ማኅበረ ቅዱሳን ለሁለት ወራት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ
ጳጉሜን ፫/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት በነቀምቴ ምሥካበ ቅዱሳን ዑራኤል ወሳሙኤል ገዳም ለሁለት ወራት ያስተማራቸውን ከ17 ወረዳዎች የተውጣጡ 32 ደቀ መዛሙርት ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሁለት ወራት የትምህርት ቆይታቸው 21 ደቀ መዛሙርት የቅስና ማእረግ የተቀበሉ ሲሆን 11 ዲያቆናት ደግሞ ለአገልግሎት ብቁ የሚያደርጋቸውን ትምህርት መማራቸው ተጠቁሟል።
ማኅበረ ቅዱሳን ባስገነባውና ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተመረቀው አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ውስጥ ሊጦን ፣ መስተበቁዕ፣ ኪዳንና የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶችን ደቀ መዛሙርቱ መማራቸውን የተገለጸ ሲሆን ይህም ለተሻለ የክህነት አገልግሎት የሚያስፈልጋቸውን ትምህርት በመማር የነበራቸውን እውቀት እንዲያጠናክሩ ያስችላቸዋል ተብሏል።
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ደረጀ ጋረደው በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት በማስተላለፍ ''በዚህ ወቅት መማራችሁ ሰፊው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚጠብቃችሁ በመሆኑ የተመረጣችሁበትን ዓላማ በውል በመረዳት በእምነት መጠበቅ እና መወሰን ይጠበቅባችኋል።" በማለት ተናግረዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም "እስከ ምድር ዳርቻ ምሥክሮች ትሆናላችሁ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በመጥቀስ ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ቃለ እግዚአብሔርን ለተራቡ በተለይ በጠረፋማ አካባቢ ለሚገኙ ምእመናን ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ አሳስበዋል።
ጳጉሜን ፫/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት በነቀምቴ ምሥካበ ቅዱሳን ዑራኤል ወሳሙኤል ገዳም ለሁለት ወራት ያስተማራቸውን ከ17 ወረዳዎች የተውጣጡ 32 ደቀ መዛሙርት ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሁለት ወራት የትምህርት ቆይታቸው 21 ደቀ መዛሙርት የቅስና ማእረግ የተቀበሉ ሲሆን 11 ዲያቆናት ደግሞ ለአገልግሎት ብቁ የሚያደርጋቸውን ትምህርት መማራቸው ተጠቁሟል።
ማኅበረ ቅዱሳን ባስገነባውና ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተመረቀው አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ውስጥ ሊጦን ፣ መስተበቁዕ፣ ኪዳንና የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶችን ደቀ መዛሙርቱ መማራቸውን የተገለጸ ሲሆን ይህም ለተሻለ የክህነት አገልግሎት የሚያስፈልጋቸውን ትምህርት በመማር የነበራቸውን እውቀት እንዲያጠናክሩ ያስችላቸዋል ተብሏል።
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ደረጀ ጋረደው በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት በማስተላለፍ ''በዚህ ወቅት መማራችሁ ሰፊው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚጠብቃችሁ በመሆኑ የተመረጣችሁበትን ዓላማ በውል በመረዳት በእምነት መጠበቅ እና መወሰን ይጠበቅባችኋል።" በማለት ተናግረዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም "እስከ ምድር ዳርቻ ምሥክሮች ትሆናላችሁ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በመጥቀስ ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ቃለ እግዚአብሔርን ለተራቡ በተለይ በጠረፋማ አካባቢ ለሚገኙ ምእመናን ተደራሽ ማድረግ እንዲችሉ አሳስበዋል።
❤22👍3🙏2
የምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ላእከ ወንጌል ቀሲስ ገረመው በቀለ በበኩላቸው " ዛሬ የተመረቃችሁ 21 ካህናት የተዘጉ 21 አብያተ ክርስቲያናትን የምትከፍቱ ናችሁ" በማለት ቤተ ክርስቲያን የጣለችባቸውን አደራ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አደራ ብለዋል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም ማኅበረ ቅዱሳን የአገልጋይ እጥረት ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን በጎ ተግባርም በማመስገን መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በኩረ ትጉሐን አሰፋ ጉደታ ማኅበሩ ባስገነባው አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን አስተምሮ ማስመረቁ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቱ የተገነባበትን ዓላማ ጅማሮ የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ዛሬ አስተምረን ማስመረቃችን ልዩ ትርጉም አለው ያሉት ኃላፊው በሀገረ ስብከቱ 480 አብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአገልጋይ እጥረት የተዘጉ በመሆናቸው የዛሬዎቹ ተመራቂዎች የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና አገልግሎቱን በማስቀጠል የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ማእከል ከዋናው ማእከል ባገኘው ድጋፍ እና የአካባቢውን ምእመናን እንዲሁም ማኅበራት በማስተባበር ከ438,720 ብር በላይ የመምህራን፣ የሠራተኞችና የደቀ መዛሙርቱን ወጪ በመሸፈን ሲያስተምር መቆየቱን ተጠቁሟል።
በመጨረሻም ማኅበሩ ከምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ጋር በጋራ በመሆን ደቀ መዛሙርትን ከተለያዩ ወረዳዎች በመመልመልና በማስተማር ለአገልግሎት የማሠማራቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም ማኅበረ ቅዱሳን የአገልጋይ እጥረት ለመቅረፍ እያደረገ ያለውን በጎ ተግባርም በማመስገን መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በኩረ ትጉሐን አሰፋ ጉደታ ማኅበሩ ባስገነባው አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን አስተምሮ ማስመረቁ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቱ የተገነባበትን ዓላማ ጅማሮ የሚያሳይ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ዛሬ አስተምረን ማስመረቃችን ልዩ ትርጉም አለው ያሉት ኃላፊው በሀገረ ስብከቱ 480 አብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን አብዛኛዎቹ በአገልጋይ እጥረት የተዘጉ በመሆናቸው የዛሬዎቹ ተመራቂዎች የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና አገልግሎቱን በማስቀጠል የሚኖራቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የነቀምቴ ማእከል ከዋናው ማእከል ባገኘው ድጋፍ እና የአካባቢውን ምእመናን እንዲሁም ማኅበራት በማስተባበር ከ438,720 ብር በላይ የመምህራን፣ የሠራተኞችና የደቀ መዛሙርቱን ወጪ በመሸፈን ሲያስተምር መቆየቱን ተጠቁሟል።
በመጨረሻም ማኅበሩ ከምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ጋር በጋራ በመሆን ደቀ መዛሙርትን ከተለያዩ ወረዳዎች በመመልመልና በማስተማር ለአገልግሎት የማሠማራቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።
❤36👍19🙏2
✝️ከአንድ ቤተሰብ፣ ለአንድ ተማሪ✝️
++++
ማኅበረ ቅዱሳን በየዓመቱ እንደሚያደርገው በማኅበራዊ ቀውስ ጉዳት የተነሣ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ በገንዘብና በዓይነት እያሰባሰሰበ ይገኛል።
ድጋፍ ለማድረግም፡-
#በገንዘብ
በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
2. በአቢሲኒያ ባንክ 37235458
3. በወጋገን ባንክ 0837331610101
4. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
#በዓይነት
ደብተር፣እስክርቢቶ፣ እርሳስና ቦርሳ ለበለጠ መረጃ
• 09 84 18 15 44
• ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት
++++
ማኅበረ ቅዱሳን በየዓመቱ እንደሚያደርገው በማኅበራዊ ቀውስ ጉዳት የተነሣ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ በገንዘብና በዓይነት እያሰባሰሰበ ይገኛል።
ድጋፍ ለማድረግም፡-
#በገንዘብ
በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
2. በአቢሲኒያ ባንክ 37235458
3. በወጋገን ባንክ 0837331610101
4. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
#በዓይነት
ደብተር፣እስክርቢቶ፣ እርሳስና ቦርሳ ለበለጠ መረጃ
• 09 84 18 15 44
• ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት
❤41🙏6👍2
ማኅበረ ቅዱሳን ለምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ያስገነባውን የአብነት ትምህርት ቤት ማስረከቡ ተገለጸ
ጳጉሜን ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት በምስካበ ቅዱሳን ዑራኤል ወሳሙኤል ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።
ይህ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ታኅሣሥ ወር 2016 ዓ.ም ተጀምሮ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም በአንድ ዓመት ውስጥ የተጠናቀቀ ሲሆን ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል።
የአብነት ት/ቤት ፕሮጀክቱ ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል ርክክብ ተፈየተደረገ ሲሆን በርክክብ መርሐ ግብሩ የምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ላእከ ወንጌል ቀሲስ ገረመው በቀለና በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ት/ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ደረጀ ጋረደው በመፈራረም ርክክቡን ፈጽመዋል።
ከ8.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት አዳሪ አብነት ት/ቤቱ የሁለት መምህራን ማደሪያ፣ የምግብ ማብሰያና መመገቢያ አዳራሽ፣ የመማሪያ ጉባኤ ቤትና የንጽሕና መጠበቂያ እንዲሁም 32 ተማሪዎችን ማስተናግድ የሚችል ደረጃቸውን የጠበቁ ማደሪያዎች ከነሙሉ ቁሳቁሳቸው ያካተተ ነው ተብሏል።
የአዳሪ አብነት ት/ቤቱ መገንባት በአካባቢው ያለውን የካህናት አገልጋይ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ማኅበረ ቅዱሳን አብነት ት/ቤት ባልተስፋፋባቸው አካባቢዎች ለሚያደርገው አብነት ት/ቤቶችን የማስፋፋት እንቅስቃሴ ማሳያ ነው።
ጳጉሜን ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት በምስካበ ቅዱሳን ዑራኤል ወሳሙኤል ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።
ይህ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት ታኅሣሥ ወር 2016 ዓ.ም ተጀምሮ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም በአንድ ዓመት ውስጥ የተጠናቀቀ ሲሆን ግንቦት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ተመርቆ አገልግሎት ጀምሯል።
የአብነት ት/ቤት ፕሮጀክቱ ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ.ም በሀገረ ስብከቱና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል ርክክብ ተፈየተደረገ ሲሆን በርክክብ መርሐ ግብሩ የምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ላእከ ወንጌል ቀሲስ ገረመው በቀለና በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ት/ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ደረጀ ጋረደው በመፈራረም ርክክቡን ፈጽመዋል።
ከ8.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት አዳሪ አብነት ት/ቤቱ የሁለት መምህራን ማደሪያ፣ የምግብ ማብሰያና መመገቢያ አዳራሽ፣ የመማሪያ ጉባኤ ቤትና የንጽሕና መጠበቂያ እንዲሁም 32 ተማሪዎችን ማስተናግድ የሚችል ደረጃቸውን የጠበቁ ማደሪያዎች ከነሙሉ ቁሳቁሳቸው ያካተተ ነው ተብሏል።
የአዳሪ አብነት ት/ቤቱ መገንባት በአካባቢው ያለውን የካህናት አገልጋይ እጥረት ለመቅረፍ የሚያስችል ከመሆኑም በተጨማሪ ማኅበረ ቅዱሳን አብነት ት/ቤት ባልተስፋፋባቸው አካባቢዎች ለሚያደርገው አብነት ት/ቤቶችን የማስፋፋት እንቅስቃሴ ማሳያ ነው።
❤37🙏8👍3👏3
ፕሮጀክቱ ተግባራዊ እንዲሆን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ምእመናን፣ በሀገረ አሜሪካ ሚኒሶታ፣ ኢንዲያፖሊስ፣ ሚያፊስና ፖርትላንድ ንኡስ ማእከል፣ በካናዳ እና አውሮፓ ማእከላት እንዲሁም በእንግሊዝ ሀገር የሚኖሩ በጎ አድራጊ ምእመናን ድጋፍ ማድረጋቸው ተጠቁሟል።
አዳሪ አብነት ት/ቤቱ ለመጀመሪያ ግዜ ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ/ም 21 ቀሳውስትና 11 ዲያቆናትን በአጠቃላይ 32 ደቀ መዛሙርትን አስተምሮ አስመርቋል።
አዳሪ አብነት ት/ቤቱ ለመጀመሪያ ግዜ ጳጉሜን 2 ቀን 2017 ዓ/ም 21 ቀሳውስትና 11 ዲያቆናትን በአጠቃላይ 32 ደቀ መዛሙርትን አስተምሮ አስመርቋል።
❤58👏16👍7🙏4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን አደረሳችሁ!
ማኅበረ ቅዱሳን ለሚያስገነባው የልህቀት ማእከል ድጋፍ የሚውል የበረከት ዕቁብ ይሳተፉ! አንድ ዕጣ በወር 500ብር ብቻ።
ለመሳተፍ-https://forms.gle/jkjeZnNBunzKHvp69
ለበለጠ መረጃ-0966636363 ይደውሉ።
ማኅበረ ቅዱሳን።
ማኅበረ ቅዱሳን ለሚያስገነባው የልህቀት ማእከል ድጋፍ የሚውል የበረከት ዕቁብ ይሳተፉ! አንድ ዕጣ በወር 500ብር ብቻ።
ለመሳተፍ-https://forms.gle/jkjeZnNBunzKHvp69
ለበለጠ መረጃ-0966636363 ይደውሉ።
ማኅበረ ቅዱሳን።
❤29🙏6👍5🥰3
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የአዲስ ዓመት አባታዊ መልዕክት ማስተላለፋቸው ተገለጸ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን መግባት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል ።
የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው።
++++++++++++++++
ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰንመቱ ዓመተ ምሕረት፤
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን!
• በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
• ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
• የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
• በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
• እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣
ኣምላክነቱን ኣውቀን እንድናመልከው ዕድሜንና ዘመናትን የሚሰጠን እግዚብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስምንት ዓመተ ምህረት የርእሰ ዐውደ ዓመት በዓል ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
‹‹ወገብረ ኵሎ ኅቡረ ወኵሎ ኣሕዛበ እምአሐዱ ዕጓለ እመሕያው ከመ ይንበሩ ዲበ ኵሉ ገጸ ምድር፤ ወሠርዐ ዕድሜሁ ወዓመታቲሁ መጠነ ይነብሩ በዘየኃሥዎ ለእግዚአብሔር፤ እመ ይረክብዎ፤ ወያደምዕዎ፤ ወኢኮነ ርሑቀ እምኵልነ፡-
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን መግባት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል ።
የቅዱስነታቸው ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው።
++++++++++++++++
ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰንመቱ ዓመተ ምሕረት፤
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን!
• በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
• ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
• የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
• በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
• እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣
ኣምላክነቱን ኣውቀን እንድናመልከው ዕድሜንና ዘመናትን የሚሰጠን እግዚብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስምንት ዓመተ ምህረት የርእሰ ዐውደ ዓመት በዓል ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
‹‹ወገብረ ኵሎ ኅቡረ ወኵሎ ኣሕዛበ እምአሐዱ ዕጓለ እመሕያው ከመ ይንበሩ ዲበ ኵሉ ገጸ ምድር፤ ወሠርዐ ዕድሜሁ ወዓመታቲሁ መጠነ ይነብሩ በዘየኃሥዎ ለእግዚአብሔር፤ እመ ይረክብዎ፤ ወያደምዕዎ፤ ወኢኮነ ርሑቀ እምኵልነ፡-
❤26🙏7
ምናልባትም እየመረመሩ ያገኙት እንደሆነ እግዚአብሔርን ይፈልጉ ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከኣንድ ፈጠረ፤ የተወሰኑትንም ዘመኖችና ለሚኖሩበት ስፍራ ደረጃ መደባላቸው፤ ቢሆንም ከእያንዳንዳችን የራቀ ኣይደለም›› (የሐ. ሥራ. ፲፯÷፳፮)፤
ፈጣሬ ፍጥረታት እግዚአብሔር ትዕይንተ ዓለምንና በውስጡ የሚገኙ ፍጥረታትን የፈጠረ ኣምላክ ነው፤ እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት የሚታዩና የማይታዩ ተብለው በጥቅል በቅዱስ መጽሓፍ ተገልጸዋል፤ የሰው ልጅ ከፍጥረታት መካከል ሆኖ ከኣንድ ወገን የተገኘ እንደሆነ በዚህ ጥቅስ ተጽፎኣል፤
የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ የተለየ ክብርና ደረጃ እንዳለው በቅዱስ መጽሓፍ በተደጋጋሚ ተገልጾኣል፤ ልዩ የሚያደርገውም ከኣፈጣጠሩ ጀምሮ ነው፤
ሰው ልዩ ፍጡር መሆኑን ከሚገለጽባቸው መካከል እግዚአብሔር በሦስትነቱ “ሰውን በኣርኣያችንና በኣምሳላችን እንፍጠር” በሚል ልዩ ኣገላለጽ መፈጠሩ፣ ኣፈጣጠሩም በእግዚአሔር መልክና ኣምሳል መሆኑ፣ በእግዚአብሔር እፍታ ሕያው ነፍስ እንዲኖረው መደረጉ፣ በሥልጣንም የፍጥረታት ሁሉ የበላይ ሆኖ መሾሙ ከሌሎች ፍጥረታት ልዩ ያደርገዋል፡፡
ከዚህ ኣንጻር ሰው በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ከፍጥረታት ሁሉ በላይ ነው፤ የሁሉም ገዥ ነው፤ በተለይም በዚህ ዓለም ከሰው በላይ ሆኖ የፍጡራን ገዥ የሆነ ፍጡር እንደሌለ ሁላችንም የምናየውና የምናውቀው ነው፤
በላይኛው ዓለምም ቢሆን መላእክትን ጨምሮ ሰማይና ምድርን ከነግሣንግሡ እየገዛ ያለው ሰው የሆነ ጌታ ነው፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ የፍጥረት ገዥ ነው፤ እሱ ሰብእናችንን በፍጹም ተዋሕዶ የተዋሓደ በመሆኑ ሰብእናችን በተዋሕዶተ ቃል ኣምላክ ሆኖ የፍጥረታት ሁሉ ገዥ ሆኖኣልና ነው፤
ቅዱስ መጽሓፍም “ወተኰነኑ ሎቱ መላእክት ወሥልጣናት ወኵሉ ኃይል፡- መላእክት፣ ሥልጠናትና ኃይል ሁሉ ተገዙለት” በማለት ይህንን ያረጋግጣል፤ ይህ እግዚአብሔር ለኛ ለሰዎች ያጐናጸፈን ግሩምና ኣስደናቂ ጸጋ ነው፤ ለዚህም ነው “ወሰብእ ይከብር እምኵሉ ፍጥረት፡- ሰው ከፍጥረት ሁሉ ይከብራል” ተብሎ የሚዘመረው፤
• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያት!
እኛ ሰዎች የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ሆነን እንድንኖር በእግዚአብሔር ስንፈጠር በሕይወት እንድንኖር ነው፤ እግዚአብሔር በምድር ላይ በሕይወት ይኖሩ ዘንድ ሰውን ከኣንድ ፈጠረ የሚለው መጽሓፍ ቅዱሳዊ ኣስተምህሮም ይህንን ያመለክታል፤
ሰዎች በምድር ላይ በሕይወት እንዲኖሩ የተፈጠሩ ሆነው እያለ በሕይወት እንዳይኖሩ ማድረግ ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር መጋጨትን ያስከትላል፤በዘመናችን ዓለማችንን እየፈተነ ያለው ተቀዳሚ ፈተና ሰዎች በሕይወት እንዳይኖሩ የማድረግ ዝንባሌ ነው፤
እንደዚህ ዓይነቱ ዝንባሌ በዓለም ባይኖር ኖሮ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ድሆች ባሉበት ዓለም ለሰው ልጅ ሕይወት ማጥፊያ የሚሆን መሳሪያ ለማምረት ኁልቈ መሣፍርት የሌለው ገንዘብ ኣይወጣም ነበር፤
ይህ ክፉ የዓለም ዝንባሌ እንደ ክፋት ብቻ ሳይሆን እንደ ሞኝነትም የሚያሳይብን ነው፤ማንኛችንም ሰዎች ‹‹ሰው ማጥፋት ይሻላል ወይስ ማዳን›› ተብለን ብንጠየቅ መልሳችን ምን እንደሚሆን ይታወቃል፤
ነገር ግን ኣንፈጽመውም፣ ሞኝነት የሚያሰኘውም እዚህ ላይ ነው፤ የሚጠቅመንንና የመሰከርንለትን ትተን የሚጐዳንንና፣ ያልመሰከርንለትን እንፈጽማለንና ነው፤
ስለሆነም በሕይወት እንዲኖር የተፈጠረውን ሰው በሕይወት የመኖር መብቱን ከመንፈግ መቆጠብ የኣዲሱ ዓመት ትልቁ ኣጀንዳ ኣድርገን ብንወስድ ለሁላችንም ይበጀናልና እንቀበለው እንላለን፤
• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት!
ሰው በሕይወት እንዲኖር በእግዚአብሔር ሲፈጠር እግዚአብሔርን የሚፈልግበትና የሚያገኝበትን ዕድሜና ዘመንም እንደተሰጠው ከተጠቀሰው ክፍለ ንባብ እንገነዘባለን፤ መቼም እግዚአብሔር ሁሉን የፈጠረ በስራ ለስራ እንደሆነ የምንስተው ኣይሆንም፤ እግዚአብሔር ዕድሜና ዘመን ለሰዎች ሲሰጥ ሊሰራበት ነው፤ ስራውም መንፈሳዊና ዓለማዊ ነው፤ ተደምሮ ሲታይ ደግሞ ለሰው ጥቅም የሚውል ነው፤
እኛ ሰዎች በተሰጠን ዕድሜና ዘመን በመንፈሳዊው ስራችን እግዚአብሔርን ፈልገን እንድናገኝ ተፈጥረናል፤ እሱን ማግኘት የማይቻል የሚመስለን ካለንም እሱ ከእያንዳንዳችን የራቀ ኣይደለም ተብለናልና በመንፈስ ከፈለግነው በመንፈስ እንደምናገኘው መጽሓፉ ያስረዳናል፤ስለሆነም በተሰጠን ዘመን ይህንን ስራ መስራት ይኖርብናል፤
በሌላ በኩል ለኑሮኣችን የሚያስፈልገንን ፍጆታ በበቂ ሁኔታ እንድናገኝ ላባችንን ኣንጠፍጥፈን መስራት ይገባናል፤ ይህም ከሰራን ያለጥርጥር የምናገኘው ነው፤ ሁለቱም የጐደሉብን በኛ ኣስተሳሰብ፣ ኣሰራርና ኣጠቃቀም እንጂ እግዚአብሔር ሳይፈቅድልን ቀርቶ ወይም ነፍጎን ኣይደለም፤ እግዚአብሔር የሰጠን ምድር በልዩ ልዩ ሀብተ ጸጋ የተሞላች እንደሆነች፣ የምንረግጠው መሬትም ወደ ሀብት መቀየር እንደሚቻል የተረጋገጠ ነው፤
ነገር ግን እኛ በምንራመድበት በእግራችን ሥር ያለውን ሀብት ትተን በሩቅ ያለውን ስንመለከት ሁሉን ያጣን ሆነን በችግር ወድቀን እንገኛለን፤ በተለይም እኛ ኢትዮጵያውያን በኣሁኑ ጊዜ እየተፈታተነን ያለው ይኸው የተሳሳተ እሳቤ ነው፤
ኢትዮጵያ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ኣድርገን በማመን በእኩልነት፣ በኣንድነትና በስምምነት ከመጠቀም ይልቅ ያ የኔ ነው ያም የኔ ነው በሚል ኣባባል ምን ያህል ዋጋ እየተከፈለ እንደሆነ እያየን ነው፤ ይህ ግለኝነት ያየለበት ኣስተሳሰብ ገታ ኣድርገን በእኩልነትና በኣብሮነት የሚያሳድገንን ኣስተሳሰብ በእጅጉ ይጠቅመናል፤ ይህንንም የኣዲሱን ዓመት ምርጥ እሳቤ ኣድርገን ብንወስድ የተሻለ መግባቢያ ሊሆን ይችላል፤ ኣዲሱ ዓመት በኣዲስ እሳቤ ካላጀብነው ኣዲስ ሊሆን ኣይችልምና ነው፤ ስለሆነም ኣዲሱን ዓመት መልካም በሆነ ኣዲስ ኣሳብ ፣እግዚአብሔርንና ሰውን በሚያገናኝ ቅዱስ ተግባር፣ በልማት፣ በሰላም፣ በፍቅር፣ በዕርቅና በስምምነት እንድንቀበለው ወቅታዊ ጥሪያችን ነው፤
በመጨረሻም ኣዲሱ ዓመት ለሀገር ሰላምና ልማት፣ ለሕዝቦች ኣንድነትና ስምምነት እንደዚሁም ኣለመግባባትን በፍትሕና በዕርቅ ለመፍታት ከልብ የምንተጋበት መልካም የስኬት ዘመን እንዲሆንልን እንጸልይ፣ በዚህም መላ ሕዝባችን ጠንክሮ እንዲሰራ ለመላ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ ኣባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር ኣምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኣሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ምንጭ:- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ፈጣሬ ፍጥረታት እግዚአብሔር ትዕይንተ ዓለምንና በውስጡ የሚገኙ ፍጥረታትን የፈጠረ ኣምላክ ነው፤ እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት የሚታዩና የማይታዩ ተብለው በጥቅል በቅዱስ መጽሓፍ ተገልጸዋል፤ የሰው ልጅ ከፍጥረታት መካከል ሆኖ ከኣንድ ወገን የተገኘ እንደሆነ በዚህ ጥቅስ ተጽፎኣል፤
የሰው ልጅ ከፍጥረታት ሁሉ የተለየ ክብርና ደረጃ እንዳለው በቅዱስ መጽሓፍ በተደጋጋሚ ተገልጾኣል፤ ልዩ የሚያደርገውም ከኣፈጣጠሩ ጀምሮ ነው፤
ሰው ልዩ ፍጡር መሆኑን ከሚገለጽባቸው መካከል እግዚአብሔር በሦስትነቱ “ሰውን በኣርኣያችንና በኣምሳላችን እንፍጠር” በሚል ልዩ ኣገላለጽ መፈጠሩ፣ ኣፈጣጠሩም በእግዚአሔር መልክና ኣምሳል መሆኑ፣ በእግዚአብሔር እፍታ ሕያው ነፍስ እንዲኖረው መደረጉ፣ በሥልጣንም የፍጥረታት ሁሉ የበላይ ሆኖ መሾሙ ከሌሎች ፍጥረታት ልዩ ያደርገዋል፡፡
ከዚህ ኣንጻር ሰው በዚህ ዓለምም ሆነ በወዲያኛው ዓለም ከፍጥረታት ሁሉ በላይ ነው፤ የሁሉም ገዥ ነው፤ በተለይም በዚህ ዓለም ከሰው በላይ ሆኖ የፍጡራን ገዥ የሆነ ፍጡር እንደሌለ ሁላችንም የምናየውና የምናውቀው ነው፤
በላይኛው ዓለምም ቢሆን መላእክትን ጨምሮ ሰማይና ምድርን ከነግሣንግሡ እየገዛ ያለው ሰው የሆነ ጌታ ነው፤ ምክንያቱም ኢየሱስ ክርስቶስ የፍጥረት ገዥ ነው፤ እሱ ሰብእናችንን በፍጹም ተዋሕዶ የተዋሓደ በመሆኑ ሰብእናችን በተዋሕዶተ ቃል ኣምላክ ሆኖ የፍጥረታት ሁሉ ገዥ ሆኖኣልና ነው፤
ቅዱስ መጽሓፍም “ወተኰነኑ ሎቱ መላእክት ወሥልጣናት ወኵሉ ኃይል፡- መላእክት፣ ሥልጠናትና ኃይል ሁሉ ተገዙለት” በማለት ይህንን ያረጋግጣል፤ ይህ እግዚአብሔር ለኛ ለሰዎች ያጐናጸፈን ግሩምና ኣስደናቂ ጸጋ ነው፤ ለዚህም ነው “ወሰብእ ይከብር እምኵሉ ፍጥረት፡- ሰው ከፍጥረት ሁሉ ይከብራል” ተብሎ የሚዘመረው፤
• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያት!
እኛ ሰዎች የእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ሆነን እንድንኖር በእግዚአብሔር ስንፈጠር በሕይወት እንድንኖር ነው፤ እግዚአብሔር በምድር ላይ በሕይወት ይኖሩ ዘንድ ሰውን ከኣንድ ፈጠረ የሚለው መጽሓፍ ቅዱሳዊ ኣስተምህሮም ይህንን ያመለክታል፤
ሰዎች በምድር ላይ በሕይወት እንዲኖሩ የተፈጠሩ ሆነው እያለ በሕይወት እንዳይኖሩ ማድረግ ከፈቃደ እግዚአብሔር ጋር መጋጨትን ያስከትላል፤በዘመናችን ዓለማችንን እየፈተነ ያለው ተቀዳሚ ፈተና ሰዎች በሕይወት እንዳይኖሩ የማድረግ ዝንባሌ ነው፤
እንደዚህ ዓይነቱ ዝንባሌ በዓለም ባይኖር ኖሮ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ድሆች ባሉበት ዓለም ለሰው ልጅ ሕይወት ማጥፊያ የሚሆን መሳሪያ ለማምረት ኁልቈ መሣፍርት የሌለው ገንዘብ ኣይወጣም ነበር፤
ይህ ክፉ የዓለም ዝንባሌ እንደ ክፋት ብቻ ሳይሆን እንደ ሞኝነትም የሚያሳይብን ነው፤ማንኛችንም ሰዎች ‹‹ሰው ማጥፋት ይሻላል ወይስ ማዳን›› ተብለን ብንጠየቅ መልሳችን ምን እንደሚሆን ይታወቃል፤
ነገር ግን ኣንፈጽመውም፣ ሞኝነት የሚያሰኘውም እዚህ ላይ ነው፤ የሚጠቅመንንና የመሰከርንለትን ትተን የሚጐዳንንና፣ ያልመሰከርንለትን እንፈጽማለንና ነው፤
ስለሆነም በሕይወት እንዲኖር የተፈጠረውን ሰው በሕይወት የመኖር መብቱን ከመንፈግ መቆጠብ የኣዲሱ ዓመት ትልቁ ኣጀንዳ ኣድርገን ብንወስድ ለሁላችንም ይበጀናልና እንቀበለው እንላለን፤
• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት!
ሰው በሕይወት እንዲኖር በእግዚአብሔር ሲፈጠር እግዚአብሔርን የሚፈልግበትና የሚያገኝበትን ዕድሜና ዘመንም እንደተሰጠው ከተጠቀሰው ክፍለ ንባብ እንገነዘባለን፤ መቼም እግዚአብሔር ሁሉን የፈጠረ በስራ ለስራ እንደሆነ የምንስተው ኣይሆንም፤ እግዚአብሔር ዕድሜና ዘመን ለሰዎች ሲሰጥ ሊሰራበት ነው፤ ስራውም መንፈሳዊና ዓለማዊ ነው፤ ተደምሮ ሲታይ ደግሞ ለሰው ጥቅም የሚውል ነው፤
እኛ ሰዎች በተሰጠን ዕድሜና ዘመን በመንፈሳዊው ስራችን እግዚአብሔርን ፈልገን እንድናገኝ ተፈጥረናል፤ እሱን ማግኘት የማይቻል የሚመስለን ካለንም እሱ ከእያንዳንዳችን የራቀ ኣይደለም ተብለናልና በመንፈስ ከፈለግነው በመንፈስ እንደምናገኘው መጽሓፉ ያስረዳናል፤ስለሆነም በተሰጠን ዘመን ይህንን ስራ መስራት ይኖርብናል፤
በሌላ በኩል ለኑሮኣችን የሚያስፈልገንን ፍጆታ በበቂ ሁኔታ እንድናገኝ ላባችንን ኣንጠፍጥፈን መስራት ይገባናል፤ ይህም ከሰራን ያለጥርጥር የምናገኘው ነው፤ ሁለቱም የጐደሉብን በኛ ኣስተሳሰብ፣ ኣሰራርና ኣጠቃቀም እንጂ እግዚአብሔር ሳይፈቅድልን ቀርቶ ወይም ነፍጎን ኣይደለም፤ እግዚአብሔር የሰጠን ምድር በልዩ ልዩ ሀብተ ጸጋ የተሞላች እንደሆነች፣ የምንረግጠው መሬትም ወደ ሀብት መቀየር እንደሚቻል የተረጋገጠ ነው፤
ነገር ግን እኛ በምንራመድበት በእግራችን ሥር ያለውን ሀብት ትተን በሩቅ ያለውን ስንመለከት ሁሉን ያጣን ሆነን በችግር ወድቀን እንገኛለን፤ በተለይም እኛ ኢትዮጵያውያን በኣሁኑ ጊዜ እየተፈታተነን ያለው ይኸው የተሳሳተ እሳቤ ነው፤
ኢትዮጵያ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ኣድርገን በማመን በእኩልነት፣ በኣንድነትና በስምምነት ከመጠቀም ይልቅ ያ የኔ ነው ያም የኔ ነው በሚል ኣባባል ምን ያህል ዋጋ እየተከፈለ እንደሆነ እያየን ነው፤ ይህ ግለኝነት ያየለበት ኣስተሳሰብ ገታ ኣድርገን በእኩልነትና በኣብሮነት የሚያሳድገንን ኣስተሳሰብ በእጅጉ ይጠቅመናል፤ ይህንንም የኣዲሱን ዓመት ምርጥ እሳቤ ኣድርገን ብንወስድ የተሻለ መግባቢያ ሊሆን ይችላል፤ ኣዲሱ ዓመት በኣዲስ እሳቤ ካላጀብነው ኣዲስ ሊሆን ኣይችልምና ነው፤ ስለሆነም ኣዲሱን ዓመት መልካም በሆነ ኣዲስ ኣሳብ ፣እግዚአብሔርንና ሰውን በሚያገናኝ ቅዱስ ተግባር፣ በልማት፣ በሰላም፣ በፍቅር፣ በዕርቅና በስምምነት እንድንቀበለው ወቅታዊ ጥሪያችን ነው፤
በመጨረሻም ኣዲሱ ዓመት ለሀገር ሰላምና ልማት፣ ለሕዝቦች ኣንድነትና ስምምነት እንደዚሁም ኣለመግባባትን በፍትሕና በዕርቅ ለመፍታት ከልብ የምንተጋበት መልካም የስኬት ዘመን እንዲሆንልን እንጸልይ፣ በዚህም መላ ሕዝባችን ጠንክሮ እንዲሰራ ለመላ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ ኣባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር ኣምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኣሜን
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
መስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ምንጭ:- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
❤42🙏6