. ሰሙነ ሕርቃል “Heraclius Week”
⊙∗⊕━━✦༒⛪༒✦━━⊕∗⊙
(መንደርደርያ ሐሳብ)
ሀገር ለቀው፣ ባህር ጠልቀው፣ ገደል ወድቀው የሚሰደዱትን መከራ ጸንቶባቸው የሚቸገሩትን በዓለም ሁሉ ያሉ ምእመናን ለስዱዳኑ ተስፋ፣ ለምንዱባኑ ረዳኤ፣ ለሕዙናን ናዛዜ፣ ለግዱፋን ዐቃቤ ፣ ለጽዑራን መጽንዔ የሆናቸው ክርስቶስ በቸርነት ይድረስላቸው🙏
እንኳን ለዐቢይ ጾም ቀዳሜ ሳምንት (ዘወረደ፣ ሙሴኒ፣ ሰሙነ ሕርቃል…) በሠላም አደረሳችሁ!
☞ «መገለጫውን ሲያይ ነው እንጂ የጾሙትስ ሐዋርያት ናቸው»
☞ «ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን»
☞ «ሰሙነ ሕርቃል ዘትከውን እምቅድመ ጾም ዐቢይ …»
#ሰሙነ_ሕርቃል ለጾመ እግዚእ የመሰናዶ ሳምንት [Preparation Weekinitial week] ተብሎ ተገልጧል። ከስምንቱ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ከቅድስት ቀድሞ ለሚጾመው የዘወረደ ሳምንት አንዱ ምክንያት ሕርቃል ንጉሠ ሮም እንደሆነ ይታወቃል።
፲፪ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ ዲሜጥሮስ ድኅረ አስተርእዮ ያለውን ፵ ዕለት ዐቢይ ጾም (A 40 day fast post Theophany) በ250 ዓ.ም. አውጆ በሮም በኢየሩሳሌምና በአንጾክያ በነበረችው አሐቲ ቤተክርስቲያን ቅቡልነት አግኝቶ ጸንቷል። ይህ ህርቃል ግን የተጨመረ በ616 እንደሆነ ይነገራል። ነገር ግን መጠሪያው የመሰናዶ ሳምንት ቀድሞ የነበረ እንጂ ሕርቃል በሚል እንዳልነበር መረጃ በማቅረብ የሚሞግቱ ቅብጣውያን አሉ። ኋላ ከ13ኛው ምዕተ ዓመት ወዲህ በኢብን አል አሰል በኩል ጾመ ሕርቃል (ሰሙነ ሕርቃል) በሚል ተለይቶ እንደተጠራ አስረጂ ጠቅሰው ይገልጻሉ።
(We find mention, of this week being referred to as “Hercules Week” as late as AD 1245 by Al-Safawy Le Ibn Al-Assal as being a fast distinct from the Great Fast proper )
በእኛም ዘንድ የጾሙን ምክንያት ሊቃውንቱም መጻሕፍቱም በተለያየ መንገድ ገልጠውታል።
፩) ጥንቱን ሐዋርያት ዐቢይ ጾምን ከእሑድ በቀር ቆጥረው ቢጎድልባቸው ቀድሞ ያለውን አምስት ቀን ከቁጥር ጨምረውታል።
፪) በኢየሩሳሌም የበራንጥያው ንጉሥ ፎቃ [Flavius Phocas Byzantine emperor ] ያደረሰባቸውን መከራ እና ጥፋት ያራቀላቸው ንጉሠ ሮም ሕርቃልን ምክንያት አድርገው ምዕመናነ ኢየሩሳሌም ስለጦሙት።
፫) የፋርስ ንጉሥ ክስራ [Kessra the king of Persia] በግብፃውያን ላይ ያደረሰውን መከራ ለማቅለል ንጉሥ ሕርቃል ዘምቶ ድል ቢነሳላቸው ሊቀ ጳጳሳቱ አባ እንድራኒቆስ በአዋጅ ከአጽዋማቱ ገብቶ እንዲቆጠር አድርገውታል።
፬) ንጉሥ ሕርቃል ግዙራን መንግሥቴን ይወስዳሉ ብሎ ቢሰጋ አይሁድን ዘምቶ ለመውጋት መሐላውን ቢያፈርስ የሮም ሊቃነ ጳጳሳት ቀሳውስት ዲያቆናት ምእመናን አንድነት ጹመውለታል። …
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምዕላድ የሆነው መጽሐፈ ስንክሳር በመጋቢት ፲ ምንባብ ሥር ነገረ መስቀሉ የሚከብርባቸውን ሁለት ምክንያቶች እንዳሉ ይነግረናል። አንደኛ ዕፀ መስቀሉ በኢየሩሳሌም ተቆፍሮ የተገኘበት ሲኾን ኹለተኛው ደግሞ ዕፀ መስቀሉ በፋርስ ንጉሥ በምርኮ ከወረደበት በሮሙ ንጉሥ ሕርቃል አማካኝነት ወደ ቆስጠንጥንያ የተመለሰበት ነው ይለናል። በአርኬውም የመጨረሻ አንጓ ላይ
"… መስቀል ተረክበ እምዘተኀብዐ ወገብረ መድምመ
በኢየሩሳሌም ቅድመ ወበፋርስ ዳግመ።" ይላል።
ከምርኮ የተመለሰበትን መንገድ በሚተርከው ክፍል ጥንተ ነገሩ እንዲህ ተቀምጧል።
✧ በሮሜ ንጉሥ በሕርቃል ዘመን የፋርስ ሰዎች በግብጽ አገር በበላይነት ኖረው ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዩ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሃን ሲበራ አይቶ ሊያነሣው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው። ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው። ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ። የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እንደማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደ ወሰዱ የሮም ንጉሥ ሕርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም #እንዲጾሙ_ምእመናንን_አዝዞ ወደ ፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ ዕፀ መስቀልንም እየፈለገ በአገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም። ያ ዲያቆናቱንና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አንጻር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው። ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷ የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉሥ ሕርቃልም ሒዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው። ይህንም ንጉሥ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋር ብዙ ሠራዊት ሁኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ። ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቆፍረውም የከበረ ዕፀ መስቀልን አገኙ ከዐዘቅቱም አወጡት ንጉሡና ሠራዊቱም ሰገዱለት። በልብስ መንግሥቱም አጐናጸፈው ታላቅ ክብርንም አከበረው ከሠራዊቱ ጋር እጅግም ደስ አለው ።
ይህንኑ በሚደግፍ ተወዳጁ ሊቅ የእስሙናዩ ቅዱስ ሳዊሮስ (Severus of El Ashmunein ﺳﺎﻭﻳﺮﺱ ﺍﻷﺷﻤﻮﻧﻴﻦ ) በድርሳኑ "ንሕነሰ ንጸውማ ንሥሓ በእንተ ሕርቃል ንጉሥ ሶበ ቀተሎሙ ለአይሁድ ወበልዐ ኪዳነ ዘተካየዶሙ ወዝንቱ ዕውቅ በዜና ሕርቃል ንጉሥ " ሲል ከነምክንያቱ አስረድቷል።
(እኛስ የምንጾመው ስለ ንጉሡ ሕርቃል ንስሐ ነው፤ አይሁድን በገደለ ጊዜ መኃላውን አፍርሷልና (ቃሉን በልቷልና) ይኽም በንጉሥ ሕርቃል ዜና የተነገረ ነው)
የመጽሐፈ ሕግ ወሥርዓት [ፍትሐ ነገሥት] ሐተታ ደግሞ መነሻው ከጥንት ሐዋርያት እንደሆነ በማውሳት ሌሎች እንደ ምክንያት የሚጠቀሱ ሁለት አጋዥ ታሪኮች አክሎ ያስቀምጥልናል።
በማከልም ከዐቢይ ጾምና ከረቡዕ ዓርብ (ጾመ ድኅነት) ውጪ የተጨመሩት አጽዋማት መነሻቸው የግብፃውያን ቀኖና እንደሆነም ፍትሐ ነገሥቱ ይጠቁማል።
«ወአጽዋምሰ አካልዓን እለ ተወስኩ ላዕለ ዝንቱ ወተሠርዑ በቤተ ክርስቲያን ቅብጣዊት። ወእምኔሆሙ ዘይከውን በአምሳለ ጾም ዐባይ በተጠናቅቆ። ወይእቲ ስሙነ ሕርቃል ዘትከውን እምቅድመ ፆም ዐቢይ»
(በዚህ ላይ የተጨመሩ ሌሎች ጾሞች ግን በግብፃውያኑ ቤተክርስቲያን የተሠሩ ናቸው፤ ከእነርሱም እንደ ዐቢይ ጾም በመጠንቀቅ የሚሆን አለ። ይህችውም ከዐቢይ ጾም ቀድማ የምትሆን የሕርቃል ጾም ናት)
በተለየ የሕርቃልን ጾም ሲያብራራ ደግሞ
⇨ ይህችውም ከዓቢይ ጾም አስቀድማ የምትሆን ስሙን ህርቃል ናት መገለጫውን ሲያይ ነው እንጂ የጾሙትስ ሐዋርያት ናቸው ሕልሙን ያየ ናቡደነፆር ሲሆን “ራእየ ዳንኤል” እንዲል
⊙∗⊕━━✦༒⛪༒✦━━⊕∗⊙
(መንደርደርያ ሐሳብ)
ሀገር ለቀው፣ ባህር ጠልቀው፣ ገደል ወድቀው የሚሰደዱትን መከራ ጸንቶባቸው የሚቸገሩትን በዓለም ሁሉ ያሉ ምእመናን ለስዱዳኑ ተስፋ፣ ለምንዱባኑ ረዳኤ፣ ለሕዙናን ናዛዜ፣ ለግዱፋን ዐቃቤ ፣ ለጽዑራን መጽንዔ የሆናቸው ክርስቶስ በቸርነት ይድረስላቸው🙏
እንኳን ለዐቢይ ጾም ቀዳሜ ሳምንት (ዘወረደ፣ ሙሴኒ፣ ሰሙነ ሕርቃል…) በሠላም አደረሳችሁ!
☞ «መገለጫውን ሲያይ ነው እንጂ የጾሙትስ ሐዋርያት ናቸው»
☞ «ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን»
☞ «ሰሙነ ሕርቃል ዘትከውን እምቅድመ ጾም ዐቢይ …»
#ሰሙነ_ሕርቃል ለጾመ እግዚእ የመሰናዶ ሳምንት [Preparation Weekinitial week] ተብሎ ተገልጧል። ከስምንቱ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ከቅድስት ቀድሞ ለሚጾመው የዘወረደ ሳምንት አንዱ ምክንያት ሕርቃል ንጉሠ ሮም እንደሆነ ይታወቃል።
፲፪ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ ዲሜጥሮስ ድኅረ አስተርእዮ ያለውን ፵ ዕለት ዐቢይ ጾም (A 40 day fast post Theophany) በ250 ዓ.ም. አውጆ በሮም በኢየሩሳሌምና በአንጾክያ በነበረችው አሐቲ ቤተክርስቲያን ቅቡልነት አግኝቶ ጸንቷል። ይህ ህርቃል ግን የተጨመረ በ616 እንደሆነ ይነገራል። ነገር ግን መጠሪያው የመሰናዶ ሳምንት ቀድሞ የነበረ እንጂ ሕርቃል በሚል እንዳልነበር መረጃ በማቅረብ የሚሞግቱ ቅብጣውያን አሉ። ኋላ ከ13ኛው ምዕተ ዓመት ወዲህ በኢብን አል አሰል በኩል ጾመ ሕርቃል (ሰሙነ ሕርቃል) በሚል ተለይቶ እንደተጠራ አስረጂ ጠቅሰው ይገልጻሉ።
(We find mention, of this week being referred to as “Hercules Week” as late as AD 1245 by Al-Safawy Le Ibn Al-Assal as being a fast distinct from the Great Fast proper )
በእኛም ዘንድ የጾሙን ምክንያት ሊቃውንቱም መጻሕፍቱም በተለያየ መንገድ ገልጠውታል።
፩) ጥንቱን ሐዋርያት ዐቢይ ጾምን ከእሑድ በቀር ቆጥረው ቢጎድልባቸው ቀድሞ ያለውን አምስት ቀን ከቁጥር ጨምረውታል።
፪) በኢየሩሳሌም የበራንጥያው ንጉሥ ፎቃ [Flavius Phocas Byzantine emperor ] ያደረሰባቸውን መከራ እና ጥፋት ያራቀላቸው ንጉሠ ሮም ሕርቃልን ምክንያት አድርገው ምዕመናነ ኢየሩሳሌም ስለጦሙት።
፫) የፋርስ ንጉሥ ክስራ [Kessra the king of Persia] በግብፃውያን ላይ ያደረሰውን መከራ ለማቅለል ንጉሥ ሕርቃል ዘምቶ ድል ቢነሳላቸው ሊቀ ጳጳሳቱ አባ እንድራኒቆስ በአዋጅ ከአጽዋማቱ ገብቶ እንዲቆጠር አድርገውታል።
፬) ንጉሥ ሕርቃል ግዙራን መንግሥቴን ይወስዳሉ ብሎ ቢሰጋ አይሁድን ዘምቶ ለመውጋት መሐላውን ቢያፈርስ የሮም ሊቃነ ጳጳሳት ቀሳውስት ዲያቆናት ምእመናን አንድነት ጹመውለታል። …
የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምዕላድ የሆነው መጽሐፈ ስንክሳር በመጋቢት ፲ ምንባብ ሥር ነገረ መስቀሉ የሚከብርባቸውን ሁለት ምክንያቶች እንዳሉ ይነግረናል። አንደኛ ዕፀ መስቀሉ በኢየሩሳሌም ተቆፍሮ የተገኘበት ሲኾን ኹለተኛው ደግሞ ዕፀ መስቀሉ በፋርስ ንጉሥ በምርኮ ከወረደበት በሮሙ ንጉሥ ሕርቃል አማካኝነት ወደ ቆስጠንጥንያ የተመለሰበት ነው ይለናል። በአርኬውም የመጨረሻ አንጓ ላይ
"… መስቀል ተረክበ እምዘተኀብዐ ወገብረ መድምመ
በኢየሩሳሌም ቅድመ ወበፋርስ ዳግመ።" ይላል።
ከምርኮ የተመለሰበትን መንገድ በሚተርከው ክፍል ጥንተ ነገሩ እንዲህ ተቀምጧል።
✧ በሮሜ ንጉሥ በሕርቃል ዘመን የፋርስ ሰዎች በግብጽ አገር በበላይነት ኖረው ወደ አገራቸው ሊመለሱ ወደዱ። ከሹማምንቶቻቸው አንዱ የጦር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢየሩሳሌም አልፎ ደረሰ ወደ ከበረ መስቀል ቤተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዩ በተተከለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሃን ሲበራ አይቶ ሊያነሣው እጁን ዘረጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለችው። ከክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንማይችል የመስቀልን የክብሩን ነገር ሰዎች ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ የከበረ መስቀልን እንዲሸከሙ አዘዛቸው። ከኢየሩሳሌምም ብዙ ሰዎችን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ። የፋርስ ሰዎች ኢየሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎች ሰዎችንም እንደማረኩና የከበረ የክርስቶስንም መስቀሉን እንደ ወሰዱ የሮም ንጉሥ ሕርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም #እንዲጾሙ_ምእመናንን_አዝዞ ወደ ፋርስ ዘምቶ ወጋቸው ብዙዎችንም ገደላቸው የከበረ ዕፀ መስቀልንም እየፈለገ በአገራቸው ሁሉ ዞረ ግን አላገኘውም። ያ ዲያቆናቱንና መስቀሉን የወሰደ መኰንን ከቦታዎች በቤቱ አንጻር ባለ በአንድ ቦታ ላይ ወስዷቸው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ የከበረ መስቀልን አስቀበረ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላቸው። ነገር ግን ያ መኰንን የማረካት የካህናት ወገን የሆነች በእርሱ ቤት የምትኖር አንዲት ብላቴና ነበረች። እርሷ የከበረ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላቸው በቤቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለከት ነበር ወደ ንጉሥ ሕርቃልም ሒዳ መኰንኑ ያደረገውን ሁሉ ነገረችው። ይህንም ንጉሥ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላቴናም መራችው ከእርሱም ጋር ብዙ ሠራዊት ሁኖ ኤጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ። ወደ ቦታውም እስከምታደርሳቸው ያቺን ልጅ ተከተሏት ቆፍረውም የከበረ ዕፀ መስቀልን አገኙ ከዐዘቅቱም አወጡት ንጉሡና ሠራዊቱም ሰገዱለት። በልብስ መንግሥቱም አጐናጸፈው ታላቅ ክብርንም አከበረው ከሠራዊቱ ጋር እጅግም ደስ አለው ።
ይህንኑ በሚደግፍ ተወዳጁ ሊቅ የእስሙናዩ ቅዱስ ሳዊሮስ (Severus of El Ashmunein ﺳﺎﻭﻳﺮﺱ ﺍﻷﺷﻤﻮﻧﻴﻦ ) በድርሳኑ "ንሕነሰ ንጸውማ ንሥሓ በእንተ ሕርቃል ንጉሥ ሶበ ቀተሎሙ ለአይሁድ ወበልዐ ኪዳነ ዘተካየዶሙ ወዝንቱ ዕውቅ በዜና ሕርቃል ንጉሥ " ሲል ከነምክንያቱ አስረድቷል።
(እኛስ የምንጾመው ስለ ንጉሡ ሕርቃል ንስሐ ነው፤ አይሁድን በገደለ ጊዜ መኃላውን አፍርሷልና (ቃሉን በልቷልና) ይኽም በንጉሥ ሕርቃል ዜና የተነገረ ነው)
የመጽሐፈ ሕግ ወሥርዓት [ፍትሐ ነገሥት] ሐተታ ደግሞ መነሻው ከጥንት ሐዋርያት እንደሆነ በማውሳት ሌሎች እንደ ምክንያት የሚጠቀሱ ሁለት አጋዥ ታሪኮች አክሎ ያስቀምጥልናል።
በማከልም ከዐቢይ ጾምና ከረቡዕ ዓርብ (ጾመ ድኅነት) ውጪ የተጨመሩት አጽዋማት መነሻቸው የግብፃውያን ቀኖና እንደሆነም ፍትሐ ነገሥቱ ይጠቁማል።
«ወአጽዋምሰ አካልዓን እለ ተወስኩ ላዕለ ዝንቱ ወተሠርዑ በቤተ ክርስቲያን ቅብጣዊት። ወእምኔሆሙ ዘይከውን በአምሳለ ጾም ዐባይ በተጠናቅቆ። ወይእቲ ስሙነ ሕርቃል ዘትከውን እምቅድመ ፆም ዐቢይ»
(በዚህ ላይ የተጨመሩ ሌሎች ጾሞች ግን በግብፃውያኑ ቤተክርስቲያን የተሠሩ ናቸው፤ ከእነርሱም እንደ ዐቢይ ጾም በመጠንቀቅ የሚሆን አለ። ይህችውም ከዐቢይ ጾም ቀድማ የምትሆን የሕርቃል ጾም ናት)
በተለየ የሕርቃልን ጾም ሲያብራራ ደግሞ
⇨ ይህችውም ከዓቢይ ጾም አስቀድማ የምትሆን ስሙን ህርቃል ናት መገለጫውን ሲያይ ነው እንጂ የጾሙትስ ሐዋርያት ናቸው ሕልሙን ያየ ናቡደነፆር ሲሆን “ራእየ ዳንኤል” እንዲል
ታሪክ ጌታ ከቅድስት ሰኞ ጀምሮ እስከ ዓርብ ኒቆዲሞስ ከቆመ ሳያርፍ ከዘረጋ ሳያጥፍ ዓርባ ቀን በትህርምት ጾሟል ሐዋርያት እሑድ እሑድን አውጥተው ቢቄጥሩ ጎደለባቸው አስቀድመው አምስት ቀን ጹመው ለስብከተ ወንጌል ይፋጠኑ ነበርና …
የኋላውንም ሁለት መነሻ ሊሆኑ የሚችሉ ታሪኮች ደግሞ እንዲህ ያብራራልናል።
① በኢየሩሳሌም ፎቃ በሮም ህርቃል ነገሠ ፎቃ በኢየሩሳሌም ባሉ ምእመናን መከራ አጸናባቸው ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን እኛ ላንተ እንገዛለን ብለው ወደ ሕርቃል ላኩበት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን "ግዙራን ይነሥእዋ ለመንግሥትከ" የሚል ራእይ አየ።
መንግሥቱን የሚወስድበት ኡመር ወልደ አድ እንደሆነ ባያውቅ "ግዙራን የተባሉ ሌላን እለ? አይሁድ አይደሉምን" ብሎ "ያን የላካችሁብኝ ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጅ" አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ሰባ ሰማንያ ዘመን ነው ይህንንስ እኛ እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በኢየሩሳሌም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቁትን ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥራት አድርገው በዓመት በዓመት የሚጾሙት ሁነዋል!
② የሮም ሊቃነ ጳጳሳት ቀሳውስት ዲያቆናት ምእመናን ጹመውታል የሮሙን ንጉሥ ከፋርሱ ንጉሥ ተጋብቶ ሲኖር ሚስቱን በድሎ ሰደዳት ሒዳ ለአባቷ አንተን ያህል አባት እያለኝ በድሎ ሰደደኝ አለችው። እሱም ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብሎ ሒዶ እኔ ከሀገሩ ጠብ የለኝም ጠቤ ካንድ ሰው ነው ጠላቴን ስጡኝ ባትሰጡኝ ግን ጠቤ ከናንተ ጋራ ነው አላቸው ቢትወደዱ «ፎቃ» ይባላል ባንድ ሰው ምክንያት ብዙ ሰው እናስጠፋለን። አውጥተን እንስጥ እንጂ አላቸው። ማን ይነግሣል አሉት እኔ እነግሣለሁ አላቸው አወጥተው ሰጡት ፎቃ ነገሠ።
የጥጦስን የአስባስያኖስን ዘመን ለመመለስ በሮም ባሉ ምእመናን አገዛዝ አጸናባቸው ኋላ ባሪያውን ለማይገባ ገረፈው ህርቃልን ቢትወደድነት ሹሞት ነበረና ሔዶ በማይገባ ገረፈኝ ብሎ ነገረው አትገድለውም አለው ማን ይነግሣል አለው እኔ እነሣለሁ አለው ጊዜ አይቶ ገደለው ህርቃል ነገሠ። ከዚህ በኋላ የሮም ምእመናን መጥተው እኛም ከወገኖቻችን ካነገሥክልን ብድራችንን እንድንመልስ አይሁድን አጥፋልን ብለው አማሉት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን ግዙራን ይነሥእዋ ለመግሥትከ የሚል ራእይ አየ ግዙራን የተባሉ ሌላ እለን አይሁድ አይደሉምን ብሎ ያን ያላችሁኝን ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጂ አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ስባ ሰማንያ ዘመን ነው። ይህነንስ #እኛ_እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በሮም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቅቱ ግን ቀድሞውም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥርዓት አድርገው ባመት ባመት የሚጾሙት ሁነዋል።
ወደ እኛ የደረሰው እንዴት እንደሆነ ለማሳየትም ለመሰናዶው ሳምንት የሕርቃልነቱን ስያሜ ተቀብለው ከዐቢይ ጾም ቀድሞ ባለው ሳምንት እንዲዘከር በድንጋጌ ያጸኑ በዘመነ ሕርቃል በእስክንድርያ የነበሩ ፴፯ኛው ፓትርያርክ አቡነ አንደራኒቆስ መሆናቸውን ዜና ጳጳሳቱ ይነግረናል።
"Pope Adronicus, the 37th Patriarch of Alexandria, acknowledged this request. From that time, “Heraclius Week” began to be observed."
በአጋዥ የታሪክ ማነጻጸሪያ ደግሞ በስንክሳራችን ዕረፍቱ ጥር ፰ የሚዘከረው በቅዱስ ማርቆስ መንበር ፴፯ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ አንደራኒቆስ በዘመኑ የፋርስ ንጉሥ ክስራ [Kessra the king of Persia] ከሮሙ ንጉሥ ህርቃል ጋር ስላደረገው ጦርነትና እስክንድርያ ባሉ ምእመናንም ላይ ይደርስ ስለነበረው መከራ ተከታዩን ታሪክ ይነግረናል።
«በሹመቱም ወራት ፀሐይን የሚያመልክ የፋርስ ንጉሥ ክስራ ተነሣና የሶርያንና የፍልስጤምን ከተሞች ወርሮ ዘረፋቸው፡፡ ወደ ግብጽም መጥቶ እስክንድድርያ ከተማ ደረሰ፡፡ በዙሪዋ በመነኮሳት የተሞሉ ሰባት መቶ ገዳማት ነበሩ፡፡ እነርሱም ገንዘብ ያላቸው በተድላ የሚኖሩ ነበሩ፡፡ ስለዚህም በእነርሱ ላይ እግዚአብሔር ሥልጣንን ሰጥቶት ገዳማቱን አፈረሰ፡፡ እነርሱንም ሸሽተው ካመለጡት በቀር ሁሉንም ገደላቸው፡፡ ገንዘባቸውንም ሁሉ ማረከ፡፡
የእስክንድርያ ሰዎችም ንጉሥ ክስራ ያደረገውን ባዩ ጊዜ የከተማውን በር ከፈቱለት፡፡ እርሱም ‹ይህችን አገር በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁ አታፍርሳት፣ በውስጧ ያሉትን ብርቱዎች ግደላቸው-ዐመፀኞች ናቸውና› እንደሚለው በሕልሙ አየ፡፡ በዚህም ጊዜ የሀገሩን ንጉሥ ይዞ ካሠረው በኋላ ለሀገሩ ሰዎች ‹‹በጦር ሠራዊት አደራጃቸዋለሁና ከ18 ዓመት ጀምሮ ያሉትን ብርታት ያላቸውንም ሁሉ ሰበስቡልኝ፣ ለእያንዳንዳቸው ደመወዛቸውን 20 የወርቅ ዲናር እከፍላለሁ›› አላቸው፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እውነት ወርቅ የሚቀበሉ መስሏቸው 8 ሺህ ብርቱዎችን ቆጥረውና መዝግበው በሰጡት ጊዜ ንጉሡ ክስራ ሁሉንም በሰይፍ ገደላቸው፡፡ ወደላይኛው ግብጽ በመሄድም ኒቅዮስ ደርሶ ሰባት መቶ በሥራቸው ክፉ የሆኑ መነኮሳትን በሰይፍ ገደላቸው፡፡ የሮም ንጉሥ ሕርቃልም የፋርሱ ንጉሥ ክስራ ያደረገውን በሰማ ጊዜ ሠራዊቱን ሰብስቦ መጥቶ ንጉሥ ክስራን ከነሠራዊቱ ሀገሩንም ጭምር አጠፋቸው፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የአባ እንድራኒቆስ ገድሉ እጅግ ያማረ ነበር፡፡ … »
ሕርቃል ከአርመናውያን ቤተሰቦች በ575 ዓ.ም. በቀጰዶቅያ ተወልዶ በ641 ዓ.ም. በቁስጠንጥንያ ያረፈ በእምነቱም የመለካውያኑ (Chalcedonian Christianity) ተከታይ የነበረ የሮማውያን ንጉሥ ቢሆንም ካቶሊካውያኑ የእኛውን ንጉሥ አፄ ካሌብን [Saint Elesbaan] በቅድስና እንደሚዘክሩት «ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን» ብለው ደጅ ለጠኑት በእስክንድርያ እና በኢየሩሳሌም ለነበሩ ምእመናን ባለውለታ በመሆኑ ኦርቶዶክሳውያኑ የልዩነት ድንበሩን ጠብቀው ሲያከብሩት ኖረዋል።
የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሰላም ፣ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ፍቅርና የኢየሱስ ክርስቶስ የረድኤቱ ሀብት የቅዱስ መስቀሉም ሞገስ ሁል ጊዜ ለዘለዓለሙ ከሁላችን አይራቅ!
ከሰሙነ ሕርቃል በረከት ያሳትፈን!
🌴 reposted from ቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ልደታ ፳፻፲፫ ዓ.ም. ተጻፈ✍
የኋላውንም ሁለት መነሻ ሊሆኑ የሚችሉ ታሪኮች ደግሞ እንዲህ ያብራራልናል።
① በኢየሩሳሌም ፎቃ በሮም ህርቃል ነገሠ ፎቃ በኢየሩሳሌም ባሉ ምእመናን መከራ አጸናባቸው ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን እኛ ላንተ እንገዛለን ብለው ወደ ሕርቃል ላኩበት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን "ግዙራን ይነሥእዋ ለመንግሥትከ" የሚል ራእይ አየ።
መንግሥቱን የሚወስድበት ኡመር ወልደ አድ እንደሆነ ባያውቅ "ግዙራን የተባሉ ሌላን እለ? አይሁድ አይደሉምን" ብሎ "ያን የላካችሁብኝ ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጅ" አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ሰባ ሰማንያ ዘመን ነው ይህንንስ እኛ እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በኢየሩሳሌም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቁትን ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥራት አድርገው በዓመት በዓመት የሚጾሙት ሁነዋል!
② የሮም ሊቃነ ጳጳሳት ቀሳውስት ዲያቆናት ምእመናን ጹመውታል የሮሙን ንጉሥ ከፋርሱ ንጉሥ ተጋብቶ ሲኖር ሚስቱን በድሎ ሰደዳት ሒዳ ለአባቷ አንተን ያህል አባት እያለኝ በድሎ ሰደደኝ አለችው። እሱም ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብሎ ሒዶ እኔ ከሀገሩ ጠብ የለኝም ጠቤ ካንድ ሰው ነው ጠላቴን ስጡኝ ባትሰጡኝ ግን ጠቤ ከናንተ ጋራ ነው አላቸው ቢትወደዱ «ፎቃ» ይባላል ባንድ ሰው ምክንያት ብዙ ሰው እናስጠፋለን። አውጥተን እንስጥ እንጂ አላቸው። ማን ይነግሣል አሉት እኔ እነግሣለሁ አላቸው አወጥተው ሰጡት ፎቃ ነገሠ።
የጥጦስን የአስባስያኖስን ዘመን ለመመለስ በሮም ባሉ ምእመናን አገዛዝ አጸናባቸው ኋላ ባሪያውን ለማይገባ ገረፈው ህርቃልን ቢትወደድነት ሹሞት ነበረና ሔዶ በማይገባ ገረፈኝ ብሎ ነገረው አትገድለውም አለው ማን ይነግሣል አለው እኔ እነሣለሁ አለው ጊዜ አይቶ ገደለው ህርቃል ነገሠ። ከዚህ በኋላ የሮም ምእመናን መጥተው እኛም ከወገኖቻችን ካነገሥክልን ብድራችንን እንድንመልስ አይሁድን አጥፋልን ብለው አማሉት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን ግዙራን ይነሥእዋ ለመግሥትከ የሚል ራእይ አየ ግዙራን የተባሉ ሌላ እለን አይሁድ አይደሉምን ብሎ ያን ያላችሁኝን ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጂ አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ስባ ሰማንያ ዘመን ነው። ይህነንስ #እኛ_እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በሮም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቅቱ ግን ቀድሞውም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥርዓት አድርገው ባመት ባመት የሚጾሙት ሁነዋል።
ወደ እኛ የደረሰው እንዴት እንደሆነ ለማሳየትም ለመሰናዶው ሳምንት የሕርቃልነቱን ስያሜ ተቀብለው ከዐቢይ ጾም ቀድሞ ባለው ሳምንት እንዲዘከር በድንጋጌ ያጸኑ በዘመነ ሕርቃል በእስክንድርያ የነበሩ ፴፯ኛው ፓትርያርክ አቡነ አንደራኒቆስ መሆናቸውን ዜና ጳጳሳቱ ይነግረናል።
"Pope Adronicus, the 37th Patriarch of Alexandria, acknowledged this request. From that time, “Heraclius Week” began to be observed."
በአጋዥ የታሪክ ማነጻጸሪያ ደግሞ በስንክሳራችን ዕረፍቱ ጥር ፰ የሚዘከረው በቅዱስ ማርቆስ መንበር ፴፯ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ አንደራኒቆስ በዘመኑ የፋርስ ንጉሥ ክስራ [Kessra the king of Persia] ከሮሙ ንጉሥ ህርቃል ጋር ስላደረገው ጦርነትና እስክንድርያ ባሉ ምእመናንም ላይ ይደርስ ስለነበረው መከራ ተከታዩን ታሪክ ይነግረናል።
«በሹመቱም ወራት ፀሐይን የሚያመልክ የፋርስ ንጉሥ ክስራ ተነሣና የሶርያንና የፍልስጤምን ከተሞች ወርሮ ዘረፋቸው፡፡ ወደ ግብጽም መጥቶ እስክንድድርያ ከተማ ደረሰ፡፡ በዙሪዋ በመነኮሳት የተሞሉ ሰባት መቶ ገዳማት ነበሩ፡፡ እነርሱም ገንዘብ ያላቸው በተድላ የሚኖሩ ነበሩ፡፡ ስለዚህም በእነርሱ ላይ እግዚአብሔር ሥልጣንን ሰጥቶት ገዳማቱን አፈረሰ፡፡ እነርሱንም ሸሽተው ካመለጡት በቀር ሁሉንም ገደላቸው፡፡ ገንዘባቸውንም ሁሉ ማረከ፡፡
የእስክንድርያ ሰዎችም ንጉሥ ክስራ ያደረገውን ባዩ ጊዜ የከተማውን በር ከፈቱለት፡፡ እርሱም ‹ይህችን አገር በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁ አታፍርሳት፣ በውስጧ ያሉትን ብርቱዎች ግደላቸው-ዐመፀኞች ናቸውና› እንደሚለው በሕልሙ አየ፡፡ በዚህም ጊዜ የሀገሩን ንጉሥ ይዞ ካሠረው በኋላ ለሀገሩ ሰዎች ‹‹በጦር ሠራዊት አደራጃቸዋለሁና ከ18 ዓመት ጀምሮ ያሉትን ብርታት ያላቸውንም ሁሉ ሰበስቡልኝ፣ ለእያንዳንዳቸው ደመወዛቸውን 20 የወርቅ ዲናር እከፍላለሁ›› አላቸው፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እውነት ወርቅ የሚቀበሉ መስሏቸው 8 ሺህ ብርቱዎችን ቆጥረውና መዝግበው በሰጡት ጊዜ ንጉሡ ክስራ ሁሉንም በሰይፍ ገደላቸው፡፡ ወደላይኛው ግብጽ በመሄድም ኒቅዮስ ደርሶ ሰባት መቶ በሥራቸው ክፉ የሆኑ መነኮሳትን በሰይፍ ገደላቸው፡፡ የሮም ንጉሥ ሕርቃልም የፋርሱ ንጉሥ ክስራ ያደረገውን በሰማ ጊዜ ሠራዊቱን ሰብስቦ መጥቶ ንጉሥ ክስራን ከነሠራዊቱ ሀገሩንም ጭምር አጠፋቸው፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የአባ እንድራኒቆስ ገድሉ እጅግ ያማረ ነበር፡፡ … »
ሕርቃል ከአርመናውያን ቤተሰቦች በ575 ዓ.ም. በቀጰዶቅያ ተወልዶ በ641 ዓ.ም. በቁስጠንጥንያ ያረፈ በእምነቱም የመለካውያኑ (Chalcedonian Christianity) ተከታይ የነበረ የሮማውያን ንጉሥ ቢሆንም ካቶሊካውያኑ የእኛውን ንጉሥ አፄ ካሌብን [Saint Elesbaan] በቅድስና እንደሚዘክሩት «ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን» ብለው ደጅ ለጠኑት በእስክንድርያ እና በኢየሩሳሌም ለነበሩ ምእመናን ባለውለታ በመሆኑ ኦርቶዶክሳውያኑ የልዩነት ድንበሩን ጠብቀው ሲያከብሩት ኖረዋል።
የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሰላም ፣ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ፍቅርና የኢየሱስ ክርስቶስ የረድኤቱ ሀብት የቅዱስ መስቀሉም ሞገስ ሁል ጊዜ ለዘለዓለሙ ከሁላችን አይራቅ!
ከሰሙነ ሕርቃል በረከት ያሳትፈን!
🌴 reposted from ቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ልደታ ፳፻፲፫ ዓ.ም. ተጻፈ✍
የንስሃ መንገዶች
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
አምስት የንስሃ መንገዶች አሉ ። የተለያዩ ቢሆኑም ቅሉ ሁሉም የሚያደርሱት ግን ርስት መንግስተ ሰማያት ነው ። እነርሱስ ምን ምን ናቸው ? ያልከኝ እንደሆነ እንድህ ብየ እመልስልሃለሁ፦
፩ኛ • የመጀመሪያው መንገድ "የራስን ኃጢአት ማመን፣ መጥላትና ማውገዝ ነው።
ይኽውም ልዑል ቃል ኢሳይያስ "እንድትጸድቅ መጀመሪያ ኃጢአትህን ተናገር እንዳለው" (ኢሳ 43 ፥26 )፤ ክቡር ዳዊትም "በደሌን አልሸፈንኩም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እንግራለሁ አልሁ ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውኽልኝ" ብሎ እንደተናገረ መዝ 31፥5 ስለዚህ አንተም ስለ ሰራኽው ኃጢአት እራስህን ውቀሰው። በዚህ እግዚአብሔር ይቅር እንዲልህ ታደርገዋለህና። ይህ ብቻ ሳይሆን ስለ ኃጢአቱ እራሱን የሚወቅስና ኃጢአቱን የሚኮንን ሰው በተመሳሳይ ኃጢአት በቀላሉ አይወድቅምና። ስለዚህ በጌታ የፍርድ ዙፋን የሚወቅስህ እንዳይኖር ዛሬ እውነተኛ ወቃሽ በኾነው ሕሊናህን አንቅተህ በራስህ ላይ ወቃሽና ከሳሽ አድርገህ ሹመው። ይህ አንዱና ደገኛው መንገድ ነው ።
፪• ሁለተኛው የንስሐ መንገድ ደግሞ
የወገኖቻችንን በደል ይቅር ማለትና በበደሉህ ላይ ቅሬታና ቂም አለመያዝ ነው።
እንዲህ ስናደርግ "ለሰወች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተንም ደግሞ ይቅር ይላችኋል" እንዲል እኛ በጌታችን ላይ ያደረግነውን በደል ይቅር እንባላለንና። ማቴ 6 ፡14
፫• ሦስተኛውን የንስሃ መንገድ መንበረ ጸባዖት የደርስ በትጋትና በጥልቅ ስሜት የሚደረግ "ከልብ የመነጨ ጸሎት ነው"
ጨካኙ ዳኛ እንዲርፈድላት ያደረገችው ያች መበለት እንዴት እንዲፈርድላት እንዳደረችገው አታያትም? ( ሉቃ 18፥3) አንተ ግን ሩኅሩኅና መሐሪ የኾነ ጌታ ነው ያለህ። እርሷ በጠላቶቿ ላይ እንዲፈርድላት ነው የጠየቀችው፤ አንተ ግን እምትጠይቀው ስለራስህ ድኅነት ነው።
፬• አራተኛ መንገድ አለ እርሱም "ምጽትዋ ነው " ይህም እጅግ በጣም ታላቅ የኾነ ኃጢአትን የሚስተርይ ኃይል አለውና።
ናቡከደነጾር ኃጢትን ንቅስ ጥቅስ አርድጎ ወደ ክኅደት ሁሉ በገባ ጊዜ እንድህ ብሎታልና፦ "ንጉስ ሆይ ! ምክሬ ደስ ያሰኝህ ኃጢአትህም ለጽድቅ በደልህን ለድኾች በመመጽወት አስቀር" (ዳ.ን 3፥27 ) ይህ ቸርነትና ሰውን መውደድስ ምንስ ይስተካከለዋል? እንዴት ያልከኝ እንደሆነ ስፍር ቁጥር የሌለውን ኃጢአት ከሰራ በኋላ ከዚያ ኹሉ በደል በኋላ እንደርሱ ለሆኑ ሰወች ርኅራኄን ቢያደርግ ከተገዳደረውና ከተጣላው አምላክ ጋር መታረቅ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታልና ።
፭• አምስተኛው መንገድ "እንዲሁም ትሕትናና እራስን ማዋረድ ኃጢአትን ያደክማል"
ይህንንም ቀራጩ ያረጋግጥልናል አይኖቹን ወደ ሰማይ ለማንሳት እንኳንስ እስኪፈራ ድረስ በታላቅ ትሕትና ራሱን ባዶ ባደረገ ጊዜ "ጻድቅ ሆኖ ሄደ ተብሏልና ።(ሉቃ 18፥13) ስለዚህም ምንም ምግባር ቢኖርህም እንኳን በደልህን ከመናር በቀር በጎ ምግባርህን አታስበው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር የበደል ሸምክህን ያራግፍልሃል።
ስለዚህ እነዚህን መንገደኞች ተመላለስባቸው እንጅ ሰነፍ አትኹን ።
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
አምስት የንስሃ መንገዶች አሉ ። የተለያዩ ቢሆኑም ቅሉ ሁሉም የሚያደርሱት ግን ርስት መንግስተ ሰማያት ነው ። እነርሱስ ምን ምን ናቸው ? ያልከኝ እንደሆነ እንድህ ብየ እመልስልሃለሁ፦
፩ኛ • የመጀመሪያው መንገድ "የራስን ኃጢአት ማመን፣ መጥላትና ማውገዝ ነው።
ይኽውም ልዑል ቃል ኢሳይያስ "እንድትጸድቅ መጀመሪያ ኃጢአትህን ተናገር እንዳለው" (ኢሳ 43 ፥26 )፤ ክቡር ዳዊትም "በደሌን አልሸፈንኩም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እንግራለሁ አልሁ ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውኽልኝ" ብሎ እንደተናገረ መዝ 31፥5 ስለዚህ አንተም ስለ ሰራኽው ኃጢአት እራስህን ውቀሰው። በዚህ እግዚአብሔር ይቅር እንዲልህ ታደርገዋለህና። ይህ ብቻ ሳይሆን ስለ ኃጢአቱ እራሱን የሚወቅስና ኃጢአቱን የሚኮንን ሰው በተመሳሳይ ኃጢአት በቀላሉ አይወድቅምና። ስለዚህ በጌታ የፍርድ ዙፋን የሚወቅስህ እንዳይኖር ዛሬ እውነተኛ ወቃሽ በኾነው ሕሊናህን አንቅተህ በራስህ ላይ ወቃሽና ከሳሽ አድርገህ ሹመው። ይህ አንዱና ደገኛው መንገድ ነው ።
፪• ሁለተኛው የንስሐ መንገድ ደግሞ
የወገኖቻችንን በደል ይቅር ማለትና በበደሉህ ላይ ቅሬታና ቂም አለመያዝ ነው።
እንዲህ ስናደርግ "ለሰወች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተንም ደግሞ ይቅር ይላችኋል" እንዲል እኛ በጌታችን ላይ ያደረግነውን በደል ይቅር እንባላለንና። ማቴ 6 ፡14
፫• ሦስተኛውን የንስሃ መንገድ መንበረ ጸባዖት የደርስ በትጋትና በጥልቅ ስሜት የሚደረግ "ከልብ የመነጨ ጸሎት ነው"
ጨካኙ ዳኛ እንዲርፈድላት ያደረገችው ያች መበለት እንዴት እንዲፈርድላት እንዳደረችገው አታያትም? ( ሉቃ 18፥3) አንተ ግን ሩኅሩኅና መሐሪ የኾነ ጌታ ነው ያለህ። እርሷ በጠላቶቿ ላይ እንዲፈርድላት ነው የጠየቀችው፤ አንተ ግን እምትጠይቀው ስለራስህ ድኅነት ነው።
፬• አራተኛ መንገድ አለ እርሱም "ምጽትዋ ነው " ይህም እጅግ በጣም ታላቅ የኾነ ኃጢአትን የሚስተርይ ኃይል አለውና።
ናቡከደነጾር ኃጢትን ንቅስ ጥቅስ አርድጎ ወደ ክኅደት ሁሉ በገባ ጊዜ እንድህ ብሎታልና፦ "ንጉስ ሆይ ! ምክሬ ደስ ያሰኝህ ኃጢአትህም ለጽድቅ በደልህን ለድኾች በመመጽወት አስቀር" (ዳ.ን 3፥27 ) ይህ ቸርነትና ሰውን መውደድስ ምንስ ይስተካከለዋል? እንዴት ያልከኝ እንደሆነ ስፍር ቁጥር የሌለውን ኃጢአት ከሰራ በኋላ ከዚያ ኹሉ በደል በኋላ እንደርሱ ለሆኑ ሰወች ርኅራኄን ቢያደርግ ከተገዳደረውና ከተጣላው አምላክ ጋር መታረቅ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታልና ።
፭• አምስተኛው መንገድ "እንዲሁም ትሕትናና እራስን ማዋረድ ኃጢአትን ያደክማል"
ይህንንም ቀራጩ ያረጋግጥልናል አይኖቹን ወደ ሰማይ ለማንሳት እንኳንስ እስኪፈራ ድረስ በታላቅ ትሕትና ራሱን ባዶ ባደረገ ጊዜ "ጻድቅ ሆኖ ሄደ ተብሏልና ።(ሉቃ 18፥13) ስለዚህም ምንም ምግባር ቢኖርህም እንኳን በደልህን ከመናር በቀር በጎ ምግባርህን አታስበው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር የበደል ሸምክህን ያራግፍልሃል።
ስለዚህ እነዚህን መንገደኞች ተመላለስባቸው እንጅ ሰነፍ አትኹን ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
"የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡" ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ድርጊት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ምሥረታ ጀምሮ ያለችና መንግሥትን ያጸናች፣ የራሳቸው የጽሑፍ ቋንቋ ካላቸው ጥቂት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን ፊደል ቀርፃ ያስተማረች፣ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን መርሐ ግብር ከማስጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት የአካባቢ ጥበቃን ስትሠራ የኖረችና አሁንም በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማትና አድባራት የአካባቢ ጥበቃ ሥራን የምትሠራ፣ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት ሥርዓተ ትምህርት ቀርፃ ያስተማረችና የሀገር መሪዎችን፣ የስነ ህንፃ ባለሙያዎችን፣ የመድኃኒት አዋቂዎችንና ተመራማሪዎችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን ከመሆኗም በላይ ተቋም መሥርታ ለዘመናት የተቋምን ምንነት ያስተማረች ራሷ ሀገር የሆነች ናት፡፡
በተለይም ደግሞ መላው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት በተያዙበት፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያንም ለመቀራመት ተስማምተው በፋሺስቱ የኢጣልያ መንግሥት አማካኝነት ሀገራችንን በወረረበት ጊዜ የንጉሱን የክተት አዋጅ ተከትሎ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲዋደቅ የሀገር ፍቅር ለምእመኗ ያስተማረች በመሆኑ እና የንጉሱም ጥሪ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖትን የመጠበቅ ጥሪም የነበረ በመሆኑ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ንጉሱን እንዲከተል ከማድረጓም በላይ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን በካህናቱ አጅባ የጦር ግንባር ድረስ በመዝመት፣ ምእመኑን እና ህዝቡን በማጽናናትና ጸሎተ ፍትሀት በማድረግ በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ሀገራችን ድል እንድትቀዳጅና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነፃነት አርማ እንድትሆን በማድረግ ትልቁን የታሪክ ድርሻ እንደምትወስድ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡
ከዚህ የድል በዓል በኋላም ኢትዮጵያ በነፃነት በቆየችባቸው ዓመታት ሁሉ ይህን የአድዋ የድል በዓል ቤተ ክርስቲያን የሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ ሕግ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ሕዝቡን በመባረክ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በታላቅ ምሥጋና እና መዝሙር በመላ ሀገሪቱ ስታከብረው የኖረች፤ ወደፊትም እየፈጸመች የምትጸናበት አኩሪ ታሪኳ ነው፡፡
ይሁን እንጂ ይህ በዓል ላለፉት ጥቂት ዓመታት የድል በዓል መሆኑ ቀርቶ የጠብ እና የጥላቻ በዓል እየሆነ መምጣቱ ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ሆኗል፡፡ በተለይም ትላንት የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትን ግን ቤተ ክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሐዘን ብቻ የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም፡፡
በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር ህዝቡ ከየቤቱ ተሰባስቦ ከጠዋቱ ፫፡፲፭ ላይ ታቦተ ሕጉ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ዑደት ካደረገና ሕዝቡን ባርኮ በዐውደ ምህረቱ ላይ ከቆመ በኋላ ሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ በማቅረብ ላይ እንዳሉ ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናን ተላልፈው በሰሜን በኩል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ፪ ጊዜ በተኮሱት አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የንግሥ በዓሉ በመረበሹ በዓሉ ተቋርጦ ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ላይ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበሩ ተመልሷል፡፡ በዚህም ምክንያት እስከአሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ከፍተኛ ረብሻ በመፈጠሩ ምክንያት ፩ ምእመን በተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸውን፣ አገልጋይ ካህናት አባቶች፣ ምእመናን እና ምእመናት ከፍተኛ የሆነ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከ፲፭ ያላነሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ተማሪዎች በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡
ይህ ድርጊት ከተፈፀመ በኋላም መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና በመዳፈር በቤተ ክርስቲያን ላይ ይህን በደል የፈፀሙ የጸጥታ መዋቅር አካላትን ለሕግ ያቀርባል፣ እንደ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ብንጠብቅም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ በዓሉን አስመልክቶ በዕለቱ ባወጣው መግለጫ ችግሩን የፈጠሩት አካላት ‹‹የአደባባይ በዓሉን ለመረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡ የጸጥታ መዋቅሩ ችግሩን ለመቆጣጠር በወሰደው እርምጃ ጉዳቱን ለመቀነስ ችሏል›› ሲል የችግሩን ሁኔታ ገልጧል፡፡
በዚህ መግለጫውም ላይ አሁንም ችግሩ የሌሎች ቡድኖች እንደሆነና የቤተ ክርስቲያኒቱን በዓል የረበሸው የእነዚህ አካላት እንቅስቃሴ ነው በማለት የሰጠው መግለጫ በቦታው ላይ ከነበረው እውነታ በእጅጉ የራቀ እና ድርጊቱ የተወሰኑ ግለሰቦች ሳይሆን የመንግሥት እውቅና ያለው መሆኑን እንዲሁም መንግሥት ችግሩን ለማረም እና መፍታት ፍላጎት የሌለው መሆኑን እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡
የመንግሥት የጸጥታ አካል በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ምእመናን ላይ ጉዳት ሲያደርስ እና የቤተ ክርስቲያንን ክብር ሲያጎድፍ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በጥር ፩ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰቡ ምእመናን ላይ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ብዙ ምእመናን እንዲጎዱ የተደረገ ሲሆን በጊዜው መንግሥት ይህን ድርጊት በፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ልክ እንደአሁኑ ችግሩ የሕገ ወጦች ነው በማለት ለድርጊቱ እውቅና ሰጥቶት አልፏል፡፡ በዚህ ድርጊት መንግሥት በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ ያሉ እና መንግሥትንና ሕዝብን እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ያለመግባባት የሚያባብሱትን ግለሰቦች እና አመራሮች ለይቶ እርምት ከመውሰድ ይልቅ ሕዝብና መንግሥትን ሆድና ጀርባ የሚያደርግ ተግባሩን አስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ለዘመናት የኖረች እና ከግማሽ የሀገሪቱ ሕዝብ በላይ የያዘችን ቤተ ክርስቲያን ክብርና ልዕልና በሚዳፈር መልኩ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ይህን ድርጊት የፈጸሙ የጸጥታ አካላትና እንዲፈፀም ያዘዙ የመንግሥት ኃላፊዎችን በ፲፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለይቶ በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ እና ይህንንም ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በግልጽ እንዲያሳውቅ እንዲሁም በተለመደው የሐሰት ውንጀላ በዓላችንን በማክበር ላይ እያሉ የመንግሥት የጸጥታ አካላት በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት በተፈጠረው ግርግር መነሻት የታሰሩ ምእመናንን ያለምንም ቅድመ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ድርጊት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ምሥረታ ጀምሮ ያለችና መንግሥትን ያጸናች፣ የራሳቸው የጽሑፍ ቋንቋ ካላቸው ጥቂት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን ፊደል ቀርፃ ያስተማረች፣ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን መርሐ ግብር ከማስጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት የአካባቢ ጥበቃን ስትሠራ የኖረችና አሁንም በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማትና አድባራት የአካባቢ ጥበቃ ሥራን የምትሠራ፣ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት ሥርዓተ ትምህርት ቀርፃ ያስተማረችና የሀገር መሪዎችን፣ የስነ ህንፃ ባለሙያዎችን፣ የመድኃኒት አዋቂዎችንና ተመራማሪዎችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን ከመሆኗም በላይ ተቋም መሥርታ ለዘመናት የተቋምን ምንነት ያስተማረች ራሷ ሀገር የሆነች ናት፡፡
በተለይም ደግሞ መላው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት በተያዙበት፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያንም ለመቀራመት ተስማምተው በፋሺስቱ የኢጣልያ መንግሥት አማካኝነት ሀገራችንን በወረረበት ጊዜ የንጉሱን የክተት አዋጅ ተከትሎ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲዋደቅ የሀገር ፍቅር ለምእመኗ ያስተማረች በመሆኑ እና የንጉሱም ጥሪ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖትን የመጠበቅ ጥሪም የነበረ በመሆኑ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ንጉሱን እንዲከተል ከማድረጓም በላይ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን በካህናቱ አጅባ የጦር ግንባር ድረስ በመዝመት፣ ምእመኑን እና ህዝቡን በማጽናናትና ጸሎተ ፍትሀት በማድረግ በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ሀገራችን ድል እንድትቀዳጅና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነፃነት አርማ እንድትሆን በማድረግ ትልቁን የታሪክ ድርሻ እንደምትወስድ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡
ከዚህ የድል በዓል በኋላም ኢትዮጵያ በነፃነት በቆየችባቸው ዓመታት ሁሉ ይህን የአድዋ የድል በዓል ቤተ ክርስቲያን የሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ ሕግ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ሕዝቡን በመባረክ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በታላቅ ምሥጋና እና መዝሙር በመላ ሀገሪቱ ስታከብረው የኖረች፤ ወደፊትም እየፈጸመች የምትጸናበት አኩሪ ታሪኳ ነው፡፡
ይሁን እንጂ ይህ በዓል ላለፉት ጥቂት ዓመታት የድል በዓል መሆኑ ቀርቶ የጠብ እና የጥላቻ በዓል እየሆነ መምጣቱ ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ሆኗል፡፡ በተለይም ትላንት የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትን ግን ቤተ ክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሐዘን ብቻ የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም፡፡
በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር ህዝቡ ከየቤቱ ተሰባስቦ ከጠዋቱ ፫፡፲፭ ላይ ታቦተ ሕጉ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ዑደት ካደረገና ሕዝቡን ባርኮ በዐውደ ምህረቱ ላይ ከቆመ በኋላ ሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ በማቅረብ ላይ እንዳሉ ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናን ተላልፈው በሰሜን በኩል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ፪ ጊዜ በተኮሱት አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የንግሥ በዓሉ በመረበሹ በዓሉ ተቋርጦ ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ላይ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበሩ ተመልሷል፡፡ በዚህም ምክንያት እስከአሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ከፍተኛ ረብሻ በመፈጠሩ ምክንያት ፩ ምእመን በተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸውን፣ አገልጋይ ካህናት አባቶች፣ ምእመናን እና ምእመናት ከፍተኛ የሆነ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከ፲፭ ያላነሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ተማሪዎች በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡
ይህ ድርጊት ከተፈፀመ በኋላም መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና በመዳፈር በቤተ ክርስቲያን ላይ ይህን በደል የፈፀሙ የጸጥታ መዋቅር አካላትን ለሕግ ያቀርባል፣ እንደ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ብንጠብቅም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ በዓሉን አስመልክቶ በዕለቱ ባወጣው መግለጫ ችግሩን የፈጠሩት አካላት ‹‹የአደባባይ በዓሉን ለመረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡ የጸጥታ መዋቅሩ ችግሩን ለመቆጣጠር በወሰደው እርምጃ ጉዳቱን ለመቀነስ ችሏል›› ሲል የችግሩን ሁኔታ ገልጧል፡፡
በዚህ መግለጫውም ላይ አሁንም ችግሩ የሌሎች ቡድኖች እንደሆነና የቤተ ክርስቲያኒቱን በዓል የረበሸው የእነዚህ አካላት እንቅስቃሴ ነው በማለት የሰጠው መግለጫ በቦታው ላይ ከነበረው እውነታ በእጅጉ የራቀ እና ድርጊቱ የተወሰኑ ግለሰቦች ሳይሆን የመንግሥት እውቅና ያለው መሆኑን እንዲሁም መንግሥት ችግሩን ለማረም እና መፍታት ፍላጎት የሌለው መሆኑን እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡
የመንግሥት የጸጥታ አካል በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ምእመናን ላይ ጉዳት ሲያደርስ እና የቤተ ክርስቲያንን ክብር ሲያጎድፍ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በጥር ፩ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰቡ ምእመናን ላይ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ብዙ ምእመናን እንዲጎዱ የተደረገ ሲሆን በጊዜው መንግሥት ይህን ድርጊት በፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ልክ እንደአሁኑ ችግሩ የሕገ ወጦች ነው በማለት ለድርጊቱ እውቅና ሰጥቶት አልፏል፡፡ በዚህ ድርጊት መንግሥት በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ ያሉ እና መንግሥትንና ሕዝብን እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ያለመግባባት የሚያባብሱትን ግለሰቦች እና አመራሮች ለይቶ እርምት ከመውሰድ ይልቅ ሕዝብና መንግሥትን ሆድና ጀርባ የሚያደርግ ተግባሩን አስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡
በመሆኑም መንግሥት ለዘመናት የኖረች እና ከግማሽ የሀገሪቱ ሕዝብ በላይ የያዘችን ቤተ ክርስቲያን ክብርና ልዕልና በሚዳፈር መልኩ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ይህን ድርጊት የፈጸሙ የጸጥታ አካላትና እንዲፈፀም ያዘዙ የመንግሥት ኃላፊዎችን በ፲፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለይቶ በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ እና ይህንንም ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በግልጽ እንዲያሳውቅ እንዲሁም በተለመደው የሐሰት ውንጀላ በዓላችንን በማክበር ላይ እያሉ የመንግሥት የጸጥታ አካላት በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት በተፈጠረው ግርግር መነሻት የታሰሩ ምእመናንን ያለምንም ቅድመ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
ሁኔታ እንዲፈቱ እየጠየቅን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ቤተ ክርስቲያን መብቷን ለማስከበር ወደ ቀጣይ እርምጃዎች የምትገባ መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ይህንንም ድርጊት ተከታትሎ የሚያሳውቅ እና የሚያስፈጽም የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደሥራ እንዲገባ የሚደረግም መሆኑን ጭምር እናሳስባለን፡፡
በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት የሊቀ ሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር በመምጣት ሕይወቱን ላጣው ልጃችን እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሃም፣ በያዕቆብና በይስሐቅ እቅፍ ያኑር፣ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን ያድልልን እያልን ቀላልም ሆነ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ የቤተ ክርስቲያን የጭንቅ ቀን ልጆች ደማችሁን እና መከራችሁን እንደ ሰማእታት ዋጋ ይቆጥርላችሁ ዘንድ ጸሎታችን ነው፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት የሊቀ ሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር በመምጣት ሕይወቱን ላጣው ልጃችን እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሃም፣ በያዕቆብና በይስሐቅ እቅፍ ያኑር፣ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን ያድልልን እያልን ቀላልም ሆነ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ የቤተ ክርስቲያን የጭንቅ ቀን ልጆች ደማችሁን እና መከራችሁን እንደ ሰማእታት ዋጋ ይቆጥርላችሁ ዘንድ ጸሎታችን ነው፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
፩. የዛሬዋ ምኩራብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት፤
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትባት፤ ሰዎች ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚያገኙባት የሐዲስ ኪዳን ምኩራብ ናት። ጌታችን በቅፍርናሆም ምኩራብ የሕይወት እንጀራ እርሱ ስለመሆኑ ያስተማረበት በዚህ በሦስተኛው ሳምንት በሰፊው ይነገራል። በዘመናችንም ‹‹የአባቴ ቤት የጸሎት ቤት ይሆናል።›› በሚል የድኾችና የምስኪኖች መጠጊያ እናት ተብላ የተነገረላት ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በዘመናችን የንግድ ቤትና የወንበዴዎች ዋሻ ወደ መሆን የተሸጋገረች ትመስላለች። በርካታ ድሆች፣ አረጋውያንና መበለቶች፣ እናት አባት የሌላቸው ሕፃናት፣ ድውያንና አካል ጉዳተኞች በደጇ የወደቁ ቤተ ክርስቲያን የእነዚህን ድሆችና ምስኪኖች ጩኸትና ዋይታ አላየኹም አልሰማውም በሚል የንግድ ቤት ግንባታ ውድድር ውስጥ ገብታለች። በኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምግባረ ሠናይ ድርጅትን በማጠናከር ረገድ እጅግ አነስተኛ ነው፤ ሌላው ቀርቶ በደጋጎቹ ነገሥታት የተቋቋሙ ምግባረ ሠናይ ድርጅቶች የሚከታተላቸው አካል በማጣታቸው የፈረሱ አሉ፤ በመፍረስ ላይ የሚገኙም አሉ፤ ለምሳሌ ከመቶ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረ ጥንታዊው የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ የአረጋውያንና የእጓለ ማውታ ድርጅት ‹‹አለ›› በማይባልበት ደረጃ እጅግ በመዳከም ላይ ይገኛል፤ ዛሬ የአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት ታላላቅ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ገንብተዋል፤ የሚገርመው ሬስቶራንትና ሱፐር ማርኬት እንጂ ግን አንዳቸውም ላይ የምግባረ ሠናይ ተቋም አናገኝም። ይህ እንደ ግመል ሽንት ወደ ኋላ መሄዳችንን ያሳያል፤ እውነቱን ለመናገር ከመቶ ዓመታት በፊት ያሉትን መሪዎችን እንኳን የመውቀስ ሆነ የማወደስም ሞራል የለንም፤ ምክንያቱም በዘረኝነት በነቀዘ በሙስና በቆሸሸ በእኛ አንደበት መወደሳቸው ለእነርሱ ውርደት እንጂ ክብር አይደለምና። እንደ ሕንድና እንደ ግብጽ ያሉ አኃት አብያተ ክርስቲያናትን ተሞክሮ ብንወስድ ለምሳሌ በሕንድ ከ፵፪ በላይ በቤተ ክህነት የሚተዳደሩ የምግባረ ሠናይ ድርጅቶች አሏቸው። በአሁኑ ጊዜ አረጋውያንን የሚጦር እጓለ ማውታ ሕፃናትን ተንከባክቦ የሚያሳድግ ምግባረ ሠናይ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ተጠናክሮ መቀጠል ሲገባው ያሉትን ከማዳከም በላይ ምን ግፍ አለ፤ በተለይ በአንዳንድ አህጉረ ስብከት ያሉ የመምሪያ ኀላፊዎች በሙስና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተመቻመቹ ቤተ ክርስቲያን ለምግባረ ሠናይ ብላ ይዛ ያቆየችው ሀብትና መሬት በሌሎች አካላት እንድትነጠቅ ከፍተኛ ደባ ተፈጽሞባታል። የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ መሆን የነበረበት ሕንጻ እየገነቡ ለሆቴልና ለሸቀጣ ሸቀጥ መሸጫ ማከራየት ሳይሆን በሃይማኖታቸው ምክንያት ከቤታቸው ለተገፉ፤ ሃይማኖታችሁን ካለወጣችሁ ማደሪያችሁን ፈልጉ እየተባሉ በገዛ ልጆቻቸው ዛቻ ለሚፈጸምባቸው ከቤታቸው ለተገፈተሩ ጧሪ ቀባሪ ላጡ አረጋውያን መርጃ እንዲሆን ማድረግ ነበር። (ምንጭ ‹‹ሰቆቃወ ቤተ ክርስቲያን›› ታኅሣሥ ፳፻፲፪ ዓም)
ቤተ ክርስቲያን ዙሪያዋን በንግድ ቤትና በሱቆች ተንቆጥቁጣ በገንዘብ ባሕር ውስጥ እየዋኘች፣ ሀብትና ንብረቷ በአስመሳዮች፣ በወንበዴዎች፣ በሙሰኞችና በአጭበርባሪ ነጋዴዎች እየተዘረፈ ባለበት በዚህ ወቅት በደጇ ለወደቁ ድሆችና ምስኪኖች ምእመናኖቿ ከሚጥሉላቸው የሳንቲም ሽርፍራፊ የልብስ እራፊ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኒቱ ለእነዚህ ድሆች ዘላቂነት ያለው ሥራ ከመሥራት ይልቅ የመቃብር ሥፍራ እንኳን ሁሉ ሳይቀር እያፈረሰች የንግድ ቤትና ሱቆችን እየገነባችና እያስፋፋች ትገኛለች። ለመሆኑ በከተማችን የትኛው ቤተ ክርስቲያን ነው ለአረጋውያን መጦሪያ፣ ለድኾች መርጃ የሚሆን ተቋም የገነባው። በጣት የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናት ለትውልድ ማፍሪያ የሚሆን የትምህርት ተቋማት መገንባታቸው እሙን ነው። እነዚህም ቢሆኑ በአብዛኛው በራቸው ክፍት የሚሆነው ኪሳቸው ዳጎስ ላሉት እንጂ ለድሆችና ረዳት ለሌላቸው አይደለም። ሆኖም ግን የቤተ ክርስቲያንን አጥር በንግድ ቤት ከሞሉት እነዚህኞቹ ሳይሻሉ አይቀርም፤ ቢያንስ ትውልድ እየቀረጹ ነውና።
በከተማይቱ እምብርት ባሉ አንዳንድ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የመዝናኛ ስፍራዎችና ጭፈራ ቤቶች እንኳን ለኻያ አራት ሰዓት የማይቋረጥ አገልግሎት በሚሰጡበት በዚህ ዘመን የዘመናችን ቤተ ክርስቲያን ግን እህል ውኃ የማያሰኝ ቆመጥና ነፍጥ ባነገቱ ዘበኞቿ በሯ ከምሽት ሰዓት በኋላ በትላልቅ ሰረገላና መሸጎሪያዎች ተቆልፈው ድሆች ከግቢዋ ተገፍትረው እየወጡ ለሌሊት ብርድና ቁር ተጋልጠው እንዲኖሩ ይፈረድባቸዋል። እናም እነዚህ ድኾችም በሺዎች በሚቆጠር ብር በሚከራዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ የንግድ ማዕከላት በረንዳ ላይ ወድቀው ኑሮአቸውን በምሬት ይገፋሉ።
ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ የዘመነ ሐዲስ ምኩራብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላዘነው መጽናናትን ለተጨነቀው መረጋጋትን የምትሰጥ፤ ደስታን የምታስታጥቅ ኀዘንን የምታርቅ እንደሆነች ሲዘምርላት እንዲህ አለ ‹‹በከመ ይቤ እግዚእነ በነቢይ ጊሥዋ ለቤተ ክርስቲያን እስመ ኵሉ ዘጌሠ ኀቤሃ ተአሥዮ ፍሥሐ። ጌታችን በነቢዩ አድሮ እንደተናገረው ቤተ ክርስቲያንን ገሥግሡባት፤ ማልዱባት ወደ እርሷ የገሠገሠውን ደስታ ትሰጠዋለችና›› በማለት ዘወትር ማልደው ወደ እርሷ የሚሄዱ ምእመናን ተጽናንተው ኀይል አግኝተው ተደስተው እንደሚመለሱ ተናግሯል። (ደብረ ዘይት ዘሐሙስ)
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትባት፤ ሰዎች ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚያገኙባት የሐዲስ ኪዳን ምኩራብ ናት። ጌታችን በቅፍርናሆም ምኩራብ የሕይወት እንጀራ እርሱ ስለመሆኑ ያስተማረበት በዚህ በሦስተኛው ሳምንት በሰፊው ይነገራል። በዘመናችንም ‹‹የአባቴ ቤት የጸሎት ቤት ይሆናል።›› በሚል የድኾችና የምስኪኖች መጠጊያ እናት ተብላ የተነገረላት ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በዘመናችን የንግድ ቤትና የወንበዴዎች ዋሻ ወደ መሆን የተሸጋገረች ትመስላለች። በርካታ ድሆች፣ አረጋውያንና መበለቶች፣ እናት አባት የሌላቸው ሕፃናት፣ ድውያንና አካል ጉዳተኞች በደጇ የወደቁ ቤተ ክርስቲያን የእነዚህን ድሆችና ምስኪኖች ጩኸትና ዋይታ አላየኹም አልሰማውም በሚል የንግድ ቤት ግንባታ ውድድር ውስጥ ገብታለች። በኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምግባረ ሠናይ ድርጅትን በማጠናከር ረገድ እጅግ አነስተኛ ነው፤ ሌላው ቀርቶ በደጋጎቹ ነገሥታት የተቋቋሙ ምግባረ ሠናይ ድርጅቶች የሚከታተላቸው አካል በማጣታቸው የፈረሱ አሉ፤ በመፍረስ ላይ የሚገኙም አሉ፤ ለምሳሌ ከመቶ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረ ጥንታዊው የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ የአረጋውያንና የእጓለ ማውታ ድርጅት ‹‹አለ›› በማይባልበት ደረጃ እጅግ በመዳከም ላይ ይገኛል፤ ዛሬ የአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት ታላላቅ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ገንብተዋል፤ የሚገርመው ሬስቶራንትና ሱፐር ማርኬት እንጂ ግን አንዳቸውም ላይ የምግባረ ሠናይ ተቋም አናገኝም። ይህ እንደ ግመል ሽንት ወደ ኋላ መሄዳችንን ያሳያል፤ እውነቱን ለመናገር ከመቶ ዓመታት በፊት ያሉትን መሪዎችን እንኳን የመውቀስ ሆነ የማወደስም ሞራል የለንም፤ ምክንያቱም በዘረኝነት በነቀዘ በሙስና በቆሸሸ በእኛ አንደበት መወደሳቸው ለእነርሱ ውርደት እንጂ ክብር አይደለምና። እንደ ሕንድና እንደ ግብጽ ያሉ አኃት አብያተ ክርስቲያናትን ተሞክሮ ብንወስድ ለምሳሌ በሕንድ ከ፵፪ በላይ በቤተ ክህነት የሚተዳደሩ የምግባረ ሠናይ ድርጅቶች አሏቸው። በአሁኑ ጊዜ አረጋውያንን የሚጦር እጓለ ማውታ ሕፃናትን ተንከባክቦ የሚያሳድግ ምግባረ ሠናይ በቤተ ክርስቲያናችን ስም ተጠናክሮ መቀጠል ሲገባው ያሉትን ከማዳከም በላይ ምን ግፍ አለ፤ በተለይ በአንዳንድ አህጉረ ስብከት ያሉ የመምሪያ ኀላፊዎች በሙስና ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተመቻመቹ ቤተ ክርስቲያን ለምግባረ ሠናይ ብላ ይዛ ያቆየችው ሀብትና መሬት በሌሎች አካላት እንድትነጠቅ ከፍተኛ ደባ ተፈጽሞባታል። የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ መሆን የነበረበት ሕንጻ እየገነቡ ለሆቴልና ለሸቀጣ ሸቀጥ መሸጫ ማከራየት ሳይሆን በሃይማኖታቸው ምክንያት ከቤታቸው ለተገፉ፤ ሃይማኖታችሁን ካለወጣችሁ ማደሪያችሁን ፈልጉ እየተባሉ በገዛ ልጆቻቸው ዛቻ ለሚፈጸምባቸው ከቤታቸው ለተገፈተሩ ጧሪ ቀባሪ ላጡ አረጋውያን መርጃ እንዲሆን ማድረግ ነበር። (ምንጭ ‹‹ሰቆቃወ ቤተ ክርስቲያን›› ታኅሣሥ ፳፻፲፪ ዓም)
ቤተ ክርስቲያን ዙሪያዋን በንግድ ቤትና በሱቆች ተንቆጥቁጣ በገንዘብ ባሕር ውስጥ እየዋኘች፣ ሀብትና ንብረቷ በአስመሳዮች፣ በወንበዴዎች፣ በሙሰኞችና በአጭበርባሪ ነጋዴዎች እየተዘረፈ ባለበት በዚህ ወቅት በደጇ ለወደቁ ድሆችና ምስኪኖች ምእመናኖቿ ከሚጥሉላቸው የሳንቲም ሽርፍራፊ የልብስ እራፊ በስተቀር ቤተ ክርስቲያኒቱ ለእነዚህ ድሆች ዘላቂነት ያለው ሥራ ከመሥራት ይልቅ የመቃብር ሥፍራ እንኳን ሁሉ ሳይቀር እያፈረሰች የንግድ ቤትና ሱቆችን እየገነባችና እያስፋፋች ትገኛለች። ለመሆኑ በከተማችን የትኛው ቤተ ክርስቲያን ነው ለአረጋውያን መጦሪያ፣ ለድኾች መርጃ የሚሆን ተቋም የገነባው። በጣት የሚቆጠሩ አብያተ ክርስቲያናት ለትውልድ ማፍሪያ የሚሆን የትምህርት ተቋማት መገንባታቸው እሙን ነው። እነዚህም ቢሆኑ በአብዛኛው በራቸው ክፍት የሚሆነው ኪሳቸው ዳጎስ ላሉት እንጂ ለድሆችና ረዳት ለሌላቸው አይደለም። ሆኖም ግን የቤተ ክርስቲያንን አጥር በንግድ ቤት ከሞሉት እነዚህኞቹ ሳይሻሉ አይቀርም፤ ቢያንስ ትውልድ እየቀረጹ ነውና።
በከተማይቱ እምብርት ባሉ አንዳንድ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የመዝናኛ ስፍራዎችና ጭፈራ ቤቶች እንኳን ለኻያ አራት ሰዓት የማይቋረጥ አገልግሎት በሚሰጡበት በዚህ ዘመን የዘመናችን ቤተ ክርስቲያን ግን እህል ውኃ የማያሰኝ ቆመጥና ነፍጥ ባነገቱ ዘበኞቿ በሯ ከምሽት ሰዓት በኋላ በትላልቅ ሰረገላና መሸጎሪያዎች ተቆልፈው ድሆች ከግቢዋ ተገፍትረው እየወጡ ለሌሊት ብርድና ቁር ተጋልጠው እንዲኖሩ ይፈረድባቸዋል። እናም እነዚህ ድኾችም በሺዎች በሚቆጠር ብር በሚከራዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ የንግድ ማዕከላት በረንዳ ላይ ወድቀው ኑሮአቸውን በምሬት ይገፋሉ።
ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ የዘመነ ሐዲስ ምኩራብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላዘነው መጽናናትን ለተጨነቀው መረጋጋትን የምትሰጥ፤ ደስታን የምታስታጥቅ ኀዘንን የምታርቅ እንደሆነች ሲዘምርላት እንዲህ አለ ‹‹በከመ ይቤ እግዚእነ በነቢይ ጊሥዋ ለቤተ ክርስቲያን እስመ ኵሉ ዘጌሠ ኀቤሃ ተአሥዮ ፍሥሐ። ጌታችን በነቢዩ አድሮ እንደተናገረው ቤተ ክርስቲያንን ገሥግሡባት፤ ማልዱባት ወደ እርሷ የገሠገሠውን ደስታ ትሰጠዋለችና›› በማለት ዘወትር ማልደው ወደ እርሷ የሚሄዱ ምእመናን ተጽናንተው ኀይል አግኝተው ተደስተው እንደሚመለሱ ተናግሯል። (ደብረ ዘይት ዘሐሙስ)
ሊቀ ጉባኤ ጌታሁን ደምፀ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
Photo
+ ተራ የማይደርሰው ተጠማቂ +
"ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ፦ ልትድን ትወዳለህን? አለው ሰውዬውም፦ ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል፡ ብሎ መለሰለት" ዮሐ.5:5-7
ይህንን ጥያቄና መልስ ሳይ በሽተኛውን ማናገር ያምረኝና እንዲህ በል ይለኛል :-
አንተ በሽተኛ ግድ የለህም የተጠየቅከውን መልስ:: እመነኝ ጠያቂህ ተራ ጠያቂ አይደለም::
የሚጠይቅህ ሲያደርቁህ እንደኖሩት አሰልቺ ጠያቂዎች አይደለም:: ጥያቄውም የሌሎችን ሰዎች ዓይነት ጥያቄ አይደለም:: ከፊትህ የቆመው የመጠመቂያውን ውኃ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሞላውን ውኃ የፈጠረ ነው::
"ወደ መጠመቂያው የሚያኖረኝ ሰው የለኝም" አልክን? የተጠየቅከውን መልስ እንጂ!
ወደ መጠመቂያው መግባት ትወድዳለህን? ብሎ ማን ጠየቀህ? ተው እንጂ! የጠየቀህ ማን እንደሆነ ባታውቅ እንኩዋን ጥያቄውን በደንብ ስማ::
ሰው የለኝም አትበለው : ስለመጠመቂያው ወረፋ አትንገረው : ስንት ሰው ቀድሞህ እንደዳነ አትቁጠርለት:: የጠየቀህ ግልፅ ጥያቄ ነው::
ልትድን ትወዳለህን?
እግዚአብሔር ፊት ስለ ችግርህ ክብደት ለምን ታወራለህ? ምን እንደሌለህማ እሱም ያውቃል:: አዎን እድን ዘንድ በለው:: ችግርህን ትተህ የምትፈልገውን ንገረው:: የችግርህ መወሳሰብና ሥር መስደድ ለእሱ የሚከብድ አይደለምና መዳን እንደምትሻ ብቻ በእምነት ንገረው የሚል ተግሣፅ በበሽተኛው በኩል ወደ እኛ ደረሰ::
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
መጻጉዕ (በሽተኛው) ቤተ ሳይዳ ከመጣ 38 ዓመት ሆነው:: ዳዊትና ሰሎሞን 40 40 ዓመት ነግሠው እንኳን ብዙ የምሬት ቅኔ ተቀኝተዋል:: ይህ ሰው አልጋ ላይ ሆኖ አርባ ዓመት ሊሞላው ሲል ምንኛ ተንገሽግሾ ይሆን?
ልብ በሉ ጌታችን በቤተልሔም ሲወለድ ይህ በሽተኛ በአልጋው ላይ ነበረ:: እረኞች ከብዙ መላእክት ጋር ሲዘምሩ እሱ የአንድን መልአክ መውረድና ውኃውን ማናወጥ እየጠበቀ ስድስተኛ ዓመቱን ደፍኖ ነበር:: ጌታችን የሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ደርሶ ወደ መጠመቂያው ሥፍራ ሲመጣም ይህ ሰው አልጋው ላይ ነው:: መጠመቂያዋን 38 ዓመት በተስፋ ሲጠብቅ ቆይቶ ሳይጠመቅባት ቀረ::
ጌታ ሆይ የማይደርሰኝን ወረፋ ከመጠበቅ አድነኝ:: እንድፈወስበት ባልፈቀድክበት ሥፍራ ዕድሜዬን እንዳልጨርስ ጠብቀኝ::
ወደ ሐዲስ ኪዳንዋ ቤተ ሳይዳ ወደ ቤተክርስቲያን ከመጣሁ ብዙ ዘመን አስቆጠርኩኝ:: ግን እስካሁንም ድረስ ከኃጢአት አልጋ ላይ አልወረድሁም:: መነሣት እፈልጋለሁ ግን አቃተኝ:: ልቤ እንጂ እግሬ ጸንቶ መቆም አልቻለም::
ፈረቃ የሌለብህን የሕይወት ውኃ አንተን ሊጠጡ ሲመጡ በዓይኔ እየተቀበልኩ ብዙዎች ጠጥተውህ ሲድኑ በዓይኔ እየሸኘሁ አልጋዬ ላይ ቀረሁ::
እኔ እንደተኛሁ ስንቱ ቀድሞኝ እንደዳነ ባየህልኝ:: ከእኔ በኁዋላ መጥተውስ ከእኔ በፊት ስንቶች ዳኑ?
ስንቱ ከኃጢአት አልጋ በንስሓ ተነሥቶ ያንተን ሥጋና ደም ተቀብሎ ተፈወሰ?
የቤተ ሳይዳው ሐኪም ሆይ ወደ አንጋፋው በሽተኛህ ወደ ጽኑዕ ሕመምተኛህ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ይሆን? ያን ሕመምተኛ "ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበረ" አውቀህ ያናገርከው ሆይ እኔን የምታናግረኝ መቼ ይሆን? እኔስ ብዙ ዘመን እንደሆነኝ አታውቅምን? ሰው የለኝም : ልብ የለኝም : ኃይል የለኝም : አቅም የለኝም ብዬ ብሶቴን የምነግርህ መቼ ይሆን?
"ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ" ዮሐ.5:8-9
አንተ ተነሥ ብለኸው የማይነሣ ማን ነው? እንኳንስ ከአልጋ ከመቃብርም ተነሥ ያልከው ይነሣ የለምን?
ግዴለህም እኔንም ተነሥ በለኝ:: ተነሥ ኃይልን ልበስ ያልከኝ እንደሆነ እንኳንስ "ሸክሜም ቀሊል ነው" ያልከው አንተ ያዘዝከኝ የራሴን ሸክም ቀርቶ የወንድሜን ሸክምም ተሸክሜ የአንተን ሕግ እፈጽማለሁ:: (ገላ. 6:2)
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
"ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ... ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ፡ አለው" ይላል::
በሽተኛው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ እንደሔደ ሳነብ አንድ ነገር ልቤን አስጨነቀው:: ይህ ሰውዬ 38 ዓመት ሙሉ የኖረው በቤተ ሳይዳ ነው:: ክርስቶስ ድንገት ፈውሶት ሒድ ሲለው እሺ ብሎ ከዚያ መጠመቂያ ሥፍራ ከወጣ በኁዋላ ወዴት ሔደ?
የሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛው ሆይ እውነት ወዴት ሔድህ? ከመጠመቂያው መውጣትህን ሰምተን አድንቀናል:: ከዚያስ ወዴት ሔድክ? ዙሪያ ገባው አልተለወጠብህም? መንገድስ አልጠፋብህም?
ወደ ዘመዶች ቤት ሔድክ እንዳልል "ሰው የለኝም" ስትል ሰምቼሃለሁ::
አልጋህንስ የት አደረስካት? መቼም ሰባብረህ እንደማትጥላት የታወቀ ነው:: አልጋ ለታመመ ብቻ ሳይሆን ለጤነኛም ያስፈልጋልና አራት እግር እያላት ጥላህ ያልሔደችውን ዘመድህን መቼም በክብር ማስቀመጥህ አይቀርም::
ለማንኛውም እዚያው ምዕራፍ ላይ ኢየሱስ ይህንን በሽተኛ ዳግም በመቅደስ አገኘው ይላል:: ዮሐ. 5:14 ጌታ ከመጠመቂያ ቦታ አድኖ ያስነሣውን ሰው በመቅደስ ቆሞ አገኘው:: ይህ በሽተኛ እግሩ ሲጸናለት የሔደው ወደ ፈጣሪ ደጅ መሆኑ ያስመሰግነዋል::
ጌታ በመጠጥ ቤት ቢያገኘው ኖሮ ያሳዝን ነበር:: እግርህን ያጸናሁልህ ለዚህ ነው ወይ ብሎ ባዘነበት ነበር:: አሁን ግን ያዳነው ጌታ በመቅደስ አግኝቶት "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" አለው::
ይህንን የምታነብ ወንድሜ ሆይ ክርስቶስ አንተንስ አላዳነህም? "ኸረ እኔ ሽባ ሆኜ አላውቅም:: ማንም እኔን ከአልጋ አላስነሣኝም ትለኝ እንደሆን እመነኝ ክርስቶስ እንደ አንተ ያዳነውስ የለም:: እርሱ እኔና አንተን ተነሡ ብሎ ያስነሣን ከ38 ሳይሆን ከዘላለም የሲኦልና የኃጢአት አልጋ ነው::
እኛን የፈወሰን አልጋችንን አሸክሞ ሳይሆን እሱ ራሱ እኛን ከነአልጋችን ተሸክሞን ነው:: ካላመንከኝ ነቢዩ ኢሳይያስን ጠይቀው "እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ" ሲልህ ትሰማዋለህ:: ኢሳ. 53:12 የእኛን በደል ተሸክሞ ጀርባው ምን ያህል እንደ ቆሰለ ባየህ:: ይህንስ ጀርባዬን ታያለህ የተባለውን ሙሴን ብትጠይቀው ሳይሻል አይቀርም::
ያዳነህ አምላክ አንተንስ የት ነው የሚያገኝህ? እንደዚህ ሰውዬ መቅደስ ያገኝህ ይሆን?
የትም ቢያገኝህ ግን ቃሉ አንድ ነው "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" ከሠላሳ ስምንት ዓመት የአልጋ ቁራኝነት የሚብስ ምን ሊመጣ ነው? ካልክስ እሱን ከማየት ይሠውረኝ ብትል ይሻልሃል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 10 2014 ዓ.ም.
ባሕር ዳር ኢትዮጵያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
"ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ፦ ልትድን ትወዳለህን? አለው ሰውዬውም፦ ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል፡ ብሎ መለሰለት" ዮሐ.5:5-7
ይህንን ጥያቄና መልስ ሳይ በሽተኛውን ማናገር ያምረኝና እንዲህ በል ይለኛል :-
አንተ በሽተኛ ግድ የለህም የተጠየቅከውን መልስ:: እመነኝ ጠያቂህ ተራ ጠያቂ አይደለም::
የሚጠይቅህ ሲያደርቁህ እንደኖሩት አሰልቺ ጠያቂዎች አይደለም:: ጥያቄውም የሌሎችን ሰዎች ዓይነት ጥያቄ አይደለም:: ከፊትህ የቆመው የመጠመቂያውን ውኃ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሞላውን ውኃ የፈጠረ ነው::
"ወደ መጠመቂያው የሚያኖረኝ ሰው የለኝም" አልክን? የተጠየቅከውን መልስ እንጂ!
ወደ መጠመቂያው መግባት ትወድዳለህን? ብሎ ማን ጠየቀህ? ተው እንጂ! የጠየቀህ ማን እንደሆነ ባታውቅ እንኩዋን ጥያቄውን በደንብ ስማ::
ሰው የለኝም አትበለው : ስለመጠመቂያው ወረፋ አትንገረው : ስንት ሰው ቀድሞህ እንደዳነ አትቁጠርለት:: የጠየቀህ ግልፅ ጥያቄ ነው::
ልትድን ትወዳለህን?
እግዚአብሔር ፊት ስለ ችግርህ ክብደት ለምን ታወራለህ? ምን እንደሌለህማ እሱም ያውቃል:: አዎን እድን ዘንድ በለው:: ችግርህን ትተህ የምትፈልገውን ንገረው:: የችግርህ መወሳሰብና ሥር መስደድ ለእሱ የሚከብድ አይደለምና መዳን እንደምትሻ ብቻ በእምነት ንገረው የሚል ተግሣፅ በበሽተኛው በኩል ወደ እኛ ደረሰ::
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
መጻጉዕ (በሽተኛው) ቤተ ሳይዳ ከመጣ 38 ዓመት ሆነው:: ዳዊትና ሰሎሞን 40 40 ዓመት ነግሠው እንኳን ብዙ የምሬት ቅኔ ተቀኝተዋል:: ይህ ሰው አልጋ ላይ ሆኖ አርባ ዓመት ሊሞላው ሲል ምንኛ ተንገሽግሾ ይሆን?
ልብ በሉ ጌታችን በቤተልሔም ሲወለድ ይህ በሽተኛ በአልጋው ላይ ነበረ:: እረኞች ከብዙ መላእክት ጋር ሲዘምሩ እሱ የአንድን መልአክ መውረድና ውኃውን ማናወጥ እየጠበቀ ስድስተኛ ዓመቱን ደፍኖ ነበር:: ጌታችን የሠላሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ ላይ ደርሶ ወደ መጠመቂያው ሥፍራ ሲመጣም ይህ ሰው አልጋው ላይ ነው:: መጠመቂያዋን 38 ዓመት በተስፋ ሲጠብቅ ቆይቶ ሳይጠመቅባት ቀረ::
ጌታ ሆይ የማይደርሰኝን ወረፋ ከመጠበቅ አድነኝ:: እንድፈወስበት ባልፈቀድክበት ሥፍራ ዕድሜዬን እንዳልጨርስ ጠብቀኝ::
ወደ ሐዲስ ኪዳንዋ ቤተ ሳይዳ ወደ ቤተክርስቲያን ከመጣሁ ብዙ ዘመን አስቆጠርኩኝ:: ግን እስካሁንም ድረስ ከኃጢአት አልጋ ላይ አልወረድሁም:: መነሣት እፈልጋለሁ ግን አቃተኝ:: ልቤ እንጂ እግሬ ጸንቶ መቆም አልቻለም::
ፈረቃ የሌለብህን የሕይወት ውኃ አንተን ሊጠጡ ሲመጡ በዓይኔ እየተቀበልኩ ብዙዎች ጠጥተውህ ሲድኑ በዓይኔ እየሸኘሁ አልጋዬ ላይ ቀረሁ::
እኔ እንደተኛሁ ስንቱ ቀድሞኝ እንደዳነ ባየህልኝ:: ከእኔ በኁዋላ መጥተውስ ከእኔ በፊት ስንቶች ዳኑ?
ስንቱ ከኃጢአት አልጋ በንስሓ ተነሥቶ ያንተን ሥጋና ደም ተቀብሎ ተፈወሰ?
የቤተ ሳይዳው ሐኪም ሆይ ወደ አንጋፋው በሽተኛህ ወደ ጽኑዕ ሕመምተኛህ ወደ እኔ የምትመጣው መቼ ይሆን? ያን ሕመምተኛ "ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደነበረ" አውቀህ ያናገርከው ሆይ እኔን የምታናግረኝ መቼ ይሆን? እኔስ ብዙ ዘመን እንደሆነኝ አታውቅምን? ሰው የለኝም : ልብ የለኝም : ኃይል የለኝም : አቅም የለኝም ብዬ ብሶቴን የምነግርህ መቼ ይሆን?
"ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ" ዮሐ.5:8-9
አንተ ተነሥ ብለኸው የማይነሣ ማን ነው? እንኳንስ ከአልጋ ከመቃብርም ተነሥ ያልከው ይነሣ የለምን?
ግዴለህም እኔንም ተነሥ በለኝ:: ተነሥ ኃይልን ልበስ ያልከኝ እንደሆነ እንኳንስ "ሸክሜም ቀሊል ነው" ያልከው አንተ ያዘዝከኝ የራሴን ሸክም ቀርቶ የወንድሜን ሸክምም ተሸክሜ የአንተን ሕግ እፈጽማለሁ:: (ገላ. 6:2)
🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌🛌
"ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ... ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ፡ አለው" ይላል::
በሽተኛው ድኖ አልጋውን ተሸክሞ እንደሔደ ሳነብ አንድ ነገር ልቤን አስጨነቀው:: ይህ ሰውዬ 38 ዓመት ሙሉ የኖረው በቤተ ሳይዳ ነው:: ክርስቶስ ድንገት ፈውሶት ሒድ ሲለው እሺ ብሎ ከዚያ መጠመቂያ ሥፍራ ከወጣ በኁዋላ ወዴት ሔደ?
የሠላሳ ስምንት ዓመት ሕመምተኛው ሆይ እውነት ወዴት ሔድህ? ከመጠመቂያው መውጣትህን ሰምተን አድንቀናል:: ከዚያስ ወዴት ሔድክ? ዙሪያ ገባው አልተለወጠብህም? መንገድስ አልጠፋብህም?
ወደ ዘመዶች ቤት ሔድክ እንዳልል "ሰው የለኝም" ስትል ሰምቼሃለሁ::
አልጋህንስ የት አደረስካት? መቼም ሰባብረህ እንደማትጥላት የታወቀ ነው:: አልጋ ለታመመ ብቻ ሳይሆን ለጤነኛም ያስፈልጋልና አራት እግር እያላት ጥላህ ያልሔደችውን ዘመድህን መቼም በክብር ማስቀመጥህ አይቀርም::
ለማንኛውም እዚያው ምዕራፍ ላይ ኢየሱስ ይህንን በሽተኛ ዳግም በመቅደስ አገኘው ይላል:: ዮሐ. 5:14 ጌታ ከመጠመቂያ ቦታ አድኖ ያስነሣውን ሰው በመቅደስ ቆሞ አገኘው:: ይህ በሽተኛ እግሩ ሲጸናለት የሔደው ወደ ፈጣሪ ደጅ መሆኑ ያስመሰግነዋል::
ጌታ በመጠጥ ቤት ቢያገኘው ኖሮ ያሳዝን ነበር:: እግርህን ያጸናሁልህ ለዚህ ነው ወይ ብሎ ባዘነበት ነበር:: አሁን ግን ያዳነው ጌታ በመቅደስ አግኝቶት "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" አለው::
ይህንን የምታነብ ወንድሜ ሆይ ክርስቶስ አንተንስ አላዳነህም? "ኸረ እኔ ሽባ ሆኜ አላውቅም:: ማንም እኔን ከአልጋ አላስነሣኝም ትለኝ እንደሆን እመነኝ ክርስቶስ እንደ አንተ ያዳነውስ የለም:: እርሱ እኔና አንተን ተነሡ ብሎ ያስነሣን ከ38 ሳይሆን ከዘላለም የሲኦልና የኃጢአት አልጋ ነው::
እኛን የፈወሰን አልጋችንን አሸክሞ ሳይሆን እሱ ራሱ እኛን ከነአልጋችን ተሸክሞን ነው:: ካላመንከኝ ነቢዩ ኢሳይያስን ጠይቀው "እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ" ሲልህ ትሰማዋለህ:: ኢሳ. 53:12 የእኛን በደል ተሸክሞ ጀርባው ምን ያህል እንደ ቆሰለ ባየህ:: ይህንስ ጀርባዬን ታያለህ የተባለውን ሙሴን ብትጠይቀው ሳይሻል አይቀርም::
ያዳነህ አምላክ አንተንስ የት ነው የሚያገኝህ? እንደዚህ ሰውዬ መቅደስ ያገኝህ ይሆን?
የትም ቢያገኝህ ግን ቃሉ አንድ ነው "እነሆ ድነሀል ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ" ከሠላሳ ስምንት ዓመት የአልጋ ቁራኝነት የሚብስ ምን ሊመጣ ነው? ካልክስ እሱን ከማየት ይሠውረኝ ብትል ይሻልሃል::
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 10 2014 ዓ.ም.
ባሕር ዳር ኢትዮጵያ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
+ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ +
"የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው::
በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ?
ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል"
"የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው::
በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ?
ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
"አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም"
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል"
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
"ዘሐይወ ኢያእመረ ዘአሕየዎ …የዳነው ያዳነውን አላወቀውም" (ዮሐ. ፭፥፲፫)
የነፍሳችንን ማሠሪያ እንዲፈታና ዓለሙን ከተያዘት የኃጢአት በሽታ እንዲያድን ለቤዛነት፤ እንዲሁም የመልካምና የበጎ ምግባራት ሁሉ አብነት ሆኖ በሥራና በቃል እንዲያስተምር ለአርአያነትም ወዳለንባት ምድር በሥጋ ቅድስት ድንግል ማርያም የወረደው እግዚአ ለሰንበት ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአራተኛው የአቢይ ጾም ሳምንት በመፃጉዕ እሑድ በ"ቤተሳይዳ" የፈጸመውን ተአምራት ቤተክርስቲያናችን ታሰባለች። በዕለቱም በዮሐንስ ወንጌል አምስተኛው ምዕራፍ የተቀመጠው ታሪክ በልዩ ልዩ ኅብረ ምሥጢር ተሰናስሎ በሊቃውንቱ ይነገራል።
መፃጉዕ ተብሎ የደረሰበት ድካመ ሥጋ ጽናት ከሕመም ከበሽታ ከደዌም በላይ መገለጫው የሆነ ሰው ለ፴፰ ዓመት በአልጋው ላይ ሆኖ ምሕረትን ሲጠባበቅባት የኖረባት ስፍራን "ቤተ ሳይዳ" ይላታል።
በቅዱስ መጽሐፍ የሥፍራዎችን ስያሜ ስንመረምር በይሁዳና በገሊላ ለሚገኙ ሁለት የተለያዩ ግዛቶች በተመሳሳይ አገባብ "ቤተ ሳይዳ" የሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸው እናገኛለን:: በሁለቱ አውራጃዎች (ይሁዳና በገሊላ) ሥር "ቤተ ሳይዳ" በሚል የተጠቀሱት ሥፍራዎች በትርጉም ፊደላቱ ያለአገባብ መሰደር ከወለዱት የሞክሼነት ስህተት (Metathetical Corruption) የተገኘ ክፍተት እንጂ ቦታዎቹስ በጥንታዊቷ የእስራኤል ግዛት ከመገኘታቸው ውጪ ምንም የሚያገናኛቸው መልክአ ምድራዊ ኩነት የለም "ጲላጦስ ጰንጤናዊ መልአከ ይሁዳ ወሄሮድስ ንጉሠ ገሊላ" (ሉቃ· ፫፥፩) እንዲል የግዛቶቹ አገረ ገዢዎችም እንዲሁ ለየቅል ነበሩ:: አገባቡን አካቶ ለመረዳት እንዲያመች የሁለቱንም መካናት ከተማና መንደር ለይቶ ማወቁ ተገቢ ነው::
🍁 በይሁዳ ግዛት ከሚገኙና እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ገቢረ ተአምራቱን ከፈጸመባቸው ሥፍራዎች ፦ ቤተሳይዳ(Bethesda) ፣ ቢታኒያ ፣ ቤተልሔም ፣ ቤተፋጌ ፣ ኢያሪኮ ፣ ጌቴሰማኒ ፣ ሊቶስጥሮስ(ገበታ) ፣ ኤማሁስ፣ ቀራንዮ(ጎልጎታ) ፣ ኢየሩሳሌም እና የደብረዘይት ተራራ የሚጠቀሱ ሲሆን፤
🍁 በገሊላ አውራጃ ደግሞ ፦ ቤተሳይዳ(Bethsaida) ፣ ሄኖን ፣ ቃና፣ ቅፍርናሆም፣ ኮራዚ፣ ጌንሳሬጥ፣ ደብረታቦር፣ ናይን እና የገሊላ ባህር ተገልጸው እናገኛልን::
እነዚህኑ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳና "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ አካባቢያዊ መገኛ ለይተው የሚያመለክቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም በይሁዳ ኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ ያለችዋን "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት" (ዮሐ ·፭፥፪) ብሎ የገለጠበትንና በገሊላ ስለምትገኘዋ ደግሞ "ወሖሩ እሙንቱሂ ኀበ ፊልጶስ ዘቤተ ሳይዳ ዘገሊላ" (ዮሐ ፲፪፥፳፩) የሚለው ማየት ይቻላል::
በሌላ መልኩ አንዳንዶች ደግሞ በሁለቱም ሥፍራዎች ክርስቶስ አምላካችን ለፈውስ ሥራ ያገኛቸውን ሰዎች አይተው ተመሳሳይ ቦታ ሲመስላቸው ይታያል ይህም "መጻጉዕ" እና "ዕውር" የነበሩትን ማዳኑ ነው:: ይኸውም "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት …በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት። (ዮሐ ·፭፥፪) የተባለውና "ወበጽሑ ቤተ ሳይዳ ወአምጽኡ ኀቤሁ ዕውረ ወአስተብቁዕዎ ይግስሶ … ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ። ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት።" (ማር· ፰፥፳፪) የሚለው ነው::
🔑 "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ (Bethsaida) በትርጉም "የማጥመጃ ቤት" የሚል ፍቺ ያለው በተለይ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ አሳ አጥማጆቹ ወንድማማቾችና ቅዱስ ፊልጶስ የነበሩባት መንደር ናት " ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።" (ዮሐ·፩፡፵፭) እንዲል።
፨ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ (Bethesda or Bethchasday) የመጠመቂያ ሥፍራ ስትሆን በግሪኩ ቤተ ዛታ ( Βηθζαθά) ወይም ቅልንብትራ (κολυμβήθρα) እንዲሁም በእብራይስጡና በአረማይኩ "ቤተ`ስዳ" (Beth hesda ( בית חסד /חסדא )) በማለት "ከማጥመጃ ቤት" ለይቶ "ቤተ ሣሕል / የምሕረት ቤት" የሚል ትርጉም ያለው መጠመቂያና መላለሻ መንገድ መሆንዋን ያመለክተናል። የግእዙ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ለዚህ በመጨነቅ የቦታውን ስያሜ ከእብራይስጡ "የአንድዮሽ ትርጉም" ስያሜ (ቤተ ሳይዳ) ጋር በግሪኩ ያለውንም መጠሪያ ጭምር አካቶ ቅልንብትራ ( κολυμβήθρα / kolumbethra) ሲል እናገኘዋለን::
ቤተ ሳይዳ ዘይሁዳ ባለ አምስት በር መመላለሻ አምስት ዓይነት ድውያን ፈውስን ከማየ ጥምቀቱ ሲጠባበቁ የሚኖሩባት በአምስተኛው የዮሐንስ ወንጌል ተጽፎ ያለ የጌታችን ማዳን የተገለጠባት ሥፍራ ናት። "እስመ ኦሪት መንፈቀ ፍጻሜ ወኅዳጠ መክፈልት" እንዲላት መልአከ እግዚአብሔር ለቀድሶተ ማይ ወርዶ ውኃውን ሲያናውጥ ቀድሞ የገባ የሚነጻባት በዕለቱ ከአንድ በቀር ለሌላው ፈውስ የማይደገምባት ቦታ ናት ይህችው "ቤተ ሳይዳ" ።
ታዲያ ከእነዚህ መካከል ነበር ይህን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል የድኅነት ተስፈኛ ሆኖ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ "መፈውስ ወማሕየዊ" ጌታችን ቀርቦ አዎን እንዲለው እያወቀ ብወዳችሁ አላዋቂ የሆነ የእናንተን ሥጋ ተዋሕጄ መጣሁላችሁ ሲለን ("አኮ ኢያእሚሮ ኅቡአተ አላ ከመ የሀብ መካነ ለጥንተ ትስብዕቱ ዘኢየአምር ኅቡአተ" እንዲል) ያንን በሽተኛ "ትፈቅድኑ ትሕየው? … ባድንህ ፈቃድህ ነውን?" አለው። የሚገርመው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራውያን መልእክቱ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፪ ላይ "የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።" ብሎ የመሰከረለት ጌታችን ፈውስን በመጠባበቅ ከመዳን ውጪ ሌላ ዓላማ ያልነበረውን ይህን ሰው ዓይቶ ፈቃዱን እያወቀ ግን ፍቀድልኝና ላድንህ አለው። " ሰው በከንቱ ወራቱ ቍጥርና እንደ ጥላ በሚያሳልፈው ዘመኑ በሕይወቱ ሳለ ለሰው የሚሻለውን የሚያውቅ ማነው? "(መክ ፮፥፲፪) እንዲል የሚያስፈልገንን ሳንነግረው የሚያውቅ የሚሰጠንም ከእርሱ ከፈጣሪው ውጪ በእውነት ማን አለ? መፃጉዕ ግን ኋላ የሚክድ ነውና "በሰንበት ላይ ያመጸ ፣ ራሱን ከአብ የሚያስተካክል ፣ ቤተመቅደሱን አፍርሱት ያለ መች አድነኝ ብየው ሳልፈቅድለት ያዳነኝና አልጋ ያሸከመኝ ነውኮ" ብሎ በዕለተ ዓርብ የሚከስበትን ሲያሳጣውና ለኋላ ጥፋቱ የገዛ ኅሊናው እንዲቀጣው ፈቃዱን ጠየቀው። "አልብየ ሰብእ" ሰው የሌለኝ ሆኖ እንጂ ያንንማ ማን ይጠላል በሚል ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ድኅነትን ፈቅዶ ገለጠ። እስከ ሁከተ ማይ ሳያቆየው "ተንሥእ ንሣእ ዓራተከ ወሑር … ተንስና አልጋህን አንስተህ ሂድ" አለው ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ ዘመን የተሸከመች ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ።
የነፍሳችንን ማሠሪያ እንዲፈታና ዓለሙን ከተያዘት የኃጢአት በሽታ እንዲያድን ለቤዛነት፤ እንዲሁም የመልካምና የበጎ ምግባራት ሁሉ አብነት ሆኖ በሥራና በቃል እንዲያስተምር ለአርአያነትም ወዳለንባት ምድር በሥጋ ቅድስት ድንግል ማርያም የወረደው እግዚአ ለሰንበት ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአራተኛው የአቢይ ጾም ሳምንት በመፃጉዕ እሑድ በ"ቤተሳይዳ" የፈጸመውን ተአምራት ቤተክርስቲያናችን ታሰባለች። በዕለቱም በዮሐንስ ወንጌል አምስተኛው ምዕራፍ የተቀመጠው ታሪክ በልዩ ልዩ ኅብረ ምሥጢር ተሰናስሎ በሊቃውንቱ ይነገራል።
መፃጉዕ ተብሎ የደረሰበት ድካመ ሥጋ ጽናት ከሕመም ከበሽታ ከደዌም በላይ መገለጫው የሆነ ሰው ለ፴፰ ዓመት በአልጋው ላይ ሆኖ ምሕረትን ሲጠባበቅባት የኖረባት ስፍራን "ቤተ ሳይዳ" ይላታል።
በቅዱስ መጽሐፍ የሥፍራዎችን ስያሜ ስንመረምር በይሁዳና በገሊላ ለሚገኙ ሁለት የተለያዩ ግዛቶች በተመሳሳይ አገባብ "ቤተ ሳይዳ" የሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸው እናገኛለን:: በሁለቱ አውራጃዎች (ይሁዳና በገሊላ) ሥር "ቤተ ሳይዳ" በሚል የተጠቀሱት ሥፍራዎች በትርጉም ፊደላቱ ያለአገባብ መሰደር ከወለዱት የሞክሼነት ስህተት (Metathetical Corruption) የተገኘ ክፍተት እንጂ ቦታዎቹስ በጥንታዊቷ የእስራኤል ግዛት ከመገኘታቸው ውጪ ምንም የሚያገናኛቸው መልክአ ምድራዊ ኩነት የለም "ጲላጦስ ጰንጤናዊ መልአከ ይሁዳ ወሄሮድስ ንጉሠ ገሊላ" (ሉቃ· ፫፥፩) እንዲል የግዛቶቹ አገረ ገዢዎችም እንዲሁ ለየቅል ነበሩ:: አገባቡን አካቶ ለመረዳት እንዲያመች የሁለቱንም መካናት ከተማና መንደር ለይቶ ማወቁ ተገቢ ነው::
🍁 በይሁዳ ግዛት ከሚገኙና እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ገቢረ ተአምራቱን ከፈጸመባቸው ሥፍራዎች ፦ ቤተሳይዳ(Bethesda) ፣ ቢታኒያ ፣ ቤተልሔም ፣ ቤተፋጌ ፣ ኢያሪኮ ፣ ጌቴሰማኒ ፣ ሊቶስጥሮስ(ገበታ) ፣ ኤማሁስ፣ ቀራንዮ(ጎልጎታ) ፣ ኢየሩሳሌም እና የደብረዘይት ተራራ የሚጠቀሱ ሲሆን፤
🍁 በገሊላ አውራጃ ደግሞ ፦ ቤተሳይዳ(Bethsaida) ፣ ሄኖን ፣ ቃና፣ ቅፍርናሆም፣ ኮራዚ፣ ጌንሳሬጥ፣ ደብረታቦር፣ ናይን እና የገሊላ ባህር ተገልጸው እናገኛልን::
እነዚህኑ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳና "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ አካባቢያዊ መገኛ ለይተው የሚያመለክቱ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህም በይሁዳ ኢየሩሳሌም በበጎች በር አጠገብ ያለችዋን "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት" (ዮሐ ·፭፥፪) ብሎ የገለጠበትንና በገሊላ ስለምትገኘዋ ደግሞ "ወሖሩ እሙንቱሂ ኀበ ፊልጶስ ዘቤተ ሳይዳ ዘገሊላ" (ዮሐ ፲፪፥፳፩) የሚለው ማየት ይቻላል::
በሌላ መልኩ አንዳንዶች ደግሞ በሁለቱም ሥፍራዎች ክርስቶስ አምላካችን ለፈውስ ሥራ ያገኛቸውን ሰዎች አይተው ተመሳሳይ ቦታ ሲመስላቸው ይታያል ይህም "መጻጉዕ" እና "ዕውር" የነበሩትን ማዳኑ ነው:: ይኸውም "ወቦ ውስተ ኢየሩሳሌም ምጥማቃት ዘጵሩጳጥቄ ቅልንብትራ (ዘውእቱ ቀላየ አባግዕ ብሂል) ወይቤልዋ ስማ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወባቲ ኃምስቱ ሕዋራት …በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት። (ዮሐ ·፭፥፪) የተባለውና "ወበጽሑ ቤተ ሳይዳ ወአምጽኡ ኀቤሁ ዕውረ ወአስተብቁዕዎ ይግስሶ … ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ። ዕውርም አመጡለት፥ እንዲዳስሰውም ለመኑት።" (ማር· ፰፥፳፪) የሚለው ነው::
🔑 "ቤተ ሳይዳ" ዘገሊላ (Bethsaida) በትርጉም "የማጥመጃ ቤት" የሚል ፍቺ ያለው በተለይ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ አሳ አጥማጆቹ ወንድማማቾችና ቅዱስ ፊልጶስ የነበሩባት መንደር ናት " ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ።" (ዮሐ·፩፡፵፭) እንዲል።
፨ "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ (Bethesda or Bethchasday) የመጠመቂያ ሥፍራ ስትሆን በግሪኩ ቤተ ዛታ ( Βηθζαθά) ወይም ቅልንብትራ (κολυμβήθρα) እንዲሁም በእብራይስጡና በአረማይኩ "ቤተ`ስዳ" (Beth hesda ( בית חסד /חסדא )) በማለት "ከማጥመጃ ቤት" ለይቶ "ቤተ ሣሕል / የምሕረት ቤት" የሚል ትርጉም ያለው መጠመቂያና መላለሻ መንገድ መሆንዋን ያመለክተናል። የግእዙ መጽሐፍ ቅዱሳችንም ለዚህ በመጨነቅ የቦታውን ስያሜ ከእብራይስጡ "የአንድዮሽ ትርጉም" ስያሜ (ቤተ ሳይዳ) ጋር በግሪኩ ያለውንም መጠሪያ ጭምር አካቶ ቅልንብትራ ( κολυμβήθρα / kolumbethra) ሲል እናገኘዋለን::
ቤተ ሳይዳ ዘይሁዳ ባለ አምስት በር መመላለሻ አምስት ዓይነት ድውያን ፈውስን ከማየ ጥምቀቱ ሲጠባበቁ የሚኖሩባት በአምስተኛው የዮሐንስ ወንጌል ተጽፎ ያለ የጌታችን ማዳን የተገለጠባት ሥፍራ ናት። "እስመ ኦሪት መንፈቀ ፍጻሜ ወኅዳጠ መክፈልት" እንዲላት መልአከ እግዚአብሔር ለቀድሶተ ማይ ወርዶ ውኃውን ሲያናውጥ ቀድሞ የገባ የሚነጻባት በዕለቱ ከአንድ በቀር ለሌላው ፈውስ የማይደገምባት ቦታ ናት ይህችው "ቤተ ሳይዳ" ።
ታዲያ ከእነዚህ መካከል ነበር ይህን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያህል የድኅነት ተስፈኛ ሆኖ የኖረ መጻጉዕን በአልጋው ተኝቶ ሳለ ደዌው እንደጠናበት ፈውስ እንደዘገየበት አይቶ "መፈውስ ወማሕየዊ" ጌታችን ቀርቦ አዎን እንዲለው እያወቀ ብወዳችሁ አላዋቂ የሆነ የእናንተን ሥጋ ተዋሕጄ መጣሁላችሁ ሲለን ("አኮ ኢያእሚሮ ኅቡአተ አላ ከመ የሀብ መካነ ለጥንተ ትስብዕቱ ዘኢየአምር ኅቡአተ" እንዲል) ያንን በሽተኛ "ትፈቅድኑ ትሕየው? … ባድንህ ፈቃድህ ነውን?" አለው። የሚገርመው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራውያን መልእክቱ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፪ ላይ "የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤ እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።" ብሎ የመሰከረለት ጌታችን ፈውስን በመጠባበቅ ከመዳን ውጪ ሌላ ዓላማ ያልነበረውን ይህን ሰው ዓይቶ ፈቃዱን እያወቀ ግን ፍቀድልኝና ላድንህ አለው። " ሰው በከንቱ ወራቱ ቍጥርና እንደ ጥላ በሚያሳልፈው ዘመኑ በሕይወቱ ሳለ ለሰው የሚሻለውን የሚያውቅ ማነው? "(መክ ፮፥፲፪) እንዲል የሚያስፈልገንን ሳንነግረው የሚያውቅ የሚሰጠንም ከእርሱ ከፈጣሪው ውጪ በእውነት ማን አለ? መፃጉዕ ግን ኋላ የሚክድ ነውና "በሰንበት ላይ ያመጸ ፣ ራሱን ከአብ የሚያስተካክል ፣ ቤተመቅደሱን አፍርሱት ያለ መች አድነኝ ብየው ሳልፈቅድለት ያዳነኝና አልጋ ያሸከመኝ ነውኮ" ብሎ በዕለተ ዓርብ የሚከስበትን ሲያሳጣውና ለኋላ ጥፋቱ የገዛ ኅሊናው እንዲቀጣው ፈቃዱን ጠየቀው። "አልብየ ሰብእ" ሰው የሌለኝ ሆኖ እንጂ ያንንማ ማን ይጠላል በሚል ጉጉቱን ከወዳጅ አልባነቱ ጋር ድኅነትን ፈቅዶ ገለጠ። እስከ ሁከተ ማይ ሳያቆየው "ተንሥእ ንሣእ ዓራተከ ወሑር … ተንስና አልጋህን አንስተህ ሂድ" አለው ወዲያው አፈፍ ብሎ በፍጥነት ያን ሁሉ ዘመን የተሸከመች ጠንካራ አልጋ ተሸክሟት ሄደ።
Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴 (ተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος))
ይህች "ቤተ ሳይዳ" ዘይሁዳ ምሣሌቷ ብዙ ኅብር ያለው ነው። ለአብነትም ያህል ምሳሌ፦
፩· ውኃው የቤተ አይሁድ ምሳሌ አምስት መመላለሻ የሕግጋተ ኦሪት የአምስቱ መፃሕፍተ ሙሴ በነዚያ ታጥረው ለመኖራቸው። ቀድሞ የገባባት አንዱ እንዲድን እነሱም አንድነት ቤተ እስራኤል ተሰኝተው ለመኖራቸው ምሳሌ ነው።
፪· በሌላ አገባብ
፠ በዚያ ውኀውን ለማወክ የወረደው መልአክ = ቀሳውስት(ካህናት) "ለቀድሶተ ማየ ጥምቀት" የመውረዳቸው ምሳሌ ነው።
፠ የመጠመቂያ ውኀው = የማየ ጥምቀት ምሳሌ ሲሆን
፠ በቤተ ሳይዳ ያለው አምስቱ እርከን(መመላለሻ) =የአምስቱ አእማደ ምስጢር በዚያ ሊያምኑ ያሉ ተስፈኞችና ያመኑባትም ልጅነትን ያገኙባታልና።
፠ አምስቱ ዓይነት ድውያንም የአምስቱ ጾታ ምዕመናን ከነ ፈተናቸው የተመሳጠረበት ምሳሌ ነው (አእሩግ=በፍቅረ ነዋቅይ....ወራዙት=በዝሙት.... አንስት=በትውዝፍት በምንዝር ጌጥ....ካህናት=በትእቢት አእምሯችን ረቂቅ መዓረጋችን ምጡቅ እያሉ... መነኮሳት=በስስት ምግብን በሹት ጊዜ ባያገኙት ይልቁንም አጽንኦ በአት እየፈቱ በአንሰሐስሖ ዘበከንቱ ይፈትናቸዋል) ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
፫· ለአዲስ ኪዳን ድኅነተ ነፍስ ምስጢራዊ ምሳሌ አገባብም አለው፤
፠ ቤተሳይዳ የበጎች በር በመባልዋ እና በኦሪቱ በጎች ወደ ቤተ መቅደስ ወጥተው ለመስዋዕት ከመቅረባቸው አስቀድሞ የሚታጠቡበት ውኀ ያለበት በመሆኑ ለበአዲስ ኪዳንም የመንፈስ ቅዱስ ልጅነት የሚገኝባትን ወደ አማናዊ መስዋዕት ቅዱስ ቁርባን የምታደርስ የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ
፠ አምስቱን መመላለሻየምታደርስ ደግሞ ወደ ፍፃሜ ሕግ ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ እግዚአብሔር አልፎም ፍጽምት ወደሆነች ወደ ሕግጋተ ወንጌልም የምታደርስ የአምስቱ ብኄረ ኦሪት መፃሕፍተ ሙሴ ምሳሌ ያደርጋቸዋል።
፠ ለሁከተ ማይ የወረደው መልአክ የሰማዩ አቃቤ ሥራይ የክርስቶስ ምሳሌ ነው
፠ ከአንድ ብቻ በቀር ሕሙም በአንድ ዕለት አለመዳኑ በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥላ ሥር አምነው ያሉ ምዕመናንና ምዕመናት ብቻ ድኅነተ ነፍስ እናዳላቸው ያሳያል።
፠ የውኀው መናወጽ የሰቃልያነ ክርስቶስ "ሁከተ አይሁድ" ምሳሌ ጥንቱን "ስቅሎ ስቅሎ " የሚለው ያ ቁጣ የዕለተ ዓርብ መድኃኒት መገኛ ነውና።
እስኪ ደግሞ በማጠቃለያው ወደ መፃጉዕ ታሪክ እንመለስና ጥቂት ፍሬ ነገር ለሕይወታችን እንስማ።
ቀድሞ በ
ዛሬም
ከደዌው :ከማጣቱ :ከችግሩ: ከሥጋ ኑሮ ጉድለቱ ዳግመኛ ለመታረቅ እንደ መፃጉዕ አምላኩን ያልረሳ ማነው?
ተአምራቱን አይቶ ቃሉን ሰምቶ አምላኩን ያስታወሰስ ማነው " ቃሉን ያይና ይሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ምክር የቆመ ማን ነውና? ቃሉንስ ያደመጠ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር. ፳፫፥፲፰) ማንም። ጌታችን ባስተማረው ማሕየዊ ቃሉ ላይ እንኳ ሳይቀር ያመጹትን አይሁድ እስኪ ተመልከቱ " ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።" ሉቃ ፲፮፥፲፬ እኛንም ቢሆን ከአዳም እስራት ነፃ ያደረገንን አምላክ ውለታ ዘንግተን በቃሉ የምናፌዝ ሁላችንን ወደ ልባችን እንድንመለስ ነቢዩ እንዲህ ሲል ይመክረናል "እስራት እንዳይጸናባችሁ አታፊዙ " ( ኢሳ· ፳፰፥፳፪ ) ይመክረናል።
በፍፃሜ ሕይወቱ በአውደ ምኩናን የሀሰት ክስ የቀረበበትን ይህን የእውነትና የሕይወት ጌታ ቀድሞ ወደ መጠመቂያው እንኳ ለመቅረብ አቅም ያልነበረው ዛሬ ግን አልጋ ለመሸከም በበቃውና ያለ ተረፈ ደዌ በጸናው ኃይሉ የጌታውን ጉንጮች በጥፊ የመምታት ጉልበትና ድፍረት አገኘ። "ዘተሰብሐ ውስተ ገጸ ሙሴ በትስብእቱ ተጸፍአ ገጾ ወተቀስፈ ዘባኖ በእንቲአነ ከመ ይፈጽም ስምዓ ነቢይ ዘይብል መጠውኩ ዘባንየ ለመቅሰፍት ወመላትሕየ ለጽፍአት… በገጹ ነፀብራቅ የሙሴን ፊት ያበራ እርሱ በነቢዩ ጀርባዬን ለግርፋት ጉንጮቼንም ለጽፍአት ሰጠሁ ተብሎ የተነገረውን ለመፈጸም ለእኛ ሲል ፊቱን በጥፊ ተመታ ጀርባውንም ተገረፈ "እንዲል (ሰይፈ ሥላሴ)
አምላከ ምሕረት እግዚአ ለሰንበት ቀድሞ "ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ … ከዚህ የጠናው "ስለ ደዌ ሥጋ ፈንታ ደዌ ነፍስ" እንዳያገኝህ ሁለተኛ እንዳትበድል" (ቁ ፲፬) ያለውን ዘንግቶ ደዌ ዘኃጢአትን ጠርቶ ተወዳጃት፤ በዕለተ ዓርብ የጌታውን ጉንጮች የጸፉች እጁም ደርቃ
"መፃጉዕ ይትዐረቅ ምስለ ብእሲት ደዌሁ
ሠላሳ አዝማነ እስመ ነበረት ምስሌሁ"
☞ መፃጉዕ ከሚስቱ ከደዌው ይታረቅ
ሠላሳ ዓመት አብራው ኖራለች ሳትርቅ
አብረው አያሌ ዓመታት የኖሩ ባልና ሚስት ሲፋቱ ተነፋፍቀው መለያየቱ እምቢኝ እንደሚላቸውና እንደሚታረቁ ሁሉ ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ተብሎ ሳለ ጌታውን ጸፍቶ መፃጉዕም ዳግመኛ ወደ ፴፰ ዓመት "የአልጋ ወዳጁ" ደዌ መመለሱን የቅኔው ምስጢር ያስተምረናል።
እንግዲህ እኛም በኃጢአት ከሚመጣ ደዌ ተጠብቀን በአባታዊ ምሕረቱ የሚጠብቀንን ቸሩ አምላካችንን እያመሰገንን በቤቱ እንድንጸና መፃጉዕን "ተነሳ" እንዳለው እኛንም ከወደቅንበት ዓራተ ዝንጋኤ፣ ዓራተ ኃጢአት በንስሃ እንዲያነሳንና ዳግም ከመበደልም እንዲጠብቀን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን። አሜን
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ☞ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ·ም· በጣልያን ሮም የተፃፈ
፩· ውኃው የቤተ አይሁድ ምሳሌ አምስት መመላለሻ የሕግጋተ ኦሪት የአምስቱ መፃሕፍተ ሙሴ በነዚያ ታጥረው ለመኖራቸው። ቀድሞ የገባባት አንዱ እንዲድን እነሱም አንድነት ቤተ እስራኤል ተሰኝተው ለመኖራቸው ምሳሌ ነው።
፪· በሌላ አገባብ
፠ በዚያ ውኀውን ለማወክ የወረደው መልአክ = ቀሳውስት(ካህናት) "ለቀድሶተ ማየ ጥምቀት" የመውረዳቸው ምሳሌ ነው።
፠ የመጠመቂያ ውኀው = የማየ ጥምቀት ምሳሌ ሲሆን
፠ በቤተ ሳይዳ ያለው አምስቱ እርከን(መመላለሻ) =የአምስቱ አእማደ ምስጢር በዚያ ሊያምኑ ያሉ ተስፈኞችና ያመኑባትም ልጅነትን ያገኙባታልና።
፠ አምስቱ ዓይነት ድውያንም የአምስቱ ጾታ ምዕመናን ከነ ፈተናቸው የተመሳጠረበት ምሳሌ ነው (አእሩግ=በፍቅረ ነዋቅይ....ወራዙት=በዝሙት.... አንስት=በትውዝፍት በምንዝር ጌጥ....ካህናት=በትእቢት አእምሯችን ረቂቅ መዓረጋችን ምጡቅ እያሉ... መነኮሳት=በስስት ምግብን በሹት ጊዜ ባያገኙት ይልቁንም አጽንኦ በአት እየፈቱ በአንሰሐስሖ ዘበከንቱ ይፈትናቸዋል) ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
፫· ለአዲስ ኪዳን ድኅነተ ነፍስ ምስጢራዊ ምሳሌ አገባብም አለው፤
፠ ቤተሳይዳ የበጎች በር በመባልዋ እና በኦሪቱ በጎች ወደ ቤተ መቅደስ ወጥተው ለመስዋዕት ከመቅረባቸው አስቀድሞ የሚታጠቡበት ውኀ ያለበት በመሆኑ ለበአዲስ ኪዳንም የመንፈስ ቅዱስ ልጅነት የሚገኝባትን ወደ አማናዊ መስዋዕት ቅዱስ ቁርባን የምታደርስ የጥምቀት ምሳሌ ሆኖ
፠ አምስቱን መመላለሻየምታደርስ ደግሞ ወደ ፍፃሜ ሕግ ፍቅረ ቢጽና ፍቅረ እግዚአብሔር አልፎም ፍጽምት ወደሆነች ወደ ሕግጋተ ወንጌልም የምታደርስ የአምስቱ ብኄረ ኦሪት መፃሕፍተ ሙሴ ምሳሌ ያደርጋቸዋል።
፠ ለሁከተ ማይ የወረደው መልአክ የሰማዩ አቃቤ ሥራይ የክርስቶስ ምሳሌ ነው
፠ ከአንድ ብቻ በቀር ሕሙም በአንድ ዕለት አለመዳኑ በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥላ ሥር አምነው ያሉ ምዕመናንና ምዕመናት ብቻ ድኅነተ ነፍስ እናዳላቸው ያሳያል።
፠ የውኀው መናወጽ የሰቃልያነ ክርስቶስ "ሁከተ አይሁድ" ምሳሌ ጥንቱን "ስቅሎ ስቅሎ " የሚለው ያ ቁጣ የዕለተ ዓርብ መድኃኒት መገኛ ነውና።
እስኪ ደግሞ በማጠቃለያው ወደ መፃጉዕ ታሪክ እንመለስና ጥቂት ፍሬ ነገር ለሕይወታችን እንስማ።
ቀድሞ በ
ቤተ ሳይዳ
እያለ የነበረበትን ያንን ሁሉ ጭንቅ ኋላ በሊቶስጥሮስ የፍርድ ገበታ ቆሞ በረሳ ጊዜ " ታዲያ ቢያድነኝ በከንቱ መች ሆነና የገዛ አልጋዬን ትቼለት የመጣሁ ለመዳኔ ዋጋ የከፈልኩበት አይደለምን?" እንኳ እንዳይል ያለ ተረፈ ደዌ አንስቶት ያለህን ይዘህ ሂድ እኔ ከአንተ አንዳች አልሻም ባሰኘ ቃል ሸኝቶታል። ግን ታዲያ ይህ ምስኪን መፃጉዕ "ሰው የለኝም" ብሎ የደረሰለትን ሰው ረሳ ማን እንደሆነ እንኳ አላወቀም። ወንጌላዊውም "ዘሐይወ ኢያእመረ ዘአሕየዎ …የዳነውኋላ የተፈወሰው ያዳነውን አላወቀውም" ( ዮሐ.፭፥፲፫) ይለዋል። ያዳነው ማን እንደሆነ ሲጠየቅ ለምሥጋና ያይደለ ለክስ ነበር ስሙን የፈለገው። በኑሮው የማንነቱ መገለጫ "ከሚጣፍጠውም ምግቤ ሆዱን ሞላ፥ እኔንም ጣለኝ።" ተብሎ ለናቡከደነፆር በነቢዩ እንደተነገረ ያለ ነው (ኤር.፶፩፥፴፬ ) በአገራችንም ካለው ብሂለ አበው "ታሞ የተነሳ ፈጣሪውን ረሳ" የሚለው እንደነዚህ ያሉትን በሚገባ ለመግለጽ የተነገረ ነው። ሊቀ ነቢያት ሙሴን በዘዳግም ፲ ቁጥር ፳፩ ላይ እንዲህ ይላል "ዓይኖችህ ያዩትን እነዚህን ታላላቆች የሚያስፈሩትንም ነገሮች ያደረገልህ እርሱ ክብርህ ነው፥ እርሱም አምላክህ ነው።" ነገር ግን ይህን ሁሉ ያደረገውን አምላክ ብዙዎች የነበሩ "ህዝበ እስራኤል" ረስተው አሳዝነውት በምድረበዳ በከንቱ ወድቀው ቀሩ ..... ዛሬም
ከደዌው :ከማጣቱ :ከችግሩ: ከሥጋ ኑሮ ጉድለቱ ዳግመኛ ለመታረቅ እንደ መፃጉዕ አምላኩን ያልረሳ ማነው?
ተአምራቱን አይቶ ቃሉን ሰምቶ አምላኩን ያስታወሰስ ማነው " ቃሉን ያይና ይሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ምክር የቆመ ማን ነውና? ቃሉንስ ያደመጠ የሰማስ ማን ነው?" (ኤር. ፳፫፥፲፰) ማንም። ጌታችን ባስተማረው ማሕየዊ ቃሉ ላይ እንኳ ሳይቀር ያመጹትን አይሁድ እስኪ ተመልከቱ " ገንዘብንም የሚወዱ ፈሪሳውያን ይህን ሁሉ ሰምተው ያፌዙበት ነበር።" ሉቃ ፲፮፥፲፬ እኛንም ቢሆን ከአዳም እስራት ነፃ ያደረገንን አምላክ ውለታ ዘንግተን በቃሉ የምናፌዝ ሁላችንን ወደ ልባችን እንድንመለስ ነቢዩ እንዲህ ሲል ይመክረናል "እስራት እንዳይጸናባችሁ አታፊዙ " ( ኢሳ· ፳፰፥፳፪ ) ይመክረናል።
በፍፃሜ ሕይወቱ በአውደ ምኩናን የሀሰት ክስ የቀረበበትን ይህን የእውነትና የሕይወት ጌታ ቀድሞ ወደ መጠመቂያው እንኳ ለመቅረብ አቅም ያልነበረው ዛሬ ግን አልጋ ለመሸከም በበቃውና ያለ ተረፈ ደዌ በጸናው ኃይሉ የጌታውን ጉንጮች በጥፊ የመምታት ጉልበትና ድፍረት አገኘ። "ዘተሰብሐ ውስተ ገጸ ሙሴ በትስብእቱ ተጸፍአ ገጾ ወተቀስፈ ዘባኖ በእንቲአነ ከመ ይፈጽም ስምዓ ነቢይ ዘይብል መጠውኩ ዘባንየ ለመቅሰፍት ወመላትሕየ ለጽፍአት… በገጹ ነፀብራቅ የሙሴን ፊት ያበራ እርሱ በነቢዩ ጀርባዬን ለግርፋት ጉንጮቼንም ለጽፍአት ሰጠሁ ተብሎ የተነገረውን ለመፈጸም ለእኛ ሲል ፊቱን በጥፊ ተመታ ጀርባውንም ተገረፈ "እንዲል (ሰይፈ ሥላሴ)
አምላከ ምሕረት እግዚአ ለሰንበት ቀድሞ "ዑቅ ኢትአብስ ዳግመ እንከ ከመ ዘየአኪ ኢይርከብከ … ከዚህ የጠናው "ስለ ደዌ ሥጋ ፈንታ ደዌ ነፍስ" እንዳያገኝህ ሁለተኛ እንዳትበድል" (ቁ ፲፬) ያለውን ዘንግቶ ደዌ ዘኃጢአትን ጠርቶ ተወዳጃት፤ በዕለተ ዓርብ የጌታውን ጉንጮች የጸፉች እጁም ደርቃ
ሰላ
ቀርታለች አንዱ ሊቅ ይህን አልሰማ ባይ መፃጉዕ እና ይቅር ባይ አምላኩን እያደነቀ በጉባዔ ቃናው ይህን ተናገረ "መፃጉዕ ይትዐረቅ ምስለ ብእሲት ደዌሁ
ሠላሳ አዝማነ እስመ ነበረት ምስሌሁ"
☞ መፃጉዕ ከሚስቱ ከደዌው ይታረቅ
ሠላሳ ዓመት አብራው ኖራለች ሳትርቅ
አብረው አያሌ ዓመታት የኖሩ ባልና ሚስት ሲፋቱ ተነፋፍቀው መለያየቱ እምቢኝ እንደሚላቸውና እንደሚታረቁ ሁሉ ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ተብሎ ሳለ ጌታውን ጸፍቶ መፃጉዕም ዳግመኛ ወደ ፴፰ ዓመት "የአልጋ ወዳጁ" ደዌ መመለሱን የቅኔው ምስጢር ያስተምረናል።
እንግዲህ እኛም በኃጢአት ከሚመጣ ደዌ ተጠብቀን በአባታዊ ምሕረቱ የሚጠብቀንን ቸሩ አምላካችንን እያመሰገንን በቤቱ እንድንጸና መፃጉዕን "ተነሳ" እንዳለው እኛንም ከወደቅንበት ዓራተ ዝንጋኤ፣ ዓራተ ኃጢአት በንስሃ እንዲያነሳንና ዳግም ከመበደልም እንዲጠብቀን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን። አሜን
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ☞ በቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ·ም· በጣልያን ሮም የተፃፈ
╔✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╗
❀…#ሥራሽ_ያውጣሽ! …❀
╚✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╝
† ከዚህም በኋላ ተርቢኖስን ሚስትህ የነበርኩ ዕሌኒ እኔ ነኝ አንተ ግን በብረት ሣጥን አድርገህ ወደ ባሕር ስትጥለኝ ዐመፅን ክፋትን የምትሠሪ አንቺ ክፉ ሴት #ሥራሽ_ያውጣሽ [ይከተልሽ]
☞ ሥራሽ መልካም ከሆነ ያድንሽ ክፉ ከሆነ ግን ያጥፋሽ ብለህ ተናገርከኝ ይህንንም እያልክ ከጥልቅ ባሕር ውስጥ ጣልከኝ። ለእኔ ግን ንጹሕ የሆነ ሥራዬ በጎ እውነተኛ ሃይማኖቴ ተከትሎኝ ክብር ይግባውና ፈጣሪዬና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ብዛት አሁን ከአለሁበት ደረጃ ላይ አደረሰኝ አለችው።
† ወእምድኅረዝ ትቤሎ ለተርቢኖስ አነ ይእቲ ዕሌኒ ብእሲትከ አንተሰ እንዘ ትገድፈኒ ውስተ ባሕር ገቢረከ በሣፁን ነበብከኒ እንዘ ትብል ኦ ብእሲት እኪት ገባሪተ ዐመፃ ወእከይ #ዝ_ግብርኪ_ለይትሉኪ ወለእመ ኮነ ሠናየ ያሕዩኪ ወለእመሰ ኮነ እኩየ ያህጕልኪ።
☞ ወዘንተ ቃለ እንዘ ትብል ወገርከኒ ውስተ ባሕር ዕሙቅ። ወሊተሰ ዘተለወኒ ግብርየ ንጹሕ ወምግባርየ ሠናይ ወሃይማኖትየ እሙን አብጽሐኒ ኀበ ዝንቱ ኀበ ሀሎኩ ቦቱ በብዝኀ ኂሩቱ አምላኪየ ወእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት።
[ድርሳነ መስቀል]
"ወይመጽእ ዳግመ በስብሐት ወበዐቢይ ክብር ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ ወይፈድዮ ለኵሉ በከመ ምግባሩ ⇨ ዳግመኛም ፡ በሕያዋንና ፡ በሙታን ፡ ይፈርድ ፡ ዘንድ ፡ በታላቅ ፡ ክብርና ፡ ጌትነት ፡ ይመጣልና ፣ ፡ ለሁሉም ፡ እንደእየ ፡ ሥራው ፡ ይከፍለዋል"
[መጽሐፈ ዲድስቅልያ 30:33]
https://youtu.be/a5Aula5LEqA
❀…#ሥራሽ_ያውጣሽ! …❀
╚✞═┉✽✥⛪✥✽┉═✞╝
† ከዚህም በኋላ ተርቢኖስን ሚስትህ የነበርኩ ዕሌኒ እኔ ነኝ አንተ ግን በብረት ሣጥን አድርገህ ወደ ባሕር ስትጥለኝ ዐመፅን ክፋትን የምትሠሪ አንቺ ክፉ ሴት #ሥራሽ_ያውጣሽ [ይከተልሽ]
☞ ሥራሽ መልካም ከሆነ ያድንሽ ክፉ ከሆነ ግን ያጥፋሽ ብለህ ተናገርከኝ ይህንንም እያልክ ከጥልቅ ባሕር ውስጥ ጣልከኝ። ለእኔ ግን ንጹሕ የሆነ ሥራዬ በጎ እውነተኛ ሃይማኖቴ ተከትሎኝ ክብር ይግባውና ፈጣሪዬና ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቸርነቱ ብዛት አሁን ከአለሁበት ደረጃ ላይ አደረሰኝ አለችው።
† ወእምድኅረዝ ትቤሎ ለተርቢኖስ አነ ይእቲ ዕሌኒ ብእሲትከ አንተሰ እንዘ ትገድፈኒ ውስተ ባሕር ገቢረከ በሣፁን ነበብከኒ እንዘ ትብል ኦ ብእሲት እኪት ገባሪተ ዐመፃ ወእከይ #ዝ_ግብርኪ_ለይትሉኪ ወለእመ ኮነ ሠናየ ያሕዩኪ ወለእመሰ ኮነ እኩየ ያህጕልኪ።
☞ ወዘንተ ቃለ እንዘ ትብል ወገርከኒ ውስተ ባሕር ዕሙቅ። ወሊተሰ ዘተለወኒ ግብርየ ንጹሕ ወምግባርየ ሠናይ ወሃይማኖትየ እሙን አብጽሐኒ ኀበ ዝንቱ ኀበ ሀሎኩ ቦቱ በብዝኀ ኂሩቱ አምላኪየ ወእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት።
[ድርሳነ መስቀል]
"ወይመጽእ ዳግመ በስብሐት ወበዐቢይ ክብር ይኰንን ሕያዋነ ወሙታነ ወይፈድዮ ለኵሉ በከመ ምግባሩ ⇨ ዳግመኛም ፡ በሕያዋንና ፡ በሙታን ፡ ይፈርድ ፡ ዘንድ ፡ በታላቅ ፡ ክብርና ፡ ጌትነት ፡ ይመጣልና ፣ ፡ ለሁሉም ፡ እንደእየ ፡ ሥራው ፡ ይከፍለዋል"
[መጽሐፈ ዲድስቅልያ 30:33]
https://youtu.be/a5Aula5LEqA
YouTube
ስራሽ ያውጣሽ + ዲ/ን ዶ/ር ቴዎድሮስ በለጠ
✝️✝️✝️የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን✝️✝️✝️የማኅበራችንን የዩቱዩብ ቻናል +++SUBSCRIBE +++ እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት እና ለሌሎች እንዲደርሳቸው ሼር በማድረግም ይተባበሩን::
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_...
እግዚአብሔር…
ከዚህ በፊት የተለቀቁ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን ለማግኘት ከስር የሚገኘውን ሊንክ ይጠቀሙ
https://www.youtube.com/channel/UCol_...
እግዚአብሔር…
የደብረ ዘይትን ሳምንት ለውይይት!
ሳምንቱን ለተከታታይ ፬ቱ ቀናት እንደ ሥሉስ ቅዱስ መልካም ፈቃድ በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ ጥያቄዎች በተከታዮቹ ፬ት ሰንበትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመምህራንና ከመጻሕፍት ያገኘኋቸውን ጥቂት ሐሳቦች በዝርዝር ሐተታ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።
እስከዛው ግን የሚሰማችሁን ሐሳብና ጥያቄ ብታሰፍሩ ለመማማር እድሉን እንደሚያሰፋልን እምነቴ ነው።
፩] ታቦተ ሰንበት
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይዝ» … መባሉ ስለምን ነው?
⚀ ሰኞ መጋቢት ፲፩ በሠርክ የሚመለስ
፪] ሰንበትና ስግደት
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
⚁ ማክሰኞ መጋቢት ፲፪ በሠርክ የሚመለስ
፫] ዕለተ ሰንበት
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ የሚመለስ
፬] ተግባረ ሰንበት
☞ የሰንበት ዕረፍት ፣ የሰንበት መብራት ፣ የሰንበት ውኃ … የሚሉት ትውፊቶች በሐዲስ ኪዳን እንዴት ይታያሉ?
⚃ ሐሙስ መጋቢት ፲፬
ምናልባት ተጨማሪ ማየት የሚገባን የሰንበት ጉዳይ ካለ ⚄ ዓርብ መጋቢት ፲፭ ከማጠቃለያ ጋር የምንመለስ ይሆናል!
ኦርቶዶክስ መልስ ናት! ኦርቶዶክሳዊ መልስ አለው።
ሳምንቱን ለተከታታይ ፬ቱ ቀናት እንደ ሥሉስ ቅዱስ መልካም ፈቃድ በተደጋጋሚ ከሚደርሱኝ ጥያቄዎች በተከታዮቹ ፬ት ሰንበትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመምህራንና ከመጻሕፍት ያገኘኋቸውን ጥቂት ሐሳቦች በዝርዝር ሐተታ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።
እስከዛው ግን የሚሰማችሁን ሐሳብና ጥያቄ ብታሰፍሩ ለመማማር እድሉን እንደሚያሰፋልን እምነቴ ነው።
፩] ታቦተ ሰንበት
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይዝ» … መባሉ ስለምን ነው?
⚀ ሰኞ መጋቢት ፲፩ በሠርክ የሚመለስ
፪] ሰንበትና ስግደት
☞ «በዕለተ ሰንበት የተከለከለው የጸጋ ስግደት እንጂ የአምልኮ ስግደት አይደለም» በሚል የሚሠጠው የጊዜው ‘ትምህርት’ እንዴት ይታያል ?
⚁ ማክሰኞ መጋቢት ፲፪ በሠርክ የሚመለስ
፫] ዕለተ ሰንበት
☞ በክብረ ሰንበት ዙርያ አንዳንዶች ሰንበት ዕለተ ‘ቀዳሚት’ ብቻ ናት ሲሉ ሌሎች ለክርስቲያኖች ‘እሑድ’ ሰንበት እንጂ ቀዳሚት ሰንበት ምናቸው ናት? የሚሉ አሉ፤ እኛስ ሁለቱንም በጋራ ለማክበርና ለመዘከር ማስረጃችን ከወዴት የተገኘ ነው?
⚂ ረቡዕ መጋቢት ፲፫ በሠርክ የሚመለስ
፬] ተግባረ ሰንበት
☞ የሰንበት ዕረፍት ፣ የሰንበት መብራት ፣ የሰንበት ውኃ … የሚሉት ትውፊቶች በሐዲስ ኪዳን እንዴት ይታያሉ?
⚃ ሐሙስ መጋቢት ፲፬
ምናልባት ተጨማሪ ማየት የሚገባን የሰንበት ጉዳይ ካለ ⚄ ዓርብ መጋቢት ፲፭ ከማጠቃለያ ጋር የምንመለስ ይሆናል!
ኦርቶዶክስ መልስ ናት! ኦርቶዶክሳዊ መልስ አለው።
ክፍል ፩] ታቦተ ሰንበት
━━━━✦✿✦━━━━
በዓለ ደብረ ዘይት እኩለ ጾም ነው፤ የጌታችን ምጽኣቱ ዓለም በተፈጠረበት ዕለት በዕለተ ሰንበት መሆኑን ቅድስት ቤተክርስቲያን ታምናለች ታስተምራለችም! ቸሩ ጌታችን "በሰንበት ኢይኩን ጉያክሙ ⇨ ስደታችሁ በሰንበት አይሁን" ብሎ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰብስቦ በዕለተ ሰንበት አሕማላት (የለመለሙ ዕፀዋት) ካሉበት ቦታ ከ"ዐጸደ ሐምል" ተራራ ዐጸደ ዘይትም ወደበዛበት ሥፍራ አስጠግቶ ነገረ ምጽአቱን ያስተማረበት መታሰቢያ በዓለ ደብረ ዘይት ይባላል። ቀኑ ለኹዳዴ እኩለ ፆም ነው!
ባለቅኔው
"ተዝካሮ ግበሩ ባሕታውያን ደቂቁ፤
ለምውት ጾም እስመ ደብረ ዘይት መንፈቁ።" እንዳለ።
ገባሬ ሕይወት እግዚአ ለሰንበት ራሱ ጌታችን የቀደሳትና ከፍ ከፍ ያደረጋት ዕለት በመሆኗ "ቀደሳ ወአልዓላ" እያልን በእርሷ ደስ ብሎን ስናከብራትና ስናገናት እንውላለን።
በእርግጥ ጊዜው የእግዚአብሔርን በዓላት ከምድር ላይ እንሻር የሚሉ የበዙበት ዘመን መሆኑን ስናይ የዳዊት ትንቢት እያነሳን የትንቢቱ መፈጸሚያ በሆኑት እንደነቃለን።
“አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር አሉ።” ☞ 【መዝ ፸፬፥፰ 】
በዓለም ታሪክ እ.አ.አ. ከ1536 በፊት «በካቶሊካዊት» ቤተ እምነት በዐመት ውስጥ 95 የሚሆኑ የ«ቤተክርስቲያኗ» በዓላትና 52 ሰንበታት ይከሩ እንደነበር፤ ነገር ግን ከ1536 አንስቶ በተሃድሷውያኑ ጫና በዓላቱን ወደ 27 አውርደዋቸዋል።
ኋላ ላይ የተነሱት ከካተሊካዊ ባህል ፕሮቴስታንቱን እናነፃለን የሚሉ ወገኖች (The Puritans) በዓላቶችን በሙሉ (ገናና ፋሲካን ሳይቀር) በመሻር ዝክረ ዕለታትን ከሁለት ወገን ይከፍላሉ፦
① ችግር ጉዳትና አደጋ ከላይ የወረደ ቁጣ ተብለው የሚዘከሩባቸው ቀናት «ዕለታተ ፆም» ( Days of Fasting) ሲባሉ
② ልዩ በረከት ከአምላክ የሚሰጡባቸው ቀናት ዕለታተ ባርኮ/የምስጋና ቀናት (Days of Thanksgiving) ብለዋቸዋል።
【James W. Baker የተጻፈው "Thanksgiving: The Biography of an American Holiday" 】
ዛሬም የእኛዋን ቤተክርስቲያን አውቀው ይሁን ሳያውቁ በዚህ ወጀብ የሚንጧትን አበልጻጊዎች አስታግሶ ፣ ከመፍቀሬ ሁከት ሰይጣን ሰውሮ ፣ በመፍቀርያነ ምሕረት መላእክቱ ከልሎ ፈተናውን ሁሉ ያሻግርልን።
ወደዛሬው የመጀመሪያ ቀን ጉዳያችን እንለፍ፤ ትናንት በተሠጠው ጥቆማ መሠረት [https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=6005958766119252&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz]
ታቦተ ሰንበትን የሚመለከቱ ጥቂት ሐሳቦች እናሳለን። መነሻ ጥያቄው እንዲህ የሚል ነው
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይት» … መባሉ ስለምን ነው?
ቀድመን የሚከተለውን ጥያቄ እናንሳ
▶ ጽላት/ታቦት ለማን ይቀረጻል (በማን ይሰየማል) ?
በአጭር መልስ በስማቸው ጽላት የሚቀረጽላቸው ፣ መቅደስ የሚታነጽላቸው ፣ ጠበል የሚፈልቅና የሚሰየምላቸው ፣ ድርሳን ገድል መልክእ የሚጻፍ የሚደረስላቸው ቅዱሳን ናቸው።
▶ ቅዱሳንስ የምንለው ማንን ነው?
የኔታ ሐረገወይን አገዘ (ሊቀ ጠበብት) ነገረ ቅዱሳንን ሲያስረዱ ቅድስና የባህሪ ገንዘቡ የሆነ አምላክነትና ፈጣሪነትን ከማንም ያልተቀበለ ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ይሁንና ግን ከባህሪ ቅድስና በታች ያሉ በሥጦታ ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ቅዱሳንም አሉ ፤ እነዚህም ቅዱሳን/ቅዱሳት ዘበጸጋ ይባላሉ።
ለዚህ የጸጋ ቅድስና ምክንያቶች (ምንጮች) ደግሞ በጥቅሉ ሦስት ናቸው።
★ በመጽናት ቅዱሳን የምንላቸው አሉ ፦ ቅዱሳን መላእክት
★ በመመረጥ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ እመቤታችን፣ ንዋያት [ታቦት፣ መስቀል፣ መካናት/መቅደስ፣ ሥዕላት ፣ ንዋያተ ቅድሳት … ] ፣ ዕለታት ፣ መጻሕፍት፣ በጸሎት የከበሩ ቅብዓት [ቅብዓ ሜሮን ፣ ቅብዕ ቅዱስ፣ ቅብዓ ቀንዲል… ]
★ በተጋድሎ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ በቅድስናው ማዕረግ ከፍ ያሉ መስተጋድላን ጻድቃን ጽኑዓን …
መጽሐፍ ‘ሰብእ ይቄድሶ ለመካን ፤ ወመካን ይቄድሶ ለሰብእ’ ይላል፤ ደግሞም ቅዱሳን የረገጡትን ቦታ ብቻ ሳይሆን ገቢረ ተዓምራት የፈጸሙባቸውን ዕለታት ጭምር ቅዱስ ያሰኛሉ።
" ኀበ ቅዱሳን ይከውን ቅዱሰ ⇨ ከቅዱሳን ጋር የሚውል ቅዱስ ይኾናልና" 【ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፻፳፮】
ሰንበት ቅድስት ዕለት ናት። በእርግጥ በገዳማትና በአንድአንድ "ሊቃውንት" አንደበት የሰንበት ታቦት የሚባል የለም "እግዚኣ ለሰንበት" እንጂ ሲሉ ይደመጣል።
በአገባቡ «እግዚኣ ሰንበትና እግዚአ ለሰንበት» የሚሉት መልእክታት ፍቺና ምሥጢራቸው ለየቅል ነው።
እስኪ ደግመን አንድ ጥያቄ እናንሳ
▶ ለዕለታትና ለንዋያት ታቦት ይቀረጻል ወይ?
መልሱ፦ አዎ።
አስረጅ ፦ በእመቤታችን ስም ጽላት/ታቦት እንደሚቀረጽ ሁላችን እናውቃለን ፤ የዕረፍቷን መታሰቢያ መነሻ አድርጎ በ፳፩ ክብረ በዓሉ የሚታሰብ ሲሆን ሌሎቹን ታቦተ ልደታ ፣ ታቦተ በዓታ … እያሉ ለቀናቱ መታሰቢያ በመስጠት ዕለታት ይዘከሩባቸዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በቅዱስ መስቀሉ ስም ጽላት/ታቦት ተቀርጾ መቅደስ ታንጾ ድርሳን ተደርሶ መልክእ ተጽፎ ሲከብር እናያለን።
ሰንበትም እንዲሁ ድርሳነ ሰንበት ፣ መልክአ ሰንበት ፣ ታቦተ ሰንበት ያለው እንዲያውም የበዓላት ኹሉ በኲር የሆነ በዓል ነው።
ከመልኩ ክፍል ይህን የሚያስረዳ መልእክት እንዲህ ሠፍሮ እናገኛለን
ሶበ አእመርኩ በስምኪ ከመ ታቦተ ይቄድሱ፡
ወድሶተኪ ወጠንኩ ለአእምሮትየ መጠነ ናእሱ፡
ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ንግሥተ መሳፍንት ስሱ፡
እለሰ ኪያኪ አርኰሱ፡
ፈቀዱ ሞተ ወኵነኔ ኃሠሡ፡፡
[በስምሽ እንደታቦት የሚቀደስ መሆኑን ባወቅኹ ጊዜ በትንሿ እውቀቴ ምስጋናሽን ጀመርኩ
ለስድስቱ መሳፍንት ንግሥት የምትሆኚ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ አንቺንስ ያረከሱ ሰዎች ሞትን ወደው መኮነንን የፈለጉ ናቸው።]
አንዳንዶች እግዚኣ ለሰንበት በሚል መጠሪያ የሰንበት ጌታ ስለሚል « ጌታ እንጂ ሰንበትን የሚወክል ታቦት የለም» ይላሉ። ይሁን እንጂ ሰንበት ራሱ ዕረፍት ነው ታቦተ ማርያም ተዝካረ ዕረፍቷ እንደሚታሰብበት ታቦታ ሰንበትም በሁለቱ ሰንበታት (ቅዳሜና እሑድ) ጌታችን ማረፉን የምንዘክርበት ጽላት/ታቦት ነው።
⇝ ቀዳሚት ሰንበት ፍጥረትን ፈጥሮ ያረፈበት በዓል ሲሆን ⇝ እሑድ (ሰንበተ ክርስቲያን) ደግሞ በሐዲስ ኪዳን ሁሉን ‘አዲስ’ ሊያደርግ ከልደቱ ጀምሮ ሲፈጽም የነበረውን የማዳን ሥራ በምድር ዕለተ ዓርብ ፈጽሞ እስከ እሑድ ነፍሳትን ከሲኦል አግዞ በትንሳኤው በሐዲስ ተፈጥሮ የመፍጠሩን ሥራ የፈጸመበት / ያረፈበት ዕለት ነው።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።” 【 ፪ኛ ቆሮ ፭፥፲፯
━━━━✦✿✦━━━━
በዓለ ደብረ ዘይት እኩለ ጾም ነው፤ የጌታችን ምጽኣቱ ዓለም በተፈጠረበት ዕለት በዕለተ ሰንበት መሆኑን ቅድስት ቤተክርስቲያን ታምናለች ታስተምራለችም! ቸሩ ጌታችን "በሰንበት ኢይኩን ጉያክሙ ⇨ ስደታችሁ በሰንበት አይሁን" ብሎ የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰብስቦ በዕለተ ሰንበት አሕማላት (የለመለሙ ዕፀዋት) ካሉበት ቦታ ከ"ዐጸደ ሐምል" ተራራ ዐጸደ ዘይትም ወደበዛበት ሥፍራ አስጠግቶ ነገረ ምጽአቱን ያስተማረበት መታሰቢያ በዓለ ደብረ ዘይት ይባላል። ቀኑ ለኹዳዴ እኩለ ፆም ነው!
ባለቅኔው
"ተዝካሮ ግበሩ ባሕታውያን ደቂቁ፤
ለምውት ጾም እስመ ደብረ ዘይት መንፈቁ።" እንዳለ።
ገባሬ ሕይወት እግዚአ ለሰንበት ራሱ ጌታችን የቀደሳትና ከፍ ከፍ ያደረጋት ዕለት በመሆኗ "ቀደሳ ወአልዓላ" እያልን በእርሷ ደስ ብሎን ስናከብራትና ስናገናት እንውላለን።
በእርግጥ ጊዜው የእግዚአብሔርን በዓላት ከምድር ላይ እንሻር የሚሉ የበዙበት ዘመን መሆኑን ስናይ የዳዊት ትንቢት እያነሳን የትንቢቱ መፈጸሚያ በሆኑት እንደነቃለን።
“አንድ ሆነው በልባቸው በየሕዝባቸው። ኑ፥ የእግዚአብሔርን በዓሎች ከምድር እንሻር አሉ።” ☞ 【መዝ ፸፬፥፰ 】
በዓለም ታሪክ እ.አ.አ. ከ1536 በፊት «በካቶሊካዊት» ቤተ እምነት በዐመት ውስጥ 95 የሚሆኑ የ«ቤተክርስቲያኗ» በዓላትና 52 ሰንበታት ይከሩ እንደነበር፤ ነገር ግን ከ1536 አንስቶ በተሃድሷውያኑ ጫና በዓላቱን ወደ 27 አውርደዋቸዋል።
ኋላ ላይ የተነሱት ከካተሊካዊ ባህል ፕሮቴስታንቱን እናነፃለን የሚሉ ወገኖች (The Puritans) በዓላቶችን በሙሉ (ገናና ፋሲካን ሳይቀር) በመሻር ዝክረ ዕለታትን ከሁለት ወገን ይከፍላሉ፦
① ችግር ጉዳትና አደጋ ከላይ የወረደ ቁጣ ተብለው የሚዘከሩባቸው ቀናት «ዕለታተ ፆም» ( Days of Fasting) ሲባሉ
② ልዩ በረከት ከአምላክ የሚሰጡባቸው ቀናት ዕለታተ ባርኮ/የምስጋና ቀናት (Days of Thanksgiving) ብለዋቸዋል።
【James W. Baker የተጻፈው "Thanksgiving: The Biography of an American Holiday" 】
ዛሬም የእኛዋን ቤተክርስቲያን አውቀው ይሁን ሳያውቁ በዚህ ወጀብ የሚንጧትን አበልጻጊዎች አስታግሶ ፣ ከመፍቀሬ ሁከት ሰይጣን ሰውሮ ፣ በመፍቀርያነ ምሕረት መላእክቱ ከልሎ ፈተናውን ሁሉ ያሻግርልን።
ወደዛሬው የመጀመሪያ ቀን ጉዳያችን እንለፍ፤ ትናንት በተሠጠው ጥቆማ መሠረት [https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=6005958766119252&id=100001155652281&mibextid=Nif5oz]
ታቦተ ሰንበትን የሚመለከቱ ጥቂት ሐሳቦች እናሳለን። መነሻ ጥያቄው እንዲህ የሚል ነው
☞ ለሰንበት ታቦት ይቀረጻል? በሳማ ሰንበት፣ በመናገሻ ጋራው መድኃኔዓለም ፣ በምሑር ኢየሱስ ፣ በአጤ ዋሻ… «ታቦተ እግዚኣ ለሰንበት» ፣ «ታቦተ ደብረ ዘይት» … መባሉ ስለምን ነው?
ቀድመን የሚከተለውን ጥያቄ እናንሳ
▶ ጽላት/ታቦት ለማን ይቀረጻል (በማን ይሰየማል) ?
በአጭር መልስ በስማቸው ጽላት የሚቀረጽላቸው ፣ መቅደስ የሚታነጽላቸው ፣ ጠበል የሚፈልቅና የሚሰየምላቸው ፣ ድርሳን ገድል መልክእ የሚጻፍ የሚደረስላቸው ቅዱሳን ናቸው።
▶ ቅዱሳንስ የምንለው ማንን ነው?
የኔታ ሐረገወይን አገዘ (ሊቀ ጠበብት) ነገረ ቅዱሳንን ሲያስረዱ ቅድስና የባህሪ ገንዘቡ የሆነ አምላክነትና ፈጣሪነትን ከማንም ያልተቀበለ ልዑል እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ይሁንና ግን ከባህሪ ቅድስና በታች ያሉ በሥጦታ ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ቅዱሳንም አሉ ፤ እነዚህም ቅዱሳን/ቅዱሳት ዘበጸጋ ይባላሉ።
ለዚህ የጸጋ ቅድስና ምክንያቶች (ምንጮች) ደግሞ በጥቅሉ ሦስት ናቸው።
★ በመጽናት ቅዱሳን የምንላቸው አሉ ፦ ቅዱሳን መላእክት
★ በመመረጥ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ እመቤታችን፣ ንዋያት [ታቦት፣ መስቀል፣ መካናት/መቅደስ፣ ሥዕላት ፣ ንዋያተ ቅድሳት … ] ፣ ዕለታት ፣ መጻሕፍት፣ በጸሎት የከበሩ ቅብዓት [ቅብዓ ሜሮን ፣ ቅብዕ ቅዱስ፣ ቅብዓ ቀንዲል… ]
★ በተጋድሎ ቅዱሳን የምንላቸው ፦ በቅድስናው ማዕረግ ከፍ ያሉ መስተጋድላን ጻድቃን ጽኑዓን …
መጽሐፍ ‘ሰብእ ይቄድሶ ለመካን ፤ ወመካን ይቄድሶ ለሰብእ’ ይላል፤ ደግሞም ቅዱሳን የረገጡትን ቦታ ብቻ ሳይሆን ገቢረ ተዓምራት የፈጸሙባቸውን ዕለታት ጭምር ቅዱስ ያሰኛሉ።
" ኀበ ቅዱሳን ይከውን ቅዱሰ ⇨ ከቅዱሳን ጋር የሚውል ቅዱስ ይኾናልና" 【ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ ፻፳፮】
ሰንበት ቅድስት ዕለት ናት። በእርግጥ በገዳማትና በአንድአንድ "ሊቃውንት" አንደበት የሰንበት ታቦት የሚባል የለም "እግዚኣ ለሰንበት" እንጂ ሲሉ ይደመጣል።
በአገባቡ «እግዚኣ ሰንበትና እግዚአ ለሰንበት» የሚሉት መልእክታት ፍቺና ምሥጢራቸው ለየቅል ነው።
እስኪ ደግመን አንድ ጥያቄ እናንሳ
▶ ለዕለታትና ለንዋያት ታቦት ይቀረጻል ወይ?
መልሱ፦ አዎ።
አስረጅ ፦ በእመቤታችን ስም ጽላት/ታቦት እንደሚቀረጽ ሁላችን እናውቃለን ፤ የዕረፍቷን መታሰቢያ መነሻ አድርጎ በ፳፩ ክብረ በዓሉ የሚታሰብ ሲሆን ሌሎቹን ታቦተ ልደታ ፣ ታቦተ በዓታ … እያሉ ለቀናቱ መታሰቢያ በመስጠት ዕለታት ይዘከሩባቸዋል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ በቅዱስ መስቀሉ ስም ጽላት/ታቦት ተቀርጾ መቅደስ ታንጾ ድርሳን ተደርሶ መልክእ ተጽፎ ሲከብር እናያለን።
ሰንበትም እንዲሁ ድርሳነ ሰንበት ፣ መልክአ ሰንበት ፣ ታቦተ ሰንበት ያለው እንዲያውም የበዓላት ኹሉ በኲር የሆነ በዓል ነው።
ከመልኩ ክፍል ይህን የሚያስረዳ መልእክት እንዲህ ሠፍሮ እናገኛለን
ሶበ አእመርኩ በስምኪ ከመ ታቦተ ይቄድሱ፡
ወድሶተኪ ወጠንኩ ለአእምሮትየ መጠነ ናእሱ፡
ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ንግሥተ መሳፍንት ስሱ፡
እለሰ ኪያኪ አርኰሱ፡
ፈቀዱ ሞተ ወኵነኔ ኃሠሡ፡፡
[በስምሽ እንደታቦት የሚቀደስ መሆኑን ባወቅኹ ጊዜ በትንሿ እውቀቴ ምስጋናሽን ጀመርኩ
ለስድስቱ መሳፍንት ንግሥት የምትሆኚ ቅድስቲቱ የክርስቲያኖች ሰንበት ሆይ አንቺንስ ያረከሱ ሰዎች ሞትን ወደው መኮነንን የፈለጉ ናቸው።]
አንዳንዶች እግዚኣ ለሰንበት በሚል መጠሪያ የሰንበት ጌታ ስለሚል « ጌታ እንጂ ሰንበትን የሚወክል ታቦት የለም» ይላሉ። ይሁን እንጂ ሰንበት ራሱ ዕረፍት ነው ታቦተ ማርያም ተዝካረ ዕረፍቷ እንደሚታሰብበት ታቦታ ሰንበትም በሁለቱ ሰንበታት (ቅዳሜና እሑድ) ጌታችን ማረፉን የምንዘክርበት ጽላት/ታቦት ነው።
⇝ ቀዳሚት ሰንበት ፍጥረትን ፈጥሮ ያረፈበት በዓል ሲሆን ⇝ እሑድ (ሰንበተ ክርስቲያን) ደግሞ በሐዲስ ኪዳን ሁሉን ‘አዲስ’ ሊያደርግ ከልደቱ ጀምሮ ሲፈጽም የነበረውን የማዳን ሥራ በምድር ዕለተ ዓርብ ፈጽሞ እስከ እሑድ ነፍሳትን ከሲኦል አግዞ በትንሳኤው በሐዲስ ተፈጥሮ የመፍጠሩን ሥራ የፈጸመበት / ያረፈበት ዕለት ነው።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።” 【 ፪ኛ ቆሮ ፭፥፲፯
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.