Telegram Web Link
Gender-Based Violence is violence that is directed against a person because of that person's gender.

It is also violence that affects persons of a particular gender disproportionately.

When a person experiences gender-based violence, the physical and emotional impact is lasting. It seeps into every sphere of their life.

Sexual abuse and rape survivors exhibit a variety of trauma-induced symptoms including

- Sleep and eating disturbances,
- Depression,
- Feelings of humiliation, anger, and self-blame,
- Fear of sex, and
- An inability to concentrate.

Beyond the emotional trauma, GBV can result in physical injuries,

- Contraction of sexually transmitted infections, including HIV,
- Interruptions to sexual health and reproductive abilities,
- Unwanted pregnancies and
- Even death.

During this #16Daysofactivism and beyond, let us #UNiTE in transformative activism against any and all forms of #violence.

- Protect not harm.
- Strengthen not weaken!

#EngenderHealth
#Yetenaweg

@melkam_enaseb
MANTE FRIDAY HEALTH NEWS ADDICTION 23 03 2015.MP3
5.3 MB
ፕ/ር ሰለሞን ተፈራ (አዲክሽን ሳይካትሪስት፤ የሬናሰንት ሪሃብ ሴንተር መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ) በሱስ ዙሪያ የሰጡትን ማብራሪያ ያድምጡ።

@melkam_enaseb
ዛሬ ስብሃቲዝም የሀሳብ ውይይት!

ሐሳብ - ንባብ - ውይይት

ዛሬ ምሽት ህዳር 27 2015 ዓ.ም ይካሄዳል።

የእለቱ እንግዳ የስነልቦና ባለሞያው እንዳልክ አሰፍ ሲሆን  "ስነ ልቡናችን" በሚል ርዕስ እይታዎቹን ያጋራል።

12:00 ሲል ውይይቱ ይጀመራል።

ቦታው: ሃያ ሁለት ታውን ሰኩዌርሞል 8ኛ ፎቅ ሲሆን መግቢያው በጊዜ መገኘት ነው ብለዋል አዘጋጆቹ።

Via: Event Addis

@melkam_enaseb
ስብዕናን ለመገንባት ቃላቶች አስፈላጊ ናቸው!!

በየቀኑ ለራሳችን የምንናገረው፤ እራሳችንን የምናይበትን መነፅር በማስተካከል ብሎም ወደ ህይወታችን የምናመጣው በረከት ላይ ጉልህ አስተዋጽዎ አለው።

ከፍቅር አጋራችን፣ ከቤተሰብ ወይም ከልብ ጓደኞቻችን ጋር ስናወራ እንደምናደርገው ሁሉ ከራስ ጋር በሚኖር ስብሰባ የድጋፍ፣ የማፅናት፣ የመተሳሰብ እና የፍቅር ቃላትን መጠቀምን ከቶዉንም ልንዘነጋዉ አይገባንም።

የምንጠቀማቸው ቃላት የመስበርም ብሎም የመጠገንም ኃይል አላቸው።

ይህን ለመረዳት ታሪክን በወጉ መቃኘት ብቻ በቂ ነው፡፡

በዓለም ላይ በአዉዳሚነቱ አቻ ያልተገኘለትን ጦርነት ያስነሳው አዶልፍ ሂትለር ምንም አይነት ምህታታዊ ኃይል አልነበረውም፤ ይልቁንስ ሃሳቡን እንዲፈፅሙለት ለጦርነት ከሚያስፈልገዉ ትጥቅና ስንቅ ዝግጅት በላይ ቃላትን ተጠቅሞ ነበር በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሠራዊት ከጎኑ ማሰልፍ የቻላዉ።

እነ ማዘር ተሬዛ፣ ማህተመ ጋንዲ፣ ማንዴላ እና ማርቲን ሉተር ኪንግ የዚህችን ዓለም ጥቁር ጠባሳ ያከሙት በተአምራዊ ሀይል ሳይሆን መልካም እሳቤዎቻቸውን በቃላት በመግለጣቸው ምክንያት ነው።

ስለዚህ እኛም ለራሳችን ሆነ ለሌሎች የምንጠቀመውን ቃላት እንምረጥ ምክንያቱም ቃል ሊገነባን ወይም ሊያፈርሰን ይችላልና።

የመልካምነት ሳምንት ይሁንልን!

#ጥበብ_እና_ማስተዋል_ለሰው_ልጆች_ሁሉ!

ሣሙኤል ተክለየሱስ (ዓለም አቀፍ የሕይወት ክህሎት አሰልጣኝ እና የቢዝነስ አማካሪ)

@melkam_enaseb
የስልጠና ማስታወቅያ!

በሙያ ማማከር ዙሪያ የሰርተፍኬት ኮርስ!

ለሙሉ መረጃ እና ምዝገባ ከታች የተቀመጠውን ሊንክ ይጠቀሙ::

Training announcement!

Vocational Guidance and Counseling Certificate course!

For full information and registration, use the link below.

https://forms.gle/g8w3teRXXjaKAwF66

(Aha Psychological Services)

@melkam_enaseb
አርቲስት ሙኒት መስፍን ስለ አእምሮ ጤና
=========================
ብዙ አስገራሚ ስራዎች ስለሰራ ወጣት አነበብኩ። ደስ የሚል ቤተሰብ አለው። ብዙ ስኬቶች አስመስግቧል። የሚገርሙ ስራዎች ይሰራ ነበር። ብዙ እቅድ ነበረው። ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ እራሱን አጥፍቶ ተገኘ።

ወገኖቼ ሲጨንቃችሁና ግራ ሲገባችሁ ለጓደኞቻችሁ ደውሉ። ለቤተሰብ አሳውቁ። የሀይማኖት ሰዎችን አማክሩ። ወደ ሀኪም ሂዱ። አንዳንዴ ሰዎችን ማናገር ይከብዳል። "ተጨናንቄያለሁ እርዱኝ" ማለትም ይከብዳል። ግን ለብቻ ሲሆን በብቸኝነት ሲሆን የበለጠ ከባድ ነው።

አሜሪካ ራስ የማጥፋት ሀሳብ ያላቸውና የጨነቃቸው ሰዎች የሚደውሉበት 24 ሰአት የሚሰራ ነፃ የስልክ መስመር 988 አለ። ሁሉም ሀገር ላይ እንደዚህ አይነት አገልግሎት መኖር አለበት። ምንም አይነት የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ብትሆን፣ ምንም አይነት ቤተሰብ ቢኖርህ፣ ምንም አይነት ስራ ላይ ብትሰማራ አእምሮ ደህና ካልሆነ ሁሉም ነገር እያለህ ምንም እንደሌለህ ልታስብ ትችላለህ። አእምሮህ ህይወት ትርጉም አልባ እንደሆነ ሊነግርህ ይችላል።

አእምሮህ አንዳንዴ ከመጠን ያለፈ ውሸት ሊነግርህ ይችላል። በማንኛውም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ሆነህ ነገሮች መልካም እንደሚሆኑ ተስፋ እንደሚኖርህ እመኛለሁ። ሁልጊዜ ተስፋ አለ። የስነ ልቦና ህክምና ውስጥ ተስፋ አለ። የቤተሰብና የጓደኛ እገዛ ውስጥ ተስፋ አለ። በእምነት ውስጥ ተስፋ አለ። በጊዜ ውስጥ ተስፋ አለ።

እገዛ ሲያስፈልግህ ከመጠየቅ ወደኋላ አትበል። ሳይረፍድ ቶሎ እገዛ ማግኘት ደግሞ የተሻለ ነው። እኔ የስነ ልቦና ህክምና አድርጌ ብዙ ተጠቅሜያለሁ። እገዛ የሚያስፈልጋችሁ ሰዎች የስነ ልቦና ህክምና እንድታደርጉ አበረታታችኋለሁ። የሚስማማኝን የስነ ልቦና ህክምና ለማግኘት ጊዜ እንደወሰደብኝ አልደብቃችሁም። ሆኖም ያስፈልገኝ ስለነበረ 'ቴራፒ' ማድረግ አልተውኩም።

ሁላችንም ብዙ የአእምሮ ጤና ጉዳዮች አሉብን። ብዙ የስነ ልቦና ጠባሳ የሚተዉ ጥቃቶች በህፃንነታችን ወይም ካደግን በኋላ ደርሶብን ይሆናል። ለብቻችን ለመቋቋም መሞከር ከባድ ነው። እገዛና ድጋፍ ከመጠየቅ ወደኋላ አትበሉ። እገዛ መጠየቅ ጥንካሬ ይፈልጋል። ለራሳችሁና ለምትወዷቸው ሰዎች ስትሉ ጠንከር ብላችሁ እገዛ ጠይቁ።

ሰላምና ፍቅር ለሁላችሁም። ሁላችሁም ደህና እንድትሆኑ እመኛለሁ። ለአእምሮ ጤና ትኩረት እንስጥ!!!!

አርቲስት ሙኒት መስፍን
ትርጉም ዶ/ር ዮናስ ላቀው

Thank you Munit🙏

@melkam_enaseb
#ብቸኝነት፡- ለህብረተሰብ ጤና ዋነኘው ተጠያቂ ነው።

በአንድ ጥላ ስር ለሚኖር ቤተሰብ ተነጣጥሎ የሚመጣ ደስታም ሆነ በረከት አይኖርም የአንዱ ደስታ ለአንዱ ይሰማል በአንዱ ሙዚቃም ሌላው ይዝናናል፡፡

ይህ ዓይነቱ ትስስር ተመሳሳይ የአኗኗር ዘይቤ፣ ተመሳሳይ የአመለካካት ውቅር እና ተመሳሳይ እጣ ፈንታ እንዲኖር ያስገድዳል፡፡

ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ አሁን አሁን በከፍተኛ ሁኔታ የህብረተሰብ ጤና አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንዲደርስ አድርጓል፡፡ የበዛ የአልኮል አወሳሰድ፣ የታዳጊዎች በአደገኛ ሁኔታ በሱስ መጠመድ እና ረዘም ላለ ሰዓት መቀመጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚጠቀሱ ሲሆን በቅርቡ የብሪገሃም ዩኒቨርስቲ የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰር በሆኑት በፕሮፌሰር ጁሊያን ሆልት ለንስታንድ የቀረበው ጥናት እንደሚያመለክተው ከሆነ ብቸኝነት አሁን ላይ ከፍተኛውን የህብረተሰብ ጤና ስጋትን በበላይነት ይመራል ብለዋል፡፡

ፕሮፌሰሩ እናዳሉት "የሰው ለሰው ግንኙነቶች ለሰው ልጅ ለመኖር እና በህይወት ለመቆየት የሚያስፈልግ መሰረታዊ ጉዳይ ነው፡፡ የጨቅላ ህጻናት ማቆያን በተመለከተ የተደረገው ጥናት እንዳሳየው ከሆነም አጠገባቸው ሰው ከነበራቸው ጨቅላ ህፃናት ይልቅ ለብቻቸው ተነጥለው ተቀምጠው የነበሩት ለሞት የመጋለጥ እድላቸው የሰፋ ነበር፡፡ ከዛም በላይ ሰዎችን ከህብረተሰባቸው ተነጥለው እንዲቆዩ ማድረግ የሰው ልጆች ለዘመናት ሲጠቀሙበት የነበረ የቅጣት ዓይነት እና ፍርድም ጭምር ነው፡፡

ይህንኑ #የብቸኝነት ጣጣን በተመለከተ AARP ያወጣው ጥናት እንሚያሳየው ከሆነ በአሜሪካ እድሜያቸው ከ45 ዓመት በላይ የሆኑ ወደ 42ሚሊዮን የሚጠጉ ጎልማሶች በአሰቃቂ የብቸኝነት ህይወትን እየገፉ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡

የፕሮፌሰሩ ጥናት አሜሪካዊያንን፣ አውሮፓዊያንን እና አሲያዊያንን ያሳተፈ የነበረ ሲሆን የጥናቱ ውጤት እንዳሳየው ከሆነ ብቸኝነት ያለእድሜ ሞትን ያስከትላል። በተጨማሪም ማህበረሳዊ ግንኙነቶች ያላቸው ሰዎች 50 በመቶ ያህል ያለእድሜ ከመሞት የማምለጥ እድል አላቸው ብሏል፡፡

በስተመጨረሻም ፕሮፌሰሩ እንደዚህ ካለው አሳሳቢ ቀውስ ለመውጣት ለተማሪዎች፣ ለህጻናት እና ለህብረተሰቡ የተለያዩ ስልጠናዎች እና ትምህርቶች መሰጠት አለበት ያሉ ሲሆን አክለውም ሀኪሞች ከበሽተኞቻቸው ጋር ቅርበት ሊኖራቸው እና ህብረተሰቡም አንዱ ከአንዱ የሚተሳሰርበት የገንዘብ ፍሰት ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡

N.B. ብቸኝነት እየሰፋ ሲሄድ ወደ አዕምሮ ጤና ቀውስ ያመራል። ስለሆነም እንዲህ የሚያጋጥምዎ ከሆነ ወይም የሚያጋጥመው ሰው ካዩ ይረዱት፣ ያዳምጡት። ችግሩ ከፍ ካለም ወደ ባለሙያ ይውሰዱት።

Source፡- RedOrbit

@melkam_enaseb
⬆️ #Psychology in general is studied in five different perspectives, each being an angle by which you look at human phenomena.

@melkam_enaseb
#ከምጽሐፍት

"አታማር! ያለፈው ሕይወትህ አጋጣሚዎች ማከማቻ አትሁን። እናም የመጀመሪያው እርምጃህ ያለፈውን መርሳት ይሁን።

የማይረባውን ተሸክመህ አትዙር። እጅግ በጣም ወሳኙን የአእምሮህን ክፍል በእንቶፈንቶ ያለፈ ገጠመኝ አትሙላው። ሐሳቦችህ ኃይለኛ ጉልበት ያላቸው መሆናቸውን አስታውስ።

ስለዚህ በማይጠቅሙ ሰዎችና ክስተቶች አታባክናቸው። ተበድለህም ከሆነ ይቅርታ አድርግና እርሳው። አሁን ሙሉ ኃይልህን በምትፈልገው ጉዳይ ላይ ብቻና ብቻ አተኩር።"

ርዕስ፦ የሐሳብ ኃይል
አዘጋጅ፦ ከድር አሰፋ

መልካም ቀን!

@melkam_enaseb
ፆታዊ ጥቃት ማለት ፆታን ማእከል ያደረገ (አንድ ሰው ሴት/ወንድ በመሆኑ ምክንያት የሚደርስ) ማንኛዉም አይነት አካላዊ፣ ወሲባዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ኢኮኖሚያዊ... የጥቃት ድርጊት ነው።

ብዙ ጊዜ አንዲት ሴት ፆታዊ ጥቃት ደረሰባት ሲባል አእምሯችን ውስጥ የሚመጣው አካላዊ ጥቃት ወይም ወሲባዊ ፆታዊ ጥቃት ነው።

ስነ-ልቦና ላይ የሚደርስ ጥቃት ብዙም ትኩረት ያላገኝ እንዲሁም ደግሞ በማህበረሰባችን ዘንድ ተቀባይነትን ያገኝ እና እንደችግር የማይቆጠር የጥቃት አይነት ነው።

ሴትን ልጅ ማሸማቀቅ፣ ማስፈራራት፣ ስሜትን በሚጎዱ ቃላት መናገር ወይም መሳደብ፣ ማዋረድ፣ እንቅስቃሴዋን ለመቆጣጠር መሞከር ስነ-ልቦናዊ ፆታዊ ጥቃት ነው።

ስነ-ልቦናዊ ፆታዊ ጥቃት አእምሮ ላይ ትልቅ ጠባሳ የሚፈጥር በመሆኑ እንደ ሌሎቹ የፆታዊ ጥቃት አይነቶች ትኩረት ሊሰጥ እና ሊወገዝ ይገባል።

የዘንድሮ የነጭ ሪቫን ቀን "ሴትን  አከብራለሁ ጥቃቷን እከላከላለው" በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።

ከነዓን በለጠ (የስነ-አእምሮ ሕክምና ባለሙያ)

@melkam_enaseb
የስማርት ስልክ ሱሰኛ መሆንዎን በቀላሉ እንዴት ማወቅ ይችላሉ?

በዚሁ አመት የተደረጉ ጥናቶችም የስማርት ስልኮች እና የተጠቃሚዎቻቸውን አስደንጋጭ አሃዛዊ ትስስር አሳይተዋል ስማርት ስልክዎ አጠገብዎ ከሌለ መተኛት ይከብድዎታል? የባትሪው መቀነስስ ጭንቀት ውስጥ ይከትዎታል? ስልክዎ ሳይጠራ የተደወለልዎ፥ መልዕክት ሳይላክልዎ መልዕክት መላኩን የሚያሳውቅ ድምጽ ሰምተው ስልክዎን ደጋግመው አይተዋል? መልስዎ አዎ ከሆነ የስማርት ስልክ ሱስ ተጠቂ ሳይሆኑ አልቀረምና ቆም ብለው ያስበቡብት።

ከተጠቃሚው ቁጥር መጨመር እኩል በስማርት ስልክ ሱስ ተጠቂ የሆኑ ሰዎች ቁጥርም እያደረ እየጨመረ መሆኑን ፔው የተሰኘው የጥናት ተቋም ያወጣው የዳሰሳ ጥናት ያመለክታል።

በአሜሪካ 47 ከመቶ የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች ስልካቸውን የሙጥኝ ያስባለ ሱስ እንደያዛቸው ያምናሉ።

71 ከመቶው የሚሆኑ የጥናቱ ተሳታፊዎችም ከፍቅር ጓደኛቸው ጋር ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ለስልካቸው ጊዜ እንደሚሰጡ ነው የተናገሩት።

በጥናቱ ምላሽ ከሰጡት ህጻናት ውስጥም ሁለት ሶስተኛው በቀን ከ4 ስአታት በላይ በስልካቸው እንደሚያጠፉ ተመላክቷል።

ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ተሳታፊዎች ስልካቸውን ሳይዙ መንቀሳቃስ ከፍተኛ የመረበሽ ስሜትና ፍርሃት ውስጥ እንደሚከታቸው የተናገሩ ሲሆን፥ ስማርት ስልኮችን እየተጠቀሙ መንዳት ከሚደርሱ አደጋዎች 20 በመቶውን ይሸፍናል ተብሏል።

ቀጣዮቹ አስደንጋጭ ቁጥሮችም የስማርክ ስልክ ተጠቃሚዎች ችላ ብለው ካለፏቸው በያዙት ስልክ ሱስ ተጠልፈው መውደቃቸውን ያሳያል ይላሉ ባለሙያዎች።

ስማርት ስልኮች አሰራራቸው በራሱ ሱስ
ውስጥ የሚከት ነው የሚለው የአሜሪካ አዲክሽን ሴንተር ድረገጽ፥ የየእለት እንቅስቃሴያችን ከስልካችን ጋር የተያያዘ መሆኑን ያወሳል።

መዝናኛው፣ መረጃ መሰብሰቢያው፣ ክፍያ መፈጸሚያው፣ አቅጣጫ ጠቋሚው፣ አማካሪው ስማርት ስልክ አጠቃቀሙ ገደብ ካልተበጀለት ግን ጉዳቱ እያመዘነ መሄዱ አይቀርም።

ከመጠን ያለፈና በሱስ ደረጃ የተቀመጠ የስማርት ስልክ አጠቃቀም የሰነልቦና ባለሙያዎች ከአዳዲስ ስያሜዎች ጋር እንዲያስተዋውቁን አድርጓል። ከነዚህም ውስጥ “ኖሞፎቢያ” (ስልክ የሌለበትን ሁኔታ መፍራት)፣ ቴክስታፍሪኒያ (መልዕክት ሳይገባልን ግን የተላከልን መስሎን የማየት ልማድ) እና ፋንተም ቫይብሬሽን (ስልካችን በስህተት የነዘረን መስሎን አውጥተን የምናይበት) የተሰኙት ይገኙበታል።

እናም እነዚህ ምልክቶችን ደጋግማችሁ ከተመለከታችሁ በስማርት ስልካችሁ ሱስ ውስጥ ተዘፍቃችሁ ሊሆን ስለሚችል ባለሙያዎችን አማክሩ።

የድብርት፣ እንቅልፍ እጦት እና የስራ መጥላት ባህሪ እየተላመደ መሄድም ከማህበራዊ ህይወት ከመራቅ ጋር ተዳምሮ ራስን ወደማጥፋት ሊያመራ ይችላል፤ ጥናቶችም ይህንኑ አሳይተዋል የሚሉት የስነልቦና ባለሙያዎች ጉዳዩን እንደቀላል ነገር መመልከት እንደማይገባም ያሳስባሉ።

Via: Alain Amharic

@melkam_enaseb
#ገጽ26

የደረሰብን መከራ ባለንበት የሚያስቀረን፣ እኛ ላይ ብቻ እንደሆነ በመስበክ ነው። እኛ ብቻ ተለይተን ተጋላጮች እንደሆንን በመንገር ነው። በገጠመህ እክል ልብህ አዝኖ ጥግህን ይዘህ ቁጭ ብለህ ሳለህ በዚህ መንገድ እኮ የወደቅከው አንተ ብቻ ነህ ይልሃል።

ኩርምት ካልክበት ስፍራ ይቀርብህና ስማኝማ ይልሃል፡፡ እንደምንም ብሎ ቀልብህን እንደሳበም ጆሮህንም እንዳገኘ "ሰነፍ ነህ አትጠቅምም! ከመንገዱ ማብቂያም አትደርስም" ይልሃል። አንተም ተሽመድምደህ ባለህበት ተጣጥፈህ እስከቆየህለት ድረስ የነገረህ ሁሉ እውነት፣ አለምም ባንተ የውድቀት ዜና ዙሪያ ብቻ የምትዞር ይመስልሃል።

እውነት ነው እኮ! የወደቅ ቀን ሁሉም ጭልም ብሎ ነው የሚታይህ። ሰው ትፈራለህ፣ መዝናናትን ትፈራለህ፣ ህብረት ማድረግን ትሸሻለህ፣ ላንተ መፍትሄው ቤትህ ውስጥ መደበቅ ብቻ ይመስልሃል። ትንሽ እንኳ መስኮቴን ገርበብ አድርጌ አካባቢዬን ልይ ብትል እንኳ ዓይንህ ራሱ መርጦ የሚያይልህ ተሰብረው የቀሩትን ብቻ ነው፡፡ ጆሮህም ሳይቀር የሚሰማው ድምፅ የከሸፈ ጥይት፣ የከሸፈ ሰው ራዕይና ፅንስ ሲጨነግፍ የሚሰማውን ብቻ ነው።

በተዘጋ ክፍል ውስጥ መሆን አንድ ነገር ነው፡፡ እኔ ግን መውጫ በር እንኳ ከሌለው ጉድጓድ ውስጥ ገብቻለሁ ትላለህ።

ይህ ሁሉ ግን እመነኝ- እምቢ ብለህ ብድግ እስክትል ድረስ ብቻ ነው። ስትነሳ መንገዱን በሙሉ እየወደቁ የሚነሱ ተነስተውም የሚሮጡ ሞልተውት እንዳሉ ይታዩሃል። ወደኋላ የቀሩበትን መንገድ እንደቀስት ለመወንጨፍ የሚጠቀሙበትን ዘዴ ታስተውላለህ። ውድቀታቸውን በበጎ እይታ የሚመለከቱትንም ልብ ትላለህ።

ያኔ ማንም ያልወደቀበት ጉዞ ቢሆን እንኳ እኔን አይቶ ለመነሻ ይሆነዋል ትላለህ። የከበበህንም ጭጋግ ትበትናለህ ከአንገትህም ቀና ትላለህ።

(ዶ/ር በጸሎት ከበደ)
#Hakim

@melkam_enaseb
"አንድ ነገር ይሳካል ብለህ ስታምን አዕምሮህ ማሳካት የምትችልበትን መንገድ ይፈልጋል። በአንጻሩ ደግሞ እንደማይሳካ ስታምን አዕምሮህ ሊሳካ የማይችልባቸውን ምክንያቶች ይደረድርልሃል።"

(የሐሳብ ኃይል መጽሐፍ)

መልካም የሥራ ሳምንት!

@melkam_enaseb
2025/07/12 05:00:28
Back to Top
HTML Embed Code: