የጭንቀት መነሻዎችና መፍትሄዎች!
የዓለም ጤና ድርጅት በፈረንጆቹ 2019 ባደረገው ጥናት በዓለም ዙሪያ 301 ሚሊየን ሰዎች በጭንቀት ውስጥ እንደሚኖሩ ገልጿል፡፡
ከእነዚህ ውስጥ 58 ሚሊየን የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት እና ወጣቶች መሆናቸውንም ነው የገለጸው።
የአዕምሮ በሽታ ተብለው ከሚጠቀሱና በማህበረሰቡ በስፋት ከሚስተዋሉት መካከል ጭንቀት አንዱ ሲሆን፥ ከራስ ጋር እና ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚኖር ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጫናን ሊፈጥር ብሎም የስራ ምርታማነትን እና ወደ ስኬት የሚደረገው ጉዞ ላይ እክል ሊፈጥር ይችላል፡፡
ይህም የተወሰነ የእድሜ ክልልን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍልን የሚያጠቃ ነው፡፡
ያለበቂ ምክንያት ወይም ሊያስጨንቅዎት የሚገባው ነገር ካለፈ በኋላ ስሜቱ ሲቀጥል ጭንቀት ይባላል።
በአሁኑ ወቅት መረጃ ከመጠን በላይ መገኘት፣ ያለአግባብ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ራስን ከሌሎች ሰዎች ጋር ማወዳደር፣ ጤና፣ ገንዘብ፣ የቤተሰብ ሁኔታ፣ የልጅነት ገጠመኞች፣ ከባድ አጋጣሚዎች፣ ለነገሩ የሚሰጡት ክብደት መጨመሩ እና ሌሎች የጭንቀት መንስዔዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
አብዛኞቹ የአዕምሮ በሽታዎች ያሉበት ደረጃ ባሕርያትና ሁኔታ ከሰውሰው ይለያያሉ፥ አንዳንዶቹ ላይ ቀለል ያለ ሌሎች ላይ ደግሞ ከባድ ወይም ውስብስብ ምልክቶችን ያሳያሉ።
የባህሪ መቀያየር እስከ ማህበራዊ ህይወት መገለል ያሉ ምልክቶችም ይታያሉ።
በተጨማሪም የእጅ መንቀጥቀጥ፣ ላብ ላብ ማለት፣ የልብ ምት መጨመር፣ የድካም ስሜት፣ የራስ ምታት፣ የተወሰኑ ነገሮች ላይ ደጋግሞ ማሰብ፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ደስታ ወይም ፍላጎት ማጣት ምልክቶች ናቸው፡፡
በአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል ሰዎች የሥነ-አዕምሮ በሽታ ተጠቂዎች እንደሆኑ አምነው ወደ ህክምና ተቋም ሄዶ መታከም አልተለመደም፤ ይህንን ተከትሎም በሽታው ከነበረበት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በመድረስ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል።
የአዕምሮ ጤና ጉዳይ ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ወደሆነ ደረጃ ተሸጋግሯል ይላሉ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን፡፡
በአካባቢና በህይወትዎ የሚፈጠሩ ክስተቶች በአግባቡ ካልተቆጣጠሩት እና ራስዎ ላይ ትኩረት አድርገው ካልሰሩ የአዕምሮ ቀውስ ውስጥ ሊከትል ይችላል፡፡
አልፎ አልፎ ጭንቀትን በተለመደው የህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ለጥቂት ጊዜ ሊያጋጥም ይችላል። ሆኖም በጭንቀት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በራሳቸው ጥረትና በህክምና ባለሙያዎች እገዛ ተደርጎላቸው መዳን ይችላሉ፡፡
በዚህም ለራስ ጊዜ በመስጠት (በጥሞና) ነገሮችን ማሰላሰል፣ ተረጋግቶ የራስን ህይወት በትኩረት ማየት፣ አስተሳሰብ ላይ ረዘም ያለ ጊዜ በመውሰድ ፍተሻ ማድረግ፣ ለነገሮች የሚሰጡትን አመክንዮ እና ራስ ላይ በማተኮር መፍትሄ መስጠት ይቻላል፡፡
ከዚህ ባስ ካለ ወይም የባለሙያ እገዛ ካስፈለግዎ ሃኪምን ማማከር ተገቢ ነው፡፡
ቴዎድሮስ ድልነሳው (የሥነ-ልቦና ባለሙያ)
@melkam_enaseb
የዓለም ጤና ድርጅት በፈረንጆቹ 2019 ባደረገው ጥናት በዓለም ዙሪያ 301 ሚሊየን ሰዎች በጭንቀት ውስጥ እንደሚኖሩ ገልጿል፡፡
ከእነዚህ ውስጥ 58 ሚሊየን የሚሆኑት ደግሞ ህጻናት እና ወጣቶች መሆናቸውንም ነው የገለጸው።
የአዕምሮ በሽታ ተብለው ከሚጠቀሱና በማህበረሰቡ በስፋት ከሚስተዋሉት መካከል ጭንቀት አንዱ ሲሆን፥ ከራስ ጋር እና ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚኖር ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጫናን ሊፈጥር ብሎም የስራ ምርታማነትን እና ወደ ስኬት የሚደረገው ጉዞ ላይ እክል ሊፈጥር ይችላል፡፡
ይህም የተወሰነ የእድሜ ክልልን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍልን የሚያጠቃ ነው፡፡
ያለበቂ ምክንያት ወይም ሊያስጨንቅዎት የሚገባው ነገር ካለፈ በኋላ ስሜቱ ሲቀጥል ጭንቀት ይባላል።
በአሁኑ ወቅት መረጃ ከመጠን በላይ መገኘት፣ ያለአግባብ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ራስን ከሌሎች ሰዎች ጋር ማወዳደር፣ ጤና፣ ገንዘብ፣ የቤተሰብ ሁኔታ፣ የልጅነት ገጠመኞች፣ ከባድ አጋጣሚዎች፣ ለነገሩ የሚሰጡት ክብደት መጨመሩ እና ሌሎች የጭንቀት መንስዔዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
አብዛኞቹ የአዕምሮ በሽታዎች ያሉበት ደረጃ ባሕርያትና ሁኔታ ከሰውሰው ይለያያሉ፥ አንዳንዶቹ ላይ ቀለል ያለ ሌሎች ላይ ደግሞ ከባድ ወይም ውስብስብ ምልክቶችን ያሳያሉ።
የባህሪ መቀያየር እስከ ማህበራዊ ህይወት መገለል ያሉ ምልክቶችም ይታያሉ።
በተጨማሪም የእጅ መንቀጥቀጥ፣ ላብ ላብ ማለት፣ የልብ ምት መጨመር፣ የድካም ስሜት፣ የራስ ምታት፣ የተወሰኑ ነገሮች ላይ ደጋግሞ ማሰብ፣ የእንቅልፍ መዛባት፣ ደስታ ወይም ፍላጎት ማጣት ምልክቶች ናቸው፡፡
በአብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል ሰዎች የሥነ-አዕምሮ በሽታ ተጠቂዎች እንደሆኑ አምነው ወደ ህክምና ተቋም ሄዶ መታከም አልተለመደም፤ ይህንን ተከትሎም በሽታው ከነበረበት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በመድረስ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል።
የአዕምሮ ጤና ጉዳይ ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ወደሆነ ደረጃ ተሸጋግሯል ይላሉ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን፡፡
በአካባቢና በህይወትዎ የሚፈጠሩ ክስተቶች በአግባቡ ካልተቆጣጠሩት እና ራስዎ ላይ ትኩረት አድርገው ካልሰሩ የአዕምሮ ቀውስ ውስጥ ሊከትል ይችላል፡፡
አልፎ አልፎ ጭንቀትን በተለመደው የህይወት እንቅስቃሴ ውስጥ ለጥቂት ጊዜ ሊያጋጥም ይችላል። ሆኖም በጭንቀት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች በራሳቸው ጥረትና በህክምና ባለሙያዎች እገዛ ተደርጎላቸው መዳን ይችላሉ፡፡
በዚህም ለራስ ጊዜ በመስጠት (በጥሞና) ነገሮችን ማሰላሰል፣ ተረጋግቶ የራስን ህይወት በትኩረት ማየት፣ አስተሳሰብ ላይ ረዘም ያለ ጊዜ በመውሰድ ፍተሻ ማድረግ፣ ለነገሮች የሚሰጡትን አመክንዮ እና ራስ ላይ በማተኮር መፍትሄ መስጠት ይቻላል፡፡
ከዚህ ባስ ካለ ወይም የባለሙያ እገዛ ካስፈለግዎ ሃኪምን ማማከር ተገቢ ነው፡፡
ቴዎድሮስ ድልነሳው (የሥነ-ልቦና ባለሙያ)
@melkam_enaseb
⬆️ የእነዚህ ሁለት ምስሎች ትርጉም ጥልቅ ነው።
ምስል 1
ውጫዊ ገጽታው በፈገግታ የታጀበ ቢመስልም ውስጡ ግን ጥልቅ ሃዘን አለ::
ለዚያም ነው የቅርብ ሰዎቻችንን በፈገግታቸው ለክተን ውስጣዊ ህመማቸውን ሳናይላቸው ራሳቸውን ለማጥፋት ሲሞክሩ/ሲያጠፋ 'እኮ እንዴት' ብለን ስንገረም የምንስተዋለው።
ምስል 2
ይህ የፊት ገጽታ ለረጅም ጊዜ በድባቴ ስሜት ውስጥ ያለፋ ሰዎች ላይ የሚታይ የፊት ገጽታ ነው።
- Veraguth's fold (የአይን ቆዳቸው ቅጭም ማለት)
- Omega sign (የግንባር ቆዳቸው ኦሜጋ የምትባለዋን ፊደል የመስራት ያህል መሸብሸብ) ያመላክታል።
እና ምን ለማለት ነው የሳቀ ሁሉ ደስተኛ አይደለም። የውስጥ ስሜት ሁሌም ፊት ላይ ላይነበብ ይችላልና!
የድብርት ህመም ውጤታማ የስነልቦና እና የመድሃኒት ህክምና አለው!
ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው (የአዕምሮ ህክምና ሬዚደንት ሃኪም)
@melkam_enaseb
ምስል 1
ውጫዊ ገጽታው በፈገግታ የታጀበ ቢመስልም ውስጡ ግን ጥልቅ ሃዘን አለ::
ለዚያም ነው የቅርብ ሰዎቻችንን በፈገግታቸው ለክተን ውስጣዊ ህመማቸውን ሳናይላቸው ራሳቸውን ለማጥፋት ሲሞክሩ/ሲያጠፋ 'እኮ እንዴት' ብለን ስንገረም የምንስተዋለው።
ምስል 2
ይህ የፊት ገጽታ ለረጅም ጊዜ በድባቴ ስሜት ውስጥ ያለፋ ሰዎች ላይ የሚታይ የፊት ገጽታ ነው።
- Veraguth's fold (የአይን ቆዳቸው ቅጭም ማለት)
- Omega sign (የግንባር ቆዳቸው ኦሜጋ የምትባለዋን ፊደል የመስራት ያህል መሸብሸብ) ያመላክታል።
እና ምን ለማለት ነው የሳቀ ሁሉ ደስተኛ አይደለም። የውስጥ ስሜት ሁሌም ፊት ላይ ላይነበብ ይችላልና!
የድብርት ህመም ውጤታማ የስነልቦና እና የመድሃኒት ህክምና አለው!
ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው (የአዕምሮ ህክምና ሬዚደንት ሃኪም)
@melkam_enaseb
ራስን ማጥፋት (suicide)
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገር በስፋት የምንሰማው ራስን የማጥፋት (suicide) ተግባር በሀገራችን በተለይም አንዲት እንስት 'ብንሄድ ይሻላል' ብላ Facebook ከለጠፈች እና ራሷን ካጠፋች ብኋላ በሀገራችን በተለይም በወጣቱ ዘንድ እንደተስፋፋ ግልፅ ነው።
ከዚህ ቀደም በሚዲያ አንሰማው ይሆናል እንጂ ይህ ራስን የማጥፋት ድርጊት በዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ የትምህርት እና ስራ ቦታዎች ላይ ሲከሰት ነበር።
ምናልባትም ይህንን በራሳችን ላይ ለመፈፀም የሚያስገድዱ ሁኔታዎች ውስጥ ያለፍን ልንኖር እንችላለን። ሰው ነፍሱን በራሱ ለማጥፋት ምክንያት የሚሆኑ በጥቂቱ ብንጠቅስ፦
ሕይወት ፊቷን ስታዞር እና ቀን ሲጨልምበት፣ በሚያመነው ሰው ሲከዳ እና ተስፋውን ሲያጣ፣ የኑሮ ፈተና ሲበዛ እና መውጫ መንገድ ሲጠፋበት፣ በሚያሰበው ልክ ነገሮች ሳይከናወኑለት ሲቀሩ፣ በሚያየው ሁሉ ነገን ኣሻግሮ ማየት ሲያቅተው፣ በቤቱ፣ በትዳሩ ክብርን እና ተቀባይነት ሲነፈግ ወ.ዘ.ተ ናቸው።
በርግጥ በግለሰቡ ሁኔታ እና ጫማ ውስጥ ሆነን ነገሩን መመልከት እስካልቻልን ድረስ ስለዚህ ሁኔታ በድፍረት መናገር አንችልም።
የራስን ማጥፋት ውሳኔ ቅፅበታዊ ነው። ጥቂት ሰከንዶች ሺህ ዘመን መስለው ይታያሉ። ስቃይ እና ፈተና ዘላለማዊ ይመስልና አዕምሯችን ለውሳኔ እንድንጣደፍ ሆርሞኖችን ይቀሰቅሳል። ከዚያ ነገሮች ያበቃሉ። ሰዎች የሰዎችን ሁኔታ አያዩም እንጂ በርካቶች ለተመሳሳይ ወጥመድ ተጋልጠው በተዓምር ይሁን በራሳቸው ብርታት አምልጠዋል። ለዚህ ምስክሮችን መጥራት አያስፈልግም።
በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ራሳችንን እንዳናገኝ እነዚህ ነገሮችን ብንተገብር መልካም ነው ብዬ አስባለው።
1. ከእምነት ተቋማት አለመራቅ። ሀይማኖታዊነትን መላበስ በራሱ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጣል ብዬ አምናለው።
2. Multi-Professional-Friends ሊኖሩን ይገባል። በአንድ ሙያ መስክ ብቻ የተሰማሩ ጓደኞች አይኑሯችሁ። ሕይወትን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሊያስመለክቱ የሚችሉ ወዳጆችን መፍጠር ያስፈልጋል።
3. በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ የምክር አገልግሎት የሚሰጡ - Counselling and Guidance Service ተቋማትን መጎብኘት ያስፈልጋል። በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚገኙ እነዚህ ተቋማት በመሰል ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ቦታዎች በየከተማው ላይ መስፋፋት አለባቸው።
ራሳቸውን ላጠፉ ፈጣሪ እዝነቱን ያድርግላቸው!
Credit: Workineh Gebeyehu Gomera
#EliasMeseret
@melkam_enaseb
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገር በስፋት የምንሰማው ራስን የማጥፋት (suicide) ተግባር በሀገራችን በተለይም አንዲት እንስት 'ብንሄድ ይሻላል' ብላ Facebook ከለጠፈች እና ራሷን ካጠፋች ብኋላ በሀገራችን በተለይም በወጣቱ ዘንድ እንደተስፋፋ ግልፅ ነው።
ከዚህ ቀደም በሚዲያ አንሰማው ይሆናል እንጂ ይህ ራስን የማጥፋት ድርጊት በዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ የትምህርት እና ስራ ቦታዎች ላይ ሲከሰት ነበር።
ምናልባትም ይህንን በራሳችን ላይ ለመፈፀም የሚያስገድዱ ሁኔታዎች ውስጥ ያለፍን ልንኖር እንችላለን። ሰው ነፍሱን በራሱ ለማጥፋት ምክንያት የሚሆኑ በጥቂቱ ብንጠቅስ፦
ሕይወት ፊቷን ስታዞር እና ቀን ሲጨልምበት፣ በሚያመነው ሰው ሲከዳ እና ተስፋውን ሲያጣ፣ የኑሮ ፈተና ሲበዛ እና መውጫ መንገድ ሲጠፋበት፣ በሚያሰበው ልክ ነገሮች ሳይከናወኑለት ሲቀሩ፣ በሚያየው ሁሉ ነገን ኣሻግሮ ማየት ሲያቅተው፣ በቤቱ፣ በትዳሩ ክብርን እና ተቀባይነት ሲነፈግ ወ.ዘ.ተ ናቸው።
በርግጥ በግለሰቡ ሁኔታ እና ጫማ ውስጥ ሆነን ነገሩን መመልከት እስካልቻልን ድረስ ስለዚህ ሁኔታ በድፍረት መናገር አንችልም።
የራስን ማጥፋት ውሳኔ ቅፅበታዊ ነው። ጥቂት ሰከንዶች ሺህ ዘመን መስለው ይታያሉ። ስቃይ እና ፈተና ዘላለማዊ ይመስልና አዕምሯችን ለውሳኔ እንድንጣደፍ ሆርሞኖችን ይቀሰቅሳል። ከዚያ ነገሮች ያበቃሉ። ሰዎች የሰዎችን ሁኔታ አያዩም እንጂ በርካቶች ለተመሳሳይ ወጥመድ ተጋልጠው በተዓምር ይሁን በራሳቸው ብርታት አምልጠዋል። ለዚህ ምስክሮችን መጥራት አያስፈልግም።
በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ራሳችንን እንዳናገኝ እነዚህ ነገሮችን ብንተገብር መልካም ነው ብዬ አስባለው።
1. ከእምነት ተቋማት አለመራቅ። ሀይማኖታዊነትን መላበስ በራሱ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጣል ብዬ አምናለው።
2. Multi-Professional-Friends ሊኖሩን ይገባል። በአንድ ሙያ መስክ ብቻ የተሰማሩ ጓደኞች አይኑሯችሁ። ሕይወትን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሊያስመለክቱ የሚችሉ ወዳጆችን መፍጠር ያስፈልጋል።
3. በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ የምክር አገልግሎት የሚሰጡ - Counselling and Guidance Service ተቋማትን መጎብኘት ያስፈልጋል። በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የሚገኙ እነዚህ ተቋማት በመሰል ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ቦታዎች በየከተማው ላይ መስፋፋት አለባቸው።
ራሳቸውን ላጠፉ ፈጣሪ እዝነቱን ያድርግላቸው!
Credit: Workineh Gebeyehu Gomera
#EliasMeseret
@melkam_enaseb
ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 4 ቀን 2016 ዓም በብይነ መረብ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል::
በዕለቱ በአእምሮ ጤና ዙሪያ የሚያጠነጥነው “የሁሉ” የልብወለድ መፅሃፍ ላይ ከዶ/ር አዜብ አሳምነው ከዶ/ር ዮናስ ላቀው እንዲሁም ከደራሲው ከዶ/ር ዳዊት አሰፋ ጋር የኦንላይን ውይይት ይደረጋል፡፡
በዕለቱ ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡፡ ⬇️
https://meet.google.com/gsd-iztg-rop
@melkam_enaseb
በዕለቱ በአእምሮ ጤና ዙሪያ የሚያጠነጥነው “የሁሉ” የልብወለድ መፅሃፍ ላይ ከዶ/ር አዜብ አሳምነው ከዶ/ር ዮናስ ላቀው እንዲሁም ከደራሲው ከዶ/ር ዳዊት አሰፋ ጋር የኦንላይን ውይይት ይደረጋል፡፡
በዕለቱ ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጠቀሙ፡፡ ⬇️
https://meet.google.com/gsd-iztg-rop
@melkam_enaseb
የውድድር ስነ-ልቦና!
የውድድር ስነ ልቦና እንደዘርፉ ባለሙያዎች ትንታኔ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡
ውድድር ሰዎች አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ለማነሳሳት እንደሚረዳና አውጥተውም እንዲያሳዩበት እድል የሚፈጥር መሆኑ ይነገራል፡፡
ሆኖም የውድድር መንፈስ እንደጥቅሙ ሁሉ በትክክል መያዝ ካልተቻለ ችግር ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ውድድርም የተለያዩ የጤና እክሎችን እንደሚያስከትልም ነው የሚነገረው፡፡
የውድድር ስነ-ልቦና ሰዎች በህይወታቸው ያልተመለከቱትን አቅጣጫ የሚመለከቱበት ነው። በተጨማሪም በተለያዩ መንገዶች የተሻለ ለመሆን እገዛ የሚያደርግ ነው።
ውድድር አሸናፊና ተሸናፊዎች ያሉበትና ሽንፈትን ፈጽሞ አለመቀበል ራስን አላስፈላጊ ጭንቀት ውስጥ ሲከት ይታያል፡፡ ከቤተሰብ ወይም ከጓደኛ አልያም በስራ አካባቢ የበዛ የውድድር መንፈስ ሲታይ ተመልክተው ይሆናል፡፡
ይህ የውድድርና የአሸናፊነት ጥማት የሌሎችን ስኬት ዕውቅና ከመንፈግ ጀምሮ የራስን ማንነት አለመቀበል ሊያስከትል እንደሚችልም ይገለጻል፡፡
ይህም ሰዎችን መዋሸት፣ ጫናዎች፣ ጭንቀት፣ የበታችነት ስሜት መሰማትና በቂ ነገር የለኝም በማለት ያሉበትን ቦታ አለመውደድ እና የማንነት ቀውስ ውስጥ ያስገባል።
ያለአግባብ የውድድር መንፈስ በራስ መተማመን የሚያመጣው ስሜት ነው፥ የራሴ ነገር በቂ አይደለም በሚል ሃሳብ ሌሎችን ለመምሰል ይሞክራሉ፡፡ ይህ ስሜት እየቆየ ሲሄድም ቁጣ፣ ንዴት፣ ቅናት እና መሰል ስሜቶች መገለጥ ይጀምራሉ፡፡
ይህ ስሜት ከየት እንደመነጨ ማስተዋል፣ የሰዎችን ስኬት መቀበል፣ የውድድሩ ፍላጎት ራስን ከማሳደግ የመነጨ ነው ወይስ ሌላ ምክንያት አለው የሚለውን መለየት ችግሩን በወቅቱ ለመፍታት እንደሚያግዝም ይነገራል፡፡
ባርኮት ጌቱ (የስነ-ልቦና አማካሪ)
@melkam_enaseb
የውድድር ስነ ልቦና እንደዘርፉ ባለሙያዎች ትንታኔ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡
ውድድር ሰዎች አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ለማነሳሳት እንደሚረዳና አውጥተውም እንዲያሳዩበት እድል የሚፈጥር መሆኑ ይነገራል፡፡
ሆኖም የውድድር መንፈስ እንደጥቅሙ ሁሉ በትክክል መያዝ ካልተቻለ ችግር ሊሆን ይችላል፡፡ ጤናማ ያልሆነ ውድድርም የተለያዩ የጤና እክሎችን እንደሚያስከትልም ነው የሚነገረው፡፡
የውድድር ስነ-ልቦና ሰዎች በህይወታቸው ያልተመለከቱትን አቅጣጫ የሚመለከቱበት ነው። በተጨማሪም በተለያዩ መንገዶች የተሻለ ለመሆን እገዛ የሚያደርግ ነው።
ውድድር አሸናፊና ተሸናፊዎች ያሉበትና ሽንፈትን ፈጽሞ አለመቀበል ራስን አላስፈላጊ ጭንቀት ውስጥ ሲከት ይታያል፡፡ ከቤተሰብ ወይም ከጓደኛ አልያም በስራ አካባቢ የበዛ የውድድር መንፈስ ሲታይ ተመልክተው ይሆናል፡፡
ይህ የውድድርና የአሸናፊነት ጥማት የሌሎችን ስኬት ዕውቅና ከመንፈግ ጀምሮ የራስን ማንነት አለመቀበል ሊያስከትል እንደሚችልም ይገለጻል፡፡
ይህም ሰዎችን መዋሸት፣ ጫናዎች፣ ጭንቀት፣ የበታችነት ስሜት መሰማትና በቂ ነገር የለኝም በማለት ያሉበትን ቦታ አለመውደድ እና የማንነት ቀውስ ውስጥ ያስገባል።
ያለአግባብ የውድድር መንፈስ በራስ መተማመን የሚያመጣው ስሜት ነው፥ የራሴ ነገር በቂ አይደለም በሚል ሃሳብ ሌሎችን ለመምሰል ይሞክራሉ፡፡ ይህ ስሜት እየቆየ ሲሄድም ቁጣ፣ ንዴት፣ ቅናት እና መሰል ስሜቶች መገለጥ ይጀምራሉ፡፡
ይህ ስሜት ከየት እንደመነጨ ማስተዋል፣ የሰዎችን ስኬት መቀበል፣ የውድድሩ ፍላጎት ራስን ከማሳደግ የመነጨ ነው ወይስ ሌላ ምክንያት አለው የሚለውን መለየት ችግሩን በወቅቱ ለመፍታት እንደሚያግዝም ይነገራል፡፡
ባርኮት ጌቱ (የስነ-ልቦና አማካሪ)
@melkam_enaseb
ታዳጊ ልጆች/ወጣቶች እና የአእምሮ ጤና፦
- የታዳጊ ልጆች እድሜ (ጉርምስና) ልዩና ወሳኝ ጊዜ ነው:: አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ለውጦቹም ከፍተኛ ናቸው።
- በዚህ ጊዜ ላይ ለድህነት፣ ለጥቃት (አካላዊም ፆታዊ) መጋለጥ እዚህ ዕድሜ ላይ ላሉ ልጆች ለአእምሮ ጤና መታወክ የበለጠ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደርጋል::
አጋላጮች፦
▫️የአቻ ግፊት
▫️አካባቢያዊ ተጽዕኖዎች
▫️አካላዊ ወይም ጾታዊ ጥቃት
▫️የቤት ውስጥ ሰላም መጓደል
▫️የማንነት ጥያቄ
▫️የሚዲያ ተጽዕኖ
▫️ከፍላጎት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮች የተወሰኑት ናቸው።
- በተለይም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፣ የተለያዩ የነርቭ ችግሮች፣ የቅርብ ቤተሰብ ድጋፍ የሌላቸው ታዳጊ ልጆች/ወጣቶች ደግሞ የበለጠ ለአዕምሮ ጤና መታወክ የተጋለጡ ናቸው።
ከስሜት ጋር የተያያዙ ችግሮች፦
* ከልክ በላይ ጭንቀት
* የስሜት መዋዠቅ
* ድባቴ፣ ራስን ማግለል አልፎም *በህይወት መቆየት አለመፈልግ
የባህሪ ችግሮች፦
° ትኩረት ማጣት፣
° ለነገሮች መቸኮል፣
° የፀባይ ለውጥ መኖር
የአመጋገብ ችግር፦
➡ ውፍረት እንዳይመጣ ከሚል ከፍተኛ የሆነ የአመጋገብ ችግር ነው።
የስነ-ልቦና ቀውስ፦
• ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ ያደርጋል።
• ራሳቸውን በተለያዩ ሱሶች ይጎዳሉ።
• ከማህበረሰብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድርበታል።
- ይህ እንዳይሆን ምን እናድርግ?
▪️ቤተሰብ ልጆቹ በሰውነታቸው ላይ ለውጥ እየተካሄደ እንደሆነ በመረዳት ለልጆቹ ከምን ጊዜውም በላይ ቅርብ መሆን አለበት።
▪️ራሳቸውን በተለያዩ ዓይነት ስራዎቸ(እንደ ስፖርት ያሉ ነገሮች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ)፣ የመፍትሄ ሰዎች እንዲሆኑ፣ በጤነኛ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ በማድረግ ሁሉም ሰው የድርሻውን ማድረግ አለበት።
#WHO #TikvahEthiopia
@melkam_enaseb
- የታዳጊ ልጆች እድሜ (ጉርምስና) ልዩና ወሳኝ ጊዜ ነው:: አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ማህበራዊ ለውጦቹም ከፍተኛ ናቸው።
- በዚህ ጊዜ ላይ ለድህነት፣ ለጥቃት (አካላዊም ፆታዊ) መጋለጥ እዚህ ዕድሜ ላይ ላሉ ልጆች ለአእምሮ ጤና መታወክ የበለጠ ተጋላጭ እንዲሆኑ ያደርጋል::
አጋላጮች፦
▫️የአቻ ግፊት
▫️አካባቢያዊ ተጽዕኖዎች
▫️አካላዊ ወይም ጾታዊ ጥቃት
▫️የቤት ውስጥ ሰላም መጓደል
▫️የማንነት ጥያቄ
▫️የሚዲያ ተጽዕኖ
▫️ከፍላጎት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮች የተወሰኑት ናቸው።
- በተለይም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፣ የተለያዩ የነርቭ ችግሮች፣ የቅርብ ቤተሰብ ድጋፍ የሌላቸው ታዳጊ ልጆች/ወጣቶች ደግሞ የበለጠ ለአዕምሮ ጤና መታወክ የተጋለጡ ናቸው።
ከስሜት ጋር የተያያዙ ችግሮች፦
* ከልክ በላይ ጭንቀት
* የስሜት መዋዠቅ
* ድባቴ፣ ራስን ማግለል አልፎም *በህይወት መቆየት አለመፈልግ
የባህሪ ችግሮች፦
° ትኩረት ማጣት፣
° ለነገሮች መቸኮል፣
° የፀባይ ለውጥ መኖር
የአመጋገብ ችግር፦
➡ ውፍረት እንዳይመጣ ከሚል ከፍተኛ የሆነ የአመጋገብ ችግር ነው።
የስነ-ልቦና ቀውስ፦
• ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዳይከታተሉ ያደርጋል።
• ራሳቸውን በተለያዩ ሱሶች ይጎዳሉ።
• ከማህበረሰብ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድርበታል።
- ይህ እንዳይሆን ምን እናድርግ?
▪️ቤተሰብ ልጆቹ በሰውነታቸው ላይ ለውጥ እየተካሄደ እንደሆነ በመረዳት ለልጆቹ ከምን ጊዜውም በላይ ቅርብ መሆን አለበት።
▪️ራሳቸውን በተለያዩ ዓይነት ስራዎቸ(እንደ ስፖርት ያሉ ነገሮች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ)፣ የመፍትሄ ሰዎች እንዲሆኑ፣ በጤነኛ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ በማድረግ ሁሉም ሰው የድርሻውን ማድረግ አለበት።
#WHO #TikvahEthiopia
@melkam_enaseb
ወርሃዊው የሜንታል ሄልዝ አዲስ መርሃ ግብር ቅዳሜ ጥር 25 ቀን 2016 ዓም አትላስ አካባቢ በሚገኘው በአዶር አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ይደረጋል::
የዚህ ወር ርዕስም፡- “እንደ ህብረተሰብ የስነልቦና ቁስልን መገንዘብ” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳችን የአሃ ሳይኮሎጂካል አገልግሎት መስራች እና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሞገስ ገ/ማሪያም ናቸው፡፡
ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡ ⬇️
https://forms.gle/Y8iPkGRELLR2cFW86
@melkam_enaseb
የዚህ ወር ርዕስም፡- “እንደ ህብረተሰብ የስነልቦና ቁስልን መገንዘብ” የሚል ሲሆን የዚህ ወር እንግዳችን የአሃ ሳይኮሎጂካል አገልግሎት መስራች እና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሞገስ ገ/ማሪያም ናቸው፡፡
ለመታደም ይህን መስፈንጠሪያ ይጫኑና ይመዝገቡ፡፡ ⬇️
https://forms.gle/Y8iPkGRELLR2cFW86
@melkam_enaseb
ጤናማ ህይወትን መምራት እንዴት ይቻላል?
ጤናማ መሆን ማለት በአዕምሮ፣ በአካልና በስሜት ሙሉ ጤንነት ሲሰማን ማለት ነው፡፡
ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን መከተል በበሽታ እንዳንጠቃ ከማገዙም በላይ ጤናችን ስንጠብቅ ለራሳችን ያለን ግምት መልካም እንደሚሆን የተለያዩ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡
ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ደስተኛ፣ የተረጋጋና ስኬታማ ህይወት እንድንኖር ይረዳናል፡፡
ምንም እንኳን የተለያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ሁኔታዎች ጤናማ ህይወትን ለመምራት አሉታዊ ተጽዕኖ ቢፈጥሩም አኗኗራችንን እና ልማዶቻችንን በመቀየር ጤናማ ህይወት መኖር እንደሚቻል ነው ጥናቶች የሚያመላክቱት።
ጤናማ ህይወት ለመኖር የሰው ልጅ የተለያዩ የህይወት ዘይቤዎችን ይተገብራል፡፡ ከእነዚህም መካከል ዋና ዋናዎቹ፦
• የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣
• የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣
• ክብደትን መለካትና መቆጣጠር፣
• በቂ ውሃ መጠጣት፣
• ለረዥም ጊዜ ያለመቀመጥና ኮምፒውተርና ሌሎች ስክሪን ላይ የምናጠፋውን ጊዜ መቀነስ፣
• በቂ እንቅልፍ መተኛት፣
• ከመጠን ያለፈ አልኮል ያለመውሰድ፣
• ቁጣና መሰል ስሜቶችን መቆጣጠር፣
• ጭንቀትን ማስወገድ፣
•የጤና ክትትል ማድረግና መሰል የጤናማ አኗኗር ዘይቤዎች ይጠቀሳሉ፡፡
በተጨማሪም ከሰዎች ጋር ያለንን ማህበራዊ ግንኙነት በትኩረት መመልከት ያስፈልጋል። ከጓደኞች፣ ከቤተሰብና ጎረቤት እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ጋር ያለንን የዕለት ተዕለት ግንኙነት ማሻሻልና መልካም ማድረግ ለጤናማ ህይወት አስፈላጊ እንደሆነ የሜዲሲን ኔት መረጃ ያመላክታል፡፡
@melkam_enaseb
ጤናማ መሆን ማለት በአዕምሮ፣ በአካልና በስሜት ሙሉ ጤንነት ሲሰማን ማለት ነው፡፡
ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን መከተል በበሽታ እንዳንጠቃ ከማገዙም በላይ ጤናችን ስንጠብቅ ለራሳችን ያለን ግምት መልካም እንደሚሆን የተለያዩ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡
ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ ደስተኛ፣ የተረጋጋና ስኬታማ ህይወት እንድንኖር ይረዳናል፡፡
ምንም እንኳን የተለያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ሁኔታዎች ጤናማ ህይወትን ለመምራት አሉታዊ ተጽዕኖ ቢፈጥሩም አኗኗራችንን እና ልማዶቻችንን በመቀየር ጤናማ ህይወት መኖር እንደሚቻል ነው ጥናቶች የሚያመላክቱት።
ጤናማ ህይወት ለመኖር የሰው ልጅ የተለያዩ የህይወት ዘይቤዎችን ይተገብራል፡፡ ከእነዚህም መካከል ዋና ዋናዎቹ፦
• የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣
• የተመጣጠነ ምግብ መመገብ፣
• ክብደትን መለካትና መቆጣጠር፣
• በቂ ውሃ መጠጣት፣
• ለረዥም ጊዜ ያለመቀመጥና ኮምፒውተርና ሌሎች ስክሪን ላይ የምናጠፋውን ጊዜ መቀነስ፣
• በቂ እንቅልፍ መተኛት፣
• ከመጠን ያለፈ አልኮል ያለመውሰድ፣
• ቁጣና መሰል ስሜቶችን መቆጣጠር፣
• ጭንቀትን ማስወገድ፣
•የጤና ክትትል ማድረግና መሰል የጤናማ አኗኗር ዘይቤዎች ይጠቀሳሉ፡፡
በተጨማሪም ከሰዎች ጋር ያለንን ማህበራዊ ግንኙነት በትኩረት መመልከት ያስፈልጋል። ከጓደኞች፣ ከቤተሰብና ጎረቤት እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ጋር ያለንን የዕለት ተዕለት ግንኙነት ማሻሻልና መልካም ማድረግ ለጤናማ ህይወት አስፈላጊ እንደሆነ የሜዲሲን ኔት መረጃ ያመላክታል፡፡
@melkam_enaseb
እራስን ካለፉ መጥፎ ክስተቶች እስር ነፃ ማውጣት!
ህይወትህ ውስጥ በተፈጠረ አንድ አሉታዊ ክስተት ምክንያት፣ በአዕምሮህ አሁንም እየተመላለሰ የሚያስቸግርህ ሃሳብ አለ? ይህ ሃሳብ ስሜቱ ጠንካራ ከመሆኑ የተነሳ እንዴት አድርጌ ልርሳው ወይም ከትውስታዬ ልፋቀው ብለህ ታውቃለህ?
አዕምሮህን እንደትልቅ ላይብረሪ ተረዳው። ከልጅነት እስከ እውቀት አንተ ጋር የተከናወኑ ነገሮች ሁሉ በትውስታ መልክ በውስጡ እንደመጽሃፍት ተሰድረውበት ይገኛሉ። ከእነዚህ ትውስታዎች አንዳንዶቹ መልካም (አውንታዊ) ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ መልካም ያልሆኑ (አሉታዊ) ሊሆኑ ይችላሉ። እነዚህ ትውስታዎች ቢያልፉም እንደተገነዘብናቸው መጠን ዛሬም ድረስ ውስጣችን አውንታዊ ወይም አሉታዊ ስሜት ይፈጥራሉ።
በተለይ የአሉታዊ ክስተቶች ተፅዕኖ አሉታዊ ስሜት ውስጣችን በመፍጠር ብቻ የሚቆም አይደለም። ብዙ ግዜ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ውስጥ ዛሬም ጣልቃ እየገቡ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳንወስን ሊከለክሉንም ይችላሉ። ከዚያም ሲያልፍ ጉዳዩ በተፈጠረበት ወቅት ከደረስንባቸው መረዳቶችና ድምዳሜዎች የተነሳ፣ ወደፊት መፍጠር ከምንፈልገው ህይወት አንጻር የማይጠቅም እይታ (አመለካከት) እንድናዳብርም ያደርጋሉ።
የሚገርመው ብዙ ግዜ አሉታዊ ስሜት የሚፈጥሩትን ትውስታዎች በቀላሉ ማስታወስ፣ እንዲያውም እነዚህ ትውስታዎች ውስጥ ለረጅም ግዜ በመቆየት ራሳችንን ቶርቸር ማድረግ ለብዙዎቻችን ቀላል ነው። ምናልባት እነዚህ የምናስታውሳቸው ክስተቶች ያለፉና የማይደገሙ እንደሆኑ ብናውቅም አዕምሯችን ግን ክስተቶቹ አሁን በዚህ ቅጽበት እየተከናወኑ ያሉ እስከሚመስል ድረስ በጠንካራ አሉታዊ ስሜት ውስጥ እንድንዘፈቅ ያደርገናል። ታዲያ እነዚህ ያለፉ፣ የማይደገሙ ክስተቶች አሁን እየፈጠሩብን ካለው አሉታዊ ስሜት፣ የውሳኔ ውስንነትና፣ ጎታች አመለካከት ተፅዕኖዎች ራሳችንን እንዴት ማላቀቅ እንችላለን?
ይህን ጥያቄ ስናነሳ ብዙዎች “እርሳው ባክህ”፣ ወይም “ለበጎ ነው” ወዘተ የሚል ምላሽ ይሰጡናል። ነገርግን “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ነውና እኛ ነገሩን ማስታወስ ፈልገን ሳይሆን አዕምሯችን ከኛ እውቅና ውጪ እያሳሰበን እንደሆነ ማን ይንገርልን?
እነዚህ በውስጣችን ተሰድረው ማለፋቸው ሳያንስ አሁንም ህይወታችንን ካመሰቃቀሉ ትውስታዎችን ለመፋታት የሚከተሉትን ማድረግ እንችላለን፦
1. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ልንማርባቸው የምንችላቸው ነገሮች ካሉ ወረቀት ላይ በጽሁፍ ማስፈር።
2. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ጉዳቱን የፈጠሩ ሰዎች ካሉ፣ በወቅቱ የነበረባቸውን የባህርይ፣ ስሜት እና የውሳኔ ውስንነት እንደገና አሁን ባለን መረዳት መመልከት። እነዚህ ውስንነቶች ባይኖሩባቸው ምን ሊያደርጉ ይችሉ እንደነበር ማሰብ፤ እነሱ የነበሩባቸውን ውስንነቶች እኛም ሳናውቅ እያንጸባረቅን እንዳልሆነ ማረጋገጥ።
3. የሚፈጥሩብን ስሜት ከባድ ከሆነና ከላይ ባደረግናቸው ልምምዶች ስሜቶቹንና ግንዛቤያችንን መለወጥ ካቃተን የባለሙያ ርዳታ እንፈልግ።
ዳንኤል አያሌው (Certified NLP Practitioner)
@melkam_enaseb
ህይወትህ ውስጥ በተፈጠረ አንድ አሉታዊ ክስተት ምክንያት፣ በአዕምሮህ አሁንም እየተመላለሰ የሚያስቸግርህ ሃሳብ አለ? ይህ ሃሳብ ስሜቱ ጠንካራ ከመሆኑ የተነሳ እንዴት አድርጌ ልርሳው ወይም ከትውስታዬ ልፋቀው ብለህ ታውቃለህ?
አዕምሮህን እንደትልቅ ላይብረሪ ተረዳው። ከልጅነት እስከ እውቀት አንተ ጋር የተከናወኑ ነገሮች ሁሉ በትውስታ መልክ በውስጡ እንደመጽሃፍት ተሰድረውበት ይገኛሉ። ከእነዚህ ትውስታዎች አንዳንዶቹ መልካም (አውንታዊ) ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ መልካም ያልሆኑ (አሉታዊ) ሊሆኑ ይችላሉ። እነዚህ ትውስታዎች ቢያልፉም እንደተገነዘብናቸው መጠን ዛሬም ድረስ ውስጣችን አውንታዊ ወይም አሉታዊ ስሜት ይፈጥራሉ።
በተለይ የአሉታዊ ክስተቶች ተፅዕኖ አሉታዊ ስሜት ውስጣችን በመፍጠር ብቻ የሚቆም አይደለም። ብዙ ግዜ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ውስጥ ዛሬም ጣልቃ እየገቡ ትክክለኛ ውሳኔ እንዳንወስን ሊከለክሉንም ይችላሉ። ከዚያም ሲያልፍ ጉዳዩ በተፈጠረበት ወቅት ከደረስንባቸው መረዳቶችና ድምዳሜዎች የተነሳ፣ ወደፊት መፍጠር ከምንፈልገው ህይወት አንጻር የማይጠቅም እይታ (አመለካከት) እንድናዳብርም ያደርጋሉ።
የሚገርመው ብዙ ግዜ አሉታዊ ስሜት የሚፈጥሩትን ትውስታዎች በቀላሉ ማስታወስ፣ እንዲያውም እነዚህ ትውስታዎች ውስጥ ለረጅም ግዜ በመቆየት ራሳችንን ቶርቸር ማድረግ ለብዙዎቻችን ቀላል ነው። ምናልባት እነዚህ የምናስታውሳቸው ክስተቶች ያለፉና የማይደገሙ እንደሆኑ ብናውቅም አዕምሯችን ግን ክስተቶቹ አሁን በዚህ ቅጽበት እየተከናወኑ ያሉ እስከሚመስል ድረስ በጠንካራ አሉታዊ ስሜት ውስጥ እንድንዘፈቅ ያደርገናል። ታዲያ እነዚህ ያለፉ፣ የማይደገሙ ክስተቶች አሁን እየፈጠሩብን ካለው አሉታዊ ስሜት፣ የውሳኔ ውስንነትና፣ ጎታች አመለካከት ተፅዕኖዎች ራሳችንን እንዴት ማላቀቅ እንችላለን?
ይህን ጥያቄ ስናነሳ ብዙዎች “እርሳው ባክህ”፣ ወይም “ለበጎ ነው” ወዘተ የሚል ምላሽ ይሰጡናል። ነገርግን “ያልተነካ ግልግል ያውቃል” ነውና እኛ ነገሩን ማስታወስ ፈልገን ሳይሆን አዕምሯችን ከኛ እውቅና ውጪ እያሳሰበን እንደሆነ ማን ይንገርልን?
እነዚህ በውስጣችን ተሰድረው ማለፋቸው ሳያንስ አሁንም ህይወታችንን ካመሰቃቀሉ ትውስታዎችን ለመፋታት የሚከተሉትን ማድረግ እንችላለን፦
1. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ልንማርባቸው የምንችላቸው ነገሮች ካሉ ወረቀት ላይ በጽሁፍ ማስፈር።
2. እነዚህን ክስተቶች ከንደገና በማስታወስ ጉዳቱን የፈጠሩ ሰዎች ካሉ፣ በወቅቱ የነበረባቸውን የባህርይ፣ ስሜት እና የውሳኔ ውስንነት እንደገና አሁን ባለን መረዳት መመልከት። እነዚህ ውስንነቶች ባይኖሩባቸው ምን ሊያደርጉ ይችሉ እንደነበር ማሰብ፤ እነሱ የነበሩባቸውን ውስንነቶች እኛም ሳናውቅ እያንጸባረቅን እንዳልሆነ ማረጋገጥ።
3. የሚፈጥሩብን ስሜት ከባድ ከሆነና ከላይ ባደረግናቸው ልምምዶች ስሜቶቹንና ግንዛቤያችንን መለወጥ ካቃተን የባለሙያ ርዳታ እንፈልግ።
ዳንኤል አያሌው (Certified NLP Practitioner)
@melkam_enaseb
ምዕናባዊ ኦቲዝም፤ የዲጅታል ዘመን ልጆች ስጋት
ባለሙያዎች እንደሚሉት በተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ በታብሌት፣ በቴሌቪዝን እና በሌሎች ዲጅታል መሳሪያዎች ላይ ረዘም ያለ ጊዜ የሚያሳልፉ ልጆች ለጭንቀት እና ለመረበሽ፣ ለትኩረት ማጣት፣ ለንግግር እና ለቋንቋ መዘግየት እንዲሁም ለግንዛቤ እድገት ውሱንነት ይዳረጋሉ። የሰዎችን ስሜት የመረዳት እና የመግባባት ችሎታቸውንም ይቀንሳል።
በዚህ ዙሪያ #DW ያዘጋጀውን ፅሁፍ ያንብቡ ⬇️
https://p.dw.com/p/4erN2?maca=amh-Facebook-dw
@melkam_enaseb
ባለሙያዎች እንደሚሉት በተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ በታብሌት፣ በቴሌቪዝን እና በሌሎች ዲጅታል መሳሪያዎች ላይ ረዘም ያለ ጊዜ የሚያሳልፉ ልጆች ለጭንቀት እና ለመረበሽ፣ ለትኩረት ማጣት፣ ለንግግር እና ለቋንቋ መዘግየት እንዲሁም ለግንዛቤ እድገት ውሱንነት ይዳረጋሉ። የሰዎችን ስሜት የመረዳት እና የመግባባት ችሎታቸውንም ይቀንሳል።
በዚህ ዙሪያ #DW ያዘጋጀውን ፅሁፍ ያንብቡ ⬇️
https://p.dw.com/p/4erN2?maca=amh-Facebook-dw
@melkam_enaseb
እኛ እራሳችንን እና ሌሎች እኛን ምን ያህል ያውቁናል?
አንዳንድ ግዜ ሰዎች እኔ እራሴን በደንብ አውቀዋለሁ ወይም እከሌን በደንብ አውቀዋለሁ ሲሉ ይደመጣል ነገር ግን የስነ-ባህሪ አጥኚዎች ሰው ራሱንም እንዲሁም ሌሎችን ሙሉ በሙሉ እንደማያውቅ እንደሚከተለው ያስረዱናል።
4ቱ ማንነቶቻችን፦
1. Open- ግልፅ ሆኖ የሚታየው የማንነት ክፍል ሲሆን እኛ ራሳችን እና ሌሎች እኛን የሚያውቁት ግልፅ የሆነው ማንነት ክፍል ነው።
2. Hidden- ድብቅ የሆነው የማንነት ክፍል ሲሆን እኛ ራሳችን የምናውቅው ሌሎች ግን ስለእኛ የማያውቁት ክፍል ነው።
3. Blind- ሰዎች ስለኛ የሚያውቁት እኛ ግን ስለራሳችን የማናውቀው የማንነት ክፍል ነው።
4. Unknown- ሌሎች ሰዎችም ሆኑ እኛ ራሳችን ስለራሳችን የማናውቀው የማንነት ክፍል ነው።
ስለዚህ ከሰዎች ጋር መልካም እና ሚዛናዊ የሆነ ግንኙነት እንዲኖረን ከላይ የተዘረዘሩትን የማንነት ክፍሎች ግምት ውስጥ ማስገባት አስፈላጊ ነው።
ካልሆነ ግን እከሌን አውቀዋለሁ ብለው ሲያስቡ አንድ ቀን ድብቁ/ የማያውቁት ማንነት ሲገለጥ ሊጎዱ ይችላሉ። እንዲሁም ራስዎትን ራሴን በደንብ አውቀዋለሁ በማለት ሌሎች ከሚሰጥዎት ምክር ባለመማር ራስዎትን ከማሳደግ እና ከማሻሻል እንዳይገደቡ ጥንንቃቄ ያድርጉ።
በ መአዛ መንክር (ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት)
@melkam_enaseb
አንዳንድ ግዜ ሰዎች እኔ እራሴን በደንብ አውቀዋለሁ ወይም እከሌን በደንብ አውቀዋለሁ ሲሉ ይደመጣል ነገር ግን የስነ-ባህሪ አጥኚዎች ሰው ራሱንም እንዲሁም ሌሎችን ሙሉ በሙሉ እንደማያውቅ እንደሚከተለው ያስረዱናል።
4ቱ ማንነቶቻችን፦
1. Open- ግልፅ ሆኖ የሚታየው የማንነት ክፍል ሲሆን እኛ ራሳችን እና ሌሎች እኛን የሚያውቁት ግልፅ የሆነው ማንነት ክፍል ነው።
2. Hidden- ድብቅ የሆነው የማንነት ክፍል ሲሆን እኛ ራሳችን የምናውቅው ሌሎች ግን ስለእኛ የማያውቁት ክፍል ነው።
3. Blind- ሰዎች ስለኛ የሚያውቁት እኛ ግን ስለራሳችን የማናውቀው የማንነት ክፍል ነው።
4. Unknown- ሌሎች ሰዎችም ሆኑ እኛ ራሳችን ስለራሳችን የማናውቀው የማንነት ክፍል ነው።
ስለዚህ ከሰዎች ጋር መልካም እና ሚዛናዊ የሆነ ግንኙነት እንዲኖረን ከላይ የተዘረዘሩትን የማንነት ክፍሎች ግምት ውስጥ ማስገባት አስፈላጊ ነው።
ካልሆነ ግን እከሌን አውቀዋለሁ ብለው ሲያስቡ አንድ ቀን ድብቁ/ የማያውቁት ማንነት ሲገለጥ ሊጎዱ ይችላሉ። እንዲሁም ራስዎትን ራሴን በደንብ አውቀዋለሁ በማለት ሌሎች ከሚሰጥዎት ምክር ባለመማር ራስዎትን ከማሳደግ እና ከማሻሻል እንዳይገደቡ ጥንንቃቄ ያድርጉ።
በ መአዛ መንክር (ክሊኒካል ሳይኮሎጂስት)
@melkam_enaseb
የጤና ወግ ዛሬ በቴሌግራም ቀጥታ ስርጭት የመማር እክል በሚል ርዕስ የሚደረገው ውይይት ላይ ይቀላቀሉ።
እንግዶች:
ተባባሪ ኘሮፌሰር አበባየሁ መሰለ (የፋና የተግባቦት እና የመሰረታዊ ትምህርት ድጋፍ መስጫ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች እና ስራ አስኪያጅ)
አቶ ያፌት ከፈለኝ (የአብርሆት ሳይኮቴራፒ ማዕከል መስራች)
የመማር እክሎች የማሰብ ችሎታ ወይም ጥረት ማነስን የሚያመለክቱ አይደሉም።
የበለጠ ለመረዳት ውይይቱን በቀጥታ ይከታተሉ!
🗓 እሁድ ሚያዚያ 13, 2016
⏰ ከምሽቱ 12 ሰዓት (በኢትዮጵያ)
ውይይቱን ለመቀላቀል እዚህ ይጫኑ ⬇️
https://www.tg-me.com/yetenaweg?livestream
@melkam_enaseb
እንግዶች:
ተባባሪ ኘሮፌሰር አበባየሁ መሰለ (የፋና የተግባቦት እና የመሰረታዊ ትምህርት ድጋፍ መስጫ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች እና ስራ አስኪያጅ)
አቶ ያፌት ከፈለኝ (የአብርሆት ሳይኮቴራፒ ማዕከል መስራች)
የመማር እክሎች የማሰብ ችሎታ ወይም ጥረት ማነስን የሚያመለክቱ አይደሉም።
የበለጠ ለመረዳት ውይይቱን በቀጥታ ይከታተሉ!
🗓 እሁድ ሚያዚያ 13, 2016
⏰ ከምሽቱ 12 ሰዓት (በኢትዮጵያ)
ውይይቱን ለመቀላቀል እዚህ ይጫኑ ⬇️
https://www.tg-me.com/yetenaweg?livestream
@melkam_enaseb
ሳይጀመር የተደመደመ ሕይወት!
Fatalistic Attitude
የሚኖሩት ኑሮ አንዴ የተወሰነና ሊለወጥ የማይችል እንደሆነ የሚያስቡ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ ፈረንጆቹ ይህንን አመለካከት fatalistic attitude ይሉታል፡፡ ያለቀለትና ቅድመ-ድምዳሜ ተወስኖለት የተጀመረ ሕይወት እንዳለን ማመንን የሚጠቁም ሃሳብ ነው፡፡
ይህ አይነቱ አመለካከት ያላቸው ሰዎች በሕይወታቸው ያለውን ምንም ነገር ለመቀየር አቅሙ እንደሌላቸው ነው የሚያስቡት፡፡ የወቅቱ ኑሯቸው ሁኔታ ለእነሱ የተመደበና ምንም ቢታገሉ ሊለወጥ እንደማይችል ያስባሉ። ስለዚህም የነበረውንና ያለውን በመቀበል ያዘግማሉ፡፡
እንደዚህ አይነት ሰዎች በዙሪያቸው ብዙ ሰዎች በማለም፣ በመስራትና በማመን ሕይወታቸውን ሲለውጡ እያዩ እንኳን ንቅንቅ አይሉም፡፡ ምክንያቱም እነዚያኞቹ በሕይወታቸው የሚያዩት ለውጥም ሳይቀር ቀድሞውኑ ለእነሱ የተወሰነላቸው እንደሆነ ስለሚስቡ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ራስን ለማሻሻል ምንም አይነት መነሳሳት ስለማይኖራቸው የመጣላቸውን እየተቀበሉና ያንኑ እየኖሩ ዘመናቸውን ይጨርሳሉ፡፡
ሕይወት ግን እንደዚያ አይደለችም፡፡ ሕይወት የምርጫ መስክ ነች፡፡ ሕይወት የዘራነውን የምናበቅልባት መሬት ነች፡፡ ሕይወት ፈቃዳችንን፣ ጉልበታችንንና ሌሎችንም እሴቶቻችንን አስተባብረን ከአንድ ደረጃ ወደሌላኛው ደረጃ እንደመሰላል የምንወጣት የምታጓጓ መስክ ናት እንጂ ታሪካቸው ተጽፎና አልቆ ያከተመለትና ፍጻሜ የተበየነባቸው ሰዎች መተራመሻ አይደለችም።
(ዶ/ር እዮብ ማሞ)
@melkam_enaseb
Fatalistic Attitude
የሚኖሩት ኑሮ አንዴ የተወሰነና ሊለወጥ የማይችል እንደሆነ የሚያስቡ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ ፈረንጆቹ ይህንን አመለካከት fatalistic attitude ይሉታል፡፡ ያለቀለትና ቅድመ-ድምዳሜ ተወስኖለት የተጀመረ ሕይወት እንዳለን ማመንን የሚጠቁም ሃሳብ ነው፡፡
ይህ አይነቱ አመለካከት ያላቸው ሰዎች በሕይወታቸው ያለውን ምንም ነገር ለመቀየር አቅሙ እንደሌላቸው ነው የሚያስቡት፡፡ የወቅቱ ኑሯቸው ሁኔታ ለእነሱ የተመደበና ምንም ቢታገሉ ሊለወጥ እንደማይችል ያስባሉ። ስለዚህም የነበረውንና ያለውን በመቀበል ያዘግማሉ፡፡
እንደዚህ አይነት ሰዎች በዙሪያቸው ብዙ ሰዎች በማለም፣ በመስራትና በማመን ሕይወታቸውን ሲለውጡ እያዩ እንኳን ንቅንቅ አይሉም፡፡ ምክንያቱም እነዚያኞቹ በሕይወታቸው የሚያዩት ለውጥም ሳይቀር ቀድሞውኑ ለእነሱ የተወሰነላቸው እንደሆነ ስለሚስቡ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ራስን ለማሻሻል ምንም አይነት መነሳሳት ስለማይኖራቸው የመጣላቸውን እየተቀበሉና ያንኑ እየኖሩ ዘመናቸውን ይጨርሳሉ፡፡
ሕይወት ግን እንደዚያ አይደለችም፡፡ ሕይወት የምርጫ መስክ ነች፡፡ ሕይወት የዘራነውን የምናበቅልባት መሬት ነች፡፡ ሕይወት ፈቃዳችንን፣ ጉልበታችንንና ሌሎችንም እሴቶቻችንን አስተባብረን ከአንድ ደረጃ ወደሌላኛው ደረጃ እንደመሰላል የምንወጣት የምታጓጓ መስክ ናት እንጂ ታሪካቸው ተጽፎና አልቆ ያከተመለትና ፍጻሜ የተበየነባቸው ሰዎች መተራመሻ አይደለችም።
(ዶ/ር እዮብ ማሞ)
@melkam_enaseb
የካርል ዩንግ ጥልቅ የፍልስፋና እና ሥነልቦናዊ ንግግሮች!
1. ”ባንተ በራስህ ውስጥ ያለዉን ጨለማ ማወቅ በሌሎች ጨለማ ላይ ለመስራት መንገዱን ይጠርግልሀል”
2. ”ንቁ ባልሆነዉ የአእምሮህ ክፍል ተቀምጠው ባንተ ላይ ተፅኖ የሚያደርጉትን ሀሳቦች ንቁ ወደ ሆነዉ ክፍል እስካላመጣህ ድረስ እነሱም አንተን መምራታቸው አንተም እጣፈንታዬ ነው እያልክ መኖርህ ይቀጥላል”
3. ”መልካም ነገሮችን ይዘዋል እና በህይወትህ ከባድ እና የሚገዳደሩ ነገሮችን አመስግን በእዉነታዉ ለጤናማ እድገት፣ ራስን ለመሆን እና እውነተኛው እኛነታችን ላይ ለመድረስ ተግዳሮት አስፈላጊ ነው“
4. ”የትኛዉም የምታገኘዉ ሰው አንተ የማታቀዉ የሆነ ነገር ያውቃል ስለሆነም ሁሌም ለማወቅ ጉጉት ይኑርህ ከነሱም ተማር”
5. ”እኔ ለመሆን የመረጥኩትን እንጂ በኔ ላይ የሆነብኝ ነገር ውጤት አይደለሁም”
6. “ዓለም ስለማንነትህ በሚጠይቅህ ግዜ ማን እንደሆንክ ካላወክ በምላሹ ዓለም በራሱ ስለአንተ ይነግርሀል"
7. “አንድ ሰው ይበልጥ ባወቀ ቁጥር ብቸኛ እየሆነ ይመጣል”
8. “በሌሎች ላይ አይተነው የሚያስቆጣን ነገር ሁሉ አራሳችንን እንድንረዳ መንገድ ይመራናል”
9. ”ህይወት የእውነት የሚጀመረው ከአርባ ዓመት በኃላ ነው እስከዛ በነበረው እየኖርክ ሳይሆን ጥናት እያደረግክ ነው”
10. ”አንተነትህ የሚገለፀዉ በድርጊትህ እንጂ በምታወራው አይደለም እና አድርገው”
ፍ/ማርያም ተስፋዬ (የሥነልቦና ባለሙያ )
@melkam_enaseb
1. ”ባንተ በራስህ ውስጥ ያለዉን ጨለማ ማወቅ በሌሎች ጨለማ ላይ ለመስራት መንገዱን ይጠርግልሀል”
2. ”ንቁ ባልሆነዉ የአእምሮህ ክፍል ተቀምጠው ባንተ ላይ ተፅኖ የሚያደርጉትን ሀሳቦች ንቁ ወደ ሆነዉ ክፍል እስካላመጣህ ድረስ እነሱም አንተን መምራታቸው አንተም እጣፈንታዬ ነው እያልክ መኖርህ ይቀጥላል”
3. ”መልካም ነገሮችን ይዘዋል እና በህይወትህ ከባድ እና የሚገዳደሩ ነገሮችን አመስግን በእዉነታዉ ለጤናማ እድገት፣ ራስን ለመሆን እና እውነተኛው እኛነታችን ላይ ለመድረስ ተግዳሮት አስፈላጊ ነው“
4. ”የትኛዉም የምታገኘዉ ሰው አንተ የማታቀዉ የሆነ ነገር ያውቃል ስለሆነም ሁሌም ለማወቅ ጉጉት ይኑርህ ከነሱም ተማር”
5. ”እኔ ለመሆን የመረጥኩትን እንጂ በኔ ላይ የሆነብኝ ነገር ውጤት አይደለሁም”
6. “ዓለም ስለማንነትህ በሚጠይቅህ ግዜ ማን እንደሆንክ ካላወክ በምላሹ ዓለም በራሱ ስለአንተ ይነግርሀል"
7. “አንድ ሰው ይበልጥ ባወቀ ቁጥር ብቸኛ እየሆነ ይመጣል”
8. “በሌሎች ላይ አይተነው የሚያስቆጣን ነገር ሁሉ አራሳችንን እንድንረዳ መንገድ ይመራናል”
9. ”ህይወት የእውነት የሚጀመረው ከአርባ ዓመት በኃላ ነው እስከዛ በነበረው እየኖርክ ሳይሆን ጥናት እያደረግክ ነው”
10. ”አንተነትህ የሚገለፀዉ በድርጊትህ እንጂ በምታወራው አይደለም እና አድርገው”
ፍ/ማርያም ተስፋዬ (የሥነልቦና ባለሙያ )
@melkam_enaseb
ጥናት!
ተመራማሪዎች በቀን ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችንን አቅም ለማሳገድ እንደሚረዳ አስታወቁ።
አዲስ የተሰራ የኒውሮሳይንስ ጥናት እንዳመለከተው ከሆነ ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችን አዲስ መረጃ ለመውሰድና ለመያዝ እንዲዘጋጅ ያደርገዋል።
በተለይም ውሳኔ ለመስጠት፣ ጭንቀትን ለመቆጣጠርና፣ በባህሪያችን ዙሪያ የሚያቅደው የአእምሯችን ክፍል ላይ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ነው ተመራማሪዎች ያስታወቁት።
ሌሎች አይነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች የአዕምሮ ጤናን ለመጠበቅ እንደሚረዱ የሚታወቅ ቢሆንም፤ ይህኛው ጥናት ግን የግር ጉዞ እና የአእምሮ አቅም ላይ ትኩረትን ያድረገ እንደሆነም አስታውቀዋል።
በዚህም በቀን ለ20 ደቂቃ እና ከዚያ በላይ የእግር ጉዞ ማድረግ የአእምሮን አቅም እንደሚያሳድግ እና ምንም እንቅስቃሴ ካለማድረግ የተወሰነ የእግር ጉዞ ማድረግ እንደሚሻልም ጥናቱ አመላክቷል።
የሳንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ጥናቱን ባከናወኑበት ወቅት ተሳታፊዎች የእግር ጉዞ የሚያደርጉ እና የማያደርጉትን በመለየት ክትትል ያደረጉ ሲሆን፤ በዚህም ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ተቀምጠው ከሚውሉት የተሻለ ሆነው ተገኝተዋል።
ተመራማሪዎች የአእምሮ እንቅስቃሴን በኤሌክትሮኤንሴፋሎግራፊ (ኢኢጂ) መለካት ምን እየተፈጠረ እንዳለ የተመለከቱ ሲሆን፤ በዚህም የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ላይ ተጨባጭ እና አወንታዊ ተፅእኖዎችን አይተዋል።
Via: Alain
@melkam_enaseb
ተመራማሪዎች በቀን ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችንን አቅም ለማሳገድ እንደሚረዳ አስታወቁ።
አዲስ የተሰራ የኒውሮሳይንስ ጥናት እንዳመለከተው ከሆነ ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችን አዲስ መረጃ ለመውሰድና ለመያዝ እንዲዘጋጅ ያደርገዋል።
በተለይም ውሳኔ ለመስጠት፣ ጭንቀትን ለመቆጣጠርና፣ በባህሪያችን ዙሪያ የሚያቅደው የአእምሯችን ክፍል ላይ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ነው ተመራማሪዎች ያስታወቁት።
ሌሎች አይነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች የአዕምሮ ጤናን ለመጠበቅ እንደሚረዱ የሚታወቅ ቢሆንም፤ ይህኛው ጥናት ግን የግር ጉዞ እና የአእምሮ አቅም ላይ ትኩረትን ያድረገ እንደሆነም አስታውቀዋል።
በዚህም በቀን ለ20 ደቂቃ እና ከዚያ በላይ የእግር ጉዞ ማድረግ የአእምሮን አቅም እንደሚያሳድግ እና ምንም እንቅስቃሴ ካለማድረግ የተወሰነ የእግር ጉዞ ማድረግ እንደሚሻልም ጥናቱ አመላክቷል።
የሳንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ጥናቱን ባከናወኑበት ወቅት ተሳታፊዎች የእግር ጉዞ የሚያደርጉ እና የማያደርጉትን በመለየት ክትትል ያደረጉ ሲሆን፤ በዚህም ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ተቀምጠው ከሚውሉት የተሻለ ሆነው ተገኝተዋል።
ተመራማሪዎች የአእምሮ እንቅስቃሴን በኤሌክትሮኤንሴፋሎግራፊ (ኢኢጂ) መለካት ምን እየተፈጠረ እንዳለ የተመለከቱ ሲሆን፤ በዚህም የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ላይ ተጨባጭ እና አወንታዊ ተፅእኖዎችን አይተዋል።
Via: Alain
@melkam_enaseb