በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል 574 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን ማስመረቁ ተጠቆመ
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አሶሳማእከል በአሶሳ ዩንቨርስቲና በአሶሳ ከተማ መንግስት ና ግል ኮሌጆች በመደበኛ ግቢ ጉባኤያት ከዓለማዊ ትምህርታቸዉ ጎን ለጎን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሲያስተምራቸዉ የነበሩ 574 ተማሪዎችን ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል በመምህራን እና ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች ቀርቦ የአደራ መስቀል ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አሶሳማእከል በአሶሳ ዩንቨርስቲና በአሶሳ ከተማ መንግስት ና ግል ኮሌጆች በመደበኛ ግቢ ጉባኤያት ከዓለማዊ ትምህርታቸዉ ጎን ለጎን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሲያስተምራቸዉ የነበሩ 574 ተማሪዎችን ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል በመምህራን እና ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች ቀርቦ የአደራ መስቀል ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ሀዋሳ ማእከል በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ፣ ግብርና ኮሌጅና ሪፈራል ግቢ ሲያስተምራቸው የነበሩ 250 ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳ ሀዋሳ ማእከል በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ፣ ግብርና ኮሌጅና ሪፈራል ግቢ ሲያስተምራቸው የነበሩ 250 ተማሪዎችን ሀዋሳ ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስመርቋል።
በማኅበ ቅዱሳን ደቡብ ማእከላት ማስተባበርያ ጽ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ እንጅነር አሰፋ ቦረና እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና አግኝቶ ከተመሠረተ ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በኀላፊነት የተሰጡትን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን በግቢ ጉባኤያት የማስተባበር፣ የማስተማር አገልግሎቱን ትናንትም ዛሬም እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
“ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት” የሚለውን የማኅበሩን ርእይ እውን ለማድረግ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦርቶዶክሳውያን ተመራቂ ተማሪዎች እንዲመጣ የፈለገው ውጤት በእናንተ ሕይወት ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግና የቤተ ክርስቲያንን ችግሮች ለመፍታት የመፍትሔው አካል ከመሆን አንጻር ከምሩቃን የምንጠብቀው አደራ ቀላል የሚባል አይደለም በማለት ተመራቂዎች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ስብሐት ቀሲስ ኪነ ጥበብ ያለው ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም በአብነት እና በአስኳላው ትምህርት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሽልማት ስነ ስርዓት ተካሂዷል።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳ ሀዋሳ ማእከል በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ፣ ግብርና ኮሌጅና ሪፈራል ግቢ ሲያስተምራቸው የነበሩ 250 ተማሪዎችን ሀዋሳ ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስመርቋል።
በማኅበ ቅዱሳን ደቡብ ማእከላት ማስተባበርያ ጽ/ቤት ኃላፊ ቀሲስ እንጅነር አሰፋ ቦረና እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና አግኝቶ ከተመሠረተ ከ1984 ዓ.ም ጀምሮ በኀላፊነት የተሰጡትን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን በግቢ ጉባኤያት የማስተባበር፣ የማስተማር አገልግሎቱን ትናንትም ዛሬም እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
“ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት” የሚለውን የማኅበሩን ርእይ እውን ለማድረግ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦርቶዶክሳውያን ተመራቂ ተማሪዎች እንዲመጣ የፈለገው ውጤት በእናንተ ሕይወት ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግና የቤተ ክርስቲያንን ችግሮች ለመፍታት የመፍትሔው አካል ከመሆን አንጻር ከምሩቃን የምንጠብቀው አደራ ቀላል የሚባል አይደለም በማለት ተመራቂዎች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።
የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ስብሐት ቀሲስ ኪነ ጥበብ ያለው ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም በአብነት እና በአስኳላው ትምህርት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሽልማት ስነ ስርዓት ተካሂዷል።
በከሚሴ ሀገረ ስብከት በከሚሴ ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን ሰበካ ጉባኤ የሚመራ ኦርቶዶክሳዊ የምክክር ተቋም ተቋቋመ ።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ማኅበራዊ ቀውሶች የሚፈጥሩትን የሥነ ልቦናና አእምሯዊ ችግር ለማቃለል በዘርፉ የሚሠሩ አመካካሪዎች ለማፍራትና ተቋማትን ለማስፋፋት ሰፊ ሥልታዊ ተግባራትን በሁሉም ማእከላት እየፈጸመ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በማኅበረ ቅዱሳን ከሚሴ ማእከል አስተባባሪነት በሁሉም ወረዳ ማእከላት ከሀገረ ስብከቱና ከሁለቱም ወረዳ ቤተ ክህነት ከከሚሴ ፣ ባቲና ጨፋ ሮቢት ወረዳ ማእከላት ጋር ሲሰጥ የነበረው ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን በሁሉም ዘርፍ የማጠናከርና የማማከር አገልግሎትን ሊያሰፋ የሚያስችል የአመካካሪነት ክህሎት፣ ትምህርተ አበ ነፍስ፣ ኦርቶዶክሳዊ የልጆች አስተዳደግና ጋብቻ፣ ሱስን ለመከላከል የኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ መፍትሔዎች፣ የምክክር አገልግሎት በሰፊው ሥልጠና ከተሰጠ በኋላ ተቋሙ የተቋቋመ መሆኑ ተገልጿል።
በተቋም ምሥረታውም ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ደጀን ተስፋዬ፣ የሀገረ ስብከቱ ሰራተኞች፣ የሁለቱም ወረዳ ቤተ ክህነት ሊቃነ ካህናትና ሠራተኞች፣ የከሚሴ ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና የሰበካ ጉባኤ አባላት፣ የማኅበረ ቅዱሳን ከሚሴ ወረዳ ማእከል ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ሥልጠናውን ሲያሳልጡ የነበሩ አሠልጣኞች ተገኝተዋል።
ይህን ተቋም ሊያስቀጥሉ የሚችሉ ከሁሉም ባለሙያ ስብጥር ያላቸው አካላት የተመረጡ ሲሆን የተመረጡት አካላትም ከቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና ከሁሉም ተቋማት ጋር በመናበብ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ሥራ መሥራት እንዳለባቸው አጽንኦት ተሰጥቶበታል ።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ማኅበራዊ ቀውሶች የሚፈጥሩትን የሥነ ልቦናና አእምሯዊ ችግር ለማቃለል በዘርፉ የሚሠሩ አመካካሪዎች ለማፍራትና ተቋማትን ለማስፋፋት ሰፊ ሥልታዊ ተግባራትን በሁሉም ማእከላት እየፈጸመ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በማኅበረ ቅዱሳን ከሚሴ ማእከል አስተባባሪነት በሁሉም ወረዳ ማእከላት ከሀገረ ስብከቱና ከሁለቱም ወረዳ ቤተ ክህነት ከከሚሴ ፣ ባቲና ጨፋ ሮቢት ወረዳ ማእከላት ጋር ሲሰጥ የነበረው ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን በሁሉም ዘርፍ የማጠናከርና የማማከር አገልግሎትን ሊያሰፋ የሚያስችል የአመካካሪነት ክህሎት፣ ትምህርተ አበ ነፍስ፣ ኦርቶዶክሳዊ የልጆች አስተዳደግና ጋብቻ፣ ሱስን ለመከላከል የኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ መፍትሔዎች፣ የምክክር አገልግሎት በሰፊው ሥልጠና ከተሰጠ በኋላ ተቋሙ የተቋቋመ መሆኑ ተገልጿል።
በተቋም ምሥረታውም ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ደጀን ተስፋዬ፣ የሀገረ ስብከቱ ሰራተኞች፣ የሁለቱም ወረዳ ቤተ ክህነት ሊቃነ ካህናትና ሠራተኞች፣ የከሚሴ ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪና የሰበካ ጉባኤ አባላት፣ የማኅበረ ቅዱሳን ከሚሴ ወረዳ ማእከል ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ሥልጠናውን ሲያሳልጡ የነበሩ አሠልጣኞች ተገኝተዋል።
ይህን ተቋም ሊያስቀጥሉ የሚችሉ ከሁሉም ባለሙያ ስብጥር ያላቸው አካላት የተመረጡ ሲሆን የተመረጡት አካላትም ከቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና ከሁሉም ተቋማት ጋር በመናበብ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ሥራ መሥራት እንዳለባቸው አጽንኦት ተሰጥቶበታል ።
የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አሰኪያጅ መልአከ ገነት ደጀን ተስፋዬ ቀጣዩን ትውልድ በምን መንገድ ነው መምራት ያለብን ዝም ብሎ በማየትና በመመልከት አንድነትን ያወቀ፣ በእውቀት የመጠቀ፣ በአዕምሮ የተራቀቀ፣ እውቀትና ክህሎት፤ እምነትና ምግባርን አጣምሮ የያዘ ትውልድ መፍጠር ለሀገርም ሆነ ለቤተክርስቲያን ወሳኝ መሆኑን አውቆና ተረድቶ ለዚህም ደግሞ ሳይሰላቹ በድካም ውስጥም ሆኖም ቢሆን መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በመጨረሻም ሥልጠናውን በትጋትና በቅንነት ሲሰጡ ለነበሩ አሠልጣኞችም የምሥጋናና እውቅና ምሥክር ወረቀት ተሰጥቷል ።
በመጨረሻም ሥልጠናውን በትጋትና በቅንነት ሲሰጡ ለነበሩ አሠልጣኞችም የምሥጋናና እውቅና ምሥክር ወረቀት ተሰጥቷል ።
ማኅበረ ቅዱሳን በሚዛን ደብረ በረከት አቡነ ተ/ሃይማኖት እና ቅ/ዑራኤል የእናቶች ገዳም ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በገዳሙ በሚገኘው የአቡነ ሕዝቅኤል አብነት ት/ቤት ሰኔ 16/2017 ዓ/ም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ለ4 ወራት ያስተማራቸውን ዲያቆናት አስመርቋል።
አጠቃላይ 24ተመራቂ ተማሪዎች ሲሆኑ ዘጠኝ የተለያዩ ቋንቋዎች ተናጋሪ ናቸው ተብሏል።
ይህም የካህናት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች በራሳቸው ቋንቋ ለማገልገል ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
ዲያቆናቱ ከካፋ ሸካ ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕ/ኦሞ ሀገረ ስብከት ስር ከሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ተመልምለው ወደ አብነት ት/ቤቱ የገቡ ሲሆን በጎ አድራጊ ምእመናንን በማስተባበር አስፈላጊውን ወጪ በመሸፈን ለአራት ወራት መሠረታዊ የክህነት ትምህርትና የትምህረተ ሃይማኖት ኮርሶችን ማስተማር የተቻለ ሲሆን ከነዚህም መካከል ሁለቱ ማእረገ ቅስና ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የካፋና ሸካ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሰዋሰወ ብርሃን ቅ/ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ በምርቃት መርሐ ግብሩ እንደተናገሩት "ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከልና የሚዛን ማእከል በጋራ በመሆን ሀገረ ስብከቱ መሥራት የነበረበትን ሥራ ሠርቷል ሲሉ ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም አገልጋይ ካህናትን የማፍራት ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥል ያሉ ሲሆን ተመራቂዎች መማራችሁ ጥሩ ነው የነፍስ ዋጋን ይዛችኋልና ሕዝባችሁን በቅንነት አገልግሉ " ሲሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
ሰኔ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በገዳሙ በሚገኘው የአቡነ ሕዝቅኤል አብነት ት/ቤት ሰኔ 16/2017 ዓ/ም የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ለ4 ወራት ያስተማራቸውን ዲያቆናት አስመርቋል።
አጠቃላይ 24ተመራቂ ተማሪዎች ሲሆኑ ዘጠኝ የተለያዩ ቋንቋዎች ተናጋሪ ናቸው ተብሏል።
ይህም የካህናት እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች በራሳቸው ቋንቋ ለማገልገል ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
ዲያቆናቱ ከካፋ ሸካ ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕ/ኦሞ ሀገረ ስብከት ስር ከሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ተመልምለው ወደ አብነት ት/ቤቱ የገቡ ሲሆን በጎ አድራጊ ምእመናንን በማስተባበር አስፈላጊውን ወጪ በመሸፈን ለአራት ወራት መሠረታዊ የክህነት ትምህርትና የትምህረተ ሃይማኖት ኮርሶችን ማስተማር የተቻለ ሲሆን ከነዚህም መካከል ሁለቱ ማእረገ ቅስና ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የካፋና ሸካ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሰዋሰወ ብርሃን ቅ/ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ በምርቃት መርሐ ግብሩ እንደተናገሩት "ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከልና የሚዛን ማእከል በጋራ በመሆን ሀገረ ስብከቱ መሥራት የነበረበትን ሥራ ሠርቷል ሲሉ ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም አገልጋይ ካህናትን የማፍራት ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥል ያሉ ሲሆን ተመራቂዎች መማራችሁ ጥሩ ነው የነፍስ ዋጋን ይዛችኋልና ሕዝባችሁን በቅንነት አገልግሉ " ሲሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
"የጉባኤቤትቆይታችሁስኬት የሚለካውባገኛችሁት ዕውቀት ብቻ ሳይሆን በምትሰማሩበት መንፈሳዊ አገልግሎት የድካምና የመሰልቸት መንፈስ ሳይሰማችሁ ቃለ እግዚአብሔር ለተጠማውና በጠረፍ ላለው ሕዝባችሁ በመድረስ ወደ ቅድስና ሕይወት ስትመሩ ነው" ያሉት ደግሞ በማኅበረ ቅዱሳን የቤ/ን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ት/ቤቶች አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ዲ/ን ደረጀ ጋረደው እንደሆኑ ተመላክቷል።
ዳይሬክተሩ ጨምረው እንደተናገሩት በዚህ ዓመት ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተመረጡ 169 የአብነት ት/ቤቶች፣ ለ229 መምህራንና 2000 የአብነት ደቀ መዛሙርት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ዕቅድ ይዞ ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ለዛሬዎቹ ተመራቂዎች ለሕክምና ፣ለትምህርት፣ ለቀለብና ለመሳሰሉት ድጋፍ አድራጊዎችን በማስተባበር 842,650.00 ብር ወጪ በማድረግ እንዲማሩ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
የሚዛን ተፈሪ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ር ጥላሁን ታደሰ በበኩላቸው የአገልጋይ ካህናት እጥረትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ብዙ ፈተናዎች ቢኖሩም ዛሬ ለአራት ወራት ያስተማርናቸው አገልጋይ ካህናትን በማስመረቃችን ደስ ብሎናል ብለዋል።
በሸካ ፣ ቤንቺ ሸኮ እና ምዕ/ ኦሞ ሀገረ ስብከት 197 አብያተ ክርስቲያናት መካከል 5ቱ ገዳማት ሲሆኑ በአገልጋይ እጥረት ምክንያት አንድ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ የተዘጋ፣ 25ቱ አብያተ ክርስቲያናት በአመት የሚቀደስባቸው፣ 5ቱ ወርሐዊ በዓላትን በመጠበቅ የሚቀደስባቸው፣ ከ100 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሰንበት ት/ቤት የሌላቸውና ሰርክ ጉባኤ የማይሰጥባቸው እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
መሠረታዊ የክህነት ት/ት የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶች የተማሩትና ለምርቃት የበቁት ደቀ መዛሙርቱ በአካባቢያቸው ቋንቋ በማስተማር እና የክህነት አገልግሎቱን በመስጠት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ዳይሬክተሩ ጨምረው እንደተናገሩት በዚህ ዓመት ከተለያዩ አህጉረ ስብከት ለተመረጡ 169 የአብነት ት/ቤቶች፣ ለ229 መምህራንና 2000 የአብነት ደቀ መዛሙርት ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ዕቅድ ይዞ ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ለዛሬዎቹ ተመራቂዎች ለሕክምና ፣ለትምህርት፣ ለቀለብና ለመሳሰሉት ድጋፍ አድራጊዎችን በማስተባበር 842,650.00 ብር ወጪ በማድረግ እንዲማሩ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
የሚዛን ተፈሪ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት መ/ር ጥላሁን ታደሰ በበኩላቸው የአገልጋይ ካህናት እጥረትን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ብዙ ፈተናዎች ቢኖሩም ዛሬ ለአራት ወራት ያስተማርናቸው አገልጋይ ካህናትን በማስመረቃችን ደስ ብሎናል ብለዋል።
በሸካ ፣ ቤንቺ ሸኮ እና ምዕ/ ኦሞ ሀገረ ስብከት 197 አብያተ ክርስቲያናት መካከል 5ቱ ገዳማት ሲሆኑ በአገልጋይ እጥረት ምክንያት አንድ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ የተዘጋ፣ 25ቱ አብያተ ክርስቲያናት በአመት የሚቀደስባቸው፣ 5ቱ ወርሐዊ በዓላትን በመጠበቅ የሚቀደስባቸው፣ ከ100 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሰንበት ት/ቤት የሌላቸውና ሰርክ ጉባኤ የማይሰጥባቸው እንደሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
መሠረታዊ የክህነት ት/ት የትምህርተ ሃይማኖት ኮርሶች የተማሩትና ለምርቃት የበቁት ደቀ መዛሙርቱ በአካባቢያቸው ቋንቋ በማስተማር እና የክህነት አገልግሎቱን በመስጠት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል።