በጎንደርና በደባርቅ ጥቃት አድራሾች በሽብርተኝነት ሊፈረጁ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማኅበር በሲያትል ጠየቀ
@nidatube
የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ!
ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት፦
👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም ሆኗል።
@nidatube
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ክርሰቲያን ወንድማችን ጥያቄ ያቀርባል
@nidatube
እጅግ በጣም የሚገርመኝ .......

በአቡ ሀይደር

የሆነን ክልል ይጠቅሱና: በክልሉ የተሰራውን ቤተ ክርስቲያን ለማገዝ ከሙስሊሞች በኩል ይህን ያህል ሚሊየን ተለገሰ፣ ለምርቃቱ ደግሞ ይህን ያህል በሬ ተሰጠ! የሚለውን ዜና እንደጉድ ያሰራጩና: በመጨረሻም:– ይህ ነው ኢትዮጲያዊነት! ይህ ነው ጨዋነት! ይህ ነው አንድነት! በማለት መልክቱን ይቋጩታል።

እኔ የምጠይቀው:– የተወራው ነገር እውነት ከሆነና: የኢትዮጲያዊነት ፀባይ አንዱ መገለጫ: የአንዱን የአምልኮ ቦታ ሌላው በእምነት የማይመስለው ወገኑ: ከቻለ በገንዘብ ካልቻለ ደግሞ የምርቃት ቀን የእርድ ከብት ማቅረቡን ከልብ አምናችሁ ከተቀበላችሁት: እናንተስ የሙስሊሙን መስጂድ ከማቃጠልና ከማፍረስ ውጭ ምን ሰርታችሁ ታውቃላችሁ? በመዲናችን አዲስ አበባ እንኳን: በህጋዊ መንገድ ፍቃድ ያገኘንበትን ቦታ በሰላም እንድንገነባ በዝምታ እንኳ መች ተባብራችሁ ታውቃላችሁ? የቱንም ያህል ቢራራቁም: ህዝቡን ለማነሳሳት ከቤ/ክርስቲያን ጎን መስጂድ ሊሰራ ነው ብላችሁ ረብሻ መቀስቀስ፣ ድንጋይ መወርወር፣ ከታቻለም መሳሪያ መተኮስ መገለጫችሁ አይደለምን? ከአንዋር መስጂድ ውጭ የትኛው መስጂድ ነው ደም ሳይፈስ በሰላም የተገነባው? ወይስ ኢትዮጲያዊ ጨዋነትና አንድነት እናንተን አይመለከትም? ወይስ ጨዋነቱና አንድነቱ የሚሰራው ለቤ/ክርስቲያን ግንባታ ሲሆን ብቻ እንጂ ለመስጂድ ግንባታ ግዜ አይሰራም? ኧረ እንደው በራሳችሁ ድርጊት እንድታፍሩ የሚገስጻችሁ የህሊናም ይሁን የሃይማኖት መካሪ የላችሁም? ለቤ/ክ ግንባታ የሙስሊሙን መሳተፍ የኢትዮጲያዊ ጨዋነት መገለጫ መሆኑ እውነት ከታመነበት: እናንተ ምንም ኢትዮጲያዊ ጨዋነት እንደሌላችሁ መስክራችኋል ማለት ነው። ሙስሊሞች ለቤ/ክርስቲያናችን ለግንባታው እና ለምርቃቱ ይህን አደረጉልን እንጂ እኛ ለነሱ መስጂድ ይህን አደረግንላቸው ብላችሁ የምታወሩት ምንም የላችሁም። አድርጋችሁብን እንጂ አድርጋችሁልን አታውቁምና!!

አል–ሐምዱ ሊላህ ዓለሰ ኒዕመቲል ኢስላም
@nidatube @nidatubebot
የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለምትፈልጉ

በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከ ሰኔ 6-12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡

ስለሆነም ይህን የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣7፣13፣14፣20፣21፣27፣28 ) ስለምናደርግ በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ እንድትይዙ ስንል በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም፡፡
.................
ሼር በማደርግ ያሰተላለፉት
@nidatube
በኢስላም ንጉስም ብትሆን ስትሞት ነጭ ከፈን እንጂ ሌላ ለብሰህ አትቀበርም!

ዛሬ በ 73 አመታቸው መሞታቸው የተገለፀው እና በህዝባቸው ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እንደነበሩ የሚነገርላቸው የተባበሩት አረብ ኢምሬትሶች ፕሬዝደንት ሼይኽ ከሊፋ ቢን ዛይድ (አላህ ይዘንላቸው) ሰርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል::

እጅግ የሃብታም ሃገር መሪ ሆነው ቢቆዩም ሲሞቱ ግን እንደማንኛውም ተራ ሰው ባለ ሶስት ነጭ ከፈን ተጠቅልለው ሰላተል ጀናዛ ተሰግዶባቸው አፈር ውስጥ ተቀብረዋል::

በኢስላም ሁሉም ሰው እኩል ነው:: ንጉስም ሁን፣ የሃገር መሪ፣ ባለስልጣን፣ ባለሃብት ፣ምሁር ፣ደሃ፣ጥቁር ሁን ነጭ ስትሞት የአቀባበርህ ሁኔታ ላይ የምትበላለጥበት መንገድ የለም:: ሃብታም ግድግዳ ውስጥ ደሃ አፈር ውስጥ የሚቀበርበት የቀብር ስነ ስርዓት በኢስላም የለም::

በኢስላም ስትሞት ሃብታም ወይንም መሪ ስለሆንክ ዘመናዊ ሙሉ ሱፍ አልያ የተሽቀረቀረ ሙሉ ልብስ ፣እጅግ ውድ እና ዘመናዊ የሬሳ ሳጥን፣እና ሌሎች አጀባዎች ወዘተ.... እንዲኖርህ አይጠበቅም::

የሃገር መሪ ስለሆንክ ታላላቅ የሃገራት መሪዎች እስኪመጡ ፣ ህዝብ አስክሬኑን እስኪሰናበተው፣ የቀብር ስነ ስርዓቱ ለማከናወን የአደባባይ ድግስ እና የሽኝት ፕሮግራም እስኪካሄድ አስክሬኑ ሳይቀበር ይቆይ የሚባል መርህ በኢስላም የለም::

ማንም ሰው ከሞተ ቶሎ አጥቦ፣በነጭ ከፈን ሸፍኖ እና ገንዞ ሰላተል ጀናዛ በመስገድ ወደ ቀብር ወስዶ መቅበር በኢስላም የተደነገገ ነው::

"የሰው ልጆች ሁሉ እንደማበጠሪያ ጥርስ እኩል ናቸው" የሚለው የነብያችን (ሰዓወ) የእኩልነት አስተምህሮ በህይወት እያሉ ብቻ ሳይሆን ሞተንም ቢሆን በቀብር ስርዓታችን ላይ አንዱ ከአንዱ የሚበላለጥበት መንገድ የዘጋ ነው::
ለሞቱት አላህ እዝነቱን ይላክላቸው

abu dawd

@nidatube
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ይቺ ሀገር የሁላችንም ናት፣ ሁላችንም በእኩል የምንኖርባት የጋራ ሀገር ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

ይቺ ሀገር የሁላችንም ናት ፣ ኦርቶዶክሱም ፣አይሁዱም ከመካከለኛው ምሰራቅ ነው የመጡት ግን ይቺ የሁላችንም ሀገር ናት ፣እዚች ሀገር ላይ የበቀሉ ክርሰቲያኖች የአረብ ክርቲያኖች ወይም የግሪክ ክርሰቲያኖች አይደለም የሚባሉት፣እንዲሁም እዚህ ምድር ላይ የበቀሉ ሙሰሊሞች ኢትዮዺያዊ እንጂ የሳኡዲ ፣ የሶሪያ ወይም የኢራቅ ሙሰሊሞች አይደሉም፣ኢትዮዺያዊ ሙሰሊሞች ናቸው።

ሁላችንም በእኩል የምንኖርባት የጋራ ሀገር ናት

ተወዳጁ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

@nidatube
‏ጎንደር ታላቅ አሊም አጣች።
‏ ሸህ ጀማል አደም ሀገር ውስጥም በሰፈር ቂራዓት በውጭም በሱዳን አፍሪካ ዩንቨርስቲ በቂርዓት አቀባበላቸው ፈጣንና ሀፊዝ ነበሩ። የጎንደር ከተማ ዑለማ ም/ቤትን በዘመናዊ አሰራር የተሻለ ሀሳብ በማምጣት ጥሩ እቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩና የጎንደር ሙስሊሞችን ግፍ በአደባባይ የተጋፈጡ ታላቅ አሊም ነበሩ። አባ-ሼህ ጀማል አደም - ከላቁ የእኛ-ዘመን ዑለሞች መካከል ተጠቃሽ ነበሩ።
‏በጎንደር-ከተማ ሚና መስጂድ፣ ኢማም፣ ኸጢብና ዋዒዝ ነበሩ።

‏የጎ/ከ/ዑለ/ም/ቤትን በነጻ፣ ለሁለት ዓመታት በፀሀፊነት አገልግለዋል። ለአምስት ዓመታት የስራ አስፈጻሚ አባል ኾነው ቆይተዋል። ለውጥ ፈጥረዋል። ‹ሼህ ጀማል አደም› ቢኾንም ስማቸው፣ በ“ሼህ ጀማል ገበሬው” ነው የሚታወቁ። በእርግጥም! የነህው፣ የሶርፍ፣ የመንጢቅ፣ የሉጛ ገበሬ ነበሩ። የዲን ገበሬ ነበሩ። በወሎና በጎንደር፣ እንዲሁም በሱዳን ሀገር ተዟዙረው ሰፊ ዒልም ያካበቱ ታላቅ ዓሊም ነበሩ።

‏ሼህ ጀማል ከወራት በፊት ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ህክምና ሲደረግላቸው ቆይተው በትናንትናው ዕለት ለህልፈት በቅተዋል። መልካም ስራቸውን አላህ ይቀበላቸው። ለወዳጅ ዘመድ፣ ለእኛም መፅናናት ይኹን። አላህ መልካሙን ተተኪ ይስጠን!!!
اللَّهُمَّ اغْفِرْ لَهُ وَارْحَمْهُ، وَعَافِهِ، وَاعْفُ عَنْهُ، وَأَكْرِمْ نُزُلَهُ، وَوَسِّعْ مُدْخَلَهُ، وَاغْسِلْهُ بِالْمَاءِ وَالثَّلْجِ وَالْبَرَدْ، وَنَقِّهِ مِنَ الْخَطَايَا كَما نَقَّيْتَ الثَّوْب الأَبْيَضَ مِنَ الدَّنَسِ، وَأَدْخِلْهُ الْجَنَّةَ، وَأَعِذْهُ مِنْ عَذَابِ الْقَبْرِ وَعَذَابِ النَّارِ
🛑 ለአዲስ አበባ ሙስሊም ማህበረሰብና ለመስጂድ ጀመዓዎቸ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተላለፈ ጥሪ

ነገ እሁድ መጋቢት 3 | 2015 ከጠዋቱ 12:30 ሰዐት ጀምሮ ጉለሌ በሚገኘው የሙስሊሞች መካነ መቃብር ቅጥር ግቢ የማይቀርበት ቀጠሮ ተይዟል።

ቀጠሮው ወጣት ወንዶችን ይመለከታል።

ስራው ወደ ጫካነት ተለውጦ የጅቦች መራቢያ፣ የሌቦች መደበቂያ፣ የሱሰኞች መነሀሪያ የሆነውን ጉለሌ መካነ መቃብርን ጫካውን በመመንጠር ምቹ የቀብር ስፍራ ማድረግ ነው።

በዚህ ትልቅ አጅር በሚያስገኘው በጉልበታችን ብቻ በሚሰራው ኸይር ስራ ላይ ወላጆች እና ሴቶች ወንድ ልጆቻችሁን እና ወንድሞቻችሁን በመላክ እና በማበረታታት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

ይህ ስፍራ የነገው የእያንዳንዳችን ማረፊያ ነው ቤታችንን እናፅዳ ቤታችንን ምቹ እናድርግ።

📌 ነገ በፍፁም አይቀርም ጠዋት 12:30 ሰዐት ላይ እንገናኝ።

የጉለሌ ሙስሊም መካነ መቃብር አድራሻውን ለማታውቁ

🛑 ከፒያሳና አካባቢው ለምትመጡ:-

እንቁላል ፋብሪካ አደባባዩን አልፋችሁ ወደ ጎጃም በረንዳ በሚወስደው መንገድ በስተ ግራ በኩል

🛑 ከአለም ባንክ፣ ጦርሀይሎችና አካባበከው ለምትመጡ:- ከአውቶብስተራ ወደ ፓስተር ስትሄዱ በስተቀኝ በኩል ሁለተኛ አስፓልት ቂያስ ወደ ሀግቤስ በሚወስደው መንገድ ላይ ወደ ግራ በሚወስደው በመታጠፍ በስተቀኝ በኩል ቀብሩን ታገኙታላችሁ

🛑 ከአስኮ እና አከባቢ ለምትመጡ:- ከፓስተር አደባባይ እንዳለፋችሁ ኖክ ማዲያ ፊት በስተቀኝ በኩል ወደ ጨው በረንዳ ስትታጠፉ ቀብሩን በግራ በኩል ታገኙታላችሁ

🛑 ከጥቁር አንበሳ ለምትመጡ ደግሞ አንዋር መስጂድን አልፋችሁ በቀኝ በኩል ወደ አዲሱ ገበያ የሚወስደውን አስፓልት አልፋችሁ ወለጋ ሆቴል በሚገኝበት አስፓልት ወደቀኝ በመግባት ውሀ ልማቱ ፊት ታገኙታላችሁ
@nidatube
🌙ነገ ጨረቃ ከታየች ሮብ ረመዳን 1 ብሎ ይጀምራል፣ ነገ ካለታየች ሀሙስ የመጀመሪየውን የረመዳን ፆም እንጀምራለን።
አላህ ያድርሰን🙏
@nidatube
መልካም የረመዷን ወር ይሁንልን
2024/04/28 06:46:02
Back to Top
HTML Embed Code: