላል!

@maninet1
@maninet1
@betsiroyal
2024/06/01 18:42:40
Back to Top
HTML Embed Code: