በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት በእንደርታ ወረዳ ለሰሰማት ትኩል ምዕራፈ ቅዱሳን ቤተ ደናግል ገዳም ሙሉ ገቢው የሚውለው "ከሞት ባሻገር" መጽሐፍ ሁለተኛ እትም
እና
ለኳታር ዶሃ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ሕንፃ ማሠሪያ ሙሉ ገቢው የሚውለው አበረታች መድኃኒት መጽሐፎች በዘመነ ትንሣኤ በአዲስ አበባና በዶሃ ታትመው በገበያ ላይ ይውላሉ::
ሁለቱም መጻሕፍት ለሁለተኛ ጊዜ የታተሙ ሲሆን ከሞት ባሻገር በገጽ ብዛት ጭማሪ የተደረገበት ክልስ እትም (revised edition) ነው::
እና
ለኳታር ዶሃ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ሕንፃ ማሠሪያ ሙሉ ገቢው የሚውለው አበረታች መድኃኒት መጽሐፎች በዘመነ ትንሣኤ በአዲስ አበባና በዶሃ ታትመው በገበያ ላይ ይውላሉ::
ሁለቱም መጻሕፍት ለሁለተኛ ጊዜ የታተሙ ሲሆን ከሞት ባሻገር በገጽ ብዛት ጭማሪ የተደረገበት ክልስ እትም (revised edition) ነው::
#ዘንባባ_እና_ሆሣዕና
✠.🌴✠🌴✠🌴.✠
ሙሽራይቱ የሆነችውን ቅድስት ቤተክርስቲያኑን መሠረት ሆኖ ያጸናት ፣ ራስ ሆኖ የሚገዛት ፣ በደሙም የዋጃትና አካሉ ሆና ያከበራት ክርስቶስ እንኳን ለዘንባባው በዓል አደረሳችሁ። 🙏 ሆሣዕና በአርያም 🙏
የቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮምን ምስክርነት መነሻ እናድርግ "ቤተክርስቲያን እንቲአነ ፍሬሃ ከመ በቀልት እንዘ አሐቲ ለሊሃ ወብዙኃት ሕንባባቲሃ … የእኛ የሆነች ቤተክርስቲያን ፍሬዋ እንደዘንባባ ፍሬ ነው ለራሷ አንዲት ስትሆን ቅርንጫፎቿ ብዙዎች ናቸው" 【ቀሌ. ፰፥፷፯】
ዘንባባ የሚለው ቃል ሰሌን፣ ጸበርት/ፀመርት ፣ ተምር፣ በቀልት … የሚሉትን ሁሉ ተክቶ የተነገረ ነው። ይሆንና ግን በቀልት የሚለው ግንዱን ፀመርት ደግሞ ቅጠሉ ሲሆን ተምር ፍሬው እንደሆነ መተርጉማን ያስረዳሉ።
በዚህ መንገድ ዘንባባ የሚለው ፍሬው ተዘርቶ የሚበቅል ቁመታም ሰሌን የቴምር ዛፍ ግእዙ በቀልት እያለ የሚጠራው ነው።
በእብራይስጡ ደግሞ ተምር (תָּמָר) ወይም ቶሜር (תֹּמֶר) የሚለው የቴምር ዛፍ ዘንባባን ወክሎ የሚነገር ሲሆን በግሪኩም ፎይኒክስ (φοῖνιξ) የሚለው የዘንባባ ዛፍን ወክሎ ተነግሯል።
በምሥጢር ግን ዘንባባ ራሱ ሆሳዕና ተብሎም ተጠርቷል!
ለምሳሌ ለቅዱስ ማቴዎስ ክርስቶስ በአምሳለ ወሬዛ(ወጣት) ተገልጾለት ካህናተ ጣዖት ወዳሉበት ሀገር ሲገባ ምን ማድረግ እንዳለበት ሲነገረው ሆሣዕና በእጅህ ያዝ እንዳለው ስንክሳራችን ይነግረናል ይህንንም ዘንባባ ነው ሲል መልሶታል።
“አንተሰ ኢትክል ከመ ትባእ ውስተ ዛቲ ሀገር ዘእንበለ ትላፂ ርእሰከ ወጽሕመከ ወዘእንበለ ትእኅዝ ሆሳዕና በእዴከ … አንተ ግን ጽሕምህን (ፂምህን) ካልተላጨህ በእጅህም ሆሣዕና/ ዘንባባ ካልያዝክ መግባት አትችልም”【ስንክሳር ጥቅምት ፲፪ ቁጥር ፲፫ 】
ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እየደጋገመ ለእመቤታችን ምሳሌ አድርጎ አስታውሶታል።
☆ በኆኅተ ብርሃን "ወደ ካህናቱ በገባ ጊዜ ለማስተማር የያዛት የማቴዎስ የሰሌን ዘንባባ አንቺ ነሽ… "
☆ በመዓዛ ቅዳሴም "የእንድርያስ የሕይወቱ መርከብ፣ ለያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ የስብከቱ መጽኛ፣ ብፁዕ ለሚሆን ለማቴዎስም የምልክቱ ዘንባባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ ነዪ"
#ሆሣዕና ለሚለው ቃል የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ሆሳና (ὡσαννά) የሚለውን የጽርእ ቃል ቀጥታ ይጠቀመው እንጂ መነሻው የእብራይስጡ «ሆሺዓህናእ» የሚለው ጥምር ቃል ነው። ይህም ሆሺዓህ (יָשַׁע) ናእ (נָא) ከሚሉት ሁለት ቃላት የተገኘ ነው።
ትርጉሙም ሆሺዓህ= አድን፣
ናእ ደግሞ አሁን/እባክህ/አቤቱ በሚለው ይገለጻል።
☞ አሁን አድን ፣ እባክህ አድን፣ አቤቱ አድን ማለት ነው።
ዘንባባ በሕይወታችን ስላለው ትርጉም ውዳሴ አምላክ የቀዳሚት ምንባብ ይህን ይላል "መልካም ፍሬን እንደምታፈራ እንደ ሰሌን ሥር ጽናት በልቡና ጽናትና በነፍስ ዝምታ በቦታዬ ትከለኝ" ከዚህ ጸሎት በመንፈሳዊው ሕይወት የዘንባባን ሃይማኖታዊ መገለጫ በሥሩ ጽናት ከቦታ አለመናወጽ ለነፍስ አለመታወክ ምሳሌ ሆኖ መጠቀሱን እንረዳለን። ውኃ በሌለበት በረሐ እየበቀለ ባለ ፍሬ መሆኑ መከራ በበዛበት ዓለም እየኖሩ ፣ በተኩላዎች መኃል እንደበግ ተልከው ስለእውነት እየመሰከሩ ፣ በመልካም ምግባር ጸንተው ፍሬ ላፈሩ… ጽኑዓን መስተጋድላን ሁሉ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
በቅዱስ መጽሐፍ ዘንባባ ያለውን ቦታ መረዳት እንድንችል ተከታዮቹን ተጨማሪ ታሪኮች እንመልከት ፦
✧ ታላቋ ባለቅኔ ሴት ዲቦራ በእስራኤል ላይ ስትፈርድ ትቀመጥ የነበረው ከዘንባባ በታች ነው። ዛፉም በስሟ ይጠራ እንደነበር መጽሐፍ እንዲህ ሲል ዘግቦልናል “እርስዋም በተራራማው በኤፍሬም አገር በራማና በቤቴል መካከል ካለው የዲቦራ ዛፍ ከሚባለው ከዘንባባው በታች ተቀምጣ ነበር፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እርስዋ ለፍርድ ይወጡ ነበር።” 【መሳ ፬፥፭】
✧ በኦሪቱ መቅደስ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዲቀርጽ (እንዲሥል) ከታዘዙት ሦስት ሥዕላት ውስጥ ሥዕለ ኪሩብ የፈነዳ አበባ እና የዘንባባ ዛፍን ነው። 【፩ኛ ነገ. ፮፥፳፱–፴፯】
✧ ታላቁ የዜና አይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን (Flavius Josephus / Yoseph Ben Mattithyahu) በዜና አይሁድ በሦስተኛው ክፍል በ፳፱ኛው ምዕራፍ ስለ ልማደ አይሁድ ሲዘግብ «በቂጣ በዓል ላይ የደስታና የክብር መገለጫ አድርገው በዘንባባ ዝንጣፊ የመማታት ጨዋታን እንደ ሕግና ልማድ ይፈጽሙት ነበር» ይላል።
✧ ሌላው በአይሁድም በሮማውያንም ዘንድ ዘንባባ ያለው ተምሳሌታዊ ሥፍራ ትልቅ ነው። ለድል አድራጊዎች በእምነታቸው ለጸኑትና ለሰላም አብሳሪዎች እንደ መገለጫ ሆኖ ያገለግላል። በተለይ ነቢያቱ የሰላም ዘመን እንዲመጣ ለሕዝቡ ለማብሰር በአሕያ ላይ ተቀምተው የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ወደ ከተማ ሲገቡ ይታዩ ነበር ፤
ቅዱስ መጽሐፋችንም ድል ነሺዎች የክብራቸው መገለጫ አድርገው በሰማዩ መቅደስ ዘንባባ ይዘው መገለጣቸውን እንዲህ ሲል ይመሰክርልናል።
“ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤” 【ራእ ፯፥፱】
በምሳሌነቱም ዘንባባ (በቀልት) የኢየሱስ ክርስቶስ ፣ የድንግል ማርያምና የሌሎቹም ቅዱሳን ጻድቃን ወኪል ሆኖ በየአገባቡ ሲመሰገኑበትና ክብራቸው ሲገለጥበት እንመለከታለን።
.🌴. ዘንባባ = ክርስቶስ
『 ስነ ቆምከ በቀልት ወመልክእከ ሕይወት ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምደ ሃይማኖት፣ ሥርግው ስነ ስብሐት በሰጊድ ስብሐት 』 ⇨ የቁመትህ ውበት ዘንባባ መልክህም ሕይወት የሆነ የሃይማኖት አምድ ክርስቶስ ሆይ ባማረ ምስጋና የተሸለምክ በመስገድ ላንተ ምስጋና እናቀርብልሃለን።
.🌴. ዘንባባ = ድንግል ማርያም
『 ለሕሊናኪ ንጽሕት እምነ ኵሉ ትውዝፍት፡ ለንጽሐ ሥጋኪ ዘአልቦ ርስሐት፡ ለቆምኪ ስነ በቀልት በሰጊድ ሰላም』 ⇨
.🌴. ዘንባባ = አቡነ ተክለሃይማኖት
『ተክለ ሃይማኖት በቀልት ወጽጌ ገነት ፡ ዘናቄርብ ለከ መዓዛ ስብሐት 』 ⇨
.🌴. ዘንባባ = አቡየ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
『 ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ኖመ ኖመ ኢየሩሳሌም በፍሥሓ ወበሐሴት፡፡ 』 ⇨
በይበልጥ ደግሞ "ጻድቅ እንደዘንባባ ያፈራል" በሚለው የነቢዩ ንጉሥ ዳዊት ቃል መነሻ በማድረግ 【መዝ ፺፪፥፲፪】በጽድቅ የኖሩ አያሌ ሰማዕታት መስተጋድላን መገለጫቸው ሆኖ ሲወሱበትና ሲወደሱበት ይታያል።
በኋላኛውም ዘመን ገዳማውያኑ መናንያን ሕይወታቸው ከዘንባባ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ሆኖ ታይቷል። ሥራቸው ሰሌን መታታት (ሠርቶ ሰፍቶ ለምንጣፍ ለቅርጫት፣ ለቆብና ለቀሚስ ማዘጋጀት) ፣ ለራሳቸውም የሚለብሱት ቆባቸውና ልብሳቸው ጭምር ከሰሌን የሚሠራ ነበር። ኋላም ዐረፍተ ዘመን ሲገታቸው የከበረ ሥጋቸው በሰሌን ተከፍኖ ግብኣተ መሬት ይፈጸምላቸዋል።
ከሰይጣን ውጊያ ለማረፍ እና ከስንፍና ለመለየት ከጸሎት ጋር መነኮሳት ሊተገብሩት ከሚገባ ተግባረ እድ ዋናው ሰሌን መታታት ሊሆን እንደሚገባ ቅዱስ መልአክ ለርእሰ መነኮሳት አባ እንጦንስ አስተምሮታል (ስንክሳር ዘጥር ፳፪) የባህታዊው አባ ጳውሊ ቀሚስ የአባ እንጦንስም ቆብ ከሰሌን የተሠራ ነበር መጽሐፈ መነኮሳቱና ዜና ገድላቸው ይነግረናል።
✠.🌴✠🌴✠🌴.✠
ሙሽራይቱ የሆነችውን ቅድስት ቤተክርስቲያኑን መሠረት ሆኖ ያጸናት ፣ ራስ ሆኖ የሚገዛት ፣ በደሙም የዋጃትና አካሉ ሆና ያከበራት ክርስቶስ እንኳን ለዘንባባው በዓል አደረሳችሁ። 🙏 ሆሣዕና በአርያም 🙏
የቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮምን ምስክርነት መነሻ እናድርግ "ቤተክርስቲያን እንቲአነ ፍሬሃ ከመ በቀልት እንዘ አሐቲ ለሊሃ ወብዙኃት ሕንባባቲሃ … የእኛ የሆነች ቤተክርስቲያን ፍሬዋ እንደዘንባባ ፍሬ ነው ለራሷ አንዲት ስትሆን ቅርንጫፎቿ ብዙዎች ናቸው" 【ቀሌ. ፰፥፷፯】
ዘንባባ የሚለው ቃል ሰሌን፣ ጸበርት/ፀመርት ፣ ተምር፣ በቀልት … የሚሉትን ሁሉ ተክቶ የተነገረ ነው። ይሆንና ግን በቀልት የሚለው ግንዱን ፀመርት ደግሞ ቅጠሉ ሲሆን ተምር ፍሬው እንደሆነ መተርጉማን ያስረዳሉ።
በዚህ መንገድ ዘንባባ የሚለው ፍሬው ተዘርቶ የሚበቅል ቁመታም ሰሌን የቴምር ዛፍ ግእዙ በቀልት እያለ የሚጠራው ነው።
በእብራይስጡ ደግሞ ተምር (תָּמָר) ወይም ቶሜር (תֹּמֶר) የሚለው የቴምር ዛፍ ዘንባባን ወክሎ የሚነገር ሲሆን በግሪኩም ፎይኒክስ (φοῖνιξ) የሚለው የዘንባባ ዛፍን ወክሎ ተነግሯል።
በምሥጢር ግን ዘንባባ ራሱ ሆሳዕና ተብሎም ተጠርቷል!
ለምሳሌ ለቅዱስ ማቴዎስ ክርስቶስ በአምሳለ ወሬዛ(ወጣት) ተገልጾለት ካህናተ ጣዖት ወዳሉበት ሀገር ሲገባ ምን ማድረግ እንዳለበት ሲነገረው ሆሣዕና በእጅህ ያዝ እንዳለው ስንክሳራችን ይነግረናል ይህንንም ዘንባባ ነው ሲል መልሶታል።
“አንተሰ ኢትክል ከመ ትባእ ውስተ ዛቲ ሀገር ዘእንበለ ትላፂ ርእሰከ ወጽሕመከ ወዘእንበለ ትእኅዝ ሆሳዕና በእዴከ … አንተ ግን ጽሕምህን (ፂምህን) ካልተላጨህ በእጅህም ሆሣዕና/ ዘንባባ ካልያዝክ መግባት አትችልም”【ስንክሳር ጥቅምት ፲፪ ቁጥር ፲፫ 】
ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እየደጋገመ ለእመቤታችን ምሳሌ አድርጎ አስታውሶታል።
☆ በኆኅተ ብርሃን "ወደ ካህናቱ በገባ ጊዜ ለማስተማር የያዛት የማቴዎስ የሰሌን ዘንባባ አንቺ ነሽ… "
☆ በመዓዛ ቅዳሴም "የእንድርያስ የሕይወቱ መርከብ፣ ለያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ የስብከቱ መጽኛ፣ ብፁዕ ለሚሆን ለማቴዎስም የምልክቱ ዘንባባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ ነዪ"
#ሆሣዕና ለሚለው ቃል የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ሆሳና (ὡσαννά) የሚለውን የጽርእ ቃል ቀጥታ ይጠቀመው እንጂ መነሻው የእብራይስጡ «ሆሺዓህናእ» የሚለው ጥምር ቃል ነው። ይህም ሆሺዓህ (יָשַׁע) ናእ (נָא) ከሚሉት ሁለት ቃላት የተገኘ ነው።
ትርጉሙም ሆሺዓህ= አድን፣
ናእ ደግሞ አሁን/እባክህ/አቤቱ በሚለው ይገለጻል።
☞ አሁን አድን ፣ እባክህ አድን፣ አቤቱ አድን ማለት ነው።
ዘንባባ በሕይወታችን ስላለው ትርጉም ውዳሴ አምላክ የቀዳሚት ምንባብ ይህን ይላል "መልካም ፍሬን እንደምታፈራ እንደ ሰሌን ሥር ጽናት በልቡና ጽናትና በነፍስ ዝምታ በቦታዬ ትከለኝ" ከዚህ ጸሎት በመንፈሳዊው ሕይወት የዘንባባን ሃይማኖታዊ መገለጫ በሥሩ ጽናት ከቦታ አለመናወጽ ለነፍስ አለመታወክ ምሳሌ ሆኖ መጠቀሱን እንረዳለን። ውኃ በሌለበት በረሐ እየበቀለ ባለ ፍሬ መሆኑ መከራ በበዛበት ዓለም እየኖሩ ፣ በተኩላዎች መኃል እንደበግ ተልከው ስለእውነት እየመሰከሩ ፣ በመልካም ምግባር ጸንተው ፍሬ ላፈሩ… ጽኑዓን መስተጋድላን ሁሉ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።
በቅዱስ መጽሐፍ ዘንባባ ያለውን ቦታ መረዳት እንድንችል ተከታዮቹን ተጨማሪ ታሪኮች እንመልከት ፦
✧ ታላቋ ባለቅኔ ሴት ዲቦራ በእስራኤል ላይ ስትፈርድ ትቀመጥ የነበረው ከዘንባባ በታች ነው። ዛፉም በስሟ ይጠራ እንደነበር መጽሐፍ እንዲህ ሲል ዘግቦልናል “እርስዋም በተራራማው በኤፍሬም አገር በራማና በቤቴል መካከል ካለው የዲቦራ ዛፍ ከሚባለው ከዘንባባው በታች ተቀምጣ ነበር፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እርስዋ ለፍርድ ይወጡ ነበር።” 【መሳ ፬፥፭】
✧ በኦሪቱ መቅደስ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዲቀርጽ (እንዲሥል) ከታዘዙት ሦስት ሥዕላት ውስጥ ሥዕለ ኪሩብ የፈነዳ አበባ እና የዘንባባ ዛፍን ነው። 【፩ኛ ነገ. ፮፥፳፱–፴፯】
✧ ታላቁ የዜና አይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን (Flavius Josephus / Yoseph Ben Mattithyahu) በዜና አይሁድ በሦስተኛው ክፍል በ፳፱ኛው ምዕራፍ ስለ ልማደ አይሁድ ሲዘግብ «በቂጣ በዓል ላይ የደስታና የክብር መገለጫ አድርገው በዘንባባ ዝንጣፊ የመማታት ጨዋታን እንደ ሕግና ልማድ ይፈጽሙት ነበር» ይላል።
✧ ሌላው በአይሁድም በሮማውያንም ዘንድ ዘንባባ ያለው ተምሳሌታዊ ሥፍራ ትልቅ ነው። ለድል አድራጊዎች በእምነታቸው ለጸኑትና ለሰላም አብሳሪዎች እንደ መገለጫ ሆኖ ያገለግላል። በተለይ ነቢያቱ የሰላም ዘመን እንዲመጣ ለሕዝቡ ለማብሰር በአሕያ ላይ ተቀምተው የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ወደ ከተማ ሲገቡ ይታዩ ነበር ፤
ቅዱስ መጽሐፋችንም ድል ነሺዎች የክብራቸው መገለጫ አድርገው በሰማዩ መቅደስ ዘንባባ ይዘው መገለጣቸውን እንዲህ ሲል ይመሰክርልናል።
“ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤” 【ራእ ፯፥፱】
በምሳሌነቱም ዘንባባ (በቀልት) የኢየሱስ ክርስቶስ ፣ የድንግል ማርያምና የሌሎቹም ቅዱሳን ጻድቃን ወኪል ሆኖ በየአገባቡ ሲመሰገኑበትና ክብራቸው ሲገለጥበት እንመለከታለን።
.🌴. ዘንባባ = ክርስቶስ
『 ስነ ቆምከ በቀልት ወመልክእከ ሕይወት ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምደ ሃይማኖት፣ ሥርግው ስነ ስብሐት በሰጊድ ስብሐት 』 ⇨ የቁመትህ ውበት ዘንባባ መልክህም ሕይወት የሆነ የሃይማኖት አምድ ክርስቶስ ሆይ ባማረ ምስጋና የተሸለምክ በመስገድ ላንተ ምስጋና እናቀርብልሃለን።
.🌴. ዘንባባ = ድንግል ማርያም
『 ለሕሊናኪ ንጽሕት እምነ ኵሉ ትውዝፍት፡ ለንጽሐ ሥጋኪ ዘአልቦ ርስሐት፡ ለቆምኪ ስነ በቀልት በሰጊድ ሰላም』 ⇨
.🌴. ዘንባባ = አቡነ ተክለሃይማኖት
『ተክለ ሃይማኖት በቀልት ወጽጌ ገነት ፡ ዘናቄርብ ለከ መዓዛ ስብሐት 』 ⇨
.🌴. ዘንባባ = አቡየ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
『 ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ኖመ ኖመ ኢየሩሳሌም በፍሥሓ ወበሐሴት፡፡ 』 ⇨
በይበልጥ ደግሞ "ጻድቅ እንደዘንባባ ያፈራል" በሚለው የነቢዩ ንጉሥ ዳዊት ቃል መነሻ በማድረግ 【መዝ ፺፪፥፲፪】በጽድቅ የኖሩ አያሌ ሰማዕታት መስተጋድላን መገለጫቸው ሆኖ ሲወሱበትና ሲወደሱበት ይታያል።
በኋላኛውም ዘመን ገዳማውያኑ መናንያን ሕይወታቸው ከዘንባባ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ሆኖ ታይቷል። ሥራቸው ሰሌን መታታት (ሠርቶ ሰፍቶ ለምንጣፍ ለቅርጫት፣ ለቆብና ለቀሚስ ማዘጋጀት) ፣ ለራሳቸውም የሚለብሱት ቆባቸውና ልብሳቸው ጭምር ከሰሌን የሚሠራ ነበር። ኋላም ዐረፍተ ዘመን ሲገታቸው የከበረ ሥጋቸው በሰሌን ተከፍኖ ግብኣተ መሬት ይፈጸምላቸዋል።
ከሰይጣን ውጊያ ለማረፍ እና ከስንፍና ለመለየት ከጸሎት ጋር መነኮሳት ሊተገብሩት ከሚገባ ተግባረ እድ ዋናው ሰሌን መታታት ሊሆን እንደሚገባ ቅዱስ መልአክ ለርእሰ መነኮሳት አባ እንጦንስ አስተምሮታል (ስንክሳር ዘጥር ፳፪) የባህታዊው አባ ጳውሊ ቀሚስ የአባ እንጦንስም ቆብ ከሰሌን የተሠራ ነበር መጽሐፈ መነኮሳቱና ዜና ገድላቸው ይነግረናል።
ገዳማዊው አባ ዳንኤል መታበይ ሲመጣበት ሔዶ ያየው ዘንድ እግዚአብሔር ወደ ንጉሥ አኖሬዎስ ልኮታል፤ ተወዳጁ ንጉሥ ሰሌን በመታታት በዘንባባ ቅጠል ምንጣፍ በመሥራት ይደክም ሸጦም ይመጸውት እንደነበር አይቶ ተምሯል (ስንክሳር ዘሕዳር ፲፮)
ታላቁ አባ ሙሴ ዘደብረ ሲሐት ልብሱ ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነበር (ስንክሳር ዘመስከረም ፫)
በሌላ መንገድ ደግሞ በዘመነ ሰማዕታት ዘንባባው የክብር መቀበያ ከሥጋ ድካም የማለፋቸው ምክንያትም የሆነላቸውን ቅዱሳንም እናገኛለን። ከነዚህም ውሥጥ በሚያዝያ ወር የሚዘከሩ በሰማዕትነት ያረፉ ቅዱስ በብኑዳና ቅድስት ኮሮና (እሥጢፋና) በዘንባባ ላይ ተሰቅለው በዘንባባ መኃል ታሥረው ለክብር መብቃታቸውን የታሪክ መድብላችን ይመሰክራል።
🌴 ሰላም እብል ለበብኑዳ ሰማዕት፣… ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳】
🌴 ሰላም ለእስጢፋና እንተ ፃመወት በሕቁ፡
ለፊቅጦር ሰማዕት ተላዊተ ዐሠሩ ወጽድቁ፡
እለ ኰነንዋ ሐራ እስከ እምፍርሀት ወድቁ፡
በጒንደ በቀልት ዘአስተላጸቁ፡
ማኅፈቀ ሥጋሃ ለ፪ኤ ሠጠቁ፡፡ [የሰማዕቱ ፊቅጦርን ፍለጋና እውነት (ሕይወትና ሃይማኖት) የተከተለች የፈረዱባት ጭፍሮች ፈርተው እስከሚወድቁ ድረስ፤ በሰሌን ዛፍ በዘንባባ ግንድ ላይ አሥረዋት ሥጋ አካሏን ለሁለት እስኪሰነጥቁት ድረስ በእጅጉ ለደከመች ለእስጢፋና (ኮሮና) ሰላም ይሁን።] 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፯】
ወደ ሆሣዕናው ታሪክ ስንመለስ የዝክረ ቅዱሳን እስትግቡእ የሆነው መጽሐፈ ስንክሳር ስለዘንባባው የትመጣና ትርጉም ተከታዩን ሐሳብ ያስቀምጥልናል ።
«ማቴዎስና ማርቆስ የዘንባባን ነገር አላስታወሱም፤ ሌሎች ከዛፍ ላይ ቅርንጫፍ፡ ዘንጥፈው በመንገድ ላይ ጐዘጐዙ አሉ እንጂ ። ሉቃስም ዝንጣፊውንም ሆነ ዘንባባውን አላወሳም፤ ሲሄዱም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር አለ እንጂ ። ዮሐንስ ግን ብቻውን የሰሌን ዛፍ ዝንጣፊ ከኢየሩሳሌም ያዙ አለ ። ሰሌን በኢየሩሳሌም የለም ነበርና ጌታችን በሕፃንነቱ ከእናቱ ከክብርት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ምድር በወረደ ጊዜ እስሙናይን ከተባለ አገር ደረሱ፤ በዚያም ሰሌን አገኙ ። ጌታችንም ከሥርዋ ተነቅላ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ትተከል ዘንድ አዘዛት ። ያን ጊዜም ወደ አየር ወጥታ በረረች በደብረ ዘይትም ላይ ተተከለች ። ከእርስዋም ዘንባባ ወስደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉት፤ ሥርዓተ ሆሣዕናን እየዞረ አሳይቷልና ።»
ዘንባባው የመጣውና ደብረ ዘይት የተተከለው ከእስሙናይ (Eshmunen) ነው ያለውን ይዘን ታላቁ ሊቅ የእስሙናይ ሊቀጳጳሳት ቅዱስ ሳዊሮስ (Severus ibn al-Muqaffa) በበዓለ ሆሣዕናው ዙሪያ በመጽሐፉ የጻፈውን በድርሳኑ ፯ኛው ክፍል ላይ የምናገኘውን እናስታውስ
* እስከ ፴ ዓመቱ ድረስ በክርስቶስነቱ ማንም ሳያምንበት ኖረ ይህም ሮማውያንን ፈርተው እንደነበር በእሑድ ሰንበት በዕለተ ሆሣዕና ግን ሰማንያ አራቱ ደቀመዛሙርት (ሰባ ሁለቱ አርድእትና አስራሁለቱ ሐዋተርያት) ከደብረዘይት ይዘውት ሲወርዱ የሚነግሥና ከሮማውያኑ አገዛዝ ነጻ የሚያወጣቸው መስሏቸው በእብራይስጡ ሆሣዕና በአርያም በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው እያሉ ሲያመሰግኑት ህዝቡ ሁሉ የወይራ ዛፍ ከዘንባባ ዝንጣፊ ጋር ይዘው ልብሳቸውን እያነጠፉ እንደተቀበሉት ወደኢየሩሳሌምን ገብቶ ወደምኩራባቸውም አምርቶ እንደነገሥታቱ ተግባሩን ሲፈጽም ታየ እያለ እንደሚከተለው አስፍሯል። *
ወደ ምሥጢራዊው ትርጉም ስናልፍ ደግሞ ለምን በዕለተ ሆሣዕና በቦታው የተገኙት ዘንባባ በመያዝ ዘመሩ ለሚለው ተከታዩ አንድምታዊ ሐተታ በሊቃውንቱ ይነገራል ፦
☞ ዘንባባ ወይም ሰሌን እሾኻም ነው ትእምርተ ኃይል ትእምርተ መዊዕ (የኃይልና የድል ነሺነት ምልክት) አለህ ሲሉ እነርሱም ዘንባባውን ይዘው ታይተዋል ። (አንድም) ዘንባባን እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል፤ ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ ከነዘንባባቸው እያጀቡት ወደ ኢየሩሳሌም ገብተዋል። (አንድም) ዘንባባ ረጅም / ልዑል/ ነው አንተም ባሕርይህ ልዑል ነው ሲሉ ዘንባባ ይዘው ተቀብለውታል፡፡
☞ የተምር ዛፍ ዝንጣፊ ነው ያሉ እንደሆነ ተምር ልዑል / ረዥም ነው ⇨ ልዑለ ባሕርይ ነህ ሲሉ። የተምር ፍሬውም በእሾህ የተከበበ ነው (ፍሬው በእሾህ የተከበበ ነው (በቀላሉ መለቀም አይቻልም) የአንተም ምስጢር አንተ ካልገለጠከው አይመረመርም ሲሉ) ⇨ በባሕርይህ አትመረመርም ሲሉ ነው፡፡ በዚያውም ላይ ፍሬው አንድ ነው ⇨ ዋህደ ባሕርይ ነህ ሲሉ ነው።
☞ ሰሌን ነው ያሉ እንደሆነ አብርሃም ይስሐቅን ይስሐቅ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፤ እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፤ ዮዲት ሆሎፎርኒስን በገደለች ጊዜ፣ ሰሌን ቆርጠው ይዘው አመስግነዋልና በዚያ ልማድ።
(በዚያ ልማድ የተባሉትን ታሪኮች በአጭሩ ለማስታወስ እንዲረዳን ጥቂት ነገር እናውሳ… )
🌴 አብርሃም ላዳነውና በሔደበት ሀገር ደስ ላሰኘው ለእግዚአብሔር በዚያ መሠዊያን ሠራ… ደስ ብሎት አከበራት የዚህችን በዓል ስሟን የእግዚአብሔር በዓል አላት … የዘልዓለም ሥርዓት ሆኖ ተጽፏልና ለዚህ ሥርዓት የተወሰነ ዘመን የለውም፤ አብርሃም የሰሌኑን ጫፍ ለጋውን ያማረ የእንጨቱን ፍሬ ይዞ በየቀኑ ዘንባባውን ይዞ ሰባት ቀን የመሰዊያውን ዙርያ ይዞር ነበር" 【ኩፋ ፲፫፥ ፱,፲፯,፳,፳፩】
የሆሣዕናው ቅዳሴም የአብርሃምና የመልከጼዴቅን ነገር ሰፊ ቦታ ሰጥቶ ሲያወሳው እናያለን። ለዑደተ ሆሣዕና መነሻውም የአብርሐም ተግባር መሆኑን የመጋቢት ፳፪ቱ ስንክሳር እንደሚከተለው ይመሰክራል
« አብርሃምም ይቺን በዓል ደስታን የተመላች የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሎ ጠራት፤ የሰሌን ዝንጣፊና ዘንባባን ይዞ መሠዊያውን ዙሮአልና»
🌴 መልከ መልካምና ደመግቡ የነበረች ታላቋ ሴት ዮዲት መቅደሱን ያሳደፉ ማደሪያውን ያረከሱ የእግዚአብሔር ጠላቶች ድል ስትነሳና የናቡከደነፆር ቢትወደድ የነበረውን ሆሎፎርኒስን ገድላ በበቅሎ ላይ ተቀምጣ ሠረገላ እየነዳች ወደ ሀገርዋ ስትገባ የእስራኤል ሴቶች ሊያይዋትና ሊመርቋት ሮጠው ወጡ "ደግ በዓል አደረጉላት ዘንባባም በእጇ ያዘች ከእርሷ ጋር ለነበሩትም ሠጠች" 【ዮዲ. ፲፭፥፲፪】
ለመቋጫ እንዲሆን ንጹሕ ክቡር የሚሆን ዐምዳዊው ስምዖን የደረሰው የሆሣዕና በዓል በተደረገ በከበረች የክርስቲያኖች ሰንበት የሚነበበውን ጸሎት ከግብረ ሕማማቱ በማስታወስ እንሰነባበት
[ … ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዘይት (የወይራ ዛፍ) ዝንጣፊና የሰሌን ዘንባባ ተሸክሜ ከአርያም የተገኘ መድኃኒት መባል ለአንተ ይገባል እያልኩ ከሕፃናት ጋራ እጮኽ ዘንድ አድለኝ ። የዳዊት ልጅ ሆይ አማኑኤል እግዚብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት እንደሆነ ከአንተ ጋር አንድ አድርገኝ ። ወገኖችህ እንሆን ዘንድ አድርገን፤ በልቡናችን የጌትነትህን ብርሃን አብራ ። ከወገንህ ልጆች ውስጥ አድርገን ። እንተ ጠባቂያችን፣ መጋቢያችን፣ መሪያችን ነህ ። አንተም ንጉሣችን እኛም የወገንህ ልጆች፤ ንጉሣችንና አምላካችን ወደ እኛ መምጣትህ የተባረከች ናት፤ ከጨለማውም ግዛት አድነህ ብርሃንንና ክብርን ወደ ተመላች መንግሥትም አድርሰን ።በጨለማው ገዥ ከመረገጥ አድነን፤ ቃል ኪዳንህንና አምላካዊ ሕግህን በላያችን አጽና፤ በስምህ የሚያድን ሕይወትህን እንወርስ ዘንድ። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ርግቦች የሚሸጡትን ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌባና የወንበዴ ዋሻ አደረጋችሁት በማለት ያሳደድኻቸው ።
ታላቁ አባ ሙሴ ዘደብረ ሲሐት ልብሱ ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነበር (ስንክሳር ዘመስከረም ፫)
በሌላ መንገድ ደግሞ በዘመነ ሰማዕታት ዘንባባው የክብር መቀበያ ከሥጋ ድካም የማለፋቸው ምክንያትም የሆነላቸውን ቅዱሳንም እናገኛለን። ከነዚህም ውሥጥ በሚያዝያ ወር የሚዘከሩ በሰማዕትነት ያረፉ ቅዱስ በብኑዳና ቅድስት ኮሮና (እሥጢፋና) በዘንባባ ላይ ተሰቅለው በዘንባባ መኃል ታሥረው ለክብር መብቃታቸውን የታሪክ መድብላችን ይመሰክራል።
🌴 ሰላም እብል ለበብኑዳ ሰማዕት፣… ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳】
🌴 ሰላም ለእስጢፋና እንተ ፃመወት በሕቁ፡
ለፊቅጦር ሰማዕት ተላዊተ ዐሠሩ ወጽድቁ፡
እለ ኰነንዋ ሐራ እስከ እምፍርሀት ወድቁ፡
በጒንደ በቀልት ዘአስተላጸቁ፡
ማኅፈቀ ሥጋሃ ለ፪ኤ ሠጠቁ፡፡ [የሰማዕቱ ፊቅጦርን ፍለጋና እውነት (ሕይወትና ሃይማኖት) የተከተለች የፈረዱባት ጭፍሮች ፈርተው እስከሚወድቁ ድረስ፤ በሰሌን ዛፍ በዘንባባ ግንድ ላይ አሥረዋት ሥጋ አካሏን ለሁለት እስኪሰነጥቁት ድረስ በእጅጉ ለደከመች ለእስጢፋና (ኮሮና) ሰላም ይሁን።] 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፯】
ወደ ሆሣዕናው ታሪክ ስንመለስ የዝክረ ቅዱሳን እስትግቡእ የሆነው መጽሐፈ ስንክሳር ስለዘንባባው የትመጣና ትርጉም ተከታዩን ሐሳብ ያስቀምጥልናል ።
«ማቴዎስና ማርቆስ የዘንባባን ነገር አላስታወሱም፤ ሌሎች ከዛፍ ላይ ቅርንጫፍ፡ ዘንጥፈው በመንገድ ላይ ጐዘጐዙ አሉ እንጂ ። ሉቃስም ዝንጣፊውንም ሆነ ዘንባባውን አላወሳም፤ ሲሄዱም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር አለ እንጂ ። ዮሐንስ ግን ብቻውን የሰሌን ዛፍ ዝንጣፊ ከኢየሩሳሌም ያዙ አለ ። ሰሌን በኢየሩሳሌም የለም ነበርና ጌታችን በሕፃንነቱ ከእናቱ ከክብርት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ምድር በወረደ ጊዜ እስሙናይን ከተባለ አገር ደረሱ፤ በዚያም ሰሌን አገኙ ። ጌታችንም ከሥርዋ ተነቅላ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ትተከል ዘንድ አዘዛት ። ያን ጊዜም ወደ አየር ወጥታ በረረች በደብረ ዘይትም ላይ ተተከለች ። ከእርስዋም ዘንባባ ወስደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉት፤ ሥርዓተ ሆሣዕናን እየዞረ አሳይቷልና ።»
ዘንባባው የመጣውና ደብረ ዘይት የተተከለው ከእስሙናይ (Eshmunen) ነው ያለውን ይዘን ታላቁ ሊቅ የእስሙናይ ሊቀጳጳሳት ቅዱስ ሳዊሮስ (Severus ibn al-Muqaffa) በበዓለ ሆሣዕናው ዙሪያ በመጽሐፉ የጻፈውን በድርሳኑ ፯ኛው ክፍል ላይ የምናገኘውን እናስታውስ
* እስከ ፴ ዓመቱ ድረስ በክርስቶስነቱ ማንም ሳያምንበት ኖረ ይህም ሮማውያንን ፈርተው እንደነበር በእሑድ ሰንበት በዕለተ ሆሣዕና ግን ሰማንያ አራቱ ደቀመዛሙርት (ሰባ ሁለቱ አርድእትና አስራሁለቱ ሐዋተርያት) ከደብረዘይት ይዘውት ሲወርዱ የሚነግሥና ከሮማውያኑ አገዛዝ ነጻ የሚያወጣቸው መስሏቸው በእብራይስጡ ሆሣዕና በአርያም በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው እያሉ ሲያመሰግኑት ህዝቡ ሁሉ የወይራ ዛፍ ከዘንባባ ዝንጣፊ ጋር ይዘው ልብሳቸውን እያነጠፉ እንደተቀበሉት ወደኢየሩሳሌምን ገብቶ ወደምኩራባቸውም አምርቶ እንደነገሥታቱ ተግባሩን ሲፈጽም ታየ እያለ እንደሚከተለው አስፍሯል። *
ወደ ምሥጢራዊው ትርጉም ስናልፍ ደግሞ ለምን በዕለተ ሆሣዕና በቦታው የተገኙት ዘንባባ በመያዝ ዘመሩ ለሚለው ተከታዩ አንድምታዊ ሐተታ በሊቃውንቱ ይነገራል ፦
☞ ዘንባባ ወይም ሰሌን እሾኻም ነው ትእምርተ ኃይል ትእምርተ መዊዕ (የኃይልና የድል ነሺነት ምልክት) አለህ ሲሉ እነርሱም ዘንባባውን ይዘው ታይተዋል ። (አንድም) ዘንባባን እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል፤ ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ ከነዘንባባቸው እያጀቡት ወደ ኢየሩሳሌም ገብተዋል። (አንድም) ዘንባባ ረጅም / ልዑል/ ነው አንተም ባሕርይህ ልዑል ነው ሲሉ ዘንባባ ይዘው ተቀብለውታል፡፡
☞ የተምር ዛፍ ዝንጣፊ ነው ያሉ እንደሆነ ተምር ልዑል / ረዥም ነው ⇨ ልዑለ ባሕርይ ነህ ሲሉ። የተምር ፍሬውም በእሾህ የተከበበ ነው (ፍሬው በእሾህ የተከበበ ነው (በቀላሉ መለቀም አይቻልም) የአንተም ምስጢር አንተ ካልገለጠከው አይመረመርም ሲሉ) ⇨ በባሕርይህ አትመረመርም ሲሉ ነው፡፡ በዚያውም ላይ ፍሬው አንድ ነው ⇨ ዋህደ ባሕርይ ነህ ሲሉ ነው።
☞ ሰሌን ነው ያሉ እንደሆነ አብርሃም ይስሐቅን ይስሐቅ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፤ እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፤ ዮዲት ሆሎፎርኒስን በገደለች ጊዜ፣ ሰሌን ቆርጠው ይዘው አመስግነዋልና በዚያ ልማድ።
(በዚያ ልማድ የተባሉትን ታሪኮች በአጭሩ ለማስታወስ እንዲረዳን ጥቂት ነገር እናውሳ… )
🌴 አብርሃም ላዳነውና በሔደበት ሀገር ደስ ላሰኘው ለእግዚአብሔር በዚያ መሠዊያን ሠራ… ደስ ብሎት አከበራት የዚህችን በዓል ስሟን የእግዚአብሔር በዓል አላት … የዘልዓለም ሥርዓት ሆኖ ተጽፏልና ለዚህ ሥርዓት የተወሰነ ዘመን የለውም፤ አብርሃም የሰሌኑን ጫፍ ለጋውን ያማረ የእንጨቱን ፍሬ ይዞ በየቀኑ ዘንባባውን ይዞ ሰባት ቀን የመሰዊያውን ዙርያ ይዞር ነበር" 【ኩፋ ፲፫፥ ፱,፲፯,፳,፳፩】
የሆሣዕናው ቅዳሴም የአብርሃምና የመልከጼዴቅን ነገር ሰፊ ቦታ ሰጥቶ ሲያወሳው እናያለን። ለዑደተ ሆሣዕና መነሻውም የአብርሐም ተግባር መሆኑን የመጋቢት ፳፪ቱ ስንክሳር እንደሚከተለው ይመሰክራል
« አብርሃምም ይቺን በዓል ደስታን የተመላች የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሎ ጠራት፤ የሰሌን ዝንጣፊና ዘንባባን ይዞ መሠዊያውን ዙሮአልና»
🌴 መልከ መልካምና ደመግቡ የነበረች ታላቋ ሴት ዮዲት መቅደሱን ያሳደፉ ማደሪያውን ያረከሱ የእግዚአብሔር ጠላቶች ድል ስትነሳና የናቡከደነፆር ቢትወደድ የነበረውን ሆሎፎርኒስን ገድላ በበቅሎ ላይ ተቀምጣ ሠረገላ እየነዳች ወደ ሀገርዋ ስትገባ የእስራኤል ሴቶች ሊያይዋትና ሊመርቋት ሮጠው ወጡ "ደግ በዓል አደረጉላት ዘንባባም በእጇ ያዘች ከእርሷ ጋር ለነበሩትም ሠጠች" 【ዮዲ. ፲፭፥፲፪】
ለመቋጫ እንዲሆን ንጹሕ ክቡር የሚሆን ዐምዳዊው ስምዖን የደረሰው የሆሣዕና በዓል በተደረገ በከበረች የክርስቲያኖች ሰንበት የሚነበበውን ጸሎት ከግብረ ሕማማቱ በማስታወስ እንሰነባበት
[ … ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዘይት (የወይራ ዛፍ) ዝንጣፊና የሰሌን ዘንባባ ተሸክሜ ከአርያም የተገኘ መድኃኒት መባል ለአንተ ይገባል እያልኩ ከሕፃናት ጋራ እጮኽ ዘንድ አድለኝ ። የዳዊት ልጅ ሆይ አማኑኤል እግዚብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት እንደሆነ ከአንተ ጋር አንድ አድርገኝ ። ወገኖችህ እንሆን ዘንድ አድርገን፤ በልቡናችን የጌትነትህን ብርሃን አብራ ። ከወገንህ ልጆች ውስጥ አድርገን ። እንተ ጠባቂያችን፣ መጋቢያችን፣ መሪያችን ነህ ። አንተም ንጉሣችን እኛም የወገንህ ልጆች፤ ንጉሣችንና አምላካችን ወደ እኛ መምጣትህ የተባረከች ናት፤ ከጨለማውም ግዛት አድነህ ብርሃንንና ክብርን ወደ ተመላች መንግሥትም አድርሰን ።በጨለማው ገዥ ከመረገጥ አድነን፤ ቃል ኪዳንህንና አምላካዊ ሕግህን በላያችን አጽና፤ በስምህ የሚያድን ሕይወትህን እንወርስ ዘንድ። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ርግቦች የሚሸጡትን ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌባና የወንበዴ ዋሻ አደረጋችሁት በማለት ያሳደድኻቸው ።
ከልቤና ከሰውነቴ የክፋት መንፈስን ሁሉና የተናቀ ነገር ማሰብን አስወግድ ። ልቡናዬንም የጸሎት ቤት አድርገው፤ ልቤንና ሐሳቤንም ስምህን ለማክበርና ለማመስገን አንቃቸው። …]
አሜን! 🙏 ሆሣዕና በአርያም 🙏
【 .🌴. ከቴዎድሮስ በለጠ ✍Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ሆሣዕና ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም. 】
አሜን! 🙏 ሆሣዕና በአርያም 🙏
【 .🌴. ከቴዎድሮስ በለጠ ✍Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ሆሣዕና ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም. 】
እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ በዚህ አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው፡፡ ብልህ አገልጋይ ቢኖር፥ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፡፡
በጾም የደከመ ቢኖር፥ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡፡ በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፥ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ፡፡
በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፥ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፡፡ በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፥ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፡፡ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ሳይጠራጠር ይቅረብ፡፡ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፡፡ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና፡፡ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፡፡
መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፡፡ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፡፡ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፡፡ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል፡፡ ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፡፡
ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ! እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፡፡ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ! በአንድነት ዘምሩ፡፡ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ! በዓሉን አክብሩት፡፡ እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ! ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፡፡
መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፡፡ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፡፡ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡
ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፥ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፡፡ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፥ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፡፡ ማንም ሞትን አይፍራ፥ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፡፡ ለእርስዋ በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡
በሞቱ ሞትን ገደለው፡፡ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፡፡
ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ መረራትም! ከንቱ አድርጓታልና መረራት! ሸንግሏታልና መረራት! ሽሯታልና መረራት!
ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት!
[መቃብር የዕሩቅ ብእሲ] ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤ ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው - መረራትም!
ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@orthodox1 @orthodox1
@orthodox1 @orthodox1
@orthodox1 @orthodox1
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
በጾም የደከመ ቢኖር፥ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡፡ በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፥ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ፡፡
በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፥ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፡፡ በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፥ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፡፡ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ሳይጠራጠር ይቅረብ፡፡ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፡፡ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና፡፡ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፡፡
መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፡፡ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፡፡ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፡፡ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል፡፡ ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፡፡
ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ! እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፡፡ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ! በአንድነት ዘምሩ፡፡ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ! በዓሉን አክብሩት፡፡ እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ! ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፡፡
መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፡፡ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፡፡ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡
ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፥ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፡፡ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፥ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፡፡ ማንም ሞትን አይፍራ፥ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፡፡ ለእርስዋ በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡
በሞቱ ሞትን ገደለው፡፡ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፡፡
ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ መረራትም! ከንቱ አድርጓታልና መረራት! ሸንግሏታልና መረራት! ሽሯታልና መረራት!
ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት!
[መቃብር የዕሩቅ ብእሲ] ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤ ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው - መረራትም!
ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
@orthodox1 @orthodox1
@orthodox1 @orthodox1
@orthodox1 @orthodox1
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
ምሕዛል ወቃለ ባሕ ዘትንሣኤ [Paschal troparion & Greeting] #የፋሲካ_አመላለስና_ሠላምታ
᳀͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͞ ͟͞ ̸ ͟͞ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ✙ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᳀
(ለትንሣኤ የተቆነጠረ ሐሳብ)
ሀገርኛው የዘውትር ሰላምታችን ሰላም ላንተ ይኹን👋 ጠላትኽን ያውድቅ ቢሰኛኽን ያርቅ! 🙏 በሚል መነሻ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚታከልበት ምኞት መግለጫና ምስጋና ማቅረቢያ ነው!
የሰላምታው መንገድ ደግሞ በሦስት ሂደት (በቃል በእጅና በአንገት) የሚከወን ነው።
🤝
መጨባበጥ (ተራክቦተ እድ ፣ ፅብጠት፣ ተጻብሖ) ☞ በእጅ የሚፈጸም ፦ በመጨባበጥ [handshake] በመተቃቀፍ [hugging] አልያም በጉንጭ በመሳሳም [cheek kissing] ይፈጸም የነበረውን በቀደሙቱ ዘንድ “አምኃ ቅድሳት” [holy kiss & kiss of peace ⇨ ἐν ἁγίω φιλήματι, και φιλί της ειρήνης ] እየተባለ የሚጠራው መንገድ ነው!
በዚኽ አጋጣሚ በወቅቱ ጉዳይ መጨባበጥ መተቃቀፍና መሳሳም ለወረርሽቹ በፍጥነት መዛመት ምክንያት መሆናቸውን አውቀን #አካላዊ_ፈቀቅታ|ን በመጠበቅ በበሽታው የምናልፍ ሳንሆን በሽታውን የምናሳልፍ ነገንም የምናይ እንድንሆን በተከታዮቹ መንገዶች ሰላምታ የምንለዋወጥ ይሁን!
🙇
"እጅ መነሳሳት" (እማኄ) ☞ ባንገት፣ በወገብና በጕልበት የሚፈጸም ነው።
🙋
የሰላምታ ቃል መለዋወጥ (በቃለ ተአምኆ) ሰላምታ በንግግር በመለዋወጥ የሚፈጸም ዋናዎቹ ናቸው!
ወደተቆነጠረው ሐሳብ እንለፍ ተዝካረ ትንሣኤው በሚታሰብበት ዐባይ ፋሲካ ፶ ዕለት በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸም የተለየ ሰላምታና የዜማ ድጋም አመላለስ አለ።
የጌታችን ተዝካረ ትንሣኤ በቤተክርስቲያናችን ሰፊ ቦታና ትርጉም ያለው በመሆኑ የዓመት ሢሦው (⅓) ነገረ ፋሲካን የሚያስታውስ ነው (የፋሲካ ጾም ⁵⁵ እና ዘመነ ትንሣኤ⁵⁰)
በቅዳሴው መግቢያ መስዋእቱ ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጣ ከትንሳኤው እስከ በዓለ ፶ ጊዜው የተለየ መሆኑን ለማሳወቅ "እመቦ ብእሲ… " በሚለው መግቢያ ፈንታ "ሃሌ ሉያ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ በሰንዱናት ለዘተንሥአ እሙታን በመንክር ኪነ ⇨ ሃሌ ሉያ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ድንቅ በሚሆን ጥበብ ከሙታን ተለይቶ የተነሣ ኢየሱስን በበፍታ ገነዙት፡፡" የሚል መልእክት በዜማ ይደርሳል!
ከዚኽ ውጪ ምሕዛል ዘትንሣኤ ወይም «የፋሲካ አመላለስ» ያልነው [Paschal troparion] እና ቃለ ባሕ ዘትንሣኤ «የፋሲካ ሰላምታ» ያልነው [Paschal Greeting] ከወትሮው በተለየ መንገድ ይፈጸማል። ሁለቱም በልሳነ ጽር (ግሪክ) #ክሪስቶስ_አኔስቲ / Χριστὸς ἀνέστη እየተባለ ይጠራል።
① #ምሕዛል_ዘትንሣኤ [Paschal troparion] የፋሲካ አመላለስ
በእርግጥ ምሕዛል አልያም ምስትሕዛል የሚባለው በድጓው ሊቃውንቱ የሚያስተዛዝሉት ዜማ ድጋም ሲሆን መነሻውን ድጓ ያደረገው በቅዳሴው ክፍል የምናገኘው ይኽ የተዝካረ ትንሣኤ ምስትሕዛል
«ህየንተ ዝውእቱ ጊዜ ባርኮት እምትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ » በሚል የገባ ሦስት ጊዜ ደጋግመን በመቀባበል የምናደርሰው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ "
በሌሎች ምሥራቃውያን (Eastern ) እና ጽባሓውያን (Orientals) ዘንድም በእጅጉ የተለመደ ነው!
በግሪክ ፓስካል ትሮፓርዮን አልያም [χριστος ανεστη] የሚባል በዜማ የሚደርስና የዘመነ ሐዋርያት ጭምር ጥንታዊ መገለጫ አለው ተብሎ የሚታመን ነው።
Χριστὸς ἀνέστη ἐκ νεκρῶν,
θανάτῳ θάνατον πατήσας,
καὶ τοῖς ἐν τοῖς μνήμασι,
ζωὴν χαρισάμενος!
የንባባዊ ፍቺው አማርኛ ትየባ (transliteration) ደግሞ ይኽን ይመስላል!
ክርስቶስ አኔስቲ ኤክ ኔክሮኒ ፣ ታናቶ ታናቶን ፓቲሳስ፣ ኬቲስ ኤን ቲስ ሚ’መሲ፣ ዞይን ካሪዛሜኖስ
በትርጉሙም የእኛው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ " ካለው ጋር አቻ ፍቺ አለው።
Christ is risen from the dead, Trampling down death by death, And upon those in the tombs, Bestowing life!
② #ቃለ_ባሕ_ዘትንሣኤ [Paschal Greeting] «የፋሲካ ሰላምታ»
በሓ ወይም ባሕ የሚባለው የሰላምታ የቡራኬ ቃል ፍሥሓ ሰላም የሚለውን የሚገልጥ ነው!
በቤተክርስቲያናችን አበው መምህራንም ቅድመ ቃለ እግዚአብሔር ፣ ድኅረ ቃለ ቡራኬ ለ፶ው ዕለት ከምእመናን ጋር የሚለዋወጡት ሰላምታ ነው! ከዚያም አልፎ ምእመናንም ከምእመናን ጋር የትንሳኤውን የምሥራች ለማብሰርና መልካም ምኞት ለመግለጥ ያውሉታል።
አቀራረቡ በአመላለስ አገባብ የሚከወን ሲሆን ሰላምታ ሰጪና ሰላምታ ተቀባይ ይኽን ይለዋወጣሉ፤
በኢትዮጵያዊቷ የተዋህዶ ቅድስት ቤተክርስቲያናችም ከ6ኛው ምዕተ ዓመት አንስቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን መረጃዎች ይገልጣሉ። በቅዱስ ያሬድ ምዕራፍ (ዘመወድስ) ውስጥ በፍታሕ ሊተ ሥር በመሪና ተመሪ የሚቀርብ ዛሬ ለፋሲካ ሰላምታ የምንገለገልበት የትንሣኤው ምስክርነት ቃል አለ። እንዲህ ይላል ፦
☞ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ይኩን ሰላም!
በመቀባበል እንዲህ ተጽፏል
☞ Christ is risen from the dead!
☜ By the highest power and authority!
☞ He chained Satan!
☜ Freed Adam!
☞ Peace!
☜ Henceforth!
☞ Is!
☜ Joy and Peace!
☞ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን!
☜ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
☞ አሰሮ ለሰይጣን!
☜ አግዐዞ ለአዳም!
☞ ሰላም!
☜እምይእዜሰ!
☞ ኮነ!
☜ ፍስሐ ወሰላም!
ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው፤ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ!
በውጪው ግን ሰጥቶ መቀበል እንጂ አመላለስ የሌለው ባለ አጭር ይዘት ሆኖ በተለያየ ስያሜ የሚጠራ ነው The Paschal Greeting / the Easter Acclamation / The Paschal troparion / Christos anesti…
᳀͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͞ ͟͞ ̸ ͟͞ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ✙ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᯼᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᳀
(ለትንሣኤ የተቆነጠረ ሐሳብ)
ሀገርኛው የዘውትር ሰላምታችን ሰላም ላንተ ይኹን👋 ጠላትኽን ያውድቅ ቢሰኛኽን ያርቅ! 🙏 በሚል መነሻ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚታከልበት ምኞት መግለጫና ምስጋና ማቅረቢያ ነው!
የሰላምታው መንገድ ደግሞ በሦስት ሂደት (በቃል በእጅና በአንገት) የሚከወን ነው።
🤝
መጨባበጥ (ተራክቦተ እድ ፣ ፅብጠት፣ ተጻብሖ) ☞ በእጅ የሚፈጸም ፦ በመጨባበጥ [handshake] በመተቃቀፍ [hugging] አልያም በጉንጭ በመሳሳም [cheek kissing] ይፈጸም የነበረውን በቀደሙቱ ዘንድ “አምኃ ቅድሳት” [holy kiss & kiss of peace ⇨ ἐν ἁγίω φιλήματι, και φιλί της ειρήνης ] እየተባለ የሚጠራው መንገድ ነው!
በዚኽ አጋጣሚ በወቅቱ ጉዳይ መጨባበጥ መተቃቀፍና መሳሳም ለወረርሽቹ በፍጥነት መዛመት ምክንያት መሆናቸውን አውቀን #አካላዊ_ፈቀቅታ|ን በመጠበቅ በበሽታው የምናልፍ ሳንሆን በሽታውን የምናሳልፍ ነገንም የምናይ እንድንሆን በተከታዮቹ መንገዶች ሰላምታ የምንለዋወጥ ይሁን!
🙇
"እጅ መነሳሳት" (እማኄ) ☞ ባንገት፣ በወገብና በጕልበት የሚፈጸም ነው።
🙋
የሰላምታ ቃል መለዋወጥ (በቃለ ተአምኆ) ሰላምታ በንግግር በመለዋወጥ የሚፈጸም ዋናዎቹ ናቸው!
ወደተቆነጠረው ሐሳብ እንለፍ ተዝካረ ትንሣኤው በሚታሰብበት ዐባይ ፋሲካ ፶ ዕለት በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸም የተለየ ሰላምታና የዜማ ድጋም አመላለስ አለ።
የጌታችን ተዝካረ ትንሣኤ በቤተክርስቲያናችን ሰፊ ቦታና ትርጉም ያለው በመሆኑ የዓመት ሢሦው (⅓) ነገረ ፋሲካን የሚያስታውስ ነው (የፋሲካ ጾም ⁵⁵ እና ዘመነ ትንሣኤ⁵⁰)
በቅዳሴው መግቢያ መስዋእቱ ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጣ ከትንሳኤው እስከ በዓለ ፶ ጊዜው የተለየ መሆኑን ለማሳወቅ "እመቦ ብእሲ… " በሚለው መግቢያ ፈንታ "ሃሌ ሉያ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ በሰንዱናት ለዘተንሥአ እሙታን በመንክር ኪነ ⇨ ሃሌ ሉያ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ድንቅ በሚሆን ጥበብ ከሙታን ተለይቶ የተነሣ ኢየሱስን በበፍታ ገነዙት፡፡" የሚል መልእክት በዜማ ይደርሳል!
ከዚኽ ውጪ ምሕዛል ዘትንሣኤ ወይም «የፋሲካ አመላለስ» ያልነው [Paschal troparion] እና ቃለ ባሕ ዘትንሣኤ «የፋሲካ ሰላምታ» ያልነው [Paschal Greeting] ከወትሮው በተለየ መንገድ ይፈጸማል። ሁለቱም በልሳነ ጽር (ግሪክ) #ክሪስቶስ_አኔስቲ / Χριστὸς ἀνέστη እየተባለ ይጠራል።
① #ምሕዛል_ዘትንሣኤ [Paschal troparion] የፋሲካ አመላለስ
በእርግጥ ምሕዛል አልያም ምስትሕዛል የሚባለው በድጓው ሊቃውንቱ የሚያስተዛዝሉት ዜማ ድጋም ሲሆን መነሻውን ድጓ ያደረገው በቅዳሴው ክፍል የምናገኘው ይኽ የተዝካረ ትንሣኤ ምስትሕዛል
«ህየንተ ዝውእቱ ጊዜ ባርኮት እምትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ » በሚል የገባ ሦስት ጊዜ ደጋግመን በመቀባበል የምናደርሰው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ "
በሌሎች ምሥራቃውያን (Eastern ) እና ጽባሓውያን (Orientals) ዘንድም በእጅጉ የተለመደ ነው!
በግሪክ ፓስካል ትሮፓርዮን አልያም [χριστος ανεστη] የሚባል በዜማ የሚደርስና የዘመነ ሐዋርያት ጭምር ጥንታዊ መገለጫ አለው ተብሎ የሚታመን ነው።
Χριστὸς ἀνέστη ἐκ νεκρῶν,
θανάτῳ θάνατον πατήσας,
καὶ τοῖς ἐν τοῖς μνήμασι,
ζωὴν χαρισάμενος!
የንባባዊ ፍቺው አማርኛ ትየባ (transliteration) ደግሞ ይኽን ይመስላል!
ክርስቶስ አኔስቲ ኤክ ኔክሮኒ ፣ ታናቶ ታናቶን ፓቲሳስ፣ ኬቲስ ኤን ቲስ ሚ’መሲ፣ ዞይን ካሪዛሜኖስ
በትርጉሙም የእኛው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ " ካለው ጋር አቻ ፍቺ አለው።
Christ is risen from the dead, Trampling down death by death, And upon those in the tombs, Bestowing life!
② #ቃለ_ባሕ_ዘትንሣኤ [Paschal Greeting] «የፋሲካ ሰላምታ»
በሓ ወይም ባሕ የሚባለው የሰላምታ የቡራኬ ቃል ፍሥሓ ሰላም የሚለውን የሚገልጥ ነው!
በቤተክርስቲያናችን አበው መምህራንም ቅድመ ቃለ እግዚአብሔር ፣ ድኅረ ቃለ ቡራኬ ለ፶ው ዕለት ከምእመናን ጋር የሚለዋወጡት ሰላምታ ነው! ከዚያም አልፎ ምእመናንም ከምእመናን ጋር የትንሳኤውን የምሥራች ለማብሰርና መልካም ምኞት ለመግለጥ ያውሉታል።
አቀራረቡ በአመላለስ አገባብ የሚከወን ሲሆን ሰላምታ ሰጪና ሰላምታ ተቀባይ ይኽን ይለዋወጣሉ፤
በኢትዮጵያዊቷ የተዋህዶ ቅድስት ቤተክርስቲያናችም ከ6ኛው ምዕተ ዓመት አንስቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን መረጃዎች ይገልጣሉ። በቅዱስ ያሬድ ምዕራፍ (ዘመወድስ) ውስጥ በፍታሕ ሊተ ሥር በመሪና ተመሪ የሚቀርብ ዛሬ ለፋሲካ ሰላምታ የምንገለገልበት የትንሣኤው ምስክርነት ቃል አለ። እንዲህ ይላል ፦
☞ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ይኩን ሰላም!
በመቀባበል እንዲህ ተጽፏል
☞ Christ is risen from the dead!
☜ By the highest power and authority!
☞ He chained Satan!
☜ Freed Adam!
☞ Peace!
☜ Henceforth!
☞ Is!
☜ Joy and Peace!
☞ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን!
☜ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን!
☞ አሰሮ ለሰይጣን!
☜ አግዐዞ ለአዳም!
☞ ሰላም!
☜እምይእዜሰ!
☞ ኮነ!
☜ ፍስሐ ወሰላም!
ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው፤ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ!
በውጪው ግን ሰጥቶ መቀበል እንጂ አመላለስ የሌለው ባለ አጭር ይዘት ሆኖ በተለያየ ስያሜ የሚጠራ ነው The Paschal Greeting / the Easter Acclamation / The Paschal troparion / Christos anesti…
የበዙቱ የቀደመ መነሻውን ከግሪኩ ተውሰው ሰላምታውንም በሰጣዊ ተሰጣዊ (ሰጪና ተቀባይ) ቃል ልውውጥ ይከውኑታል እንዲህ ሲሉ
#ሰጣዊ ☞ ክሪስቶስ አኔስቲ Χριστός ἀνέστη! Christ is Risen! ✧ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
#ተሰጣዊ ☜ አሊቶስ አኔስቲ "Ἀληθῶς ἀνέστη! " - "Truly He is Risen!" or "He Has Risen Indeed!" ✧ (አሜን) በአማን ተንሥአ
በአረማይኩ ግን ጥቂት የተሰጣዊ ምላሽ ልዩነት ያለው ሆኖ ይነገራል
☞ ክሪስቶስ ሃሪያቭ ኢ ሜሬሎዝ Քրիստոս հարյա՜վ ի մեռելոց: Christ is risen! ክርስቶስ ተንስሥኣ እሙታን
☜ ኦርኺያል ኤ ኻሮውቲዮን ክሪስቶስ Օրհնյա՜լ է Հարությունը Քրիստոսի: Blessed is the resurrection of Christ!" ቡሩክ ትንሣኤሁ ለክርስቶስ
በሀገርኛ ልሣናት አገባቡ እንዲህ ሊገለጥ ይችላል
⇝ በአማርኛ (☞ ክርስቶስ ተነስቷል ፣ ☜ በእርግጥ ተነስቷል!)
⇝ ኦሮሚፋ /Oromiffa (☞ Kiristoos du'aa ka'eera ፣ ☜ Dhugumaan ka'eera)
⇝ በትግሪኛ (☞ ክርስቶስ ተንሢኡ፣ ☜ በኻቂ ተንሲኡ)
⇝ በጉራጊኛ (☞ ክርስቶስ ተረሳም ፣ ☜ በውረም ተረሳም)
.
.
.
⇨ (በሌሎችም ሀገርኛ ልሳናት የቻላችሁትን ጨምሩበት)
(ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ በማዕዶት ፳፻፲፪ ዓ.ም. ተጽፎ በማሻሻያ ለዛሬ በድጋሚ የተለጠፈ )
#ሰጣዊ ☞ ክሪስቶስ አኔስቲ Χριστός ἀνέστη! Christ is Risen! ✧ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
#ተሰጣዊ ☜ አሊቶስ አኔስቲ "Ἀληθῶς ἀνέστη! " - "Truly He is Risen!" or "He Has Risen Indeed!" ✧ (አሜን) በአማን ተንሥአ
በአረማይኩ ግን ጥቂት የተሰጣዊ ምላሽ ልዩነት ያለው ሆኖ ይነገራል
☞ ክሪስቶስ ሃሪያቭ ኢ ሜሬሎዝ Քրիստոս հարյա՜վ ի մեռելոց: Christ is risen! ክርስቶስ ተንስሥኣ እሙታን
☜ ኦርኺያል ኤ ኻሮውቲዮን ክሪስቶስ Օրհնյա՜լ է Հարությունը Քրիստոսի: Blessed is the resurrection of Christ!" ቡሩክ ትንሣኤሁ ለክርስቶስ
በሀገርኛ ልሣናት አገባቡ እንዲህ ሊገለጥ ይችላል
⇝ በአማርኛ (☞ ክርስቶስ ተነስቷል ፣ ☜ በእርግጥ ተነስቷል!)
⇝ ኦሮሚፋ /Oromiffa (☞ Kiristoos du'aa ka'eera ፣ ☜ Dhugumaan ka'eera)
⇝ በትግሪኛ (☞ ክርስቶስ ተንሢኡ፣ ☜ በኻቂ ተንሲኡ)
⇝ በጉራጊኛ (☞ ክርስቶስ ተረሳም ፣ ☜ በውረም ተረሳም)
.
.
.
⇨ (በሌሎችም ሀገርኛ ልሳናት የቻላችሁትን ጨምሩበት)
(ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ በማዕዶት ፳፻፲፪ ዓ.ም. ተጽፎ በማሻሻያ ለዛሬ በድጋሚ የተለጠፈ )
+++ ጣዖት ምንድን ነው? +++
[እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?]
«ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ)
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት ማለት ከዕንጨትና ከቀለጡ ማዕድናት የተሠራ፣ የማምለኪያ ምስል...» እያለ ይተረጒምና ምእመናን ከጣዖት መራቅ እንዳለባቸው ገልጦ «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» በማለት ደምድሞ አስቀምጦታል።
ይህች ዓለም ጣዖትን ያመለኩ በርካታ ነጋሽ እና አንጋሾችን አፍርታለች። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክም ይሁን በገድላትና በድርሳናት እንደምናነበው «ሃይማኖታችሁን ካዱ፥ ለጣዖት ስገዱ» በማለት እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ደጋግ አባቶችን ሲያሳርዱ የነበሩ ክፉ ጣዖታሞች ነበሩ። አሉ። ለወደፊቱም ይኖራሉ።
እነዚህ ልበ ደንዳኖች ምስል ቀርጸው፣ ጣዖት አቊመው፣ ዕጣን አጢሰው፣ ለምስሉ ሲሰግዱና ሲያሰግዱ በመኖራቸው እንደ ክፋታቸው መጠን በየጊዜው ዋጋቸውን አግኝተዋል። ለወደፊት እነሣለሁ የሚሉም ዋጋቸውን ያገኛሉ።
ጣዖት የምንለው የተቀረጸ ምስል ብቻ አይደለም። እግዚአብሔር የማይከብርበት ከንቱ ሥራ ሁሉ ጣዖት ነው። አንዲት ሴት መልክና ደም ግባቷን በመስታውት እያዬች ዘወትር የምትኮፈስ ከሆነ መልኳ ደምግባቷ ለእሷ ጣዖት ሆኖባታል። አንድ ሰው የዝሙት ልምድ ካለውና ያንን ክፉ ሥራ መልቀቅ ካልሻተ ዝሙቱ ጣዖት ነው። «ወዘመዉ በጣዖቶሙ» እንዲል (መዝ ፻፮፥፴፰)
ወዳጄ በየቤቱ ብዙ ጣዖት ያቆመ አለ። ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚበልጥበት ራሱ ያቋቋመው ቀኖና ጣዖት ሆኖበት የሚያስቸግረው ስንቱ ነው? ጫቱ፣ ሲጋራው፣ መጠጡ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው? ዝሙቱ፣ መዳራቱ፣ ውንብድናው፣ ፍቅረ ነዋዩ፣ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው?
ለዚህ አይደል ሐዋርያው «የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፩) ብሎ የዘጋው። ቅዱስ ጳውሎስ አድበስብሶ አላለፈም። ይልቊንም «ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፬) ሲል ቊርጥ ያለ ቃል አስቀምጧል። ወልደ ነጐድጓድ ዮሐንስም በመልእክቱ «ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።» ሲል ያስጠነቅቃል። (፩ኛ ዮሐ ፭፥፳፩)
ከዚህ አንጻር እግር ኳስ ጣዖት ነው አይደለም ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ ምን ያሕል ሞኝ መሆኑን እንመን። ወዳጄ አንተነትህን ለማያውቅህ ለአውሮጳ ኳስ ተጫዋች ጨርቅህን ጥለህ ስታብድለት እየዋልህ ጣዖትነቱን እንዴት ዘነጋኸው? በቴሌቪዥን ስክሪን አፍጥጠህ ስታይ እያመሸህና አጋንንት እንደተቆጣጠረው ድውይ ልብህ እስኪወልቅ ስትጮህ እያደርህ ጣዖት መሆኑ እንዴት ተረሳህ?
ልብ በል እንጅ! «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ [ባዕድ] ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» ተባልህ'ኮ። ደግሞስ የኳስ ጥቅሙ ምንድን ነው? የሚረባህንና የሚጠቅምህን ሳትይዝ ስለ አውሮጳ እግር ኳስ ልብህ እስኪወልቅ መደገፍ ምን ይሉታል?
አንተ ከድጋፍ (በሌላው ከመደ'ገፍ) ሳትወጣ የአውርጳን ኳስ ትደግፋለህ አይደል? አንተ ከሰው ጫንቃ ሳትወር የሌላው ደጋፊ መሆንህ አይገርምም? እስኪ ወደራሳችን እንመለስ? ሀገር እንዲህ በሰላም እጦት ተወጥራ ከኳስ ጋር ልናብድ ይገባል? መንፈሳውያን ነን የሚሉ ሰዎች ብሰው ሳይ አዝናለሁ።
«ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፫)
© ቀሲስ ጌትነት ዐይተነው (ክንፈ ገብርኤል)
ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም
[እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?]
«ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ)
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት ማለት ከዕንጨትና ከቀለጡ ማዕድናት የተሠራ፣ የማምለኪያ ምስል...» እያለ ይተረጒምና ምእመናን ከጣዖት መራቅ እንዳለባቸው ገልጦ «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» በማለት ደምድሞ አስቀምጦታል።
ይህች ዓለም ጣዖትን ያመለኩ በርካታ ነጋሽ እና አንጋሾችን አፍርታለች። በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክም ይሁን በገድላትና በድርሳናት እንደምናነበው «ሃይማኖታችሁን ካዱ፥ ለጣዖት ስገዱ» በማለት እግዚአብሔርን የሚያመልኩ ደጋግ አባቶችን ሲያሳርዱ የነበሩ ክፉ ጣዖታሞች ነበሩ። አሉ። ለወደፊቱም ይኖራሉ።
እነዚህ ልበ ደንዳኖች ምስል ቀርጸው፣ ጣዖት አቊመው፣ ዕጣን አጢሰው፣ ለምስሉ ሲሰግዱና ሲያሰግዱ በመኖራቸው እንደ ክፋታቸው መጠን በየጊዜው ዋጋቸውን አግኝተዋል። ለወደፊት እነሣለሁ የሚሉም ዋጋቸውን ያገኛሉ።
ጣዖት የምንለው የተቀረጸ ምስል ብቻ አይደለም። እግዚአብሔር የማይከብርበት ከንቱ ሥራ ሁሉ ጣዖት ነው። አንዲት ሴት መልክና ደም ግባቷን በመስታውት እያዬች ዘወትር የምትኮፈስ ከሆነ መልኳ ደምግባቷ ለእሷ ጣዖት ሆኖባታል። አንድ ሰው የዝሙት ልምድ ካለውና ያንን ክፉ ሥራ መልቀቅ ካልሻተ ዝሙቱ ጣዖት ነው። «ወዘመዉ በጣዖቶሙ» እንዲል (መዝ ፻፮፥፴፰)
ወዳጄ በየቤቱ ብዙ ጣዖት ያቆመ አለ። ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚበልጥበት ራሱ ያቋቋመው ቀኖና ጣዖት ሆኖበት የሚያስቸግረው ስንቱ ነው? ጫቱ፣ ሲጋራው፣ መጠጡ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው? ዝሙቱ፣ መዳራቱ፣ ውንብድናው፣ ፍቅረ ነዋዩ፣ ጣዖት የሆነበት ስንቱ ነው?
ለዚህ አይደል ሐዋርያው «የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፩) ብሎ የዘጋው። ቅዱስ ጳውሎስ አድበስብሶ አላለፈም። ይልቊንም «ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፲፬) ሲል ቊርጥ ያለ ቃል አስቀምጧል። ወልደ ነጐድጓድ ዮሐንስም በመልእክቱ «ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።» ሲል ያስጠነቅቃል። (፩ኛ ዮሐ ፭፥፳፩)
ከዚህ አንጻር እግር ኳስ ጣዖት ነው አይደለም ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ ምን ያሕል ሞኝ መሆኑን እንመን። ወዳጄ አንተነትህን ለማያውቅህ ለአውሮጳ ኳስ ተጫዋች ጨርቅህን ጥለህ ስታብድለት እየዋልህ ጣዖትነቱን እንዴት ዘነጋኸው? በቴሌቪዥን ስክሪን አፍጥጠህ ስታይ እያመሸህና አጋንንት እንደተቆጣጠረው ድውይ ልብህ እስኪወልቅ ስትጮህ እያደርህ ጣዖት መሆኑ እንዴት ተረሳህ?
ልብ በል እንጅ! «እግዚአብሔር ከሰጠን ውጭ ሌላ [ባዕድ] ነገር እንዲኖረን መመኘት ጣዖት ነው» ተባልህ'ኮ። ደግሞስ የኳስ ጥቅሙ ምንድን ነው? የሚረባህንና የሚጠቅምህን ሳትይዝ ስለ አውሮጳ እግር ኳስ ልብህ እስኪወልቅ መደገፍ ምን ይሉታል?
አንተ ከድጋፍ (በሌላው ከመደ'ገፍ) ሳትወጣ የአውርጳን ኳስ ትደግፋለህ አይደል? አንተ ከሰው ጫንቃ ሳትወር የሌላው ደጋፊ መሆንህ አይገርምም? እስኪ ወደራሳችን እንመለስ? ሀገር እንዲህ በሰላም እጦት ተወጥራ ከኳስ ጋር ልናብድ ይገባል? መንፈሳውያን ነን የሚሉ ሰዎች ብሰው ሳይ አዝናለሁ።
«ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።» (፩ኛ ቆሮ ፲፥፳፫)
© ቀሲስ ጌትነት ዐይተነው (ክንፈ ገብርኤል)
ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - 🇴🇷🇹🇭🇴🇩🇴🇽 🇹🇪🇼🇦🇭🇩🇴
+++ ጣዖት ምንድን ነው? +++ [እግር ኳስ ጣዖት ነው ወይስ አይደለም?] «ጣዖት» ለአንድ ነው። ለብዙ ሲሆን «ጣዖታት» ይሆናል። በዕብራውያን ቋንቋ «ጣዑት» ይሉታል። «ጣዖት» ማለት ስሕተት የሆነ ሥራ፣ በቊሙ ግልፎ፥ ስብኮ፣ የጥጃ፥ የእንቦሳ፥ የሰው፥ የእንስሳ ምስል፣ ስሑታን ሰዎች የሚያመልኩት ተብሎ ይተረጒማል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ሐዲስ) የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላትም «ጣዖት…
🎍🎍🎍
++ በሰንበት መፍረስ ++
የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?! እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡
ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡
ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ኝ የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡
እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!
ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
++ በሰንበት መፍረስ ++
የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?! እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡
ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡
ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ኝ የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡
እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!
ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
#መፆር_እምዕፀወ_ሊባኖስ (የሊባኖስ እንጨቶች ዙፋን ) ቅድስት ድንግል ማርያም!
በወንጌል "ዕፅ ሰናይ ፍሬ ሰናየ ይፈሪ" (ማቴ ፯፥፲፯) እንዳለው ከመልካም ዛፍ ቤተሰብ የተኘች ምግባረ መልካም ደምግባተ ቀና፣ የሊባኖሷ ብላቴና አማናዊት መፆር (ዙፋን) እግዝእትነ ማርያም ናት! እርሷ ፆረቶ በከርሳ ፣ፆረቶ ዲበ ዘባና ፆረቶ ዘኢይፀወር እያሉ ሊቃውንቱ የሚያወድሷት ለአምጻኤ ዓለማት መፆሩ ፣ ለመጋቤ ዓለማት አገሩ ፣ ለአኅላፌ ዓለማት መንበሩ ናት!
♧ በሰቆቃ ወድንግል "አብርሂ አብርሂ ናዝሬት ሀገሩ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መፆሩ። … ናዝሬት ሀገሩ አብሪ አብሪ ከዙፋኑ ማርያም ጋር ንጉስሽ ወዳንቺ ደርሷልና" ተብላለች፤
♧ በሰአታቱ ገነይነ ለኪ እና ኵሎሙ ዘእግዝእትነ ምስጋናው አፈ ሊቃውንት አባ ጊዮርጊስ
♢ "ሐዳስ መቅደስ መፆረ ንጉሥ። ወላዲቱ ለኢየሱስ።… አዲሲቷ መቅደስ የንጉስ ዙፋኑ ለኢየሱስ ወላዲቱ " ብሏታል፤
♢ "አንቲ ውእቱ ለንጉሠ ነገሥት መፆሩ ለአዳም ተድላ መንበሩ ብኪ ተመይጠ ኅበ ዘቀዳሚ ማኅደሩ።… ለነገሥታቱ ንጉሥ ዙፋኑ ፣ ለአዳም ወደቀደመ ማደሪያው መመለሻ የደስታው ማረፊያ አንቺ ነሽ" ሲል ይገልጣታል፤
♧ የተአምረ ማርያማችን መቅድም "አልቦ ዘፆረ እሳተ ወአልቦ ዘኢገብረ ኅጢአተ እንበለ እግዝእትነ ማርያም። … ከእመቤታችን በቀር ኀጢአትን ያልሠራ ለእሳት ዙፋን የሆነ የለም " ይለናል
♧ ውዳሴ ማርያም ከአንቀጸ ብርሃንና ከቅዳሴው ጋር በምስጢር እየተሳሰረ "ማዕጠንት ዘወርቅ እንተ ፆርኪ ፍሕመ እሳት … የእሳተ መለኮት ዙፋን የወርቅ ማዕጠንት" ይላታል።
♧ የመልክአ ቁርባን ምስጋናም "ናዛዝትነ እምኃዘን ወኃይለ ውርዙትነ እምርስዓን በማኅፀንኪ ተፀውረ ብሉየ መዋዕል ሕፃን።… ከሃዘን የምታረጋጋ መጽናኛችነን፣ ከድካም የምታበረታን የወጣትነት ኃይላችን ፣ ዘመኑ ጥንት የሆነው ሕፃን ማኅፀንሽን ዙፋን አድርጎ አደረ" እንላታለን።
#መፆረ_ገብረ_ለርእሱ (ለራሱ ዙፋን ሰራ)
ይህንን በመሰለው ምሥጢር ውስጥ የተገለጡ ሁለት ፍሬ ነገሮችን እንመርምር
፩ ለራሱ ዙፋኑን የሠራት ራሱ ነው!
ይችን ወላዲተ ቃል መሠረተ ንጽሕ ድንግል
በዚህም በአባት ዘር ከሚመጣ ቁራኝነት በእናት ደም ከሚያርፍ የመርገም ጽነት ለይቶ እኩያት ፍትወታት ኀጣውእ ሳይደርሱባት ራሱ ሠራት ቅዱስ ያሬድ "ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ፀዓዳ … ማርያምስ በአዳም ገላ ውስጥ እንደ ነጭ እንቁ ታበራ ነበር " እንዳላት
ቅድስናዋ የመመረጥ አንድም እንድትመረጥ ሆና በተገባ ለመገኘት ጽናት ያለበት ነውና! ሊቁ "አቀባ መንፈስ ቅዱስ እምከርሰ እማ" ያለውን እንዲህ አብራርቶታል "የበጎ ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ የሚሆን እግዚአብሔር ብዙ ስጦታ ከብዞች መናፍስት የሚቀዳ አይደለም ካንድ መንፈስ ነው እንጂ የክፉ ዕድል ፈንታ ግን የሚገኝ ከሰይጣን ነው፡ እንዳትበድል ድንግልን ከናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ እንዳትረክስም ያነጻት ለወልድ ዋህድም ማደሪያ ያደረጋት እርሱ ነው፡፡ አብ ወደዳት ወልድ ከርሷ ሥጋ ለበሰ መንፈስ ቅዱስ ጋረዳት፡፡ "
፪ ራሱ የሠራት ለራሱ ዙፋንነት ነው!
ይኽችን የንጉሥ ዙፋን የአብ ሙሽራ (መርዓቱ) ፣ የወልድ እናት (ወላዲቱ)፣ የመንፈስ ቅዱስ እልፍኝ (ጽርሐ ቤቱ) ከሰማይ ከወረደ ቃል በቀር ሌላ አድሮባል እንዳያሰኝ "ወትረ ድንግል ማርያም" ብለን እንድናምን እና ድንግሊቱ "ብቻ መውለድን ቀምሶ አቀመሰኝ" እንዳለች ከእርሱ ውጪ ሌላ ልጅ እንደሌላት "እምድኅረ ወለደት ኪያሁ ነበረት በድንግልና" ብለን እንድንመሰክር ዙፋኑን ለራሱ ሠራ ይላል።
ሁለቱ የሊባኖስ እፀው ቅድስት ሀናና ቅዱስ ኢያቄም መሰላቸውን ሳይተኩ በመቆየታቸው ያዘኑት ሐዘን ማንም የማይተካትን የዓለም ሁሉ መክበሪያ አስገኘ! ይህስ ሐዘን የፍጥረት ሁሉ ሐዘን ነበር ዳግሚት ሰማይ ዳግሚት ምድር በመውለድ ደስታቸውን ወደ መካፈል አሳደጉን ከዚቁ ይህን ብለን የዛሬውን በዛሬ እንቋጭ፦
" አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ
ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ
ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ
ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ
ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ
ምስራቀ ምስራቃት ሙፃዕ ፀሐይ
እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ "
አረጋውያኑ ― በእጅጉ ቢያለቅሱ፣
በደል በምታርቅ ― በሴት ልጅ ተካሱ፤
ለወንጌልም ልጆች ― መሸሻቸው ካለም ፣
ሰማይን ወለዱ ― ሃናና ኢያቄም ፣
ሰማይዋም (ሰማዯም) ፀሐይን ― አውጥታለች ለዓለም፤
የምሥራቃት ምሥራቅ ― መውጫዋ ለፀሐይ ፣
የፍጥረት እመቤት ― የመናዋ ሙዳይ ፣
ዛሬ ተወለደች ― ዳግማዊቷ ሰማይ ።
⊙✧⇥ ይቆየን !
ከቴዎድሮስ በለጠ ( ክፍለሥላሴ)
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓፦ ግንቦት ፩ ቀን ፳፻፲ ዓ·ም ከደብረ እንቊ ልደታ ለማርያም
በወንጌል "ዕፅ ሰናይ ፍሬ ሰናየ ይፈሪ" (ማቴ ፯፥፲፯) እንዳለው ከመልካም ዛፍ ቤተሰብ የተኘች ምግባረ መልካም ደምግባተ ቀና፣ የሊባኖሷ ብላቴና አማናዊት መፆር (ዙፋን) እግዝእትነ ማርያም ናት! እርሷ ፆረቶ በከርሳ ፣ፆረቶ ዲበ ዘባና ፆረቶ ዘኢይፀወር እያሉ ሊቃውንቱ የሚያወድሷት ለአምጻኤ ዓለማት መፆሩ ፣ ለመጋቤ ዓለማት አገሩ ፣ ለአኅላፌ ዓለማት መንበሩ ናት!
♧ በሰቆቃ ወድንግል "አብርሂ አብርሂ ናዝሬት ሀገሩ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መፆሩ። … ናዝሬት ሀገሩ አብሪ አብሪ ከዙፋኑ ማርያም ጋር ንጉስሽ ወዳንቺ ደርሷልና" ተብላለች፤
♧ በሰአታቱ ገነይነ ለኪ እና ኵሎሙ ዘእግዝእትነ ምስጋናው አፈ ሊቃውንት አባ ጊዮርጊስ
♢ "ሐዳስ መቅደስ መፆረ ንጉሥ። ወላዲቱ ለኢየሱስ።… አዲሲቷ መቅደስ የንጉስ ዙፋኑ ለኢየሱስ ወላዲቱ " ብሏታል፤
♢ "አንቲ ውእቱ ለንጉሠ ነገሥት መፆሩ ለአዳም ተድላ መንበሩ ብኪ ተመይጠ ኅበ ዘቀዳሚ ማኅደሩ።… ለነገሥታቱ ንጉሥ ዙፋኑ ፣ ለአዳም ወደቀደመ ማደሪያው መመለሻ የደስታው ማረፊያ አንቺ ነሽ" ሲል ይገልጣታል፤
♧ የተአምረ ማርያማችን መቅድም "አልቦ ዘፆረ እሳተ ወአልቦ ዘኢገብረ ኅጢአተ እንበለ እግዝእትነ ማርያም። … ከእመቤታችን በቀር ኀጢአትን ያልሠራ ለእሳት ዙፋን የሆነ የለም " ይለናል
♧ ውዳሴ ማርያም ከአንቀጸ ብርሃንና ከቅዳሴው ጋር በምስጢር እየተሳሰረ "ማዕጠንት ዘወርቅ እንተ ፆርኪ ፍሕመ እሳት … የእሳተ መለኮት ዙፋን የወርቅ ማዕጠንት" ይላታል።
♧ የመልክአ ቁርባን ምስጋናም "ናዛዝትነ እምኃዘን ወኃይለ ውርዙትነ እምርስዓን በማኅፀንኪ ተፀውረ ብሉየ መዋዕል ሕፃን።… ከሃዘን የምታረጋጋ መጽናኛችነን፣ ከድካም የምታበረታን የወጣትነት ኃይላችን ፣ ዘመኑ ጥንት የሆነው ሕፃን ማኅፀንሽን ዙፋን አድርጎ አደረ" እንላታለን።
#መፆረ_ገብረ_ለርእሱ (ለራሱ ዙፋን ሰራ)
ይህንን በመሰለው ምሥጢር ውስጥ የተገለጡ ሁለት ፍሬ ነገሮችን እንመርምር
፩ ለራሱ ዙፋኑን የሠራት ራሱ ነው!
ይችን ወላዲተ ቃል መሠረተ ንጽሕ ድንግል
በዚህም በአባት ዘር ከሚመጣ ቁራኝነት በእናት ደም ከሚያርፍ የመርገም ጽነት ለይቶ እኩያት ፍትወታት ኀጣውእ ሳይደርሱባት ራሱ ሠራት ቅዱስ ያሬድ "ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ፀዓዳ … ማርያምስ በአዳም ገላ ውስጥ እንደ ነጭ እንቁ ታበራ ነበር " እንዳላት
ቅድስናዋ የመመረጥ አንድም እንድትመረጥ ሆና በተገባ ለመገኘት ጽናት ያለበት ነውና! ሊቁ "አቀባ መንፈስ ቅዱስ እምከርሰ እማ" ያለውን እንዲህ አብራርቶታል "የበጎ ዕድል ፈንታ ጽዋ ተርታ የሚሆን እግዚአብሔር ብዙ ስጦታ ከብዞች መናፍስት የሚቀዳ አይደለም ካንድ መንፈስ ነው እንጂ የክፉ ዕድል ፈንታ ግን የሚገኝ ከሰይጣን ነው፡ እንዳትበድል ድንግልን ከናቷ ሆድ ጀምሮ የጠበቃት መንፈስ ቅዱስ እንዳትረክስም ያነጻት ለወልድ ዋህድም ማደሪያ ያደረጋት እርሱ ነው፡፡ አብ ወደዳት ወልድ ከርሷ ሥጋ ለበሰ መንፈስ ቅዱስ ጋረዳት፡፡ "
፪ ራሱ የሠራት ለራሱ ዙፋንነት ነው!
ይኽችን የንጉሥ ዙፋን የአብ ሙሽራ (መርዓቱ) ፣ የወልድ እናት (ወላዲቱ)፣ የመንፈስ ቅዱስ እልፍኝ (ጽርሐ ቤቱ) ከሰማይ ከወረደ ቃል በቀር ሌላ አድሮባል እንዳያሰኝ "ወትረ ድንግል ማርያም" ብለን እንድናምን እና ድንግሊቱ "ብቻ መውለድን ቀምሶ አቀመሰኝ" እንዳለች ከእርሱ ውጪ ሌላ ልጅ እንደሌላት "እምድኅረ ወለደት ኪያሁ ነበረት በድንግልና" ብለን እንድንመሰክር ዙፋኑን ለራሱ ሠራ ይላል።
ሁለቱ የሊባኖስ እፀው ቅድስት ሀናና ቅዱስ ኢያቄም መሰላቸውን ሳይተኩ በመቆየታቸው ያዘኑት ሐዘን ማንም የማይተካትን የዓለም ሁሉ መክበሪያ አስገኘ! ይህስ ሐዘን የፍጥረት ሁሉ ሐዘን ነበር ዳግሚት ሰማይ ዳግሚት ምድር በመውለድ ደስታቸውን ወደ መካፈል አሳደጉን ከዚቁ ይህን ብለን የዛሬውን በዛሬ እንቋጭ፦
" አዕሩግ አመ በከዩ ብካየ
ረከቡ ወለተ ዘታሥተሰሪ ጌጋየ
ለወንጌላውያን ኩልነ ዘኮነተነ ምጉያየ
ኢያቄም ወሀና ወለዱ ሰማየ
ሰማዮሙኒ አሥረቀት ፀሐየ
ምስራቀ ምስራቃት ሙፃዕ ፀሐይ
እግዝእትየ ዘመና ሙዳይ
ተወልደት ዮም ዳግሚት ሰማይ "
አረጋውያኑ ― በእጅጉ ቢያለቅሱ፣
በደል በምታርቅ ― በሴት ልጅ ተካሱ፤
ለወንጌልም ልጆች ― መሸሻቸው ካለም ፣
ሰማይን ወለዱ ― ሃናና ኢያቄም ፣
ሰማይዋም (ሰማዯም) ፀሐይን ― አውጥታለች ለዓለም፤
የምሥራቃት ምሥራቅ ― መውጫዋ ለፀሐይ ፣
የፍጥረት እመቤት ― የመናዋ ሙዳይ ፣
ዛሬ ተወለደች ― ዳግማዊቷ ሰማይ ።
⊙✧⇥ ይቆየን !
ከቴዎድሮስ በለጠ ( ክፍለሥላሴ)
Яερ๑รтεδ ƒя๑๓፦ ግንቦት ፩ ቀን ፳፻፲ ዓ·ም ከደብረ እንቊ ልደታ ለማርያም
«ተውኔተ ጵጵስና ☞ የጵጵስና ጨዋታ»
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
የኩላዊት ቤተክርስቲያናችንን ትውፊት [παραδοσις] ትምህርት [διδασκαλια] እና እምነት [πιστις] ከመነሻው ስንመለከት በክርስቶስ የተሠጠ በሐዋርያት የተሰበከና በአበው የተጠበቀ መንገድ ነው። በዚህም ቤተክርስቲያን ተመሠረተች!【ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ】
በቀደመው ዘመንማ የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው!
በክርስትና ማኅተም ያልከበርክ
እንዴት ለጵጵስና ተመረጥክ? 【አባ ጊዮርጊስ】
ዛሬ ግንቦት ፯ ቀን በሃይማኖት የተዋቀረ ፦ የማይናወጥ መሠረት፣ የማይፈርስ ግድግዳ ፣ የማያዘነብል ምሰሶ የተባለ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፳ኛው የኢትዮጵያና የግብፅ ፓትርያርክ በ፬፻፸፬ ዓ.ም. ከሥጋ ድካም ያረፈበትን ቀን ቤተክርስቲያናችን ትዘክራለች። ይህ የምሥጢር ምንጭ የጉባኤ ኒቅያ አፈ ጉባኤ ደገኛው መምህር ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ለ፵፯ ዓመት በፕትርክና ሲቆይ ሢሦውን 【፲፭ ዓመት】በስደት ነበር ያሳለፈው።
ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን ጳጳስ ቅዱስ ፍሬምናጦስን【አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን】የሾመልን ባለውለታችንና በመንበረ ማርቆስ የተቀመጠ ፳ኛው ፓትርያርካችን ነው። («ወማርቆስ ወንጌላዊ ‘ወኮነ ሰባኬ ወመጥምቀ ወሠያሜ ካህናት’ በእስክንድርያ ወግብፅ ወኖባ ወምድረ ኢትዮጵያ እስከ ጽንፋ» እንዲል መጽሐፈ ግጽው ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፩ )
ቅዱስ አትናቴዎስ ወደ ክርስትናው የመጣበትና ለጵጵስና የበቃበት መንገድ እጅጉን የሚደንቅና አስተማሪ ነው። ስንክሳራችን በቀደመ ሕይወቱ ከአረማውያን ቤተሰብ የተገኘ አረማዊ እንደነበርና ለመጠራቱ ምክንያት ስለሆነች «የጵጵስና ጨዋታ» እንዲህ እያለ ይነግረናል
ውእቱ ይነብር ምስለ ሕፃናት እለ ይትሜህሩ ኀበ መምህር ርእዮሙ ለእሙንቱ ውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይገብሩ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወይትዋነዩ በበይናቲሆሙ ወይረስዩ እምኔሆሙ ዲያቆናተ ወኤጲስ ቆጶሳተ አደሞ ተላህዮቶሙ። ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ወይቤሎሙ ውእቱ አነ እከውን ክርስቲያናዌ ወተፈሥሑ ቦቱ።
【 እርሱም ከመምህር ከሚማሩ ሕፃናት ጋራ እያለ እርስ በርሳቸው በመጫወት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ ከእነርሱ ውስጥ ዲያቆናትን ኤጲስ ቆጶሳትንም ሲያደርጉ እሊያን የክርስቲ ያንን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእሳቸው ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት እርሱም ክርስቲያን እሆናለሁ አላቸው እነርሱም ደስ ተሰኙበት።】
ወነሥእዎ አሜሃ ወረሰይዎ አምሳለ ሊቀ ጳጳሳት ወመትሕቲሁ አምሳለ መንበር። ወእኀዙ ይስግዱ ሎቱ ወበውእቱ ጊዜ ኀለፈ አባ እለእስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት። ወሶበ ርእዮሙ ለውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይትዋነዩ ይቤሎሙ ለእለ ሀለዉ ምስሌሁ ወለዎ ለዝንቱ ሕፃን ይሠየም ሢመተ ክብርተ ወልዕልተ።
【ያን ጊዜም ወስደው በሊቀ ጳጳሳት አምሳል አደረጉት ከበታቹም ወንበር አድርገው ይሰግዱለት ጀመር። በዚያን ጊዜም ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ በዚያ አለፈ የክርስቲያን ልጆች ሲጫወቱ በአያቸው ጊዜ አብረውት ላሉ ይህ ሕፃን ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች ሹመትን ይሾም ዘንድ አለው አላቸው።】
ወንድማለም እንግዲህ ስማ መሾም ስለምትፈልግ ብቻ አትሾምም! እንኳን ሢመቱ ጭውውቱም ቢሆን ሥርዓት አለው። እንዳየኸው ጥንቱን የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው! መጽሐፉም ቢሆን እንኳን ራስህን በቦታው ልታስቀምጥ በቦታው ተቀመጥ እንኳ ቢሉህ እምቢኝ በል ነው የሚል።
【"ኢመፍትው ለመኑሂ እምሰብእ ይምሥጥ ሢመተ ክህነት ለርእሱ አላ ለእመ ተውህበ እምእግዚአብሔር ☞ #የክህነትን_ሹመት ከእግዚአብሔር ካልተሠጠው በቀር ከሰው ወገን ማንም ለራሱ ይገባኛል ብሎ ቀምቶ እጅ አያድርጋት" መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ ፩፥፷፩】
ዛሬ የሕጻናቱን ያኽል ድፍረት አጥተን መሰል እምነት የሌለው ኢጥሙቅ ልብሰ ጵጵስና ለብሶ ሲተውን አይተን ዝም ከማለት አለፍንና በበር ያልገቡ «መስኮተኞች» አይደለም ጵጵስናው ፕትርክናውም ሳይቀር ይገባናል ሲሉ እየሰማን «ሃይ–ባይ» አለመገኘቱ በእጅጉ ያሳዝናል። «ኧረ ተዉ» የሚል መገስጽ ብቅ ሲል ተቆጪውን መቆጣት ከመንገድ ማጥፋት ሥራችን ሆኖ አረፍነው።
ኧረ ጉድ የዚያ ዘመን የእስክንድርያ ሕጻናት እንዴት አድርገው እንደሚበልጡን እዩልኝማ
«ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ☞ #እሊያን_የክርስቲያን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእነርሱ ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት »
እንዲህ ያለውን ጨዋታ ወዳጅ ፡ አልፎ ሂያጅ «ና ግባና ጰጵስ» ለሚሉ ድንበር አፍራሾች እንዲህ ባለው የሌባ መንገድ እንዳልመጣ የምናውቀው ራሱ ቅዱስ አትናቴዎስ በድርሳኑ "ንሕነሰ ኢንኌልቆ ምስለ ክርስቲያን አላ ምስለ አረሚ ወዐላውያን ☞ እኛ ግን እንዲህ ያለውን ከማያምኑና ከሚያምጹት እንጂ ከክርስቲያን ወገን እንኳ አንቆጥረውም!” እያለ ይዘልፋል 【ሃይ አበው ፳፱፥፲፭】
አባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታና የእግዚአብሔር ምርጫ የሆነውን ሹመት በራሱ ጳጳስ ነኝ ይገባኛል ለሚል ንሥጥሮሳዊ በላከው ተግሳጽ ይህን ይላል ፦
እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ?
ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና
እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ?
ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ
【በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ፡ በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ ?】
【መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፮】
«ወአንተሰ ተመሰልከ ተክለ ዘእንበለ ፍሬ: ወዖመ ዘእንበለ ቈጽል: ፈለገ ዘእንበለ ውሒዝ : ወዐዘቅተ ዘእንበለ ማይ፡ ንጉሠ ዘእንበለ ጌራ መንግሥት : ሐራዌ ዘእንበለ ንዋየ ሐቅል : ደመና ዘእንበለ ዝናም : ወሰዊተ ዘእንበለ መስበልት : አበ ዘእንበለ ሀብተ ሲሳይ : ወእመ ዘእንበለ አጥባት : ንድቀ ዘእንበለ ተድባብ : ወኆኅተ ዘእንበለ ማዕፆ : መርዓዌ ዘእንበለ አክሊል : ወመርዓተ ዘእንበለ ባዝግና : ካህነ ዘእንበለ ኤፉድ : ምሥዋዐ ዘእንበለ ቊርባን : ኖትያዌ ዘእንበለ ሥርዐተ ሐመር : ወምሥያጣዌ ዘእንበለ ንዋይ : ሠረገላዌ ዘእንበለ ድርዐ ሐጺን : ወፈረሳዌ ዘእንበለ ኲያንው! እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ? ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና ፣ እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ? ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ »
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥
የኩላዊት ቤተክርስቲያናችንን ትውፊት [παραδοσις] ትምህርት [διδασκαλια] እና እምነት [πιστις] ከመነሻው ስንመለከት በክርስቶስ የተሠጠ በሐዋርያት የተሰበከና በአበው የተጠበቀ መንገድ ነው። በዚህም ቤተክርስቲያን ተመሠረተች!【ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ】
በቀደመው ዘመንማ የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው!
በክርስትና ማኅተም ያልከበርክ
እንዴት ለጵጵስና ተመረጥክ? 【አባ ጊዮርጊስ】
ዛሬ ግንቦት ፯ ቀን በሃይማኖት የተዋቀረ ፦ የማይናወጥ መሠረት፣ የማይፈርስ ግድግዳ ፣ የማያዘነብል ምሰሶ የተባለ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፳ኛው የኢትዮጵያና የግብፅ ፓትርያርክ በ፬፻፸፬ ዓ.ም. ከሥጋ ድካም ያረፈበትን ቀን ቤተክርስቲያናችን ትዘክራለች። ይህ የምሥጢር ምንጭ የጉባኤ ኒቅያ አፈ ጉባኤ ደገኛው መምህር ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ለ፵፯ ዓመት በፕትርክና ሲቆይ ሢሦውን 【፲፭ ዓመት】በስደት ነበር ያሳለፈው።
ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን ጳጳስ ቅዱስ ፍሬምናጦስን【አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃንን】የሾመልን ባለውለታችንና በመንበረ ማርቆስ የተቀመጠ ፳ኛው ፓትርያርካችን ነው። («ወማርቆስ ወንጌላዊ ‘ወኮነ ሰባኬ ወመጥምቀ ወሠያሜ ካህናት’ በእስክንድርያ ወግብፅ ወኖባ ወምድረ ኢትዮጵያ እስከ ጽንፋ» እንዲል መጽሐፈ ግጽው ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፩ )
ቅዱስ አትናቴዎስ ወደ ክርስትናው የመጣበትና ለጵጵስና የበቃበት መንገድ እጅጉን የሚደንቅና አስተማሪ ነው። ስንክሳራችን በቀደመ ሕይወቱ ከአረማውያን ቤተሰብ የተገኘ አረማዊ እንደነበርና ለመጠራቱ ምክንያት ስለሆነች «የጵጵስና ጨዋታ» እንዲህ እያለ ይነግረናል
ውእቱ ይነብር ምስለ ሕፃናት እለ ይትሜህሩ ኀበ መምህር ርእዮሙ ለእሙንቱ ውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይገብሩ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወይትዋነዩ በበይናቲሆሙ ወይረስዩ እምኔሆሙ ዲያቆናተ ወኤጲስ ቆጶሳተ አደሞ ተላህዮቶሙ። ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ወይቤሎሙ ውእቱ አነ እከውን ክርስቲያናዌ ወተፈሥሑ ቦቱ።
【 እርሱም ከመምህር ከሚማሩ ሕፃናት ጋራ እያለ እርስ በርሳቸው በመጫወት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ ከእነርሱ ውስጥ ዲያቆናትን ኤጲስ ቆጶሳትንም ሲያደርጉ እሊያን የክርስቲ ያንን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእሳቸው ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት እርሱም ክርስቲያን እሆናለሁ አላቸው እነርሱም ደስ ተሰኙበት።】
ወነሥእዎ አሜሃ ወረሰይዎ አምሳለ ሊቀ ጳጳሳት ወመትሕቲሁ አምሳለ መንበር። ወእኀዙ ይስግዱ ሎቱ ወበውእቱ ጊዜ ኀለፈ አባ እለእስክንድሮስ ሊቀ ጳጳሳት። ወሶበ ርእዮሙ ለውሉደ ክርስቲያን እንዘ ይትዋነዩ ይቤሎሙ ለእለ ሀለዉ ምስሌሁ ወለዎ ለዝንቱ ሕፃን ይሠየም ሢመተ ክብርተ ወልዕልተ።
【ያን ጊዜም ወስደው በሊቀ ጳጳሳት አምሳል አደረጉት ከበታቹም ወንበር አድርገው ይሰግዱለት ጀመር። በዚያን ጊዜም ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስ በዚያ አለፈ የክርስቲያን ልጆች ሲጫወቱ በአያቸው ጊዜ አብረውት ላሉ ይህ ሕፃን ከፍ ከፍ ያለችና የከበረች ሹመትን ይሾም ዘንድ አለው አላቸው።】
ወንድማለም እንግዲህ ስማ መሾም ስለምትፈልግ ብቻ አትሾምም! እንኳን ሢመቱ ጭውውቱም ቢሆን ሥርዓት አለው። እንዳየኸው ጥንቱን የገሃዱ ሢመት ቀርቶ የሕጻናቱ ተውኔት እንኳ ደርዝ ነበረው! መጽሐፉም ቢሆን እንኳን ራስህን በቦታው ልታስቀምጥ በቦታው ተቀመጥ እንኳ ቢሉህ እምቢኝ በል ነው የሚል።
【"ኢመፍትው ለመኑሂ እምሰብእ ይምሥጥ ሢመተ ክህነት ለርእሱ አላ ለእመ ተውህበ እምእግዚአብሔር ☞ #የክህነትን_ሹመት ከእግዚአብሔር ካልተሠጠው በቀር ከሰው ወገን ማንም ለራሱ ይገባኛል ብሎ ቀምቶ እጅ አያድርጋት" መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ ፩፥፷፩】
ዛሬ የሕጻናቱን ያኽል ድፍረት አጥተን መሰል እምነት የሌለው ኢጥሙቅ ልብሰ ጵጵስና ለብሶ ሲተውን አይተን ዝም ከማለት አለፍንና በበር ያልገቡ «መስኮተኞች» አይደለም ጵጵስናው ፕትርክናውም ሳይቀር ይገባናል ሲሉ እየሰማን «ሃይ–ባይ» አለመገኘቱ በእጅጉ ያሳዝናል። «ኧረ ተዉ» የሚል መገስጽ ብቅ ሲል ተቆጪውን መቆጣት ከመንገድ ማጥፋት ሥራችን ሆኖ አረፍነው።
ኧረ ጉድ የዚያ ዘመን የእስክንድርያ ሕጻናት እንዴት አድርገው እንደሚበልጡን እዩልኝማ
«ሰአሎሙ ዝንቱ አብ ለውሉደ ክርስቲያን ከመ ይሳተፍ ምስሌሆሙ በተላህዮቶሙ። ወከልእዎ ወይቤልዎ እስመ አንተ አረማዊ ኢንዴመር ምስሌከ ☞ #እሊያን_የክርስቲያን ልጆች አይቶ ጨዋታቸው ደስ ስለአለው ከእነርሱ ጋራ በጨዋታቸው አንድ ይሆን ዘንድ የክርስቲያንን ልጆች ለመናቸው። እነርሱም አንተ አረማዊ ነህና ከእኛ ጋራ አትደመርም ብለው ከለከሉት »
እንዲህ ያለውን ጨዋታ ወዳጅ ፡ አልፎ ሂያጅ «ና ግባና ጰጵስ» ለሚሉ ድንበር አፍራሾች እንዲህ ባለው የሌባ መንገድ እንዳልመጣ የምናውቀው ራሱ ቅዱስ አትናቴዎስ በድርሳኑ "ንሕነሰ ኢንኌልቆ ምስለ ክርስቲያን አላ ምስለ አረሚ ወዐላውያን ☞ እኛ ግን እንዲህ ያለውን ከማያምኑና ከሚያምጹት እንጂ ከክርስቲያን ወገን እንኳ አንቆጥረውም!” እያለ ይዘልፋል 【ሃይ አበው ፳፱፥፲፭】
አባ ጊዮርጊስ የመንፈስ ቅዱስ ሥጦታና የእግዚአብሔር ምርጫ የሆነውን ሹመት በራሱ ጳጳስ ነኝ ይገባኛል ለሚል ንሥጥሮሳዊ በላከው ተግሳጽ ይህን ይላል ፦
እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ?
ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና
እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ?
ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ
【በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ፡ በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ ?】
【መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፮】
«ወአንተሰ ተመሰልከ ተክለ ዘእንበለ ፍሬ: ወዖመ ዘእንበለ ቈጽል: ፈለገ ዘእንበለ ውሒዝ : ወዐዘቅተ ዘእንበለ ማይ፡ ንጉሠ ዘእንበለ ጌራ መንግሥት : ሐራዌ ዘእንበለ ንዋየ ሐቅል : ደመና ዘእንበለ ዝናም : ወሰዊተ ዘእንበለ መስበልት : አበ ዘእንበለ ሀብተ ሲሳይ : ወእመ ዘእንበለ አጥባት : ንድቀ ዘእንበለ ተድባብ : ወኆኅተ ዘእንበለ ማዕፆ : መርዓዌ ዘእንበለ አክሊል : ወመርዓተ ዘእንበለ ባዝግና : ካህነ ዘእንበለ ኤፉድ : ምሥዋዐ ዘእንበለ ቊርባን : ኖትያዌ ዘእንበለ ሥርዐተ ሐመር : ወምሥያጣዌ ዘእንበለ ንዋይ : ሠረገላዌ ዘእንበለ ድርዐ ሐጺን : ወፈረሳዌ ዘእንበለ ኲያንው! እፎ ተኀረይከ ለጵጵስና ? ዘኢተቀደስከ በማኅተመ ክርስትና ፣ እፎ ተኀረይከ ለተክህኖ ? ዘኢተሠርጎከ በተአምኖ »
☞ አንተ ግን ፍሬ በሌለው ተክል ፣ ቅጠል በሌለውም ዛፍ ፣ ፈሳሽ በሌለው ወንዝ ፣ ውኃ በሌለው ጉድጓድ ፣ የመንግሥት ዘውድ በሌለው ንጉሥ ፣ የጦር መሣሪያ በሌለው ወታደር ፣ ዝናም በሌለው ደመና ፣ ፍሬ በሌለው እሸት ፣ ለምግብ የሚሆን ሀብት በሌለው አባት ፣ ጡቶች በሌላት እናት ፣ ጣሪያ በሌለው ሕንፃ፡ መዝጊያ በሌለው ደጃፍ፡ አክሊል ባልደፋ ሙሽራ ፣ ጌጥ በሌላት ሙሽሪት፣ ልብሰ ተክህኖ በሌለው ካህን ፣ ቁርባን በሌለው መሠዊያ ፣ የመርከብ ሥርዓት በማያውቅ ዋናተኛ ፣ ገንዘብ በሌለው ገበያተኛ ፣ የብረት ጥሩር በሌለው ባለሠረገላ፣ ጦሮች በሌሉት ፈረሰኛ ትመሰላለህ ! በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ? በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ?
Let us look from the beginning at that very tradition, teaching, and faith of the «Orthodox Church» which the Lord gave (εδωκεν), the apostles preached (εκηρυςαν) and the Fathers preserved (εφυλαςαν). Upon this the Church is founded. 【Athanasius of Alexandria (First Letter to Serapion, 28)】
በቃን ማለት አልቻልንበትምና ሥሉስ ቅዱስ ራሱ በቃችሁ ይበለን!
✍ ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም 📍ከሀረር መካነ ሥላሴ ካቴድራል
Let us look from the beginning at that very tradition, teaching, and faith of the «Orthodox Church» which the Lord gave (εδωκεν), the apostles preached (εκηρυςαν) and the Fathers preserved (εφυλαςαν). Upon this the Church is founded. 【Athanasius of Alexandria (First Letter to Serapion, 28)】
በቃን ማለት አልቻልንበትምና ሥሉስ ቅዱስ ራሱ በቃችሁ ይበለን!
✍ ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም 📍ከሀረር መካነ ሥላሴ ካቴድራል
መምህራችን ክቡር ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ (Hibret Yeshitila Hibret) ከዛሬ 10 ዓመት በፊት ያጋሩን ጽሑፍ ነው! በየዓመቱ እንደ አዲስ የሚነበብና ባለብዙኅ ምሥጢር ትምህርት በመሆኑ ተደጋግሞ እንዲነበብ አጋርቻለሁ!
በጎ ጾም መልካም ንባብ ያድርግልን!
✮༒✮ #ጾመ_ሐዋርያት ✮༒✮
(በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ)
በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ) የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡
እነዚህ አጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸውእሁድ ሲሆን የሚገቡት ደግሞሰኞ ቀን ነው፡፡
በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡ ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27 ሰኞ ዛሬ ተጅምሯል ፡፡ (ጽሑፉ የተለጠፈበትን ዓመት ያመለክታል ለዘንድሮው ሰኔ 1 ዛሬ ሰኞ) ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡
የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውን ያህል እጽፍ ዘንድብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝ አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋና ይድረሰው! አሜን!
ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾም እንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክ በርካታ ምስክሮች አሉ ስለዚህ ጾሙን እንደ እንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎ ማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለት ያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመን አመጣሽአድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾም መሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡
ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)
በመቀጠል እስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይ የሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብ ሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ
ታሪኩን ማንበብ ወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ›› በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናት ያህል ዘግይቶ እንጂወዲያው አይጀምርም ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታ ጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶ ያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል ይህም በጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂ የፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይ ምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾም እንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱ ምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት የተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋ መንፈስቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡
ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ስለጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስት ዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹ በምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊ መልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራ እንመለከታቸዋለን፡፡
①ኛ...‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸ ንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለው የመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣ የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራው መውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድና በኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞመርዓት (ሴት ሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› ሲልሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰት ሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውም እንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂ በሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾም ተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያትኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግን ከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩ ያስረዳል፡፡
በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋ አይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣት ይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋ ግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ከጸጸትና ከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)
②ኛ...‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞ ሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይም መጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም) ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥ እንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱን ማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌው ስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
በጎ ጾም መልካም ንባብ ያድርግልን!
✮༒✮ #ጾመ_ሐዋርያት ✮༒✮
(በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ)
በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ) የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡
እነዚህ አጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸውእሁድ ሲሆን የሚገቡት ደግሞሰኞ ቀን ነው፡፡
በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡ ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27 ሰኞ ዛሬ ተጅምሯል ፡፡ (ጽሑፉ የተለጠፈበትን ዓመት ያመለክታል ለዘንድሮው ሰኔ 1 ዛሬ ሰኞ) ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡
የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውን ያህል እጽፍ ዘንድብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝ አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋና ይድረሰው! አሜን!
ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾም እንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክ በርካታ ምስክሮች አሉ ስለዚህ ጾሙን እንደ እንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎ ማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለት ያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመን አመጣሽአድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾም መሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡
ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)
በመቀጠል እስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይ የሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብ ሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ
ታሪኩን ማንበብ ወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ›› በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናት ያህል ዘግይቶ እንጂወዲያው አይጀምርም ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታ ጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶ ያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል ይህም በጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂ የፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይ ምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾም እንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱ ምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት የተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋ መንፈስቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡
ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ስለጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስት ዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹ በምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊ መልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራ እንመለከታቸዋለን፡፡
①ኛ...‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸ ንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለው የመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣ የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራው መውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድና በኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞመርዓት (ሴት ሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› ሲልሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰት ሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውም እንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂ በሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾም ተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያትኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግን ከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩ ያስረዳል፡፡
በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋ አይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣት ይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋ ግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ከጸጸትና ከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)
②ኛ...‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞ ሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይም መጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም) ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥ እንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱን ማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌው ስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
በምሳሌው መሠረት በጣፊ ወይም በልብስ ሰፊ የተመሰለው ኢየሱስክርስቶስ ነው፡፡ በአዲስ እራፊ ጨርቅ ምሳሌነት የተወከለው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንድንጾመው የሠራልን ጾም ነው፡፡ የተቀደደውና መጣፊያ የሚያስፈልገው ልብስ ደግሞ የሐዋርያት ሕይወት ምሳሌ ነው፡፡
እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶች ይባላሉ፡፡
‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናን እሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹ ምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ክርስቶስም ለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ሐዋርያው ‹‹እናንተ የተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸው ማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞ ለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ ነውራቸውንየሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱ ነው ማለት ነው፡፡
ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድ እንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውን ነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይ ከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀል ትረዳዋለች፡፡
‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖ ሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውን የአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትን አያዛቸውም ማለት ነው፡፡
ሰውነታቸው ሲታደስ ያን ጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡
ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለ አቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታ መሆኑን ያሳያል፡፡
እንዴት ቢባል ሐዋርያትን ሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉ እንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼ ሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትን ያልሰጣቸው ስለዚህነው፡፡ ቢሰጣቸውም ሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰው የራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡
በታላላቅ ተአምራት ከባርነት ካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህ ከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይ የሆነ ነገርፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነው ሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡
③ኛ... ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግንአቁማዳው ይፈነዳል: የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውና የመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡
በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወት ሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችን በወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግን የሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ (በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀ አቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰ ሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡
ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱ በኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝ በመሆኑ በወይንተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይን የሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15) ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁ ታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡ እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትም ይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊት ይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁ ከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለውማር ያልሱታል (ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜ ይሰጡታል፡፡
በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይ ከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለት ያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምም ሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብ በአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤት ቤተክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግር የለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላ እንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንም በከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለ መልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋው እንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችን በሕግ ከተሠራልን በላይ ሠዓቱ እንዳይበዛና ከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤ እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንም መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውን ስፍራ ይዘን በሕገ ቤተክርስቲያን መሠረት በጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛው ምሳሌ ያስረዳናል፡፡
ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስ የወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳ መሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱ አቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትም በአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመ ሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡
አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣል ያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋል እንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑም አቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳው ወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውን ያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ›› የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡ ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ (እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁ ናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱን ትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህ ነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙ ለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብ ወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም ‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅን ይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡
ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋ ቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳ ነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩ አገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነት ያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂ ከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትን በጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀት እንጂእንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመች በጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊጉዞ ይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)
ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም ‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉ በመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠት ምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስ ትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላምን ሊሆን ይችላል?
እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶች ይባላሉ፡፡
‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናን እሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹ ምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ክርስቶስም ለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ሐዋርያው ‹‹እናንተ የተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸው ማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞ ለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ ነውራቸውንየሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱ ነው ማለት ነው፡፡
ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድ እንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውን ነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይ ከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀል ትረዳዋለች፡፡
‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖ ሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውን የአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትን አያዛቸውም ማለት ነው፡፡
ሰውነታቸው ሲታደስ ያን ጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡
ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለ አቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታ መሆኑን ያሳያል፡፡
እንዴት ቢባል ሐዋርያትን ሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉ እንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼ ሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትን ያልሰጣቸው ስለዚህነው፡፡ ቢሰጣቸውም ሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰው የራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡
በታላላቅ ተአምራት ከባርነት ካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህ ከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይ የሆነ ነገርፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነው ሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡
③ኛ... ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግንአቁማዳው ይፈነዳል: የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውና የመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡
በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወት ሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችን በወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግን የሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ (በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀ አቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰ ሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡
ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱ በኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝ በመሆኑ በወይንተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይን የሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15) ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁ ታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡ እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትም ይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊት ይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁ ከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለውማር ያልሱታል (ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜ ይሰጡታል፡፡
በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይ ከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለት ያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምም ሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብ በአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤት ቤተክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግር የለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላ እንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንም በከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለ መልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋው እንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችን በሕግ ከተሠራልን በላይ ሠዓቱ እንዳይበዛና ከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤ እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንም መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውን ስፍራ ይዘን በሕገ ቤተክርስቲያን መሠረት በጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛው ምሳሌ ያስረዳናል፡፡
ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስ የወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳ መሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱ አቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትም በአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመ ሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡
አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣል ያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋል እንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑም አቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳው ወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውን ያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ›› የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡ ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ (እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁ ናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱን ትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህ ነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙ ለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብ ወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም ‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅን ይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡
ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋ ቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳ ነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩ አገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነት ያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂ ከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትን በጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀት እንጂእንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመች በጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊጉዞ ይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)
ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም ‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉ በመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠት ምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስ ትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላምን ሊሆን ይችላል?