ከ13 ወረዳ ማእከላት ለተውጣጡ ሥራ አስፈጻሚዎች የሥልጠና እና ውይይት መርሐ ግብር መካሄዱን የደብረ ታቦር ማእከል ገለጸ
ኅዳር ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ታቦር ማእከል ከ13 ወረዳ ማእከላት ለተውጣጡ 71 ሥራ አስፈጻሚዎች የሥልጠና እና ውይይት መርሐ ግብር ከጥቅምት 28 ቀን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄዱን ተገልጿል፡፡
በመርሐ ግብሩ 2018 ዓ.ም በጸደቀው እቅድ ላይ ገለጻ እና ውይይት የተደረገ ሲሆን የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ወረዳ ማእከላት የልምድ ልውውጥና ተሞክሮዎችን አካፍለዋል፡፡
በተጨማሪም በወርኃዊ አስተዋጽኦ፣ ኦዲት፣ ሥነ ምግባር መመሪያዎች፤ የግቢ ጉባዔ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር እና የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር ሥራዎችን የሚሠሩባቸው መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል።
የደብረ ታቦር ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ዶ/ር ለማ ጉልላት “ኦርቶዶክሳዊ የሕይወት ክህሎት” በሚል ርእሰ ጉዳይ ሥልጠና የሰጡ ሲሆን መንፈሳዊ አገልግሎትን፣ ግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ሕይወትን በጥበብ ለመምራት የሚያግዝ ችሎታ መሆኑን ለተሳታፊዎቹ አስረድተዋል፡፡
ከዋናው ማእከል በቨርችዋል (በበይነ መረብ) ̏አባላትን መምራት እና ማሰማራት˝ በሚል ርዕስ የአባላት አገልግሎት ማስተባበሪያ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ሽመልስ ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ እና የሀገር ውስጥ ማእከላት አግልግሎት ዋና ክፍል ኀላፊ ዲ/ን መንግሥት ሰጠው እንደ ዋና ማእከል ለተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ተሳታፊዎች ማእከሉ ያስገነባውንና የመማር ማስተማር ሥራ ያስጀመረበትን ባለ 18 ክፍል G+1 የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ሕንጻ ግንባታ ጎብኝተዋል፡፡
ኅዳር ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ታቦር ማእከል ከ13 ወረዳ ማእከላት ለተውጣጡ 71 ሥራ አስፈጻሚዎች የሥልጠና እና ውይይት መርሐ ግብር ከጥቅምት 28 ቀን እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄዱን ተገልጿል፡፡
በመርሐ ግብሩ 2018 ዓ.ም በጸደቀው እቅድ ላይ ገለጻ እና ውይይት የተደረገ ሲሆን የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ወረዳ ማእከላት የልምድ ልውውጥና ተሞክሮዎችን አካፍለዋል፡፡
በተጨማሪም በወርኃዊ አስተዋጽኦ፣ ኦዲት፣ ሥነ ምግባር መመሪያዎች፤ የግቢ ጉባዔ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አተገባበር እና የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር ሥራዎችን የሚሠሩባቸው መንገዶች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል።
የደብረ ታቦር ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ዶ/ር ለማ ጉልላት “ኦርቶዶክሳዊ የሕይወት ክህሎት” በሚል ርእሰ ጉዳይ ሥልጠና የሰጡ ሲሆን መንፈሳዊ አገልግሎትን፣ ግላዊም ሆነ ማኅበራዊ ሕይወትን በጥበብ ለመምራት የሚያግዝ ችሎታ መሆኑን ለተሳታፊዎቹ አስረድተዋል፡፡
ከዋናው ማእከል በቨርችዋል (በበይነ መረብ) ̏አባላትን መምራት እና ማሰማራት˝ በሚል ርዕስ የአባላት አገልግሎት ማስተባበሪያ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ሽመልስ ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ እና የሀገር ውስጥ ማእከላት አግልግሎት ዋና ክፍል ኀላፊ ዲ/ን መንግሥት ሰጠው እንደ ዋና ማእከል ለተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ተሳታፊዎች ማእከሉ ያስገነባውንና የመማር ማስተማር ሥራ ያስጀመረበትን ባለ 18 ክፍል G+1 የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤት ሕንጻ ግንባታ ጎብኝተዋል፡፡
👏22❤21👍6🙏2
ማኅበረ ቅዱሳን በዘንድሮው ዓመት ሁለት አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች ግንባታ አጠናቅቆ ለሀገረ ስብከታቸው እንደሚያስረክብ አስታወቀ
ኅዳር ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም ሁለት አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች ግንባታ አጠናቅቆ ለሀገረ ስብከታቸው እንደሚያስረክብ አስታውቋል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶችን መገንባት የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማስፈጸም ብቁ የሆኑ ደቀ መዛሙርትንና ከፍ ሲልም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን በማፍራት ለምእመናን አስፈላጊውን የሃይማኖት አገልግሎት መስጠት በሚችሉበት መንገድ እንዲወጡ የሚያደርግ በመሆኑ አስፈላጊነቱ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በፕሮጀክት ደረጃ የሚሠራቸውን ሥራዎች በሙሉ ጥናት በማድረግ የሚሠራ ተቋም ሲሆን በዚህም በአንድ ሀገረ ስብከት ቢያንስ አንድ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት እንዲኖር እየገነባና ነባር አብነት ትምህርት ቤቶችን ደግሞ የማጠናከር ሥራ ለረጅም ጊዜያት እየሠራ ይገኛል ሲሉ ኃላፊዋ ተናግረዋል፡፡
ኅዳር ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም ሁለት አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች ግንባታ አጠናቅቆ ለሀገረ ስብከታቸው እንደሚያስረክብ አስታውቋል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶችን መገንባት የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማስፈጸም ብቁ የሆኑ ደቀ መዛሙርትንና ከፍ ሲልም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን በማፍራት ለምእመናን አስፈላጊውን የሃይማኖት አገልግሎት መስጠት በሚችሉበት መንገድ እንዲወጡ የሚያደርግ በመሆኑ አስፈላጊነቱ ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በፕሮጀክት ደረጃ የሚሠራቸውን ሥራዎች በሙሉ ጥናት በማድረግ የሚሠራ ተቋም ሲሆን በዚህም በአንድ ሀገረ ስብከት ቢያንስ አንድ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤት እንዲኖር እየገነባና ነባር አብነት ትምህርት ቤቶችን ደግሞ የማጠናከር ሥራ ለረጅም ጊዜያት እየሠራ ይገኛል ሲሉ ኃላፊዋ ተናግረዋል፡፡
❤33🙏3
በዘንድሮ ዓመትም በቤንሻንጉል ጉሙዝ የአሶሳ ሀገረ ስብከት የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ በአሶሳ አምባ አራት ሐመረ ኖህ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም እና የካፋ ሀገረ ስብከት ቦንጋ የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ በቦንጋ ከተማ እየተገነቡ የሚገኙት፣ በአዳሪነት 32ተማሪዎች የሚያስተናግዱ ሲሆን በአጠቃላይ ከ40 በላይ ደቀ መዛሙርት በአንድ ጊዜ የማስተማር አቅም ያላቸው ሁለቱ አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆኑ ኢ/ር ማስተዋል አበበ አክለው ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በዚህ ዓመት የሚጀመሩ አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች እንደሚኖሩ እና አገልግሎት ላይ ለሚገኙ ደግሞ ከሀገረ ስብከታቸው ጋር በመነጋገር ልዩ ልዩ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግላቸው የገለጹት ኢ/ር ማስተዋል አበበ በመጨረሻም ከአብነት ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ደቀ መዛሙርት ለቤተ ክርስቲያን፣ ለማኅበረሰብና ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች በመሆናቸው ማንኛውም አካል የአብነት ትምህርት ቤቶቻችንን ሊጠብቃቸውና ሊደግፋቸው ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡👇👇👇👇👇👇👇
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://www.tg-me.com/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
:- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905
በተጨማሪም በዚህ ዓመት የሚጀመሩ አዳዲስ አዳሪ አብነት ትምህርት ቤቶች እንደሚኖሩ እና አገልግሎት ላይ ለሚገኙ ደግሞ ከሀገረ ስብከታቸው ጋር በመነጋገር ልዩ ልዩ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግላቸው የገለጹት ኢ/ር ማስተዋል አበበ በመጨረሻም ከአብነት ትምህርት ቤቶች የሚገኙ ደቀ መዛሙርት ለቤተ ክርስቲያን፣ ለማኅበረሰብና ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎች በመሆናቸው ማንኛውም አካል የአብነት ትምህርት ቤቶቻችንን ሊጠብቃቸውና ሊደግፋቸው ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡👇👇👇👇👇👇👇
የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች ይቀላቀሉ
ቴሌግራም፡- http://www.tg-me.com/mkpublicrelation
የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/
ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org
ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK
:- https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤41🙏13👍5
"...ምእመናን የሚገዟቸውን ቅዱሳት መጻሕፍት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር የትኛው አካል ኃላፊነት እንደወሰደበት ማጣራት አለባቸው... "በመልእክት ዐምድ ✍️ ሐመር መጽሔት ኅዳር ፳፻፲፰ ዓ.ም
༺ ༻
#የኅትመት ዘመን ፦#ኅዳር ፳፻፲፰ ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
• ገጽ ብዛት፦፳፰
ዋጋ ፦፵ ብር
• ሐመር መጽሔት ፴፪ ኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ #ኅዳር ፳፻፲፰ ዓ.ም መልእክት #ዘማኅበረ ቅዱሳን " #በውሸት ዕውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍ ራቅ "በሚል በመልእክት ዐምዷ ታስነብባለች።
.#ዐውደ ስብከት ሥር”#በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ "በሚል ርእስ ስለጾም በስፋት ታስነብባለች።
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “#ፀሐይን የተጎናጸፈች ሴት አየሁ " በሚል ዐቢይ ርእስ ቅዱሳት መጻሕፍት በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአኃት አብያተ ክርስቲያን ምን ትማር? ክፍል -፫ በሚል በዲ/ን ዶ/ር #ታደለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአኃት አብያተ ክርስቲያን ምን ትማር? የሚሉ ተያያዥ ነጥቦችን በዝርዝር ያሳያል ።ክህነትን ስለመጠበቅ፤ገዳማዊ ሕይወትን ስለመጠበቅ ፣ወጣቱን ትውልድ ከመታደግ አንጻር ፣መንፈሳዊ ሕይወትን ከዓለማዊ ሕይወት ጋር አስተባብሮ ከመያዝ አንጻር ፣ሁለንተናዊ አቅምን በማሳደግ ለመጪው ትውልድ ከማስተላለፍ አንጻር ከሌሎቹ ምን እንማ፤የኢኮኖሚ አቅምን ማጠናከር እና ተግዳሮቶችን መቋቋም የሚሉት ጉዳዮች ተዳሰዋል።
༺ ༻
#የኅትመት ዘመን ፦#ኅዳር ፳፻፲፰ ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
• ገጽ ብዛት፦፳፰
ዋጋ ፦፵ ብር
• ሐመር መጽሔት ፴፪ ኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ #ኅዳር ፳፻፲፰ ዓ.ም መልእክት #ዘማኅበረ ቅዱሳን " #በውሸት ዕውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍ ራቅ "በሚል በመልእክት ዐምዷ ታስነብባለች።
.#ዐውደ ስብከት ሥር”#በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ "በሚል ርእስ ስለጾም በስፋት ታስነብባለች።
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “#ፀሐይን የተጎናጸፈች ሴት አየሁ " በሚል ዐቢይ ርእስ ቅዱሳት መጻሕፍት በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአኃት አብያተ ክርስቲያን ምን ትማር? ክፍል -፫ በሚል በዲ/ን ዶ/ር #ታደለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከአኃት አብያተ ክርስቲያን ምን ትማር? የሚሉ ተያያዥ ነጥቦችን በዝርዝር ያሳያል ።ክህነትን ስለመጠበቅ፤ገዳማዊ ሕይወትን ስለመጠበቅ ፣ወጣቱን ትውልድ ከመታደግ አንጻር ፣መንፈሳዊ ሕይወትን ከዓለማዊ ሕይወት ጋር አስተባብሮ ከመያዝ አንጻር ፣ሁለንተናዊ አቅምን በማሳደግ ለመጪው ትውልድ ከማስተላለፍ አንጻር ከሌሎቹ ምን እንማ፤የኢኮኖሚ አቅምን ማጠናከር እና ተግዳሮቶችን መቋቋም የሚሉት ጉዳዮች ተዳሰዋል።
❤13🙏9🤔5👍1
• #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#ኦርቶዶክሳዊ ኅብረት "በሚል ርእስ የኦርቶዶክሳዊ ኅብረት ጥቅሞች ፤የኦርቶዶክሳዊ ኅብረት መገለጫ ምን መሆን እንዳለበት ታሰተምራለች።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኘውን “የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን " ክፍል አንድ በሚል ርእስ ስለ አመሠራረቱ ታስቃኛለች ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር “ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከእኛ ምን ይጠበቃ? ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከእኛ የሚጠበቁትን መሠረታዊ ነጥቦች በመዘርዘር ታስነብባለች።
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "# ሩሐማ " ክፍል አንድ በሚል ታስነብባለች ።
• #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ ወይም የአዲሱ ዘመን መንፈሳዊነት # ክፍል_፩ " በሚል ርእስና ተያያዥ ጉዳዮች መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ ጋር የተደረገ ጥያቄና መልስ ይዛለች ።
ሐመር መጽሔት ፴፪ ኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !
magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔት ዝግጅት ክፍል
━━━━━༺✞༻━━━━
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኘውን “የረቢ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን " ክፍል አንድ በሚል ርእስ ስለ አመሠራረቱ ታስቃኛለች ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር “ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከእኛ ምን ይጠበቃ? ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከእኛ የሚጠበቁትን መሠረታዊ ነጥቦች በመዘርዘር ታስነብባለች።
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "# ሩሐማ " ክፍል አንድ በሚል ታስነብባለች ።
• #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ ወይም የአዲሱ ዘመን መንፈሳዊነት # ክፍል_፩ " በሚል ርእስና ተያያዥ ጉዳዮች መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ ጋር የተደረገ ጥያቄና መልስ ይዛለች ።
ሐመር መጽሔት ፴፪ ኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !
magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔት ዝግጅት ክፍል
━━━━━༺✞༻━━━━
❤40🙏9👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የዕጣው መውጫ ቀን ደረሰ! ይፍጠኑ! አሁኑኑ ትኬቱን በመግዛትና ለሌሎችም በማሠራጨት ኦርቶዶክሳዊ ግዴታዎን ይወጡ፡፡
🙏30❤19👍9
