መርሐግብሩን - Join Zoom Meeting
meeting ID: 849 6710 2865
Passcode: 825584
ወይም ደግሞ
https://www.tg-me.com/+e_alNr2w1RpmNDY0 ቴሌግራም ላይ ይከታተሉ።
meeting ID: 849 6710 2865
Passcode: 825584
ወይም ደግሞ
https://www.tg-me.com/+e_alNr2w1RpmNDY0 ቴሌግራም ላይ ይከታተሉ።
❤26🙏7👏6👍1🤔1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ማኅበረ ቅዱሳን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሥነ-ልቡና የተረዱ፣ ብቁና በቂ ኦርቶዶክሳውያን መምህራንን ለማፍራት ለመማሪያ መጻሕፍት ዝግጅትና ኅትመት፣ እንዲሁም የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የመምህራን ሥልጠና መስጠት የሚያስችል የሥልጠና ማእከል ማቋቋምና ሌሎችም አገልግሎቶች ተግባራዊ ለማድረግ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ የዕጣ ትኬት አዘጋጅቶ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሥርጭት ላይ መሆኑ ማኅበሩ ባሉት የተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ሲገለጽ ቆይቷል፡፡
እርስዎም በአንድ በኩል ዕድሎዎን እየሞከሩ ማኅበረ ቅዱሳን ዘመኑን የዋጀ ንቁ ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ ለማፍራት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ፕሮጀክቶቹን ለመደገፍ የድርሻዎን ይወጡ፡፡
እርስዎም በአንድ በኩል ዕድሎዎን እየሞከሩ ማኅበረ ቅዱሳን ዘመኑን የዋጀ ንቁ ኦርቶዶክሳዊ ትውልድ ለማፍራት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ፕሮጀክቶቹን ለመደገፍ የድርሻዎን ይወጡ፡፡
❤92🙏14👍5🤔2
መርሐግብሩን ለመከታተል- Join Zoom Meeting
meeting ID: 849 6710 2865
Passcode: 825584
ወይም ደግሞ
https://www.tg-me.com/+e_alNr2w1RpmNDY0 ቴሌግራም ላይ ይከታተሉ።
meeting ID: 849 6710 2865
Passcode: 825584
ወይም ደግሞ
https://www.tg-me.com/+e_alNr2w1RpmNDY0 ቴሌግራም ላይ ይከታተሉ።
❤19🙏6👏1
በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት በዳዉሮ ሀገረ ስብከት ዛባ ጋዞ ወረዳ የተገነባው የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በተገኙበት መመረቁ ተገለጸ
ጥቅምት ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማዳራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማእከል በዳዉሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት በዛባ ጋዞ ወረዳ ቤተ ክህነት በዱጋ ያስገነባዉን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን አስመረቋል፡፡
የዳዉሮ፤ ኮንታ፣ ካምባታ፣ ጣምባሮ እና ሀላባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በመስከረም 30/2018 ዓ.ም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ባርከዉ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበረ ክብሩ መግባቱን የተገለጸ ሲሆን ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዕነታቸዉን ጨምሮ የዳዉሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል፣ የየመምሪያዉ ኃላፊዎች፣ የዛባ ጋዞ ወረዳ ምክትል አስተዳዳር፣ እንዲሁም የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣ የወረዳዉ የየአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ካህናት አባቶች፣ ከሁሉም ወረዳ ማእከላት የተሳተፉ ምእመናን፣ የዋናዉ ማእከል ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ምእመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡
የዳዉሮ፤ ኮንታ፣ ካምባታ፣ ጣምባሮ እና ሀላባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ እና የቅዱስ ስኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በንግግራቸዉ ”ይህን የመሰለ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገንብቶ እንዲህ ደምቀን፣ በዝተን በክብር ላቆመን እግዚአብሔር ምስጋና አቅርበዉ″ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ጥቅምት ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማዳራጃ መምሪያ ማኀበረ ቅዱሳን ዋናዉ ማእከል በዳዉሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት በዛባ ጋዞ ወረዳ ቤተ ክህነት በዱጋ ያስገነባዉን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን አስመረቋል፡፡
የዳዉሮ፤ ኮንታ፣ ካምባታ፣ ጣምባሮ እና ሀላባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በመስከረም 30/2018 ዓ.ም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ባርከዉ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበረ ክብሩ መግባቱን የተገለጸ ሲሆን ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዕነታቸዉን ጨምሮ የዳዉሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል፣ የየመምሪያዉ ኃላፊዎች፣ የዛባ ጋዞ ወረዳ ምክትል አስተዳዳር፣ እንዲሁም የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣ የወረዳዉ የየአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ካህናት አባቶች፣ ከሁሉም ወረዳ ማእከላት የተሳተፉ ምእመናን፣ የዋናዉ ማእከል ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ምእመናን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡
የዳዉሮ፤ ኮንታ፣ ካምባታ፣ ጣምባሮ እና ሀላባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ እና የቅዱስ ስኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በንግግራቸዉ ”ይህን የመሰለ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገንብቶ እንዲህ ደምቀን፣ በዝተን በክብር ላቆመን እግዚአብሔር ምስጋና አቅርበዉ″ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
❤20👏3🙏1
ብጹዕ አቡነ ጢሞቴዎስ አክለውም ይህን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ለገነባዉ ማኀበረ ቅዱሳን እና የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ ግለሰብ ከፍተኛ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ከቤተ ክርስቲያን ይዞታ ጋር ተያይዞ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት ለተባበሩ ለወረዳ መንግሥት፣ ለዱጋ ማዘጋጃዊ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት እና የአካባቢን ሕዝብ በማመስገን አያይዘውም በሀገር ስብከቱ ያሉ ችግሮችን በመፍታት እንደዚህ በቅንጅት መሥራት የሚያስፈልግ በመሆኑ የማኀበረ ቅዱሳን ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ይህ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ሕዝቡ እንዲገለገልበት፣ እንዲባረክበት፣ እግዚአብሔር እንዲከብርበት፣ለአካባቢ ሰላም፣ በረከት እንዲመጣ የሚፀለይበት በመሆኑ ሕዝበ ምእመናን መበርታት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
የዛባ ጋዞ ወረዳ ምክትል አስተዳዳር አቶ ተመስገን ሳዊሮ የኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሀገር ባለዉለታ በመሆኗ እንደዚህ ዓይነት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በወረዳችን መገንባቱ ለአካባቢ በረከት በመሆኑ የወረዳዉ መንግሥት ከቤተ ክርስቲያኗ ጎን መሆኑን በንግግራቸዉ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዳዊት ዳና የወረዳዉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በበኩላቸዉ ቤተ ክርስቲያኒቷ የሰላም፣ የአንድነት እና የፍቅር ተመሳሌት መሆኗን በማዉሳት በማንኛዉም ጉዳዮች ድጋፋቸዉ እንደማይለይ በማረጋገጥ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማእከል ትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ በበኩላቸው ይህ ቤተ ክርስቲያን የአካባቢ ነባራዊ ሁኔታውን መሠረት በማድረግ በቀረበው ጥናት ማእከሉ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እንዲገነባ በመፍቀድ በየካቲት ወር 21/2017 ዓ.ም ግንባታው በይፋ ተጀምሮ በነሐሴ 2017 ዓ.ም በስድስት ወራት ውስጥ የህንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን ገልጸዋል፡፡
የግንባታው አጠቃላይ ወጪ 6.4 ሚሊዮን ብር የፈጀ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ይህ ግንባታን ከጅምር እስከ ፍጻሜ ድረስ አባታዊ ስምሪት በመስጠት ክትትልና ድጋፍ ላደረጉ ለብጹዕነታቸዉ፣ ለዳዉሮ ሀገረ ስብከት፣ ለማኀበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል፣ ለወረዳ መንግሥት፣ ግንባታዉን ላካሄደ ኮንትራከተር እና ለአካባቢው ምእመን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በስተመጨረሻም በሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ በዳዉሮ ሀገረ ስብከት፣ በማኀበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል እና በወረዳ ቤተ ክህነት የተዘጋጀዉን የእዉቅና ሰርተፍኬት የተሰጠ ሲሆን በዕለቱ ስድሳ/60/ አዳዲስ አማኒያን ተጠምቀዉ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደተቀላቀሉ ተጠቁሟል፡፡
ብፁዕነታቸው ይህ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ሕዝቡ እንዲገለገልበት፣ እንዲባረክበት፣ እግዚአብሔር እንዲከብርበት፣ለአካባቢ ሰላም፣ በረከት እንዲመጣ የሚፀለይበት በመሆኑ ሕዝበ ምእመናን መበርታት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
የዛባ ጋዞ ወረዳ ምክትል አስተዳዳር አቶ ተመስገን ሳዊሮ የኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሀገር ባለዉለታ በመሆኗ እንደዚህ ዓይነት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በወረዳችን መገንባቱ ለአካባቢ በረከት በመሆኑ የወረዳዉ መንግሥት ከቤተ ክርስቲያኗ ጎን መሆኑን በንግግራቸዉ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዳዊት ዳና የወረዳዉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በበኩላቸዉ ቤተ ክርስቲያኒቷ የሰላም፣ የአንድነት እና የፍቅር ተመሳሌት መሆኗን በማዉሳት በማንኛዉም ጉዳዮች ድጋፋቸዉ እንደማይለይ በማረጋገጥ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ማእከል ትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ በበኩላቸው ይህ ቤተ ክርስቲያን የአካባቢ ነባራዊ ሁኔታውን መሠረት በማድረግ በቀረበው ጥናት ማእከሉ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እንዲገነባ በመፍቀድ በየካቲት ወር 21/2017 ዓ.ም ግንባታው በይፋ ተጀምሮ በነሐሴ 2017 ዓ.ም በስድስት ወራት ውስጥ የህንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን ገልጸዋል፡፡
የግንባታው አጠቃላይ ወጪ 6.4 ሚሊዮን ብር የፈጀ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው ይህ ግንባታን ከጅምር እስከ ፍጻሜ ድረስ አባታዊ ስምሪት በመስጠት ክትትልና ድጋፍ ላደረጉ ለብጹዕነታቸዉ፣ ለዳዉሮ ሀገረ ስብከት፣ ለማኀበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል፣ ለወረዳ መንግሥት፣ ግንባታዉን ላካሄደ ኮንትራከተር እና ለአካባቢው ምእመን ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በስተመጨረሻም በሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ የበኩላቸዉን አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ በዳዉሮ ሀገረ ስብከት፣ በማኀበረ ቅዱሳን ታርጫ ማእከል እና በወረዳ ቤተ ክህነት የተዘጋጀዉን የእዉቅና ሰርተፍኬት የተሰጠ ሲሆን በዕለቱ ስድሳ/60/ አዳዲስ አማኒያን ተጠምቀዉ ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደተቀላቀሉ ተጠቁሟል፡፡
❤42👏13🙏3
፵፬ኛው የሰበካ ጉባኤ ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ በቅዱስ ፓትርያሪኩ ቡራኬ መከፈቱ ተገለጸ
በጉባኤው ከመላው ዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት ተወካዮች እየተሳተፉበት ይገኛል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው
በጉባኤው ከመላው ዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት ተወካዮች እየተሳተፉበት ይገኛል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው
❤19🙏3
"ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው ዓቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ሰብእና በንጽሕና እና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እልፍ አእላፍ አበው እንዳልነበሯት ዛሬ የተሻለ ኑሮና ደመወዝ እያገኘን እግዚአብሔርን እንደቀኖናው በጥንቃቄ ማገልገል አቅቶናል" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ
ጥቅምት ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ
የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ
የአዲስ አበባና ሐድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች ፣
ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር የመጣችሁ የየሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆችና የየክፍሉ ተወካዮች፣
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኃላፊዎች፣
የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ተወካዮች
የምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ጉባኤ የተገኛችሁ ክቡራና ክቡራት
እግዚአብሔር አምላካችን ዓመቱን ጠብቆ በከፍተኛ ጉጉት ለምንጠብቀው 44ኛው የሰበካ ጉባኤ አጠቃላይ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡ እናንተንም እንኳን በደኅና መጣችሁ እንላለን፡፡
ጥቅምት ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ
የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ
የአዲስ አበባና ሐድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች ፣
ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር የመጣችሁ የየሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆችና የየክፍሉ ተወካዮች፣
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኃላፊዎች፣
የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ተወካዮች
የምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች፣
በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ጉባኤ የተገኛችሁ ክቡራና ክቡራት
እግዚአብሔር አምላካችን ዓመቱን ጠብቆ በከፍተኛ ጉጉት ለምንጠብቀው 44ኛው የሰበካ ጉባኤ አጠቃላይ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡ እናንተንም እንኳን በደኅና መጣችሁ እንላለን፡፡
❤17👏2👍1🙏1
“ዑቁ እንከ ዘከመ ተሓውሩ ከመ ጠቢባን በንጽሕ ወአኮ ከመ ዓብዳን፤ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት በንጽሕና እንደምትመላለሱ ዕወቁ” (ኤፌ. 5*15)፤ ሁሉንም መስጠትና መንሣት የሚችለው እግዚአብሔር አምላክ ጥበብን ለሰው ልጆች ሰጥቶአል፤ የሚሰጠው የጥበቡ ደረጃ የተለያየ ቢሆንም እግዚአብሔር ከጥበብ ባዶ አድርጎ የፈጠረው ግን የለም፤ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ለፍጡራን ሲሰጡ ሊጠቀሙባቸው እንጂ እንዲሁ በከንቱ ሊያባክኑዋቸው አይደለም፡፡
ቅዱስ መጽሐፍ ስለ ጥበብ አስፈላጊነት በብዙ ቦታ ያስተምራል፤ በተለይም ጠቢቡ ሰሎሞን “ጥበብ ትኄይስ እምኲሉ መዛግብት ወኲሉ ክብር ኢመጠና ላቲ፤ ከሀብት ሁሉ ጥበብ ትበልጣለች፤ ክብርም ሁሉ አይመጣጠናትም፤” በማለት የጥበብ ብልጫ ተወዳዳሪ የሌላት እንደሆነች ያስገነዝበናል፤ እግዚአብሔርም ሥራውን ሁሉ በጥበብ እንደሚሠራ “ወኲሎ በጥበብ ገበርከ፤ ሁሉንም በጥበብ አደረግህ” በሚል ተጽፎ ይገኛል፤ እግዚአብሔር ሥራውን በጥበብ እንደሚሠራ፣ እኛንም በጥበብ መሥራት እንዳለብን ሲያስተምረን፣ ‹‹ኩኑ ጠቢባነ ከመ አርዌ ምድር እንደ እባብ ብልሆች ሁኑ›› ብሎናል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የጉባኤው ተሳታፊዎች!
ዘመንና ቦታ ሳይገድበን ምንጊዜም ሥራችንን በጥበብ መሥራት እንዳለብን ቢታወቅም ዛሬ ላይ ከምን ጊዜውም በበለጠ በጥበብ መመላለስ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፤ የዛሬዎቹ ችግሮች በአንድ አካባቢ ብቻ ያሉ ሳይሆኑ ዓለም ዓለፍ ቅርጽ ያላቸው እንደሆኑ ታላላቅ መሪዎች ሳይቀሩ በዓለም መድረክ ላይ ስሞታ ሲያቀርቡ በዓይናችን አይተናል፤ በጆሮአችንም ሰምተናል፤ በሁኔታውም የክርስትና ሃይማኖት በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ የኦርቶዶክሱ ወገን የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደሆነ እየተስተዋለ ነው ፡፡
እኛም የዚሁ ወገን አካል በመሆናችን የችግሩ ቀማሽ መሆናችን አልቀረም፤ በየቀኑ ካህናትና ምእመናን ይገደሉብናል፤ አብያ ክርስቲያናት ይቃጠሉብናል፤ የእምነትና የኅሊና ነጻነት በእጅጉ የሳሳ ሆኖብናል፤ አላስፈላጊ ጫናዎችም በዝተውብናል፤ ከውጭና ከውስጥ በተቀነባበረ ስሌት የቤተክርስቲያናችንን ስም ማጥፋት የዕለት ተግባራቸው ያደረጉ አካላት ተበራክተዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን ከነባሩና ረጅም ዘመን ካስቈጠረው ሰፊ ማእዷ እያበላቻቸው ያለች መሆኗን ዘንግተው እንብላሽ፣ እንዋጥሽ የሚሉዋት ወገኖች በዝተዋል፣ በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች አባቶች እንደልብ ተንቀሳቅሰው መሥራት የማይችሉባቸው አጋጣሚዎች እየተፈጠሩ ነው፤ የወለጋው ችግር ለዚህ በዋናነት ተጠቃሽ ነው፡፡
ታድያ እነዚህን ፈተናዎች ለማለፍ ጥበብ ያስፈልጋል፤ ነገር ግን ጥበብ መከተል ማለት ዝም ብሎ ማለፍ ወይም አይተው እንዳላዩ ሆኖ መኖር ማለት አይደለም፤ በጥበብ መመላለስ ማለት ከሁሉ በፊት ችግሮችንና የችግሮችን መንሥኤዎች በአግባቡ መረዳትና መለየት መቻል ነው፤ ከዚያም ራስን ለከፋ አደጋ በማያጋልጥ መልኩ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም መሸጋገር መቻል ነው፤ በዚህ ዘመን እንዲህ ያለ ጥበብ መጠቀም የግድ ያስፈልጋል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የጉባኤው ተሳታፊዎች! ቤተ ክርስቲያናችን እየተፈተነች ያለችው ከውጭ ብቻ ሳይሆን ከውስጥም ጭምር እንደሆነ መካድ የለብንም፤ ንጽሕትና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥር የሰደደ የቅድስና ሕይወትና በፈሪሀ እግዚአብሔር የተቃኘ ሥነ ምግባር ያላት ቤተ ክርስቲያን ናት፤
በአሁኑ ጊዜ ግን እነዚህ ሁሉ ቦታቸውን እየለቀቁ ያሉ መስለዋል፤ ቤተ ክርስቲያን በረጅሙ ታሪኳ ሲያስተምሩም ሆነ ሲማሩ፣ ሲመንኑም ሆነ ሲመነኲሱ፣ ሲቀድሱም ሆነ ሲያስቀድሱ ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው ዓቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ሰብእና በንጽሕና እና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እልፍ አእላፍ አበው እንዳልነበሯት ዛሬ የተሻለ ኑሮና ደመወዝ እያገኘን እግዚአብሔርን እንደቀኖናው በጥንቃቄ ማገልገል አቅቶናል፤ ምእመናንም በዚህ ምክንያት እየተሰናከሉ እንደሆነ እየተስተዋለ ነው፡፡ ሚድያውም ስሕተቶችን ወደ ውጭ በማውጣት ሰድቦ ለሰዳቢ እየዳረገን ነው፤ ይህ ሊሆን የቻለው የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረት በአግባቡ በመያዝ ለታለመለት ዓላማ ማዋል አለመቻላችን ነው፤ ይህ ችግር ባለበት ከቀጠለ ሌላ ጦስ ይዞብን እንዳይመጣ ሁነኛ ለከት ማኖር የግድ ይሆናል፡፡
የሰበካ ጉባኤ አደረጃጀት የቤተ ክርስቲያናችንን ሀብተ ጸጋ በማሳደግ ረገድ አስተማማኝ ስልት እንደሆነ በተግባር የተረጋገጠ ነው፤ ሆኖም ሲጀመር ሳለ የነበረ መነቃቃት በአሁኑ ጊዜ የቀነሰ መስሎ ይታያል፤ አሁን በቤተ ክርስቲያን ሰፊ ሽፋን ይዞ የሚገኘው የሙዳየ ምጽዋት ገቢ እንጂ የሰበካ ጉባኤ አስተዋፅኦ እንደአይደለ ሁላችንም እናውቃለን፤ በተለይም በከተሞች ውስጥ ነገሩ ጎልቶ ይታያል፡፡
ይህ የሆነበት ምክንያት ምናልባትም በየደረጃው በኃላፊነት ያለን ሰዎች ሻል ያለ ደመወዝ ስለምናገኝ የሰበካ ጉባኤው ተልእኮ ከሚፈለገው ደረጃ ላይ የደረሰ መስሎን ይሆናል፤ ነገር ግን ከ85% ያላነሰ የገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ መምህርና ካህን አሁንም ያለ ደመወዝ የሚኖር ነው፤ ሕዝበ ክርስቲያኑም ከቤተ ክርስቲያኑ ሊያገኘው የሚገባ የበጎ አድራጎት የጤና የትምህርትና የማኅበራዊ ዋስትና አገልግሎት በሚጠበቀው ደረጃ ሊያገኝ አልቻለም፤ የገዳማትና የአብነት ት/ቤቶች ችግሮችም በነበሩበት የልመና ኑሮ እየቀጠሉ ነው፤ በውጤቱም በችግር የሚኖሩ ገዳማት የተዘጉ የአብነት ት/ቤቶችና አብያተ ክርስቲያናት ከተበራከቱ ሰነባብቶአል፡፡
ታድያ ይህንን ሁሉ መልክ ማስያዝና ቤተ ክርስቲያንን ለቀጣዩ ትውልድ ማሸጋገር የሚቻለው በጥበብና በጥበብ ብቻ መሥራት ሲቻል ነው፤ ይህንን ችግር መፍታት የሚያስችል ጥበብ ደግሞ በዘመናችን አለ፤ የጠፋው ቅንነቱና ፈቃደኝነቱ ነው፡፡
በየዓመቱ የምናካሄደው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እንደነዚህ ያሉትን ችግሮች መቅረፍ የሚያስችል ካልሆነ ተሰብስበናል ማለቱ ብቻ ትርጉም ሊኖረው አይችልም፤ ስለሆነም ከዚህ በላይ የተጠቃቀሱና ሌሎችም የቤተ ክርስቲያናችን ተግዳሮቶች ካሉ በዚህ ጉባኤ በማንሣት በማየትና በመገምገም ለቤተ ክርስቲያን አሻጋሪና ጥበባዊ ውሳኔ እንዲያሳልፍ አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም
ዓመታዊው ዓለም ዓቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎተ ወንጌል የተከፈተ መሆኑን በእግዚአብሔር ስም እናበስራለን፡፡
መልካም ጉባኤ ያድርግልን
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ !!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር !!!
አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፬ ቀን ፳፻፲8 ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
ቅዱስ መጽሐፍ ስለ ጥበብ አስፈላጊነት በብዙ ቦታ ያስተምራል፤ በተለይም ጠቢቡ ሰሎሞን “ጥበብ ትኄይስ እምኲሉ መዛግብት ወኲሉ ክብር ኢመጠና ላቲ፤ ከሀብት ሁሉ ጥበብ ትበልጣለች፤ ክብርም ሁሉ አይመጣጠናትም፤” በማለት የጥበብ ብልጫ ተወዳዳሪ የሌላት እንደሆነች ያስገነዝበናል፤ እግዚአብሔርም ሥራውን ሁሉ በጥበብ እንደሚሠራ “ወኲሎ በጥበብ ገበርከ፤ ሁሉንም በጥበብ አደረግህ” በሚል ተጽፎ ይገኛል፤ እግዚአብሔር ሥራውን በጥበብ እንደሚሠራ፣ እኛንም በጥበብ መሥራት እንዳለብን ሲያስተምረን፣ ‹‹ኩኑ ጠቢባነ ከመ አርዌ ምድር እንደ እባብ ብልሆች ሁኑ›› ብሎናል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የጉባኤው ተሳታፊዎች!
ዘመንና ቦታ ሳይገድበን ምንጊዜም ሥራችንን በጥበብ መሥራት እንዳለብን ቢታወቅም ዛሬ ላይ ከምን ጊዜውም በበለጠ በጥበብ መመላለስ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፤ የዛሬዎቹ ችግሮች በአንድ አካባቢ ብቻ ያሉ ሳይሆኑ ዓለም ዓለፍ ቅርጽ ያላቸው እንደሆኑ ታላላቅ መሪዎች ሳይቀሩ በዓለም መድረክ ላይ ስሞታ ሲያቀርቡ በዓይናችን አይተናል፤ በጆሮአችንም ሰምተናል፤ በሁኔታውም የክርስትና ሃይማኖት በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ የኦርቶዶክሱ ወገን የችግሩ ገፈት ቀማሽ እንደሆነ እየተስተዋለ ነው ፡፡
እኛም የዚሁ ወገን አካል በመሆናችን የችግሩ ቀማሽ መሆናችን አልቀረም፤ በየቀኑ ካህናትና ምእመናን ይገደሉብናል፤ አብያ ክርስቲያናት ይቃጠሉብናል፤ የእምነትና የኅሊና ነጻነት በእጅጉ የሳሳ ሆኖብናል፤ አላስፈላጊ ጫናዎችም በዝተውብናል፤ ከውጭና ከውስጥ በተቀነባበረ ስሌት የቤተክርስቲያናችንን ስም ማጥፋት የዕለት ተግባራቸው ያደረጉ አካላት ተበራክተዋል፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን ከነባሩና ረጅም ዘመን ካስቈጠረው ሰፊ ማእዷ እያበላቻቸው ያለች መሆኗን ዘንግተው እንብላሽ፣ እንዋጥሽ የሚሉዋት ወገኖች በዝተዋል፣ በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች አባቶች እንደልብ ተንቀሳቅሰው መሥራት የማይችሉባቸው አጋጣሚዎች እየተፈጠሩ ነው፤ የወለጋው ችግር ለዚህ በዋናነት ተጠቃሽ ነው፡፡
ታድያ እነዚህን ፈተናዎች ለማለፍ ጥበብ ያስፈልጋል፤ ነገር ግን ጥበብ መከተል ማለት ዝም ብሎ ማለፍ ወይም አይተው እንዳላዩ ሆኖ መኖር ማለት አይደለም፤ በጥበብ መመላለስ ማለት ከሁሉ በፊት ችግሮችንና የችግሮችን መንሥኤዎች በአግባቡ መረዳትና መለየት መቻል ነው፤ ከዚያም ራስን ለከፋ አደጋ በማያጋልጥ መልኩ የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም መሸጋገር መቻል ነው፤ በዚህ ዘመን እንዲህ ያለ ጥበብ መጠቀም የግድ ያስፈልጋል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት!
ክቡራን የጉባኤው ተሳታፊዎች! ቤተ ክርስቲያናችን እየተፈተነች ያለችው ከውጭ ብቻ ሳይሆን ከውስጥም ጭምር እንደሆነ መካድ የለብንም፤ ንጽሕትና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥር የሰደደ የቅድስና ሕይወትና በፈሪሀ እግዚአብሔር የተቃኘ ሥነ ምግባር ያላት ቤተ ክርስቲያን ናት፤
በአሁኑ ጊዜ ግን እነዚህ ሁሉ ቦታቸውን እየለቀቁ ያሉ መስለዋል፤ ቤተ ክርስቲያን በረጅሙ ታሪኳ ሲያስተምሩም ሆነ ሲማሩ፣ ሲመንኑም ሆነ ሲመነኲሱ፣ ሲቀድሱም ሆነ ሲያስቀድሱ ያለምንም ደመወዝ በራሳቸው ዓቅም በግብርና እየተዳደሩ ቤተ ክርስቲያንን በጥሩ ሰብእና በንጽሕና እና በቅድስና ጠብቀው ያስረከቡ እልፍ አእላፍ አበው እንዳልነበሯት ዛሬ የተሻለ ኑሮና ደመወዝ እያገኘን እግዚአብሔርን እንደቀኖናው በጥንቃቄ ማገልገል አቅቶናል፤ ምእመናንም በዚህ ምክንያት እየተሰናከሉ እንደሆነ እየተስተዋለ ነው፡፡ ሚድያውም ስሕተቶችን ወደ ውጭ በማውጣት ሰድቦ ለሰዳቢ እየዳረገን ነው፤ ይህ ሊሆን የቻለው የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረት በአግባቡ በመያዝ ለታለመለት ዓላማ ማዋል አለመቻላችን ነው፤ ይህ ችግር ባለበት ከቀጠለ ሌላ ጦስ ይዞብን እንዳይመጣ ሁነኛ ለከት ማኖር የግድ ይሆናል፡፡
የሰበካ ጉባኤ አደረጃጀት የቤተ ክርስቲያናችንን ሀብተ ጸጋ በማሳደግ ረገድ አስተማማኝ ስልት እንደሆነ በተግባር የተረጋገጠ ነው፤ ሆኖም ሲጀመር ሳለ የነበረ መነቃቃት በአሁኑ ጊዜ የቀነሰ መስሎ ይታያል፤ አሁን በቤተ ክርስቲያን ሰፊ ሽፋን ይዞ የሚገኘው የሙዳየ ምጽዋት ገቢ እንጂ የሰበካ ጉባኤ አስተዋፅኦ እንደአይደለ ሁላችንም እናውቃለን፤ በተለይም በከተሞች ውስጥ ነገሩ ጎልቶ ይታያል፡፡
ይህ የሆነበት ምክንያት ምናልባትም በየደረጃው በኃላፊነት ያለን ሰዎች ሻል ያለ ደመወዝ ስለምናገኝ የሰበካ ጉባኤው ተልእኮ ከሚፈለገው ደረጃ ላይ የደረሰ መስሎን ይሆናል፤ ነገር ግን ከ85% ያላነሰ የገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ መምህርና ካህን አሁንም ያለ ደመወዝ የሚኖር ነው፤ ሕዝበ ክርስቲያኑም ከቤተ ክርስቲያኑ ሊያገኘው የሚገባ የበጎ አድራጎት የጤና የትምህርትና የማኅበራዊ ዋስትና አገልግሎት በሚጠበቀው ደረጃ ሊያገኝ አልቻለም፤ የገዳማትና የአብነት ት/ቤቶች ችግሮችም በነበሩበት የልመና ኑሮ እየቀጠሉ ነው፤ በውጤቱም በችግር የሚኖሩ ገዳማት የተዘጉ የአብነት ት/ቤቶችና አብያተ ክርስቲያናት ከተበራከቱ ሰነባብቶአል፡፡
ታድያ ይህንን ሁሉ መልክ ማስያዝና ቤተ ክርስቲያንን ለቀጣዩ ትውልድ ማሸጋገር የሚቻለው በጥበብና በጥበብ ብቻ መሥራት ሲቻል ነው፤ ይህንን ችግር መፍታት የሚያስችል ጥበብ ደግሞ በዘመናችን አለ፤ የጠፋው ቅንነቱና ፈቃደኝነቱ ነው፡፡
በየዓመቱ የምናካሄደው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እንደነዚህ ያሉትን ችግሮች መቅረፍ የሚያስችል ካልሆነ ተሰብስበናል ማለቱ ብቻ ትርጉም ሊኖረው አይችልም፤ ስለሆነም ከዚህ በላይ የተጠቃቀሱና ሌሎችም የቤተ ክርስቲያናችን ተግዳሮቶች ካሉ በዚህ ጉባኤ በማንሣት በማየትና በመገምገም ለቤተ ክርስቲያን አሻጋሪና ጥበባዊ ውሳኔ እንዲያሳልፍ አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም
ዓመታዊው ዓለም ዓቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎተ ወንጌል የተከፈተ መሆኑን በእግዚአብሔር ስም እናበስራለን፡፡
መልካም ጉባኤ ያድርግልን
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ !!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር !!!
አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፬ ቀን ፳፻፲8 ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
❤25👍10🥰7🤔1🙏1
"መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ልዕልና የሚለካው በተሰጠን የማእረግ ስም ሳይሆን በምንሠራው ሥራ ነው!" ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
ጥቅምት ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት በሚካሄደው 44ኛው የመንፈሳዊ ሰበካ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የምስካየ ኃዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ ዘመኑ ሳይቀድመን በአገልግሎት በርትተን ጉድለታችንን ማረም ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ አገልግሎት በሚገባን ልክ እና መጠን ተዘጋጅተን ለሃይማኖት መስፋፋት፣ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ክብር እና አንድነት እንዲሁም ለምእመናን ደኅንነት የተሰጠንን ኃላፊነት መወጣት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ብፁዕነታቸው አክለውም መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ልዕልና የሚለካው በምንለብሰው ልብስ፣በተሰጠን የማእረግ ስም ሳይሆን በተግባር በምንሠራው እውነተኛ ሥራ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡
በአንድ ቢሮ ሆነን የምንሰጠው አገልግሎት ወደ ኋላ እንዳይል መሥራት ይጠበቅብናል ያሉት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በባለፈው በጀት ዓመት ያከናወነውን የሥራ ትሩፋት በበለጠ ኃላፊነት ማጠናከር ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
ጥቅምት ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 4 ቀናት በሚካሄደው 44ኛው የመንፈሳዊ ሰበካ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የምስካየ ኃዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ ዘመኑ ሳይቀድመን በአገልግሎት በርትተን ጉድለታችንን ማረም ይኖርብናል ብለዋል፡፡
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ አገልግሎት በሚገባን ልክ እና መጠን ተዘጋጅተን ለሃይማኖት መስፋፋት፣ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ክብር እና አንድነት እንዲሁም ለምእመናን ደኅንነት የተሰጠንን ኃላፊነት መወጣት ይኖርብናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ብፁዕነታቸው አክለውም መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ልዕልና የሚለካው በምንለብሰው ልብስ፣በተሰጠን የማእረግ ስም ሳይሆን በተግባር በምንሠራው እውነተኛ ሥራ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡
በአንድ ቢሮ ሆነን የምንሰጠው አገልግሎት ወደ ኋላ እንዳይል መሥራት ይጠበቅብናል ያሉት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በባለፈው በጀት ዓመት ያከናወነውን የሥራ ትሩፋት በበለጠ ኃላፊነት ማጠናከር ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
❤34🤔15🙏11