Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1000046305
<unknown>
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1000046304
<unknown>
ይህ ግጥም ብዙ Like ካገኘ በድምፅ እና በፅሑፍ እንቀጥላለን
ነበርኩ_መች_ያድናል
@ort_poem @ort_poem
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!
Like 👍 አድርጉ ቤተሰብ 👍
ነበርኩ_መች_ያድናል
@ort_poem @ort_poem
ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!
Like 👍 አድርጉ ቤተሰብ 👍
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1000046993
<unknown>
ይህ ግጥም ብዙ Like ካገኘ በድምፅ እና በፅሑፍ እንቀጥላለን
ምስክር ነኝ አኔ
@ort_poem
ምስክር ነኝ አኔስ ሳለሁ በህይወቴ
ኦርቶዶክስ ነችና አንዲቷ እምነቴ
ከጥንት አባቶቼ የዘረስኳት ማንነቴ
ተዋህዶ ነችና የዘለዓለም ቤቴ
ሀጢያትን ሰርቼ ብዙ በድያለሁ
ትዕዛዙንም ጥሼ ሰውንም ንቄያለሁ
አንድ ተስፋ እንዳለኝ አሁን አውቄያለሁ
ስታመም ድኜበት ስቸገር አግኝቼ ሳዝንም ተደስቼ መጥቻለሁና ሁሉንም አግኝቼ
የጎደለው ሞልቷል ወደ አንቺ መጥቼ
ዛሬን መስክሬያለው ሁሉንም አይቼ
ነፅቻለሁና ንስሀ ገብቼ
ለስጋ ወደሙ ክብርም በቃሁኝ
ሰላም የሞላበት ህይወትን አየሁኝ
በተዋህዶ ዕምነቴ ክብር አገኘሁኝ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Like 👍 አድርጉ ቤተሰብ 👍
✍️@Diriba_16
ምስክር ነኝ አኔ
@ort_poem
ምስክር ነኝ አኔስ ሳለሁ በህይወቴ
ኦርቶዶክስ ነችና አንዲቷ እምነቴ
ከጥንት አባቶቼ የዘረስኳት ማንነቴ
ተዋህዶ ነችና የዘለዓለም ቤቴ
ሀጢያትን ሰርቼ ብዙ በድያለሁ
ትዕዛዙንም ጥሼ ሰውንም ንቄያለሁ
አንድ ተስፋ እንዳለኝ አሁን አውቄያለሁ
ስታመም ድኜበት ስቸገር አግኝቼ ሳዝንም ተደስቼ መጥቻለሁና ሁሉንም አግኝቼ
የጎደለው ሞልቷል ወደ አንቺ መጥቼ
ዛሬን መስክሬያለው ሁሉንም አይቼ
ነፅቻለሁና ንስሀ ገብቼ
ለስጋ ወደሙ ክብርም በቃሁኝ
ሰላም የሞላበት ህይወትን አየሁኝ
በተዋህዶ ዕምነቴ ክብር አገኘሁኝ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Like 👍 አድርጉ ቤተሰብ 👍
✍️@Diriba_16
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Audio
እርሱ ብቻ የማይሞተው ነው
@ORTHO_mezmure
እርሱ ብቻ የማይሞት ነው
በብርሃን የሚኖር ነው
በአባቱ ቀኝ አለ ነግሦ
አማኑኤል ክብርን ለብሶ(*2)
አዝ<><>
ትላንትናን ዛሬን ውጧል
ሁሉም ነገር ይለወጣል
ሳይደበዝዝ የሚያበራ
ሁሌም ጽኑ የእርሱ ስራ
አዝ<><>
የአይሁድ ትግል ያልነቀለው
ክፋታቸው ያልሸፈነው
የደም ሐውልት ምሰሷችን
በእርሱ ጸንቷል ከፍታችን
አዝ<><>
የዓለም ጀግኖች ተቀብረዋል
የበረቱ ተሰብረዋል
ገዳዩን ሞት የገደለ
እንደ ጌታ ወዴት አለ?
አዝ<><>
መቃብርን የቀበረ
ኃይለኛውን የሰበረ
ኢየሱስ ነው ጽኑ ጌታ
ማይሸነፍ ማይረታ
@ORTHO_mezmure
እርሱ ብቻ የማይሞት ነው
በብርሃን የሚኖር ነው
በአባቱ ቀኝ አለ ነግሦ
አማኑኤል ክብርን ለብሶ(*2)
አዝ<><>
ትላንትናን ዛሬን ውጧል
ሁሉም ነገር ይለወጣል
ሳይደበዝዝ የሚያበራ
ሁሌም ጽኑ የእርሱ ስራ
አዝ<><>
የአይሁድ ትግል ያልነቀለው
ክፋታቸው ያልሸፈነው
የደም ሐውልት ምሰሷችን
በእርሱ ጸንቷል ከፍታችን
አዝ<><>
የዓለም ጀግኖች ተቀብረዋል
የበረቱ ተሰብረዋል
ገዳዩን ሞት የገደለ
እንደ ጌታ ወዴት አለ?
አዝ<><>
መቃብርን የቀበረ
ኃይለኛውን የሰበረ
ኢየሱስ ነው ጽኑ ጌታ
ማይሸነፍ ማይረታ
ጾመ ሐዋርያት/የሰኔ ጾም
ጾመ ሐዋርያት ሐዋርያት በጽራሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመግባታቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ከመበተናቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ የጾሙበትም ምክንያት በማርቆስ ፪፥፳ እና በማቴወስ ፱፥፲፬ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን መሰረት በማድረግ ነው፡፡
ይኸውም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳዊያን ብዙ ጊዜ የምንጾመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጾሙት ስለ ምንድን ነው? አሉት፡፡ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡-ሚዜወች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ፡፡››ብሎ እንደመለሰላቸው፡፡
በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ሙሽራ የተባለው ካባ በመደረብ ፈንታ ዕርቃኑን ሆኖ በአክሊል ፈንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ በሚዜወቹ ፈንታ በጠላት ተከቦ በመዝሙርና በደስታ ፈንታ በልቅሶና በዋይታ ታጂቦ በክብር ዙፋን መቀመጥ ፈንታ በመስቀል ተሰቅሎ በጭንካር ተወጥሮ በቀራንይዎ አደባባይ ስለ እኛ የተሞሸረው/የተሰቀለው/ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
ሚዜዎቹ የተባሉት ደግሞ ምንም እንኳን በሰርጉ እለት ከአንዱ በቀር (ከወንጌላዊ ዮሐንስ/ ከጎኑ ባይገኙም ኋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው በሕይወትም በሞትም ሙሽራውን/ኢየሱስ ክርስቶስን/ የመሰሉ ሐዋርያት ናቸው፡፡
ይወሰዳል መባሉም እርገቱን ለመናገር ሲሆን ከዚያ በኋላ ይጾማሉ መባላቸው ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያርግ መንፈስ ቅዱስ ይመጣልና፡፡ በዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ጉዳይ ጾም በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ በሐዲስ ኪዳንም የቀጠለ ሥርዓት መሆኑን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረ ስለመሆኑ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት እና አይሁድ ብዙ ጊዜ ይጾሙ እንደነበረ ተጽፏል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት"እናንተና አይሀድ የጾማችሁት ባለማወቅ ወይም በስህተት ስለሆነ ደቀ መዛሙርቴ አይጾሙም" አላለም፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ከእኔ ጋር ናቸው ደስ ሊላቸው ይገባል፡፡ ከሄድኩ በኋላ ግን ይጾማሉ ብሏል፡፡ ይኸውም ጾም ከአዳም ጀምሮ እስከ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና ደቀ መዛሙርቱ ከዚያም በክርስቶስ ታድሶና ተቀድሶ ለደቀ መዛሙርቱ የተሰጠ ከዚያም ለእኛ ለተከታይዮቻቸው የተላለፈ ሥርዓት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ለጊዜው ሐዋርያት ሊጾሙበት ያልቻሉበት ምክንት ሊቃውንት ሲያብራሩ ፡-አንደኛ ጾም ሐዘን ነውና ሐዘኑም ኃላፊነትን ከመሸከም ጋር ተያያዥነት ያለው ነውና፡፡ ምክናያቱም መጾም አላማው ንስሐ እንደመሆኑ እንደ ቅዱስ ዳዊት ለግል ኃጢያት አሊያም እንደነነዌ ሰዎች ስለሀገር ጥፋት የሚያለቅሱበት የሚያዝኑበት ሁኔታ አለው፡፡ ክርስቶስ ደግሞ በስጋው ወራት ከአምላክነቱና ከሁሉ አባትነቱ ባሻገር ለሐዋርይት እንደ ሥጋ አባትም ወንድምም በመሆን የእነርሱን ኃላፊነት ተሸክሞላቸዋልና እርሱ በአካለ ሥጋ በአጠገባቸው እስካለ ድረስ ማዘን አልተገባቸውም፡፡
በሁለተኛነት ደግሞ ጾም ኃላፊነት ነው፡፡ኃላፊነቱን ለመሸከም ደግሞ ኃይል የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋቸው ነበርና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ እንዲጾሙ ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ሦስተኛው ምክነያት አይሁድ ይጾሙት የነበረው በብሉይ ኪዳን ስርዓት ውስጥ ሆነው ነበር፡፡ ሐዋርያት ደግሞ የሐዲስ ኪዳን ልጆች ስለሆኑ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው አሊያም አዲሱ ሰው በተባለው በክርስቶስ ደም ተጽናንተውና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው አዲሱን ሰው ለብሰው በአዲስ መንፈስና ኃይል በአዲስ ስርዓት መጾም ስለነበረባቸው በጊዜው አልጾሙም ነበር፡፡/ማቴ ፱፥፲፮-፲፯/
ይቀጥላል
ጾመ ሐዋርያት ሐዋርያት በጽራሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ወደ አገልግሎት ከመግባታቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ከመበተናቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው፡፡ የጾሙበትም ምክንያት በማርቆስ ፪፥፳ እና በማቴወስ ፱፥፲፬ ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን መሰረት በማድረግ ነው፡፡
ይኸውም የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው እኛና ፈሪሳዊያን ብዙ ጊዜ የምንጾመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጾሙት ስለ ምንድን ነው? አሉት፡፡ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡-ሚዜወች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ፡፡››ብሎ እንደመለሰላቸው፡፡
በዚህ ምሳሌያዊ አነጋገር ሙሽራ የተባለው ካባ በመደረብ ፈንታ ዕርቃኑን ሆኖ በአክሊል ፈንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ በሚዜወቹ ፈንታ በጠላት ተከቦ በመዝሙርና በደስታ ፈንታ በልቅሶና በዋይታ ታጂቦ በክብር ዙፋን መቀመጥ ፈንታ በመስቀል ተሰቅሎ በጭንካር ተወጥሮ በቀራንይዎ አደባባይ ስለ እኛ የተሞሸረው/የተሰቀለው/ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
ሚዜዎቹ የተባሉት ደግሞ ምንም እንኳን በሰርጉ እለት ከአንዱ በቀር (ከወንጌላዊ ዮሐንስ/ ከጎኑ ባይገኙም ኋላ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው በሕይወትም በሞትም ሙሽራውን/ኢየሱስ ክርስቶስን/ የመሰሉ ሐዋርያት ናቸው፡፡
ይወሰዳል መባሉም እርገቱን ለመናገር ሲሆን ከዚያ በኋላ ይጾማሉ መባላቸው ደግሞ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ኢየሱስ ሲያርግ መንፈስ ቅዱስ ይመጣልና፡፡ በዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን ጉዳይ ጾም በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ በሐዲስ ኪዳንም የቀጠለ ሥርዓት መሆኑን ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበረ ስለመሆኑ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት እና አይሁድ ብዙ ጊዜ ይጾሙ እንደነበረ ተጽፏል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት"እናንተና አይሀድ የጾማችሁት ባለማወቅ ወይም በስህተት ስለሆነ ደቀ መዛሙርቴ አይጾሙም" አላለም፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ከእኔ ጋር ናቸው ደስ ሊላቸው ይገባል፡፡ ከሄድኩ በኋላ ግን ይጾማሉ ብሏል፡፡ ይኸውም ጾም ከአዳም ጀምሮ እስከ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና ደቀ መዛሙርቱ ከዚያም በክርስቶስ ታድሶና ተቀድሶ ለደቀ መዛሙርቱ የተሰጠ ከዚያም ለእኛ ለተከታይዮቻቸው የተላለፈ ሥርዓት መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ለጊዜው ሐዋርያት ሊጾሙበት ያልቻሉበት ምክንት ሊቃውንት ሲያብራሩ ፡-አንደኛ ጾም ሐዘን ነውና ሐዘኑም ኃላፊነትን ከመሸከም ጋር ተያያዥነት ያለው ነውና፡፡ ምክናያቱም መጾም አላማው ንስሐ እንደመሆኑ እንደ ቅዱስ ዳዊት ለግል ኃጢያት አሊያም እንደነነዌ ሰዎች ስለሀገር ጥፋት የሚያለቅሱበት የሚያዝኑበት ሁኔታ አለው፡፡ ክርስቶስ ደግሞ በስጋው ወራት ከአምላክነቱና ከሁሉ አባትነቱ ባሻገር ለሐዋርይት እንደ ሥጋ አባትም ወንድምም በመሆን የእነርሱን ኃላፊነት ተሸክሞላቸዋልና እርሱ በአካለ ሥጋ በአጠገባቸው እስካለ ድረስ ማዘን አልተገባቸውም፡፡
በሁለተኛነት ደግሞ ጾም ኃላፊነት ነው፡፡ኃላፊነቱን ለመሸከም ደግሞ ኃይል የሚሆናቸው መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋቸው ነበርና መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ እንዲጾሙ ጊዜ ሰጣቸው፡፡ ሦስተኛው ምክነያት አይሁድ ይጾሙት የነበረው በብሉይ ኪዳን ስርዓት ውስጥ ሆነው ነበር፡፡ ሐዋርያት ደግሞ የሐዲስ ኪዳን ልጆች ስለሆኑ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው አሊያም አዲሱ ሰው በተባለው በክርስቶስ ደም ተጽናንተውና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው አዲሱን ሰው ለብሰው በአዲስ መንፈስና ኃይል በአዲስ ስርዓት መጾም ስለነበረባቸው በጊዜው አልጾሙም ነበር፡፡/ማቴ ፱፥፲፮-፲፯/
ይቀጥላል
ብዙ ሳይጣጣር
እምብዛም ሳይለፋ
ከዓይን የራቀ
ከምናብ የሰፋ
ይህን ዓለም ሠራ
ያለ ጭንቀት ጥበት
ሆነለት “ሁን” ሲለው
እንዲሁ በዘበት
…
ሕዋውን በሙሉ
ግዑዙን ተፈጥሮ
በቃሉ ትዕዛዝ
እንዲህ አሳምሮ
ለድንጋዩ ራርቶ
የንብ መንጋ መርቶ
አበባን አፍክቶ
ወፊቱን አብልቶ
…
እኔ ትንሽ ነገር
ከሕይወት ቢጨንቀኝ
አደራህን ብለው
“እሺ ቆይ” እያለ
ይህን ሁሉ ዓመት
የሚያጠባብቀኝ
እንዴት ብከብደው ነው
ወይ እንዴት ቢንቀኝ ?
….
By henok bekele
እምብዛም ሳይለፋ
ከዓይን የራቀ
ከምናብ የሰፋ
ይህን ዓለም ሠራ
ያለ ጭንቀት ጥበት
ሆነለት “ሁን” ሲለው
እንዲሁ በዘበት
…
ሕዋውን በሙሉ
ግዑዙን ተፈጥሮ
በቃሉ ትዕዛዝ
እንዲህ አሳምሮ
ለድንጋዩ ራርቶ
የንብ መንጋ መርቶ
አበባን አፍክቶ
ወፊቱን አብልቶ
…
እኔ ትንሽ ነገር
ከሕይወት ቢጨንቀኝ
አደራህን ብለው
“እሺ ቆይ” እያለ
ይህን ሁሉ ዓመት
የሚያጠባብቀኝ
እንዴት ብከብደው ነው
ወይ እንዴት ቢንቀኝ ?
….
By henok bekele
---
የአብስራ ሳሙኤል
*・꙳・꙳・꙳・꙳・・*
እጠራሀለው
በስምህ አቤት በለኝ ከሰማኀው
"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልከው
ከፀሀይ ጀርባ ምን አለ?
ከህይወት አድማስ ባሻገር
ሞት የህይወት ፍጻሜ ነው?
ወይስ ድልድይ የሚሻገር?
አላዛር ያኔ ቢጠየቅ
የሞተ ግዜ የት ነበር?
ወዴት ነው
የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ነው መጠናቀቂያው?
ነፍሴን የማጽናናበት
ምኞቴን የምዳኝበት
ምን አለ ከጸሀይ ጀርባ?
ወዴት ነው ነፍሴ የምትሸሸው?
ይብቃህ እረፍ ተብዬ
የስቃይ ቀኔ የሚያመሸው
አውቃለሁ እንደ ነገርከኝ
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ
ማ? በለኝና ማን ልመን
ብዙ ነው ስምና ገጽህ
*"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር・・・ራባይ*
―☾―
አየሁኝ
እውር አንበሣን
አንካሳ ነብር ሲመራው
እንዲህ ነው መንግስት የሚዘልቅ
እንዲህ ነው ፍጡር የሚመራው
ካልተማመነ
መንገዱን በነብር አይን ተረድቶ
መጠራጠር ይገላል
አንዱን ከአንዱ አባልቶ
ይኀው ነው የነፍሴ ጣሯ
አታምነኝ ወይም አላምናት
ማ? በለኝና ማን ልበል
በየቱ ቃልህ ላባብላት
ማመን ነው
የተስፋ ምርኩዝ
መከተል የአይኑ ብርሀን
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ይሆን የመራኀን?
―✦―
እጠራሀለው
በስም አቤት በለኝ ከሰማኀው
ጠይቁ ብለህ አልነበር
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልኀው
ከጸሀይ ጀርባ ምን አለ?
ኦና'ነት ወይ ፍጻሜ
የት ይሆን ጅምር መቋጫው?
ስንት ይሆን የመኖር እድሜ?
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ነው መጠናቀቂያው?
አውቃለሁ
እንደ ነገርከኝ
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ
ማ? በለኝና ማን ልመን
ብዙ ነው ስምና ገጽህ
የአብስራ ሳሙኤል
*・꙳・꙳・꙳・꙳・・*
እጠራሀለው
በስምህ አቤት በለኝ ከሰማኀው
"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልከው
ከፀሀይ ጀርባ ምን አለ?
ከህይወት አድማስ ባሻገር
ሞት የህይወት ፍጻሜ ነው?
ወይስ ድልድይ የሚሻገር?
አላዛር ያኔ ቢጠየቅ
የሞተ ግዜ የት ነበር?
ወዴት ነው
የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ነው መጠናቀቂያው?
ነፍሴን የማጽናናበት
ምኞቴን የምዳኝበት
ምን አለ ከጸሀይ ጀርባ?
ወዴት ነው ነፍሴ የምትሸሸው?
ይብቃህ እረፍ ተብዬ
የስቃይ ቀኔ የሚያመሸው
አውቃለሁ እንደ ነገርከኝ
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ
ማ? በለኝና ማን ልመን
ብዙ ነው ስምና ገጽህ
*"ጠይቁ?" ብለህ አልነበር・・・ራባይ*
―☾―
አየሁኝ
እውር አንበሣን
አንካሳ ነብር ሲመራው
እንዲህ ነው መንግስት የሚዘልቅ
እንዲህ ነው ፍጡር የሚመራው
ካልተማመነ
መንገዱን በነብር አይን ተረድቶ
መጠራጠር ይገላል
አንዱን ከአንዱ አባልቶ
ይኀው ነው የነፍሴ ጣሯ
አታምነኝ ወይም አላምናት
ማ? በለኝና ማን ልበል
በየቱ ቃልህ ላባብላት
ማመን ነው
የተስፋ ምርኩዝ
መከተል የአይኑ ብርሀን
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ይሆን የመራኀን?
―✦―
እጠራሀለው
በስም አቤት በለኝ ከሰማኀው
ጠይቁ ብለህ አልነበር
እጠይቃለሁ አንተ እንዳልኀው
ከጸሀይ ጀርባ ምን አለ?
ኦና'ነት ወይ ፍጻሜ
የት ይሆን ጅምር መቋጫው?
ስንት ይሆን የመኖር እድሜ?
ወዴት ነው የመኖር ማብቂያው?
ወዴት ነው መጠናቀቂያው?
አውቃለሁ
እንደ ነገርከኝ
ብረዳም ከድርሳን ቅጽህ
ማ? በለኝና ማን ልመን
ብዙ ነው ስምና ገጽህ
መቼ ነው አንድ ቀን ??
===============
ስንጠጋው ሚሸሽ
ስንቀርበው ሚርቀን
ዕድሜያችንን ሁሉ
ስንኖር ሚናፍቀን
በተስፋ ጠቅልለው ይመጣል የሚሉን
መቼ ነው ' አንድ ቀን ' ??
===============
ስንጠጋው ሚሸሽ
ስንቀርበው ሚርቀን
ዕድሜያችንን ሁሉ
ስንኖር ሚናፍቀን
በተስፋ ጠቅልለው ይመጣል የሚሉን
መቼ ነው ' አንድ ቀን ' ??
ቤትሽ ግድግዳ ላይ
አስቱ✍️
ለእናታቹ 🥰
ቤትሽ ግድግዳ ላይ
ማርያም ልጇን አቅፋ ምትታየው ምስል
ለምን አንደሆነ እንጃ
ቁርጥ እራስሽን አንቺን ስትመስል
[እርግጥ ነው]
እርግጥ ነው ከአናትሽ
የንግስና ተምሳል ዘውድ አልተደፋም
እርግጥ ነው ፀዳልሽ
እንደ እመቤታችን በፍፁም አልፋፋም
ውብ አለባበሷ
ካንቺ ብጫቂ ጨርቅ እየተጣመረ
ድኩም አምሮዬ
ምስጢር ስጦታሽን አየመረመረ
(እአየመዘመረ)
የመለኮት ሀይልሽ
የቱ ጋር እንዳለ ላይገባኝ ቢቀርም
ቤትሽ ግድግዳ ላይ ያለቺውን ማርያም
ሁሌ እንደምትመስይ አልጠራጠርም
ተመልከቻት እሷን
በሀለት እጆቿ ንጉሱን ታቅፋ
ስለክብሩ ብላ አንገቷን ስትደፋ
ተመልከቺ ልጇን
ከበግ ስር እንዳለ ብላቴና ግልገል
ከጡት አፈትልኮ
ከእናት ስር አምልጦ ለመሮጥ ሲታገል
ሁሌም ልሂድ ሲላት አትሂድ ትላለች
እናቱ ናትና ከሄደ በሗላ
ምን እንደሚገጥመው ቀድማ ታውቀዋለች
(አየሽ እኔም ልጅሽ)
የማይጨብጠው ተስፋዬን ጨበጬ
አትሂድ ከሚለኝ ከእቅፍሽ አምልጬ
ግብሬን ሁሉ ስቼ
አንቺን እረስቼ
ያሰርሺልኝ እውነት ማህተመ ከላላ
ስንት ጊዜ ሆነው ስንት ጊዜ ሞላ
አየሽ እኔ ልጅሽ
በኖርኩት ዘመኔ
ልጄ ሆይ ያለችን እንቴን ያልረዳሁ
እምነት የጎደለኝ
ትንቢቴን የፈራሁ ቤቴን ያልተረዳሁ
እዳዬን ፈርቼ
ስቃዬን ፈርቼ መስቀል እየሸሸሁ
በጉብዝናዬ ወር
ቀሽም ቀን ሳሳልፍ ስንት ግዜ አመሸሁ
አየሽ አይደል እማ
ከንቱነት ነው ለካ
እናቱን ማያምን እናቱን ማይሰማ
እውነትም እኔ ነኝ
መንገድም እኔው ነኝ ለራሴ እንዳላልኩኝ
መሄጃው ሲጠፋኝ
አማላጅ ፍለጋ ከእቅፍሽ ላይ ዋልኩኝ
መገመት የሚከብድ ለሀሳብ የረቀቀ
መፍረድ የማይችል ሆድ ክክፋት የራቀ
በዚህ ሁሉ ሽሽት በዚህ ሁሉ ምሽት
እንዴት አልተቆጣ እንዴት አልረገመኝ
እውነት እማማዬ ማርያምን ነው ምልሽ
እቅፍሽ ገረመኝ
ቤትሽ ግድግዳ ላይ
ማርያም ልጇን አቅፋ ምትታየው ምስል
ለምን አነደሆነ እንጃ
ቁርጥ እራስሽን አንቺን ስትመስል
አስቱ✍️
ለእናታቹ 🥰
ቤትሽ ግድግዳ ላይ
ማርያም ልጇን አቅፋ ምትታየው ምስል
ለምን አንደሆነ እንጃ
ቁርጥ እራስሽን አንቺን ስትመስል
[እርግጥ ነው]
እርግጥ ነው ከአናትሽ
የንግስና ተምሳል ዘውድ አልተደፋም
እርግጥ ነው ፀዳልሽ
እንደ እመቤታችን በፍፁም አልፋፋም
ውብ አለባበሷ
ካንቺ ብጫቂ ጨርቅ እየተጣመረ
ድኩም አምሮዬ
ምስጢር ስጦታሽን አየመረመረ
(እአየመዘመረ)
የመለኮት ሀይልሽ
የቱ ጋር እንዳለ ላይገባኝ ቢቀርም
ቤትሽ ግድግዳ ላይ ያለቺውን ማርያም
ሁሌ እንደምትመስይ አልጠራጠርም
ተመልከቻት እሷን
በሀለት እጆቿ ንጉሱን ታቅፋ
ስለክብሩ ብላ አንገቷን ስትደፋ
ተመልከቺ ልጇን
ከበግ ስር እንዳለ ብላቴና ግልገል
ከጡት አፈትልኮ
ከእናት ስር አምልጦ ለመሮጥ ሲታገል
ሁሌም ልሂድ ሲላት አትሂድ ትላለች
እናቱ ናትና ከሄደ በሗላ
ምን እንደሚገጥመው ቀድማ ታውቀዋለች
(አየሽ እኔም ልጅሽ)
የማይጨብጠው ተስፋዬን ጨበጬ
አትሂድ ከሚለኝ ከእቅፍሽ አምልጬ
ግብሬን ሁሉ ስቼ
አንቺን እረስቼ
ያሰርሺልኝ እውነት ማህተመ ከላላ
ስንት ጊዜ ሆነው ስንት ጊዜ ሞላ
አየሽ እኔ ልጅሽ
በኖርኩት ዘመኔ
ልጄ ሆይ ያለችን እንቴን ያልረዳሁ
እምነት የጎደለኝ
ትንቢቴን የፈራሁ ቤቴን ያልተረዳሁ
እዳዬን ፈርቼ
ስቃዬን ፈርቼ መስቀል እየሸሸሁ
በጉብዝናዬ ወር
ቀሽም ቀን ሳሳልፍ ስንት ግዜ አመሸሁ
አየሽ አይደል እማ
ከንቱነት ነው ለካ
እናቱን ማያምን እናቱን ማይሰማ
እውነትም እኔ ነኝ
መንገድም እኔው ነኝ ለራሴ እንዳላልኩኝ
መሄጃው ሲጠፋኝ
አማላጅ ፍለጋ ከእቅፍሽ ላይ ዋልኩኝ
መገመት የሚከብድ ለሀሳብ የረቀቀ
መፍረድ የማይችል ሆድ ክክፋት የራቀ
በዚህ ሁሉ ሽሽት በዚህ ሁሉ ምሽት
እንዴት አልተቆጣ እንዴት አልረገመኝ
እውነት እማማዬ ማርያምን ነው ምልሽ
እቅፍሽ ገረመኝ
ቤትሽ ግድግዳ ላይ
ማርያም ልጇን አቅፋ ምትታየው ምስል
ለምን አነደሆነ እንጃ
ቁርጥ እራስሽን አንቺን ስትመስል
አሸን መሰናክል በጫንቃዬ አዝዬ
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት
በጸሎቴ መሀል የሀሰትን መና
ሽቅብ አንጠልጥሎ ሰቅሎ ከደመና
"ይብቃህ ዳዊት መድገም - ተው ውዳሴ ማርያም
ምስጋና፣ መሻትህ - ደርሷል ከአርያም
ተመልከት ወደ ላይ - አንጋጥጥ በጥብቅ
አየህ በረከትክን አንተን ሲጠብቅ"
እያለ ይጮኻል - ከንቱ ወናፍ ላንቃ
ከመች ጀምሮ ነው
ጸሎት የሚቋረጥ ምስጋናስ ሚበቃ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል ረዳቴ - ዞርኩኝ ወደ ምስልህ
አሳቼን አየኹት ሲንፈራገጥ ከእግርህ
በስምህ ልዘክር - ካለኝ ላይ ቀንሼ
በደስታ እያበራኹ ከደጅህ ደርሼ
ስከፍት ሞሰቤን እጄን እያነቀ
በአዛኝ ከንፈሩ የፌዝ እየሳቀ
የኑሮን ውድነት እየዘረዘረ
"ገነት ለገባ ነፍስ - ጸድቆ ለበረረ
ገንዘብ የሚያባክን ምጽዋት ምን ሊበጅ?
ከሞት አያነቃ ህይወት አያደረጅ"
ይለኛል አስሬ እየዘጋ መንገድ
ከመቼ ወዲህ ነው
ምጽዋት ተለግሶ ውድቀት የሚታጨድ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል አጋዤ ምስልህን ስታቀፍ
ጠላቴን አየሁት ከመኖር ሲቀረፍ
ክብርህ ያልገባቸው ምልጃህን ሊያጎድፉ
ጥቅስ እያጣቀሱ ቃል ሲለፈልፉ
ላስረዳቸው ስጥር ገድልህን አንብቤ
እንድትገልጥላቸው ስጽልይ በልቤ
የኔን እየተው ሊጫኑኝ በጩኸት
አፋቸው ደጋግሞ በውድቀት ሲከፈት
መዳረቅን ሽሽት ስሄድ ጥያቼው
እየተዘባበቱ በጉድፍ ቃላቸው
መክሰሬን ሲገልጹ አንተን በማክበሬ
የፌዝ ሳቅ አንግቤ - ሳያቸው ዞሬ
"ሂድና በላቸው ጥርሳቸውን አርግፍ
እንዴት ዝም ትላለህ - ክብሬ ሲጎድፍ"
የሚል ቁጣ ትዕዛዝ - ገባ ወደ ዕዝኔ
መቼ ይሆን ደግሞ
ስላንተ መምታትን የተማርኩት እኔ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
አልመስልህ አለኝ እውን ያንተ ቃል
ለስምህ መሞት እንጂ - መግደል ያጸድቃል?
ሚካኤል አዳኜ
አወጣኹ ምስልህን - ኪሴ ውስጥ መዝዤ
አነቀኝ አንዳች ኃይል - ቀረኹኝ ፈዝዤ
ባጣ መታገያ አቅም - ወረደ እንባዬ
ብቻ ግን ደስ አለኝ - አልሳትኩም ተታልዬ
ልጅህን የማትተው በፈተና ቃርሚያ
አዳንከኝ ሚካኤል ልክ እንደ አፎሚያ
አሸን መሰናክል በጫንቃዬ አዝዬ
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት
#ኤልዳን
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት
በጸሎቴ መሀል የሀሰትን መና
ሽቅብ አንጠልጥሎ ሰቅሎ ከደመና
"ይብቃህ ዳዊት መድገም - ተው ውዳሴ ማርያም
ምስጋና፣ መሻትህ - ደርሷል ከአርያም
ተመልከት ወደ ላይ - አንጋጥጥ በጥብቅ
አየህ በረከትክን አንተን ሲጠብቅ"
እያለ ይጮኻል - ከንቱ ወናፍ ላንቃ
ከመች ጀምሮ ነው
ጸሎት የሚቋረጥ ምስጋናስ ሚበቃ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል ረዳቴ - ዞርኩኝ ወደ ምስልህ
አሳቼን አየኹት ሲንፈራገጥ ከእግርህ
በስምህ ልዘክር - ካለኝ ላይ ቀንሼ
በደስታ እያበራኹ ከደጅህ ደርሼ
ስከፍት ሞሰቤን እጄን እያነቀ
በአዛኝ ከንፈሩ የፌዝ እየሳቀ
የኑሮን ውድነት እየዘረዘረ
"ገነት ለገባ ነፍስ - ጸድቆ ለበረረ
ገንዘብ የሚያባክን ምጽዋት ምን ሊበጅ?
ከሞት አያነቃ ህይወት አያደረጅ"
ይለኛል አስሬ እየዘጋ መንገድ
ከመቼ ወዲህ ነው
ምጽዋት ተለግሶ ውድቀት የሚታጨድ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
ሚካኤል አጋዤ ምስልህን ስታቀፍ
ጠላቴን አየሁት ከመኖር ሲቀረፍ
ክብርህ ያልገባቸው ምልጃህን ሊያጎድፉ
ጥቅስ እያጣቀሱ ቃል ሲለፈልፉ
ላስረዳቸው ስጥር ገድልህን አንብቤ
እንድትገልጥላቸው ስጽልይ በልቤ
የኔን እየተው ሊጫኑኝ በጩኸት
አፋቸው ደጋግሞ በውድቀት ሲከፈት
መዳረቅን ሽሽት ስሄድ ጥያቼው
እየተዘባበቱ በጉድፍ ቃላቸው
መክሰሬን ሲገልጹ አንተን በማክበሬ
የፌዝ ሳቅ አንግቤ - ሳያቸው ዞሬ
"ሂድና በላቸው ጥርሳቸውን አርግፍ
እንዴት ዝም ትላለህ - ክብሬ ሲጎድፍ"
የሚል ቁጣ ትዕዛዝ - ገባ ወደ ዕዝኔ
መቼ ይሆን ደግሞ
ስላንተ መምታትን የተማርኩት እኔ?
እንጃ ግራ ገባኝ
አለማወቅ ጎዳኝ
አልመስልህ አለኝ እውን ያንተ ቃል
ለስምህ መሞት እንጂ - መግደል ያጸድቃል?
ሚካኤል አዳኜ
አወጣኹ ምስልህን - ኪሴ ውስጥ መዝዤ
አነቀኝ አንዳች ኃይል - ቀረኹኝ ፈዝዤ
ባጣ መታገያ አቅም - ወረደ እንባዬ
ብቻ ግን ደስ አለኝ - አልሳትኩም ተታልዬ
ልጅህን የማትተው በፈተና ቃርሚያ
አዳንከኝ ሚካኤል ልክ እንደ አፎሚያ
አሸን መሰናክል በጫንቃዬ አዝዬ
መቆም እስኪከብደኝ በፈተና ዝዬ
እየዳኹኩ በጉልበት - ስቆም ምስልህ ፊት
ሚካኤል አባቴ
ተልጦ ይረግፋል የውድቀቴ ቅርፊት
#ኤልዳን
የደሃውን ልመና ችል አትበል፡፡ በነፍሱ የመረረው ነውና ቢረግምህ እግዚአብሔርአቤቱታውን ይሰማዋል ፤ ፈጥኖም ይደርስብሃል፡፡ ስለዚህ ደሃን በድህነቱ ምከንያት አታቃለው፤ አንተንም ይረግምህ ዘንድ ምከንያት አትሁነው፡፡
ልብሶቹ ቢያድፋበት በውኃ እጠብለት፤ አዲስም ልብስ ገዝተህ አልብሰው፤ ደሃው ወደ ቤት የገባ እንደሆነ እግዚአብሔር ወደ ቤትህ ይገባል፤ በመኖሪያህም ያድራል፡፡ ከመከራ ከስቃይ ያላቀቀኸው ያ ድሃ አንተንም ከሚመጣብህ መከራና ስቃይ ያላቅቅሃል።
የእንግዳውን እግር አጠብክን ? የበዛ ኃጢአትህን አጥበህ አስወገድከው፡፡ ለድሃው ይመገብ ዘንድ ማዕድን አቀረብክለትን ? እነሆ እግዚአብሔር አብ ከማዕድህ በላ፤ ክርስቶስም ለደሃው ካቀረብከለት ውኃ ጠጥቶ ረካ፤ መንፈስ ቅዱስም ማደሪያ ቤቱ አደረገህ፡፡
ድሃው ካቀረብክለት በልቶና ጠጥቶ ደስ አለውን? ጌታ ክርስቶስን ደስ አሰኘኸው፤ እርሱ ያደረግህለትን መልካም ችሮታ የሚረሳ አይደለምና በመላእከትና በሰዎች ፊት ያከብርሃል፡፡ ከርሃቡ እንዳሳረፍከው በመጨረሻው ቀን ይመሠክርልሃል፤ ለጥማቱ የሚጠጣ ስላቀረብክለት በመላእክቱ ፊት ያመስግንሃል፡፡
ልጄ ሆይ መልካም ዘርን በደስታና እግዚአብሔርን ተስፋ በማድረግ ዝራ፤ ልፋትህም ፍሬ ይስጥህ፡፡ ገበሬ ዘሩን በተስፋ ይዘራል፣ ነጋዴም በተስፋ አተርፋለሁ ብሎ ባሕር አቋርጦ ይጓዛል፤ አንተም አዝመራ የሚሆን ፍሬን ትፈልጋለህ፣ ስታገኝም በተስፋ ትዘራለህ፤ ምርቱንም በተስፋ ትጠባበቃለህ፡፡
ልጄ ሆይ ማናቸውንም ነገር በምትፈጽምበት ጊዜ ሥራህን በጸሎት ጀምር፡፡ የምትሠራቸውን ሥራዎች ሁሉ በትምህርተ መሰቀል ባርካቸው። በምትበላም፣ በምትጠጣም ጊዜ፣ በምትተኛም በምትነቃም ጊዜ፣ በቤት ውስጥም ሳለህ ይሁን በጎዳና ፣ በዕረፍትም ወቅት ቢሆን፣ ማማተብን አትዘንጋ፡፡ (የጌታህን ስቅለት አስታውሶ) ከክፋት የሚጠብቅህ ይህን የመሰለ ጠባቂ ከቶ አታገኝምና፤ እርሱ ለምታደርጋቸው ድርጊቶችህ ሁሉ እንደ ግንብ ነው (ማስተዋልን ይሰጥሃል)፡፡ ማማተብን በሥርዓት ይፈጽሙት ዘንድ (የከርስቶስ ኢየሱስንም ስቅለት ሁሌም በፊታቸው ይስሉ ዘንድ) ለልጆችህ በጥንቃቄ አስተምራቸው።
በትከክለኛው ትርጉም ነጻ ሰው ትባል ዘንድ ራስህን ከእግዚአብሔር ሕግ ቀንበርበታች አድርግ፡፡ ከእግዚአበሔር ፈቃድ ውጪ የሆነውን የነፍስን ፈቃድ አታድርግ፡፡
ስለአንተ መዳን ምን ያህል ትእዛዛትን ልጻፍልህ? ምን ያህልስ ሕግጋትን ልቅረጽልህ? ነጻነትህን የምትሻት ከሆንህ ሕግጋትን ከሥነፍጥረት የምትማራቸው አይደሉምን? ቅድስናን የምትወድ ከሆነ አንተው ራስህ ይህንን ለሌሎች ማስተማር ትችላለህ፡፡
ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ፤ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፤ ከእነርሱ ሕግጋትን ተማር፡፡ በተመሰጦም ሆነ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ሕግጋት መርምረህ ተረዳ፡፡ ፀሐይ በመውጣቷና በመግባቷ ለሥራ ዕርፍት አንደሚያስፈልግህ ታስተምርሃለች፡፡ ሌሊትም በጸጥታ ለሥራዎችህ መጨረሻ እንዳላቸው ጮኻ ትነግርሃለች፡፡ በምድር ላይ የሚፈሩ ፍራፍሬዎችም ለሁሉ ነገር ወቅት ወቅት እንዳላቸው ያውጁልሃል። በክረምት የዘራኸውን ዘር በበጋ ትሰበስባዋለህ፤ እንዲሁ በምድር የጽድቅን ዘር የዘራህ ከሆነ በትንሣኤ ፍሬውን ትሰበስባለህ፡፡
(ስብከት ወተግሣጽ ዘቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ገጽ 75-76 በመምህር ሽመልስ መርጊያ የተተረጎመ)
ልብሶቹ ቢያድፋበት በውኃ እጠብለት፤ አዲስም ልብስ ገዝተህ አልብሰው፤ ደሃው ወደ ቤት የገባ እንደሆነ እግዚአብሔር ወደ ቤትህ ይገባል፤ በመኖሪያህም ያድራል፡፡ ከመከራ ከስቃይ ያላቀቀኸው ያ ድሃ አንተንም ከሚመጣብህ መከራና ስቃይ ያላቅቅሃል።
የእንግዳውን እግር አጠብክን ? የበዛ ኃጢአትህን አጥበህ አስወገድከው፡፡ ለድሃው ይመገብ ዘንድ ማዕድን አቀረብክለትን ? እነሆ እግዚአብሔር አብ ከማዕድህ በላ፤ ክርስቶስም ለደሃው ካቀረብከለት ውኃ ጠጥቶ ረካ፤ መንፈስ ቅዱስም ማደሪያ ቤቱ አደረገህ፡፡
ድሃው ካቀረብክለት በልቶና ጠጥቶ ደስ አለውን? ጌታ ክርስቶስን ደስ አሰኘኸው፤ እርሱ ያደረግህለትን መልካም ችሮታ የሚረሳ አይደለምና በመላእከትና በሰዎች ፊት ያከብርሃል፡፡ ከርሃቡ እንዳሳረፍከው በመጨረሻው ቀን ይመሠክርልሃል፤ ለጥማቱ የሚጠጣ ስላቀረብክለት በመላእክቱ ፊት ያመስግንሃል፡፡
ልጄ ሆይ መልካም ዘርን በደስታና እግዚአብሔርን ተስፋ በማድረግ ዝራ፤ ልፋትህም ፍሬ ይስጥህ፡፡ ገበሬ ዘሩን በተስፋ ይዘራል፣ ነጋዴም በተስፋ አተርፋለሁ ብሎ ባሕር አቋርጦ ይጓዛል፤ አንተም አዝመራ የሚሆን ፍሬን ትፈልጋለህ፣ ስታገኝም በተስፋ ትዘራለህ፤ ምርቱንም በተስፋ ትጠባበቃለህ፡፡
ልጄ ሆይ ማናቸውንም ነገር በምትፈጽምበት ጊዜ ሥራህን በጸሎት ጀምር፡፡ የምትሠራቸውን ሥራዎች ሁሉ በትምህርተ መሰቀል ባርካቸው። በምትበላም፣ በምትጠጣም ጊዜ፣ በምትተኛም በምትነቃም ጊዜ፣ በቤት ውስጥም ሳለህ ይሁን በጎዳና ፣ በዕረፍትም ወቅት ቢሆን፣ ማማተብን አትዘንጋ፡፡ (የጌታህን ስቅለት አስታውሶ) ከክፋት የሚጠብቅህ ይህን የመሰለ ጠባቂ ከቶ አታገኝምና፤ እርሱ ለምታደርጋቸው ድርጊቶችህ ሁሉ እንደ ግንብ ነው (ማስተዋልን ይሰጥሃል)፡፡ ማማተብን በሥርዓት ይፈጽሙት ዘንድ (የከርስቶስ ኢየሱስንም ስቅለት ሁሌም በፊታቸው ይስሉ ዘንድ) ለልጆችህ በጥንቃቄ አስተምራቸው።
በትከክለኛው ትርጉም ነጻ ሰው ትባል ዘንድ ራስህን ከእግዚአብሔር ሕግ ቀንበርበታች አድርግ፡፡ ከእግዚአበሔር ፈቃድ ውጪ የሆነውን የነፍስን ፈቃድ አታድርግ፡፡
ስለአንተ መዳን ምን ያህል ትእዛዛትን ልጻፍልህ? ምን ያህልስ ሕግጋትን ልቅረጽልህ? ነጻነትህን የምትሻት ከሆንህ ሕግጋትን ከሥነፍጥረት የምትማራቸው አይደሉምን? ቅድስናን የምትወድ ከሆነ አንተው ራስህ ይህንን ለሌሎች ማስተማር ትችላለህ፡፡
ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ፤ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፤ ከእነርሱ ሕግጋትን ተማር፡፡ በተመሰጦም ሆነ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ሕግጋት መርምረህ ተረዳ፡፡ ፀሐይ በመውጣቷና በመግባቷ ለሥራ ዕርፍት አንደሚያስፈልግህ ታስተምርሃለች፡፡ ሌሊትም በጸጥታ ለሥራዎችህ መጨረሻ እንዳላቸው ጮኻ ትነግርሃለች፡፡ በምድር ላይ የሚፈሩ ፍራፍሬዎችም ለሁሉ ነገር ወቅት ወቅት እንዳላቸው ያውጁልሃል። በክረምት የዘራኸውን ዘር በበጋ ትሰበስባዋለህ፤ እንዲሁ በምድር የጽድቅን ዘር የዘራህ ከሆነ በትንሣኤ ፍሬውን ትሰበስባለህ፡፡
(ስብከት ወተግሣጽ ዘቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ገጽ 75-76 በመምህር ሽመልስ መርጊያ የተተረጎመ)
እናት አለኝ
በመንገዴ...
ከኔ ቀድማ የምትገኝ
ቀን ሲከዳኝ ሲያሻኝ ማረፍ
ቀሚሷ ነው የኔ መዳፍ
እናት አለኝ
ቃል ኪዷኗ 'ሚደግፈኝ
ክንዴ ሲዝል ለመኖር ስደክም
እኩል ከኔ ታማ ቁስሌን የምታክም
ሳዝን የሚጨንቃት ሲከፋኝ የማትወድ
በሄድኩበት ሁሉ አብራኝ የምትሄድ
እናት አለኝ
በሀዘን ተከብቤ እንዳልታይባት
የኔን ድካም ወስዳ የምትሰጠኝ ብርታት
እናት አለኝ
@MekuanenetM
በመንገዴ...
ከኔ ቀድማ የምትገኝ
ቀን ሲከዳኝ ሲያሻኝ ማረፍ
ቀሚሷ ነው የኔ መዳፍ
እናት አለኝ
ቃል ኪዷኗ 'ሚደግፈኝ
ክንዴ ሲዝል ለመኖር ስደክም
እኩል ከኔ ታማ ቁስሌን የምታክም
ሳዝን የሚጨንቃት ሲከፋኝ የማትወድ
በሄድኩበት ሁሉ አብራኝ የምትሄድ
እናት አለኝ
በሀዘን ተከብቤ እንዳልታይባት
የኔን ድካም ወስዳ የምትሰጠኝ ብርታት
እናት አለኝ
@MekuanenetM
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሲነግሩሽ ሰሚነሽ |@Z_TEWODROS
✞ ያለሽ ልዩ ፀጋ
ያለሽ ልዩ ፀጋ ያለሽ ልዪ ክብር
የሁሉ እመቤት በሰማይ በምድር
አቁራሪተ መዐልት ምራገ ፀሎት
ሲነግሩሽ ሰሚነሽ ኪዳነምህረት
በመከራ ላለው ሁኝለት መፅናኛ
ዕንባውን አብሺው አይዘን ዳግመኛ
ጉድለቱን ሙይለት በፈረሰው ቆመሽ
ስለምታስምሪ በልዩ ኪዳንሽ
ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው
እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው
አዝ__
ይበጠሰ ከእጁ የወህኒው ሰንሰለት
የሞቱ ደብዳቤ ይቀየር በህይወት
አዲስ ተስፋ ሞልተሽ አዲስ ሰው አድርጊው
መቅበዝበዙ ይርሳ ድንግል አረጋጊው
ከኪዳንም በላይ•••••••••••••
አዝ____
በዕንባ የመጣው ይመለስ በደስታ
መጠማቱ ይቅር ይሞላ በእርካታ
ስለቱ ሰምሮለት ይቁም ለምስጋና
የአብራኩን ክፋይ አሳቅፊውና
ከኪዳንም በላይ••••••••••••
አዝ__
ተይዞ ለሚኖር በአልጋ ቁራኛ
አንቺው እመቤቴ የዴውም ዳኛ
መንገርስ ላንቺ ነው መማፀን ወዳንቺ
ተስፋን ለምትቀጥይ ህልምን ለምትፈቺ
ከኪዳንም በላይ••••••••
ሊቀ-መዘምራን
ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ያለሽ ልዩ ፀጋ ያለሽ ልዪ ክብር
የሁሉ እመቤት በሰማይ በምድር
አቁራሪተ መዐልት ምራገ ፀሎት
ሲነግሩሽ ሰሚነሽ ኪዳነምህረት
በመከራ ላለው ሁኝለት መፅናኛ
ዕንባውን አብሺው አይዘን ዳግመኛ
ጉድለቱን ሙይለት በፈረሰው ቆመሽ
ስለምታስምሪ በልዩ ኪዳንሽ
ከኪዳንም በላይ ኪዳንሽ ልዩ ነው
እናቴ የሚልሽ አምላክሽ ልጅሽ ነው
አዝ__
ይበጠሰ ከእጁ የወህኒው ሰንሰለት
የሞቱ ደብዳቤ ይቀየር በህይወት
አዲስ ተስፋ ሞልተሽ አዲስ ሰው አድርጊው
መቅበዝበዙ ይርሳ ድንግል አረጋጊው
ከኪዳንም በላይ•••••••••••••
አዝ____
በዕንባ የመጣው ይመለስ በደስታ
መጠማቱ ይቅር ይሞላ በእርካታ
ስለቱ ሰምሮለት ይቁም ለምስጋና
የአብራኩን ክፋይ አሳቅፊውና
ከኪዳንም በላይ••••••••••••
አዝ__
ተይዞ ለሚኖር በአልጋ ቁራኛ
አንቺው እመቤቴ የዴውም ዳኛ
መንገርስ ላንቺ ነው መማፀን ወዳንቺ
ተስፋን ለምትቀጥይ ህልምን ለምትፈቺ
ከኪዳንም በላይ••••••••
ሊቀ-መዘምራን
ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ