† እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል (ደብረ ምጥማቅ) በሰላም አደረሳችሁ †
†ደብረ ምጥማቅ †
=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:
+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::
+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::
+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::
+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::
+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን ይደርብን:: †††
"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ::
+"+ (መዝ. 44:12-17)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
†ደብረ ምጥማቅ †
=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:
+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::
+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::
+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::
+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::
+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን ይደርብን:: †††
"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ::
+"+ (መዝ. 44:12-17)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ስርዓተ ኦሪት ስርዓተ ሀዲስ ከተፈጸሙባቸው 5 መቅደሶች መሐከል እንዷ የሆነችው የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች።
~~~
የደቡብ ክልል የክርስትና መነሻ እና የጥንታዊ ህገ እግዚአብሔር አምልኮ ማዕከል የሆነችው በጋሞ ጎፋ ሀገረስብከት የምትገኘው ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በደምቀት ታከብራለች።
በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሰዋተ ኦሪት ከተፈጸመባቸው 5ቱ መቅደሶች መሀከል አንዷ የሆነችው ብርብር ማርያም ገዳም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላትን እንደ ብሔራዊ በዓላት ልክ የአከባቢው ምዕመናንን እንደሚያከብሩ ይታወቃል።
የቴሌግራም ቻናላችን ከታች ያለውን ሊንክን በመስፈንጠር ቤተሰብ ይሁኑን፤
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
የደቡብ ክልል የክርስትና መነሻ እና የጥንታዊ ህገ እግዚአብሔር አምልኮ ማዕከል የሆነችው በጋሞ ጎፋ ሀገረስብከት የምትገኘው ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በደምቀት ታከብራለች።
በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሰዋተ ኦሪት ከተፈጸመባቸው 5ቱ መቅደሶች መሀከል አንዷ የሆነችው ብርብር ማርያም ገዳም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላትን እንደ ብሔራዊ በዓላት ልክ የአከባቢው ምዕመናንን እንደሚያከብሩ ይታወቃል።
የቴሌግራም ቻናላችን ከታች ያለውን ሊንክን በመስፈንጠር ቤተሰብ ይሁኑን፤
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
❖ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ።
#ዕርገት
ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ዕርገትን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያነችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።
ዐረገ በስብሐት
ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
❖ መልካም በዓል #ምሽት/ቀን ይሁንልን።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ዕርገት
ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ዕርገትን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያነችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።
ዐረገ በስብሐት
ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
❖ መልካም በዓል #ምሽት/ቀን ይሁንልን።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ሰንበተ ክርስትያን
እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።
ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)
ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።
መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።
ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)
ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።
መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
☞ግንቦት 26 እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት በዓላቸው
በሰላም አደረሳችሁ፡፡
☞አባታቸው ፍሬ ቡሩክ እናታቸው ዮስቴና የሚባሉ በሕገ እግዚአብሔር፡
በሃይማኖት በምግባር ጸንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች የገኙ አባት ናቸው፡፡
☞አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ፅንሰታቸው ነሐሴ 26፤ ውልደታቸው ግንቦት
26፤ ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖት አቡነ ሀብተማርያምን አምስት መቅሰፍታት እንዲጠፋ
በደጄ በደብረ ሊባኖስ ተቀበርልኝ ብለው የለመኗቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ይህ
እንዴት ነው ቢሉ
☞አቡነ ተክለሃይማኖት እኔ ከተቀበርኩበት ቦታ እድትቀበር ቃልኪዳን ግባልኝ
ብለው ጠየቋቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተማርያምም አባቴ ሆይ ይህንን አደርግ ዘንድ ሰለምን ትወዳለህ?
አላቸወ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅስፍቶች አሉና
ሰለዚህ ነው እነዚህም አንዱ መብረቅ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ሦስተኛው ረሀብ
ነው፤ አራተኛው ወረርሽኝ ነው አምስተኛው የእሳት ቃጠሎ ነው፡፡ የአንተ አጽም
በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ ከነዚህ መቅስፍታት ትድናለች አሏቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተ ማርያም ንዑድ ክቡድ የምትሆን አባቴ ሆይ ልዩ ክብር በሚሆን
በአንተ አጽም መቀበር ያልዳነች በእኔ አጽም መቀበር ድኅነትን ታገኛለችን?
ብለው ተከራከሩ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት መልሰው
☞አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው
ክብር አለህና ሰለዚህ ነው፡፡ ይልቅስ እንዳልኩህ በተቀበርኩበት ቦታ እንድቀበር
ቃልኪን ግባልኝ ብለው ማለዷቸው፡፡
☞ይህንንም ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣላቸው ከወዳጄ ከሀብተ ማርያም
እንደበት ይህ ቃል አይወጣም፤ ዳግመኛም ወዳጄ ተክለሃይማኖት ሆይ እርሱ
በወደደው የሚቀበር አይደለምንና እኔ ከተቀበሩኩበት እንድትቀበር ብለህ
የምታስገድደው ለምንድ ነው?
☞እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትንም እየለመኑና እየሰገዱከሥላሴ ዙፋን ተንበረከኩ፡፡
☞በሦስተኛውም ይሁን እንዳልከው ይቀበርልህ የሚል ቃል ተሰማ፡፡
☞ዳግመኛ በአንተም አጽም በሀብተ ማርያምም አጽም ቦታህ ከመቅሰፍት
ትድናለህ ልጆችህ ግን በቸነፈር ደዌ ቢሞቱ ከሰማዕትነት ተቆጥሮላቸው ወደ
መንግሥት ሰማያት እንዲገቡ በራሴ ምዬ ቃልኪን ገብቼለሃለሁ አላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት እጅግ ደስ ተሰኙ፡፡
(ገድለ አቡነ ሀብተማርያም)
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
በሰላም አደረሳችሁ፡፡
☞አባታቸው ፍሬ ቡሩክ እናታቸው ዮስቴና የሚባሉ በሕገ እግዚአብሔር፡
በሃይማኖት በምግባር ጸንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች የገኙ አባት ናቸው፡፡
☞አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ፅንሰታቸው ነሐሴ 26፤ ውልደታቸው ግንቦት
26፤ ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖት አቡነ ሀብተማርያምን አምስት መቅሰፍታት እንዲጠፋ
በደጄ በደብረ ሊባኖስ ተቀበርልኝ ብለው የለመኗቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ይህ
እንዴት ነው ቢሉ
☞አቡነ ተክለሃይማኖት እኔ ከተቀበርኩበት ቦታ እድትቀበር ቃልኪዳን ግባልኝ
ብለው ጠየቋቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተማርያምም አባቴ ሆይ ይህንን አደርግ ዘንድ ሰለምን ትወዳለህ?
አላቸወ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅስፍቶች አሉና
ሰለዚህ ነው እነዚህም አንዱ መብረቅ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ሦስተኛው ረሀብ
ነው፤ አራተኛው ወረርሽኝ ነው አምስተኛው የእሳት ቃጠሎ ነው፡፡ የአንተ አጽም
በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ ከነዚህ መቅስፍታት ትድናለች አሏቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተ ማርያም ንዑድ ክቡድ የምትሆን አባቴ ሆይ ልዩ ክብር በሚሆን
በአንተ አጽም መቀበር ያልዳነች በእኔ አጽም መቀበር ድኅነትን ታገኛለችን?
ብለው ተከራከሩ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት መልሰው
☞አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው
ክብር አለህና ሰለዚህ ነው፡፡ ይልቅስ እንዳልኩህ በተቀበርኩበት ቦታ እንድቀበር
ቃልኪን ግባልኝ ብለው ማለዷቸው፡፡
☞ይህንንም ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣላቸው ከወዳጄ ከሀብተ ማርያም
እንደበት ይህ ቃል አይወጣም፤ ዳግመኛም ወዳጄ ተክለሃይማኖት ሆይ እርሱ
በወደደው የሚቀበር አይደለምንና እኔ ከተቀበሩኩበት እንድትቀበር ብለህ
የምታስገድደው ለምንድ ነው?
☞እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትንም እየለመኑና እየሰገዱከሥላሴ ዙፋን ተንበረከኩ፡፡
☞በሦስተኛውም ይሁን እንዳልከው ይቀበርልህ የሚል ቃል ተሰማ፡፡
☞ዳግመኛ በአንተም አጽም በሀብተ ማርያምም አጽም ቦታህ ከመቅሰፍት
ትድናለህ ልጆችህ ግን በቸነፈር ደዌ ቢሞቱ ከሰማዕትነት ተቆጥሮላቸው ወደ
መንግሥት ሰማያት እንዲገቡ በራሴ ምዬ ቃልኪን ገብቼለሃለሁ አላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት እጅግ ደስ ተሰኙ፡፡
(ገድለ አቡነ ሀብተማርያም)
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
🔴 መድኃኔአለም 🔴
✍️✍️✍️
መድኃኔአለም ማለት አለምን ያዳነ የአለም መድኃኒት ማለት ነው። ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀድሞ ክብሩ መለሰው። ምን አይነት ፍቅርነው?????
ወንድሜ /እህቴ አስባችሁታል ግን እኛን ለማዳን ብሎእኮ ነው
የተሰቀለው፡ራቁቱን በመስቀል ምን ያህል
አሳፋሪ እንደሆነ እናውቀዋለን
ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ መስቀሉን ናቀው።
በፈጠራቸው ፍጥረት ተተፋበት።
እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት
እየቻለ እርሱ ግን
💖በፍቅር እያዩ የማያውቁትን አያውቁምና
አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር።
ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድበት
አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም
ሲታበዩበት ሁሉ እርስ ግን በትህትና ያያቸው ነበር።
💖ታዲያ እኛ ደግሞ እራሳችንን ለማዳን ሰዎች ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።
ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንባላለን።
በ 5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።
በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያም ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ። አንተም በመስቀሉ ስር
ለመገኘት ከፈለግህ ትእግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።
መድኃኔአለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።
#27 ❤️
"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}
{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )
[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}
መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !
( መልክአ - መድኃኔአለም )27❤
@ortodoxtewahedo
✍️✍️✍️
መድኃኔአለም ማለት አለምን ያዳነ የአለም መድኃኒት ማለት ነው። ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀድሞ ክብሩ መለሰው። ምን አይነት ፍቅርነው?????
ወንድሜ /እህቴ አስባችሁታል ግን እኛን ለማዳን ብሎእኮ ነው
የተሰቀለው፡ራቁቱን በመስቀል ምን ያህል
አሳፋሪ እንደሆነ እናውቀዋለን
ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ መስቀሉን ናቀው።
በፈጠራቸው ፍጥረት ተተፋበት።
እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት
እየቻለ እርሱ ግን
💖በፍቅር እያዩ የማያውቁትን አያውቁምና
አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር።
ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድበት
አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም
ሲታበዩበት ሁሉ እርስ ግን በትህትና ያያቸው ነበር።
💖ታዲያ እኛ ደግሞ እራሳችንን ለማዳን ሰዎች ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።
ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንባላለን።
በ 5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።
በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያም ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ። አንተም በመስቀሉ ስር
ለመገኘት ከፈለግህ ትእግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።
መድኃኔአለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።
#27 ❤️
"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}
{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )
[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}
መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !
( መልክአ - መድኃኔአለም )27❤
@ortodoxtewahedo
መ/ር ልደተቃል
ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ልደተዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ልደተዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#በዓለ ጰራቅሊጦስ
የቤ/ክ የልደት ቀን
‹‹ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም›› /ዮሐ. 14፥18/
ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ ‹‹ኢይደንግድክሙ ልብክሙ እመኑ በእግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ›› (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) /ዮሐ. 14፥1)
እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14፥18/ ላይ እንደተጻፈው ‹‹ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ›› (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡
/በሉቃስ ወንጌል 24 ቁጥር 49/ ላይ እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም›› (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ፡፡ እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን የጰራቅሊጦስ እለት ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡
አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ነበሩ፡፡ እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡- የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡ ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም ‹‹እግዚአብሔር ይላል በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ምልክቶችንም በታች በምድር ደምም፣ እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል የታወቀችዋም ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል›› /ኢዩ. 2፥28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡
ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተነካ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ ተጠመቁ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው
ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ ብሎ መከራቸው፡፡ በዚህ ቀን ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡
እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር ‹‹የቤተክርስቲያን የልደት ቀን›› ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡ እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡ በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23፥10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እሥራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በያይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኩራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም ‹‹ቀዳምያት›› ይባላል፡፡ የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው እግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡
በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡-ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ›› ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡ ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት›› (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም እንዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም።
ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ›› (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28፥17/
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በሰማንያ ቀን የተሰጠን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ቅዱሳን በአማላጅነታቸው ይርዱን፡፡ አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡
***
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
የቤ/ክ የልደት ቀን
‹‹ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም›› /ዮሐ. 14፥18/
ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ ‹‹ኢይደንግድክሙ ልብክሙ እመኑ በእግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ›› (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) /ዮሐ. 14፥1)
እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14፥18/ ላይ እንደተጻፈው ‹‹ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ›› (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡
/በሉቃስ ወንጌል 24 ቁጥር 49/ ላይ እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም›› (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ፡፡ እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን የጰራቅሊጦስ እለት ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡
አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ነበሩ፡፡ እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡- የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡ ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም ‹‹እግዚአብሔር ይላል በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ምልክቶችንም በታች በምድር ደምም፣ እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል የታወቀችዋም ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል›› /ኢዩ. 2፥28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡
ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተነካ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ ተጠመቁ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው
ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ ብሎ መከራቸው፡፡ በዚህ ቀን ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡
ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡
እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር ‹‹የቤተክርስቲያን የልደት ቀን›› ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡ እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡ በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23፥10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እሥራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በያይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኩራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም ‹‹ቀዳምያት›› ይባላል፡፡ የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው እግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡
በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡-ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ›› ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡ ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት›› (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም እንዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም።
ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ›› (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28፥17/
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በሰማንያ ቀን የተሰጠን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ቅዱሳን በአማላጅነታቸው ይርዱን፡፡ አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡
***
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ብዙ ስለበደልኩ በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ የሚቻለኝ አይደለሁም አትበል፡፡ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ተስፋ በመቁረጥ ምክንያት ኃጢአትህን አትጨምር፡፡
መሓሪ በሆነው _ አምላክ ርዳታ ወደ ቀደመ ማንነትህ መመለስ ይቻልሃል፡፡ እርሱ እንዲህ ብሏልና፡- ወደእኔ የመጣውን ወደውጪ _ አላወጣውም፡፡/ዮሐ 6፡37/
እርሱ ንጽሐ ባሕርይ ስለሆነ ወደ እርሱ የሚቀርቡ ወገኖችን እንደሚያነጻቸው እንደሚቀድሳቸውም እውነተኛ የሆነ ንስሐን እመን፡፡
እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡-
« ከክፋት ተመልሰህ መልካም ነገርን አድርግ፡፡/1ኛ ጴጥ 3፡11/
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
መሓሪ በሆነው _ አምላክ ርዳታ ወደ ቀደመ ማንነትህ መመለስ ይቻልሃል፡፡ እርሱ እንዲህ ብሏልና፡- ወደእኔ የመጣውን ወደውጪ _ አላወጣውም፡፡/ዮሐ 6፡37/
እርሱ ንጽሐ ባሕርይ ስለሆነ ወደ እርሱ የሚቀርቡ ወገኖችን እንደሚያነጻቸው እንደሚቀድሳቸውም እውነተኛ የሆነ ንስሐን እመን፡፡
እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡-
« ከክፋት ተመልሰህ መልካም ነገርን አድርግ፡፡/1ኛ ጴጥ 3፡11/
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
"ጾመ ሀዋርያት(የሰኔ ጾም)"
ይህ ፆም ሐዋርያት ለማገልገል ከመሰማራታቸው በፊት አገልግሎታቸው የቀና እንዲሆን ለመንፈስ ቅዱስ ስራ መለየትን እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው በመለመን የፆሙት ፆም ነው ::
ሐዋ 13:1-3
መሰረታችን ሐዋርያት ናቸውና የዋኖቻችንን ሥራ እኛም መፈጸም ስላለብን እንጾመዋለን፡፡
ሐዋርያትን እንዳፀናቸው በአገልግሎቱም እንዳበረታቸውና እንደለያቸው ሁሉ እኛም እንዲያፀናን እንዲያበረታን በመማፀን ለመልካሙ ሥራ እንተጋ ዘንድ በመለመን እፆመዋለን ከጵራቅሊጦስ ማግስት ጀምሮ ሐምሌ 5 በመፆም ይፈጸማል።
እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን የበረከት ጾም ይሁንልን
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ይህ ፆም ሐዋርያት ለማገልገል ከመሰማራታቸው በፊት አገልግሎታቸው የቀና እንዲሆን ለመንፈስ ቅዱስ ስራ መለየትን እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው በመለመን የፆሙት ፆም ነው ::
ሐዋ 13:1-3
መሰረታችን ሐዋርያት ናቸውና የዋኖቻችንን ሥራ እኛም መፈጸም ስላለብን እንጾመዋለን፡፡
ሐዋርያትን እንዳፀናቸው በአገልግሎቱም እንዳበረታቸውና እንደለያቸው ሁሉ እኛም እንዲያፀናን እንዲያበረታን በመማፀን ለመልካሙ ሥራ እንተጋ ዘንድ በመለመን እፆመዋለን ከጵራቅሊጦስ ማግስት ጀምሮ ሐምሌ 5 በመፆም ይፈጸማል።
እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን የበረከት ጾም ይሁንልን
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
— 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
የወርቅ መሰላል፥ ምሥጢር እና ትርጓሜ፥...
EOTC Germany Archdiocese የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
✝የወርቅ መሠላል✝
Size:-132.4MB
Length:-2:23:00
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Size:-132.4MB
Length:-2:23:00
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Audio
✝ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው✝
በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰
🕹 #ጊዜ_አጠቃቀም
👍 #የጊዜ_አጠቃቀም_ጥቅሞች
🔸የጊዜ አጠቃቀም ጥቅሞች እንደየሰው ቁጥራቸው ሊጨምርና ሊያንስ ይችላል፡፡ እዚህም ጋር የሚከተሉት ሦስት ዋና ዋና ጥቅሞች ቀርበዋል፡፡
1⃣ በሌሎች ዘንድ የሚኖረን ተቀባይነት ከፍ ይላል
🔹አገልጋዮች ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊ ቁርኝት የሚጠበቅብን በመሆኑ የጊዜ አጠቃቀሙን መጀመርና መልመድ በምናደርገው ግንኙነት የሚጠበቅብንን በጊዜው እንድናከናውን ይረዳናል፡፡
🔸በዚህም በሰዎች ዘንድ የተግባር ሰው፣ ቃል አክባሪ፣ ትጉህ፣ ወዘተ የእኛ መገለጫዎች ይሆናሉ፡፡
🔹እነዚህ እሴቶች ደግሞ በመንፈሳዊውም ሆና ዓለማዊው እንቅስቃሴያችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጉልናል፡፡
2⃣ የተመጣጠነ ሕይወት እንድንመራ ያስችለናል
🔸የጊዜ አጠቃቀምም በመንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቋማችን የተመጣጠነ እንዲሆን ይረዳናል፡፡
3⃣ ውጤታማነታችን ያሳድጋል
🔹ውጤታማነት ሲለካ ሥራው መሠራቱ ብቻ ሳይሆን የሚታየው ሥራው የፈጀውም ጊዜ አንዱ መለኪያ በመሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ይገባል፡፡
🔸ጊዜያችን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ በሁሉም ረገድ በትንሽ ጊዜ ብዙ ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡
#ማጠቃለያ
❇️ጊዜ ሀብት ነው፤ እንዲሁም ጊዜ ለእያንዳንዳችን እኩል የተሰጠን ሀብት ነው፤ በመሆኑም እያንዳንዳችን አጠቃቀሙን ተረድተን ይህን ሀብታችንን ለውጤታማነት ልናውለው ይገባል፡፡
❇️ምንም እንኳ ጊዜ ሀብት ቢሆንም አጠቃቀሙን ካላወቅንበት፣ ሀብትነቱን ካልተረዳን ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡
👌ይህም ማለት ጊዜ ካወቅንበት እና ከሠራንበት የሚጠቅመን ሲሆን ካላወቅንበት ግን ምንም ጥቅም የለውም፡፡
❇️ጊዜ ለሁላችን እኩል የታደለ ሀብት ቢሆንም ጠቀሜታው ግን ለሁላችን እኩል አይደለም፡፡
👌ምክንያቱም የጊዜን ሀብትነት ተረድተው በአግባቡ የተጠቀሙበት ውጤት ሲያገኙበት ይህንን ያልተረዱ ግን ተጠቃሚ አይሆኑም፡፡
❇️ጊዜ ለእያንዳንዷ እንቅስቃሴአችን አስፈላጊ እና ጠቃሚ ሀብት በመሆኑ ትኩረትን ይሻል፡፡
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
📌ምንጭ
↪️ @Tewahedo12 Channel
⏰⏰⏰
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰
🙏 ሼር ማድረግ አይርሱ 🙏
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
📩Coment- @YeBiruk
- @Samiabush
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
🕹 #ጊዜ_አጠቃቀም
👍 #የጊዜ_አጠቃቀም_ጥቅሞች
🔸የጊዜ አጠቃቀም ጥቅሞች እንደየሰው ቁጥራቸው ሊጨምርና ሊያንስ ይችላል፡፡ እዚህም ጋር የሚከተሉት ሦስት ዋና ዋና ጥቅሞች ቀርበዋል፡፡
1⃣ በሌሎች ዘንድ የሚኖረን ተቀባይነት ከፍ ይላል
🔹አገልጋዮች ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊ ቁርኝት የሚጠበቅብን በመሆኑ የጊዜ አጠቃቀሙን መጀመርና መልመድ በምናደርገው ግንኙነት የሚጠበቅብንን በጊዜው እንድናከናውን ይረዳናል፡፡
🔸በዚህም በሰዎች ዘንድ የተግባር ሰው፣ ቃል አክባሪ፣ ትጉህ፣ ወዘተ የእኛ መገለጫዎች ይሆናሉ፡፡
🔹እነዚህ እሴቶች ደግሞ በመንፈሳዊውም ሆና ዓለማዊው እንቅስቃሴያችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጉልናል፡፡
2⃣ የተመጣጠነ ሕይወት እንድንመራ ያስችለናል
🔸የጊዜ አጠቃቀምም በመንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቋማችን የተመጣጠነ እንዲሆን ይረዳናል፡፡
3⃣ ውጤታማነታችን ያሳድጋል
🔹ውጤታማነት ሲለካ ሥራው መሠራቱ ብቻ ሳይሆን የሚታየው ሥራው የፈጀውም ጊዜ አንዱ መለኪያ በመሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ይገባል፡፡
🔸ጊዜያችን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ በሁሉም ረገድ በትንሽ ጊዜ ብዙ ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡
#ማጠቃለያ
❇️ጊዜ ሀብት ነው፤ እንዲሁም ጊዜ ለእያንዳንዳችን እኩል የተሰጠን ሀብት ነው፤ በመሆኑም እያንዳንዳችን አጠቃቀሙን ተረድተን ይህን ሀብታችንን ለውጤታማነት ልናውለው ይገባል፡፡
❇️ምንም እንኳ ጊዜ ሀብት ቢሆንም አጠቃቀሙን ካላወቅንበት፣ ሀብትነቱን ካልተረዳን ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡
👌ይህም ማለት ጊዜ ካወቅንበት እና ከሠራንበት የሚጠቅመን ሲሆን ካላወቅንበት ግን ምንም ጥቅም የለውም፡፡
❇️ጊዜ ለሁላችን እኩል የታደለ ሀብት ቢሆንም ጠቀሜታው ግን ለሁላችን እኩል አይደለም፡፡
👌ምክንያቱም የጊዜን ሀብትነት ተረድተው በአግባቡ የተጠቀሙበት ውጤት ሲያገኙበት ይህንን ያልተረዱ ግን ተጠቃሚ አይሆኑም፡፡
❇️ጊዜ ለእያንዳንዷ እንቅስቃሴአችን አስፈላጊ እና ጠቃሚ ሀብት በመሆኑ ትኩረትን ይሻል፡፡
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን
📌ምንጭ
↪️ @Tewahedo12 Channel
⏰⏰⏰
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰
🙏 ሼር ማድረግ አይርሱ 🙏
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
📩Coment- @YeBiruk
- @Samiabush
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo