Forwarded from ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ (💠 ✞ SAMI ✞ BREAVHEART💠)
.#የእለቱ_መልእክት ⬇️
በአንድ ህንፃ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ።ሚስትየው አዘውትራ በመስኮት መስታወት ውስጥ ወደ ጎረቤቶቿ ጊቢ የማየት ልምድ ነበራት።እናም አንድ ቀን አሻግራ ጎረቤቶቿ አጥበው ያሰጡትን ልብስ ስታይ ቆይታባሏን ጠራችውና "ውዴ ልብሶቹን አየሀቸው በደንብ አልነፁም ምናልባት ማጠብ አይችሉም ይሆናል" አለችው።በሌላ ቀንም እንዲሁ የጎረቤቶቿን ልብሶች ካየች በሗላ ባሏን ጠርታ"ዛሬም ሳያፀዱ ነው ያጠቡት ምናልባት ሳሙና የላቸውም ይሆናል አልያም ውሀ የላቸውም" አለችው።
በሌላ ቀንም እንዲሁ በመስታወት ውስጥ አሻግራ ስታይ አሁንም ልብሶቹ አልነፁም። አሁንም ባሏን ጠርታ "ዛሬም ልብሶቹ አልነፁም በእርግጠኛነት ሰዎቹ ሰነፎች ናቸው"አለችው።
አንድ ቀን
ማለዳ እንደ ለመደችው አሻግራ ስታይ ያየችውን ማመን አቃታት።ልብሶቹ ያለወትሯቸው በጣም ነፅተዋል ባሏን ጠራችውና
"ተመልከት ልብሶቹ ነፅተው!!!!!" አለችው።
ባሏም
"ውዴ.....በጠዋት ተነስቼ መስታወቱን ስላፀዳሁት እኮ ነው።እስካሁን የቆሸሸ የመሰለሽ ልብሶቹ ቆሽሸው ሳይሆን መስታወቱ ቆሽሾ ስለ ነበር ነው። አሁን በንፁህ መስታወት እውነታውን ተመልከቺ "አላት።
ምን ለማለት ፈልጌ ነው::ጥቃቅን ነገሮች እውነታን እንዳናይ ይጋርዱናል። የምናይበትን መነፅር ስናስተካክል ሁኔታዎችም አብረው ይስተካከላሉ።
እስቲ የሰውን ጉድፍ ከመጠቆማችን በፊት ጉድፉ አይናችን ላይ አለመኖሩን እርግጠኛ እንሁን!!
መልካም ቀን 💚💛❤️
በአንድ ህንፃ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ።ሚስትየው አዘውትራ በመስኮት መስታወት ውስጥ ወደ ጎረቤቶቿ ጊቢ የማየት ልምድ ነበራት።እናም አንድ ቀን አሻግራ ጎረቤቶቿ አጥበው ያሰጡትን ልብስ ስታይ ቆይታባሏን ጠራችውና "ውዴ ልብሶቹን አየሀቸው በደንብ አልነፁም ምናልባት ማጠብ አይችሉም ይሆናል" አለችው።በሌላ ቀንም እንዲሁ የጎረቤቶቿን ልብሶች ካየች በሗላ ባሏን ጠርታ"ዛሬም ሳያፀዱ ነው ያጠቡት ምናልባት ሳሙና የላቸውም ይሆናል አልያም ውሀ የላቸውም" አለችው።
በሌላ ቀንም እንዲሁ በመስታወት ውስጥ አሻግራ ስታይ አሁንም ልብሶቹ አልነፁም። አሁንም ባሏን ጠርታ "ዛሬም ልብሶቹ አልነፁም በእርግጠኛነት ሰዎቹ ሰነፎች ናቸው"አለችው።
አንድ ቀን
ማለዳ እንደ ለመደችው አሻግራ ስታይ ያየችውን ማመን አቃታት።ልብሶቹ ያለወትሯቸው በጣም ነፅተዋል ባሏን ጠራችውና
"ተመልከት ልብሶቹ ነፅተው!!!!!" አለችው።
ባሏም
"ውዴ.....በጠዋት ተነስቼ መስታወቱን ስላፀዳሁት እኮ ነው።እስካሁን የቆሸሸ የመሰለሽ ልብሶቹ ቆሽሸው ሳይሆን መስታወቱ ቆሽሾ ስለ ነበር ነው። አሁን በንፁህ መስታወት እውነታውን ተመልከቺ "አላት።
ምን ለማለት ፈልጌ ነው::ጥቃቅን ነገሮች እውነታን እንዳናይ ይጋርዱናል። የምናይበትን መነፅር ስናስተካክል ሁኔታዎችም አብረው ይስተካከላሉ።
እስቲ የሰውን ጉድፍ ከመጠቆማችን በፊት ጉድፉ አይናችን ላይ አለመኖሩን እርግጠኛ እንሁን!!
መልካም ቀን 💚💛❤️
"ሰዎች ማን እንደሆኑ ሲያሳዩህ በመጀመሪያው ቀን እመናቸው" ትላለች ማያ አንጀሎ
ይህንን ጽሑፍ ከትናንት በስቲያ ጽፌው ስሜታዊ ሆኜ እንዳይሆን በሚል ትንሽ ቆይቼ ልመልከተው ብዬ አሳደርኩት:: በቆይታ ሃሳቤ ሊቀየር ስላልቻለ እንደወረደ ለጥፌዋለሁ:: የምናገረው ነገርም እሳቸው ስለ ድንግል ማርያም ከተናገሩት አይከፋም:: ነገረ ሃይማኖታዊ መልስ ከበቂ በአደባባይ ተሰጥቶበታል:: ጉዳዩ ላይ ግን የምለውን ልበል::
ፍኖተ ድድቅ የሚባል እባጭ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከወጣ ጀምሮ አንዴ ዘፈን በሚመስል መዝሙሩ ፣ አንዴ ምንፍቅናን በሚያገሣ ስብከቱ ምእመናንን ሲያወዛግብ ሰንበትበት ብሎ ነበር:: ጌታ በወንጌል "ኀበ ሀሎ ገደላ ህየ ይትጋብዑ አንሥርት" "በድን ባለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ" እንዳለው የፍኖተ ድድቅ ባለቤት ሙዳ ሥጋ ይጥላል ብለው ተስፋ ያደረጉ ሰዎች ዙሪያውን ስለከበቡት ላለፉት ጥቂት ዓመታት ቤተ ክርስቲያን ከነንፍጡ ካልወደደችው ብለው ሲሟገቱ ከርመዋል:: በመሠረቱ ሁኔታው ሰውዬው ደኃ ቢሆን ኖሮ ገና ድሮ ተወግዞ ነበር እንድል ያደርገኛል:: ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ማኅበር ለማጥራት ጊዜው አሁን ነው::
"ከእኛ ወገን ነህ ወይንስ ከጠላቶቻችን?" የሚል ኢያሱያዊ ጥያቄ ለመጠየቅ ጊዜው አሁን ነው::
ሰሞኑን ደግሞ በፖለቲካ ቤዛነት የተሾሙ የሆኑ አንድ ጳጳስ ድንግል ማርያም ቤዛ አትባልም ብለው በፍኖተ ድድቅ አዳራሽ ሲያስጨበጭቡ ሰማን:: ከንዑሰ ክርስቲያን ያነሰ እውቀት ያላቸው እኚህ ጳጳስ ሽልማት እንደሚጠባበቅ አዝማሪ ሰውዬውን ያስደስታል ብለው ያሰቡትን ሁሉ ሲዘባርቁ ነበር::
ከቅርብ ዘመናት ወዲህ እንደ ፓስተር ለማውራት የሚጋጋጡ አባቶች ማየት ከጀመርን ሰነበትን:: አይናቸውን አስሬ የሚጨፍኑ ፣ በግድ እየጨመቁ ዕንባ ለማውጣት የሚታገሉ ፣ ከአሁን አሁን በልሳን ለፈለፉ ብለን በስጋት የምናያቸው ምሁር ለመባል የቤተ ክርስቲያንን ነባር እሴቶች የሚያጣጥሉ የቤተ ክርስቲያን ማድያቶች ብቅ ብቅ ካሉ ሰነበቱ::
ያሁኑ ጳጳስ ትንሽ የሚለዩት ምንም ፈሊጥ የሌለው ያልተለሳለሰ ምንፍቅና ስለሚናገሩ ብቻ ነው:: የሆነ ቪድዮ ላይ Faith Alone የሚለውን የሉተር ትምህርት የኦርቶዶክስ ቆብ ደፍተው ሲሰብኩ ትንሽ እንኩዋን አላፈሩም:: በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተሹመው ተሸልመው ክህደት እያስተማሩ መቀጠል እንደማይቻል ለማሳየትና አንዴ ከጰጰሱ ምንም አይኮንም ዓይነት አመለካከትን ለማረም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ዕድል ሊጠቀም ይገባዋል:: በ3ኛው ክፍለ ዘመን ጳውሎስ ሳምሰጢ (Paul of Samosata) በአንጾኪያ ሲኖዶስ የተወገዘው ፣ ንስጥሮስ በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተወገዘው ጳጳስ ከሆኑ በኋላ ነው:: ቤተ ክርስቲያን መናፍቃንን ለመለየት ጵጵስናቸውን ፈርታ አታውቅም::
በወላዲተ አምላክ የነገረ ድኅነት ሱታፌ ላይ በጳጳስ ደረጃ ሲቀለድ አይተን ዝም ልንል አንችልም:: ከቅዱስ ሲኖዶስ ጠንከር ያለ ውሳኔ እንጂ ማስተባበያ አንጠብቅም:: የተነቃነቀ ጥርስ ቀን ይጠብቃል እንጂ መውለቁ አይቀርም:: እንደ ተራ ስኅተት ይቅርታ እንዲጠይቁም አንጠብቅም:: ያስተማሩት የታሰበበት ክህደት ነውና የተብራራ መልስ ከቀኖና ጋር እንጠብቃለን:: "የበራላቸው" ለመባል የብርሃን እናትን ሊጋርዱ የሚጥሩ ሰዎች ማላገጫ ሆነንም አንቀርም::
ሙሴ ቤዛ በተባለበት መጽሐፍ ቅዱስ እያመኑ ድንግል ማርያም ቤዛ አትባልም ላሉት ጳጳስ ቅዱስ ሲኖዶስ ቤዛ ሲሆናቸው ማየት አንፈልግም:: ጠንከር ያለ ቀኖናዊ እርምጃ እንጠብቃለን::
ርጉመ ይኩን ዘይረግመኪ
ወቡሩከ ይኩን ዘይባርከኪ
ነገራተ ክልዔ ኢይርሳዕ ልብኪ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ገሊላ ፳ኤል
ሚያዝያ 15 2017 ዓ.ም.
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ይህንን ጽሑፍ ከትናንት በስቲያ ጽፌው ስሜታዊ ሆኜ እንዳይሆን በሚል ትንሽ ቆይቼ ልመልከተው ብዬ አሳደርኩት:: በቆይታ ሃሳቤ ሊቀየር ስላልቻለ እንደወረደ ለጥፌዋለሁ:: የምናገረው ነገርም እሳቸው ስለ ድንግል ማርያም ከተናገሩት አይከፋም:: ነገረ ሃይማኖታዊ መልስ ከበቂ በአደባባይ ተሰጥቶበታል:: ጉዳዩ ላይ ግን የምለውን ልበል::
ፍኖተ ድድቅ የሚባል እባጭ ቤተ ክርስቲያን ላይ ከወጣ ጀምሮ አንዴ ዘፈን በሚመስል መዝሙሩ ፣ አንዴ ምንፍቅናን በሚያገሣ ስብከቱ ምእመናንን ሲያወዛግብ ሰንበትበት ብሎ ነበር:: ጌታ በወንጌል "ኀበ ሀሎ ገደላ ህየ ይትጋብዑ አንሥርት" "በድን ባለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ" እንዳለው የፍኖተ ድድቅ ባለቤት ሙዳ ሥጋ ይጥላል ብለው ተስፋ ያደረጉ ሰዎች ዙሪያውን ስለከበቡት ላለፉት ጥቂት ዓመታት ቤተ ክርስቲያን ከነንፍጡ ካልወደደችው ብለው ሲሟገቱ ከርመዋል:: በመሠረቱ ሁኔታው ሰውዬው ደኃ ቢሆን ኖሮ ገና ድሮ ተወግዞ ነበር እንድል ያደርገኛል:: ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ማኅበር ለማጥራት ጊዜው አሁን ነው::
"ከእኛ ወገን ነህ ወይንስ ከጠላቶቻችን?" የሚል ኢያሱያዊ ጥያቄ ለመጠየቅ ጊዜው አሁን ነው::
ሰሞኑን ደግሞ በፖለቲካ ቤዛነት የተሾሙ የሆኑ አንድ ጳጳስ ድንግል ማርያም ቤዛ አትባልም ብለው በፍኖተ ድድቅ አዳራሽ ሲያስጨበጭቡ ሰማን:: ከንዑሰ ክርስቲያን ያነሰ እውቀት ያላቸው እኚህ ጳጳስ ሽልማት እንደሚጠባበቅ አዝማሪ ሰውዬውን ያስደስታል ብለው ያሰቡትን ሁሉ ሲዘባርቁ ነበር::
ከቅርብ ዘመናት ወዲህ እንደ ፓስተር ለማውራት የሚጋጋጡ አባቶች ማየት ከጀመርን ሰነበትን:: አይናቸውን አስሬ የሚጨፍኑ ፣ በግድ እየጨመቁ ዕንባ ለማውጣት የሚታገሉ ፣ ከአሁን አሁን በልሳን ለፈለፉ ብለን በስጋት የምናያቸው ምሁር ለመባል የቤተ ክርስቲያንን ነባር እሴቶች የሚያጣጥሉ የቤተ ክርስቲያን ማድያቶች ብቅ ብቅ ካሉ ሰነበቱ::
ያሁኑ ጳጳስ ትንሽ የሚለዩት ምንም ፈሊጥ የሌለው ያልተለሳለሰ ምንፍቅና ስለሚናገሩ ብቻ ነው:: የሆነ ቪድዮ ላይ Faith Alone የሚለውን የሉተር ትምህርት የኦርቶዶክስ ቆብ ደፍተው ሲሰብኩ ትንሽ እንኩዋን አላፈሩም:: በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተሹመው ተሸልመው ክህደት እያስተማሩ መቀጠል እንደማይቻል ለማሳየትና አንዴ ከጰጰሱ ምንም አይኮንም ዓይነት አመለካከትን ለማረም ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ዕድል ሊጠቀም ይገባዋል:: በ3ኛው ክፍለ ዘመን ጳውሎስ ሳምሰጢ (Paul of Samosata) በአንጾኪያ ሲኖዶስ የተወገዘው ፣ ንስጥሮስ በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተወገዘው ጳጳስ ከሆኑ በኋላ ነው:: ቤተ ክርስቲያን መናፍቃንን ለመለየት ጵጵስናቸውን ፈርታ አታውቅም::
በወላዲተ አምላክ የነገረ ድኅነት ሱታፌ ላይ በጳጳስ ደረጃ ሲቀለድ አይተን ዝም ልንል አንችልም:: ከቅዱስ ሲኖዶስ ጠንከር ያለ ውሳኔ እንጂ ማስተባበያ አንጠብቅም:: የተነቃነቀ ጥርስ ቀን ይጠብቃል እንጂ መውለቁ አይቀርም:: እንደ ተራ ስኅተት ይቅርታ እንዲጠይቁም አንጠብቅም:: ያስተማሩት የታሰበበት ክህደት ነውና የተብራራ መልስ ከቀኖና ጋር እንጠብቃለን:: "የበራላቸው" ለመባል የብርሃን እናትን ሊጋርዱ የሚጥሩ ሰዎች ማላገጫ ሆነንም አንቀርም::
ሙሴ ቤዛ በተባለበት መጽሐፍ ቅዱስ እያመኑ ድንግል ማርያም ቤዛ አትባልም ላሉት ጳጳስ ቅዱስ ሲኖዶስ ቤዛ ሲሆናቸው ማየት አንፈልግም:: ጠንከር ያለ ቀኖናዊ እርምጃ እንጠብቃለን::
ርጉመ ይኩን ዘይረግመኪ
ወቡሩከ ይኩን ዘይባርከኪ
ነገራተ ክልዔ ኢይርሳዕ ልብኪ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ገሊላ ፳ኤል
ሚያዝያ 15 2017 ዓ.ም.
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ሰበር ሰበር ዜና
የኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ።
*****
ሚያዚያ ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
*****
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
++++++++++++
መምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር በጻፈው ደብዳቤ ማኅበሩ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቱዕ እምነትን ከሥነ ምግባር ጋር ይዞ የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያን ያሳዘነ፣ እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለጠላት መሳለቂያ እንድትሆን ያደረገ ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ጋር የሚቃረን እመቤታችን
ቤዛ አይደለችም የሚል ጤናማ ያልሆነ ትምህርት ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓም በማኅበሩ ሚዲያ ማስተላለፉን እንደተመለከተ ገልጾ የማኀበራት ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጸድቆ በተሰጠው ደንብ መሠረት በማኅበራት መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ጥያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮች ሲፈጠሩ ተገቢውን ክትትልና አስፈላጊውን እርምት የመስጠት ሓላፊነት ያለበት በመሆኑ በደብዳቤው ለተጠቀሱ አምስት ነጥቦችን በማኅበሩ በኩል አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥባቸው በጥብቅ አሳስቧል።
መምሪያው በጻፈው ደብዳቤ ላይም በዕለተ ስቅለት የተላለፈው ትምህርት ቪዲዩ በአስቸኳይ ከማኅበሩ ዩቲዩብ እንዲወርድ እንዲያደርግና በዕለቱ የተላለፈውን ትምህርት ሙሉ ቪዲዮ ቅጂ ለመምሪያው እንዲያቀርብ ጥብቅ መመሪያ ሰጥቷል።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
የኢ/ ኦ/ተ/ቤ/ ክ/የኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አስቸኳይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ።
*****
ሚያዚያ ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
*****
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
++++++++++++
መምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር በጻፈው ደብዳቤ ማኅበሩ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቱዕ እምነትን ከሥነ ምግባር ጋር ይዞ የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያን ያሳዘነ፣ እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለጠላት መሳለቂያ እንድትሆን ያደረገ ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ጋር የሚቃረን እመቤታችን
ቤዛ አይደለችም የሚል ጤናማ ያልሆነ ትምህርት ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓም በማኅበሩ ሚዲያ ማስተላለፉን እንደተመለከተ ገልጾ የማኀበራት ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ጸድቆ በተሰጠው ደንብ መሠረት በማኅበራት መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ጥያቄ የሚያስነሱ ጉዳዮች ሲፈጠሩ ተገቢውን ክትትልና አስፈላጊውን እርምት የመስጠት ሓላፊነት ያለበት በመሆኑ በደብዳቤው ለተጠቀሱ አምስት ነጥቦችን በማኅበሩ በኩል አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥባቸው በጥብቅ አሳስቧል።
መምሪያው በጻፈው ደብዳቤ ላይም በዕለተ ስቅለት የተላለፈው ትምህርት ቪዲዩ በአስቸኳይ ከማኅበሩ ዩቲዩብ እንዲወርድ እንዲያደርግና በዕለቱ የተላለፈውን ትምህርት ሙሉ ቪዲዮ ቅጂ ለመምሪያው እንዲያቀርብ ጥብቅ መመሪያ ሰጥቷል።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶት የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው መታገዱ ተገለጸ።
ሚያዝያ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚሰሩ ኦርቶዶክሳውያን የሚዲያ ተቋማት በአንድ ማዕከል እንዲያገለግሉ፣ የመረጃ ፍሰቱ ወጥነት ያለውና ተቋማዊ መሆን ይችል ዘንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የሁለት ቀናት ሥልጠና ተሰጥቶ የቤተ ክርስቲያን መሠረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብረው በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ ማከናወን የሚችሉበት ፈቃድ ከመምሪያው መሰጠቱ ይታወሳል።
ከእነዚህ የሚዲያ ተቋማት መካከልም የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን አንዱ ሆኖ ዘገባዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት "ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም።" በሚል ርእስ የተላለፈው ትምህርትን ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያችን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው የታገደ መሆኑን እንገልጻለን።
ምንጭ:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
@ortodoxtewahedo
ሚያዝያ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚሰሩ ኦርቶዶክሳውያን የሚዲያ ተቋማት በአንድ ማዕከል እንዲያገለግሉ፣ የመረጃ ፍሰቱ ወጥነት ያለውና ተቋማዊ መሆን ይችል ዘንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የሁለት ቀናት ሥልጠና ተሰጥቶ የቤተ ክርስቲያን መሠረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብረው በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ ማከናወን የሚችሉበት ፈቃድ ከመምሪያው መሰጠቱ ይታወሳል።
ከእነዚህ የሚዲያ ተቋማት መካከልም የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን አንዱ ሆኖ ዘገባዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል።
ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት "ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም።" በሚል ርእስ የተላለፈው ትምህርትን ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያችን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው የታገደ መሆኑን እንገልጻለን።
ምንጭ:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
@ortodoxtewahedo
‘’ክብር በምግብ ቢሆን ጅብ ይበልጠን ...
ሀገሬ ቴሌቪዥን Hagerie TV
✝ክብር በምግብ ቢሆን ጅብ ይበልጠን ነበር✝
ቆይታ ከሀገሬ ቴሌቪዥን ጋር
Size:-83.4MB
Length:-1:30:06
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ቆይታ ከሀገሬ ቴሌቪዥን ጋር
Size:-83.4MB
Length:-1:30:06
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
+++ ይህ የአባቶቻችን የሐዋርያት ትዕዛዝ ነው፡፡
ሰው በልቦናው ቂምንና በቀልን ቅንዓትንና ጠብን
በባልንጀራው ላይ በማንም ላይ ቢሆን አይያዝ፡፡
+++
~~~~ ቅዳሴ ~~~
@ortodoxtewahedo
ሰው በልቦናው ቂምንና በቀልን ቅንዓትንና ጠብን
በባልንጀራው ላይ በማንም ላይ ቢሆን አይያዝ፡፡
+++
~~~~ ቅዳሴ ~~~
@ortodoxtewahedo
"ድንግል ሆይ አንቺን የሰደበ ሰው እንዴት ይኖራል " አይኖርም እንጂ ምክንያቱም በልጅሽ የፍርድ መፅሐፍ ላይ እናት አባቱን የሰደበ ሰው ይሙት ይላል የጌታን እናት ሰድቦ እንዴት ይኖራል።
#አባ ፅጌ ድንግል
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#አባ ፅጌ ድንግል
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#ምክረ አበው!
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው"
#ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል"
#ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
#ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
#ቅዱስ ባስልዮስ
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር"
#ሊቁ ጠርጡለስ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው"
#ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል"
#ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
#ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
#ቅዱስ ባስልዮስ
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር"
#ሊቁ ጠርጡለስ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
🌿 🌿 🌿 🌿 🌿 🌿 🌿 🌿 🌿
#እንኳን_ለዳግመ_ትንሣኤ_አደረሳችሁ_በአሉ_የሰላም_የፍቅር_የደስታ_በአል_ይሁንላችሁ!!!
#ዳግመ_ትንሳኤ!!!
ዳግመ ትንሳኤ የተባለበት ምክንያት፦ዳግም ትንሳኤ ሲባል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ ተቀብሮ ዳግም ተነሳ ሳይሆን በድጋሜ ቅዱስ ቶማስ ባለበት ልክ በመጀመሪያ እንደተገለጠላቸው ሆኖ ስለታያቸው ነው።
#ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአስሩ ሀዋርያት ሲገለጥላቸው ሀዋርያው ቶማስ አልነበረም መጥቶ በተገናኛቸው ጊዜ እሱም ጌታችን እንደተነሳ መጥቶ ሰላምታ እንደሰጣቸው እንዳዩት ሲነግሩት ግን"የተቸነከረውን እጅና እግሩን በጦር የተወጋውን ጎኑን ካላየሁ አላምንም አለ።"ዮሐ 20:25 ይሄን ሊል የቻለው ሀዋርያው ቶማስ የተጠራው ትንሳኤ ሙታን የለም ከሚሉት ከሰዱቃውያን ወገን ነበርና አንድም ሌሎች ሐዋርያት ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ አየነው እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን ሰማሁ ብዬ ላስተምር ነው።ጌታም የቶማስን ጥርጣሬ ያስወግድለት ዘንድ በተነሳ በስምንተኛው ቀን ቅዱስ ቶማስ ከሌሎች ሐዋር ጋር ሳለ እንደገና በትንሳኤ እንዲታያቸው ሆኖ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ሀዋርያው ቶማስን ለይቶ"ቶማስ ቶማስ ና በችንካር የተቸኘከሩ እጆቼን እይ እንዲሁም እጅህን አምጥተህ በጦር ወደተወጋው ጎኔ አግብተህ ዳሰኝ ያመንክ እንጂ ተጠራጣሪ አትሁን ባለው ጊዜ ቶማስ እጁን በጦር የተወጋ ጎኑን በእጆቹ በዳሰሰ ጊዜ ከእሳት እንደገባ ጅማት ኩምትርትር ሲል ጌታዬ አምላኬ ብሎ ተጣራ አምላክነቱንም መሰከረ።አንተ አይተሃል አምነሃል ነገር ግን"ሳያዩ የሚያምኑ ብፁአን ናቸው"ብሎ ፈውሶታል።ዮሐ 20:29 በአከባበር ስርአት የመጀመሪያውን ትንሳኤ ስለሚመስል ነው።ትንሳኤ እለቱ የሚባለው እግዚአብሔር ሳይለወጥ በሙሉ በዚህ ቀን ይደገማል።ከዚህም ሌላ፦
#ሁለት_መጠሪያ_ስሞች_አሉት።
እነዚህም"ፈጸምነ አግብአተ ግብር"ይባላሉ።
1.ፈጸምነ የተባለበትም፣የሰሞነ ትንሳኤ በአል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው።
2.አግብአተ ግብር የተባለበትም፤ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ"አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ....እኔ ልሰራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር ላይ አከበርኩህ"ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው።ዮሐ 17:4
🌿ወስብሐት ለእግዚአብሔር🌿
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#እንኳን_ለዳግመ_ትንሣኤ_አደረሳችሁ_በአሉ_የሰላም_የፍቅር_የደስታ_በአል_ይሁንላችሁ!!!
#ዳግመ_ትንሳኤ!!!
ዳግመ ትንሳኤ የተባለበት ምክንያት፦ዳግም ትንሳኤ ሲባል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ ተቀብሮ ዳግም ተነሳ ሳይሆን በድጋሜ ቅዱስ ቶማስ ባለበት ልክ በመጀመሪያ እንደተገለጠላቸው ሆኖ ስለታያቸው ነው።
#ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአስሩ ሀዋርያት ሲገለጥላቸው ሀዋርያው ቶማስ አልነበረም መጥቶ በተገናኛቸው ጊዜ እሱም ጌታችን እንደተነሳ መጥቶ ሰላምታ እንደሰጣቸው እንዳዩት ሲነግሩት ግን"የተቸነከረውን እጅና እግሩን በጦር የተወጋውን ጎኑን ካላየሁ አላምንም አለ።"ዮሐ 20:25 ይሄን ሊል የቻለው ሀዋርያው ቶማስ የተጠራው ትንሳኤ ሙታን የለም ከሚሉት ከሰዱቃውያን ወገን ነበርና አንድም ሌሎች ሐዋርያት ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ አየነው እያሉ ሲያስተምሩ እኔ ግን ሰማሁ ብዬ ላስተምር ነው።ጌታም የቶማስን ጥርጣሬ ያስወግድለት ዘንድ በተነሳ በስምንተኛው ቀን ቅዱስ ቶማስ ከሌሎች ሐዋር ጋር ሳለ እንደገና በትንሳኤ እንዲታያቸው ሆኖ በዝግ ቤት ገብቶ ሰላምታ ከሰጣቸው በኋላ ሀዋርያው ቶማስን ለይቶ"ቶማስ ቶማስ ና በችንካር የተቸኘከሩ እጆቼን እይ እንዲሁም እጅህን አምጥተህ በጦር ወደተወጋው ጎኔ አግብተህ ዳሰኝ ያመንክ እንጂ ተጠራጣሪ አትሁን ባለው ጊዜ ቶማስ እጁን በጦር የተወጋ ጎኑን በእጆቹ በዳሰሰ ጊዜ ከእሳት እንደገባ ጅማት ኩምትርትር ሲል ጌታዬ አምላኬ ብሎ ተጣራ አምላክነቱንም መሰከረ።አንተ አይተሃል አምነሃል ነገር ግን"ሳያዩ የሚያምኑ ብፁአን ናቸው"ብሎ ፈውሶታል።ዮሐ 20:29 በአከባበር ስርአት የመጀመሪያውን ትንሳኤ ስለሚመስል ነው።ትንሳኤ እለቱ የሚባለው እግዚአብሔር ሳይለወጥ በሙሉ በዚህ ቀን ይደገማል።ከዚህም ሌላ፦
#ሁለት_መጠሪያ_ስሞች_አሉት።
እነዚህም"ፈጸምነ አግብአተ ግብር"ይባላሉ።
1.ፈጸምነ የተባለበትም፣የሰሞነ ትንሳኤ በአል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው።
2.አግብአተ ግብር የተባለበትም፤ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ"አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ....እኔ ልሰራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር ላይ አከበርኩህ"ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው።ዮሐ 17:4
🌿ወስብሐት ለእግዚአብሔር🌿
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ተገናኝቶ ሻይ ቡና ብሎ መለያየት ❌
ተገናኝቶ አንድ ሁለት ብሎ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ስለ ኳስ ስለ ፊልም አውርቶ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ስለ ሰው አውርቶ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ሃጢአት ሰርቶ መለያየት ❌
#ተገናኝቶ_አብሮ_ንስሐ_ገብቶ_አብሮ_መቁረብ። 🙏🙏🙏
(አንዳንድ እህቶች እና ወንድሞች ቅዱስ ቁርባን እንደሚፈሩት እግዚአብሔርን ቢፈሩት መልካም ነበር። ቅዱስ ቁርባን ፈርተው ይቀርቡታል እንጂ ፈርተው አይርቁትም፥ የቅዱስ ቁርባን ክብሩ እኛ ስንቀበለው ነው። ከቆረብኩ በኋላ ሀጢአት ብሰራ ባል ባላገኝ ወዘተ የሚሉ ሰይጣናዊ ህሳቤዎችን ወደጎን በመተው ጉዞ ወደ ቅዱስ ቁርባን።)
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ተገናኝቶ አንድ ሁለት ብሎ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ስለ ኳስ ስለ ፊልም አውርቶ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ስለ ሰው አውርቶ መለያየት ❌
ተገናኝቶ ሃጢአት ሰርቶ መለያየት ❌
#ተገናኝቶ_አብሮ_ንስሐ_ገብቶ_አብሮ_መቁረብ። 🙏🙏🙏
(አንዳንድ እህቶች እና ወንድሞች ቅዱስ ቁርባን እንደሚፈሩት እግዚአብሔርን ቢፈሩት መልካም ነበር። ቅዱስ ቁርባን ፈርተው ይቀርቡታል እንጂ ፈርተው አይርቁትም፥ የቅዱስ ቁርባን ክብሩ እኛ ስንቀበለው ነው። ከቆረብኩ በኋላ ሀጢአት ብሰራ ባል ባላገኝ ወዘተ የሚሉ ሰይጣናዊ ህሳቤዎችን ወደጎን በመተው ጉዞ ወደ ቅዱስ ቁርባን።)
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
***
ሚያዚያ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ዘ፯ ዓ.ም
+++++++++++++++++++
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
"""""""""""""""""""""""""""
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል።
መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation ,EOTC ነው።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
***
ሚያዚያ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ዘ፯ ዓ.ም
+++++++++++++++++++
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
"""""""""""""""""""""""""""
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል።
በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣
2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣
3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል።
መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation ,EOTC ነው።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#ሊቀ ሰማዕታት ፀሐይ ዘልዳ
#ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡-
ጊዮርጊስ ማለት ‹‹ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ›› ማለት ነው፡፡ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀገሩ ፍልስጤም ልዩ ስሟ ልዳ ሲሆን የተወለደው በ277 ዓ.ም ጥር 20 ቀን ነው፡፡ አባቱ ዞሮንቶስ ወይም አንስጣስዮስ የ...ልዳ መኳንንት ሆኖ ተሹሞ ይኖር ነበር፤ እናቱ ቴዎብስታ ወይም አቅሌስያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ሌላ ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዳለች፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐሥር ዓመት በሆመው ጊዜ አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ አሳደገው፡፡ መድፍኑም በጦር ኃይል አሰለጠነው፡፡ ሃያ ዓመትም በሞላው ጊዜ መስፍኑ የ15 ዓመት ቆንጆ ልጅ ነበረችውና እርሷን አግብቶ ሀብቴን ወርሶ ይኑር ብሎ ድግስ ሲያስደግስ ጌታችን ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ፡፡ በቤሩት ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጆቻቸውን ይገብሩለት ስለነበር ሰማዕቱ ደራጎኑን በኃይለ መስቀል ድል ነስቶት ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል፡፡
ወደፋርስ ቢመለስ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት አቁሞ ሲሰግድ ሲያሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖቱ ቀናዒ ነውና ከቤተመንግስቱ ገብቶ በከሃዲያኑ ሰባው ነገሥታት ፊት ክርስቲያን መሆኑን በመመስከር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ዱድያኖስም ማንነቱን ከተረዳ በኋላ ‹‹አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ‹‹ሹመት ሽልማትህ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ዱድያኖስ እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን ‹‹ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት›› በማለት መከራውን ይታገስ ዘንድ ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ፈቃዱን ይፈጽምለት ብዙ በመከራው ሁሉ ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ ሦስት ጊዜም ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡
በመጀመሪያም ዱድያኖስ በእንጨት ላይ ካሰቀለው በኋላ ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምቶት ሂድ አለው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ሥጋውንም በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ነሰነሰበት፡፡ ሥጋውም ተቆራርጦ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ከፈወሰውና ‹‹ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ›› ካለው በኋላ በመከራውም ሁሉ እርሱ እንደማይለየው ነገረው፡፡
ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከዚያ ካደረሰበት አሠቃቂ መከራዎች ሁሉ ድኑ ፍጹም ጤነኛ መሆኑን በተመለከተ ጊዜ እጅግ ደንግጦ ‹‹የሚያሸንፍልኝ ቢኖር ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ›› ብሎ ተናገረ፡፡ አትናስዮስ የተባለ መሰርይ አንዲትን ላም በጆሮዋ ሲያንሾካሹክባት ለሁለት ተሰንጥቃ ስትሞት ለንጉሡ አሳየውና ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲሚያሸንፍ ምልክት አሳየ፡፡ ንጉሡም ያሸንፍልኛል ብሎ ደስ አለው፡፡ መሰርይውም ሆድ በጥብጦ አንጀት ቆራርጦ የሚገድል መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት እንዲጠጣው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፡፡ በዚህም ጊዜ ጠንቋዩ ማረኝ ብሎ ከእግሩ ሥር ወደቀ፡፡
+
ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በመንኰራኩር አስፈጭቶ ከትልቅ ጉድጓድ ጥሎት ደንጊያ ዘግቶበት አትሞበት ሄደ፡፡ ጌታችንም የተፈጨውን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ በእጁ ዳስሶ ፈውሶታል፡፡ ወደ ከሃዲውም ንጉሥ ተመልሶ ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› በማለት መሰከረ፡፡ ንጉሡም ዳግመኛ በብረት አልጋ አስቸንክሮ ከበታቹ እሳት አነደደበት ነገር ግን እሳቱ ደሙ ሲንጠባጠብበት ጠፍቷል፡፡ ጌታችንም ፈወሰው፡፡ ከዚህም በኋላ ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ‹‹ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አሳየኝ›› ቢለው የለመለሙትን ዕፅ አድርቆ፣ የደረቁትን ደግሞ አለምልሞ፣ ከሞቱ 430 ዓመት የሆናቸውን ሙታንን አስነሥሰቶ አሳይቶታል፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ልቡ ክፉ ነውና በርኃብና በጽም ይሙት ብሎ ምንም ከሌላት መበለት ቤት አሳስሮታል። እርሷም የሚቀመስ ስትፈልግ ቤቷን በእህል አትረፍርፎ የታሰረበትን ግንድ ማለትም የቤቱን ምሰሶ አለምልሞታል፡፡ ልጇም ጆሮው የማይሰማ ነበርና ፈወሰላት፡፡ መበለቲቷንም ከነልጆቿ አጥምቆአቸው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከእስራቱ ፈትቶት ተመልሷል፡፡
ዳግመኛም ንጉሡ ዱድያኖስ ጭፍሮቹን ‹‹በመንኰራኩር ፈጭታችሁ አጥንቱን ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ ወስዳችሁ ዝሩት›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥጋ በመንኰራኩር ፈጭተው ወስደው በተራራው ላይ ቢረጩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣ ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ ‹‹ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣ ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር›› እያሉ አመስግነዋል፡፡ አሁንም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣውና ሥጋውን ፈጭተው በተራራም ላይ ሥጋውን በትነውት ወደ ንጉሡ የሚመለሱትን ወታደሮች በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ ደረሰባቸውና ‹‹ቆዩኝ ጠብቁኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እጅግ ደንግጠው ይህ እንዴት እንደሆነ ሲጠይቁት ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› አላቸው፡፡ ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠው ከእግሩ ስር ወድቀው ይቅር በለን ብለው በአምላኩ እንደሚያምኑ መሰከሩለት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከመሬት ላይ ውሃ አመንጭቶ በጸሎት ጌታችንን ቢጠይቅ ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ አጥምቋቸዋል፡፡ እነርሱም በንጉሣቸው ፊት ሄደው ስለጌታችን በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐፅሙ ተቃጥሎ አጥንቱ ተፈጭቶ በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የተበተነው በዛሬዋ ዕለት ነው፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፤ የዓሥራት አገሩን ቅድስት ኢትዮጵያን ይጠብቅልን፡፡
#ምንጭ፡ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
፠፠፠
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የወለድ የመንፈስ ቅዱስ ልባቸው አብ ሆይ ላንተ ሰላምታ ይገባሃል፡፡
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የአብ ፤ የመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ወልድ ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል፡፡
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የአብና የወልድ ሕይወታቸው እስትንፋሳቸው መንፈስ ቅዱስ ሆይ ላንተ ሰላምታ ይገባሃል፡፡
+ የፀጋው ብዛት የማይታወቅ: ከዋክብት የሚያመሰግኑት በስማቸውም የሚጠራቸው: ጌታችን አምላካችና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሥጢሩን ይግለጽልን: ክብር ምስጋና ይግባው።
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር
ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ ድ ን ግ ል
ወ ለ መ ስ ቀ ሉ ክ ቡ ር
†† † † ††
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#ቅዱስ_ጊዮርጊስ፡-
ጊዮርጊስ ማለት ‹‹ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ›› ማለት ነው፡፡ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀገሩ ፍልስጤም ልዩ ስሟ ልዳ ሲሆን የተወለደው በ277 ዓ.ም ጥር 20 ቀን ነው፡፡ አባቱ ዞሮንቶስ ወይም አንስጣስዮስ የ...ልዳ መኳንንት ሆኖ ተሹሞ ይኖር ነበር፤ እናቱ ቴዎብስታ ወይም አቅሌስያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ሌላ ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዳለች፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐሥር ዓመት በሆመው ጊዜ አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ አሳደገው፡፡ መድፍኑም በጦር ኃይል አሰለጠነው፡፡ ሃያ ዓመትም በሞላው ጊዜ መስፍኑ የ15 ዓመት ቆንጆ ልጅ ነበረችውና እርሷን አግብቶ ሀብቴን ወርሶ ይኑር ብሎ ድግስ ሲያስደግስ ጌታችን ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ፡፡ በቤሩት ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጆቻቸውን ይገብሩለት ስለነበር ሰማዕቱ ደራጎኑን በኃይለ መስቀል ድል ነስቶት ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል፡፡
ወደፋርስ ቢመለስ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት አቁሞ ሲሰግድ ሲያሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖቱ ቀናዒ ነውና ከቤተመንግስቱ ገብቶ በከሃዲያኑ ሰባው ነገሥታት ፊት ክርስቲያን መሆኑን በመመስከር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ዱድያኖስም ማንነቱን ከተረዳ በኋላ ‹‹አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ‹‹ሹመት ሽልማትህ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ዱድያኖስ እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን ‹‹ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት›› በማለት መከራውን ይታገስ ዘንድ ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ፈቃዱን ይፈጽምለት ብዙ በመከራው ሁሉ ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ ሦስት ጊዜም ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡
በመጀመሪያም ዱድያኖስ በእንጨት ላይ ካሰቀለው በኋላ ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምቶት ሂድ አለው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ሥጋውንም በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ነሰነሰበት፡፡ ሥጋውም ተቆራርጦ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ከፈወሰውና ‹‹ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ›› ካለው በኋላ በመከራውም ሁሉ እርሱ እንደማይለየው ነገረው፡፡
ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከዚያ ካደረሰበት አሠቃቂ መከራዎች ሁሉ ድኑ ፍጹም ጤነኛ መሆኑን በተመለከተ ጊዜ እጅግ ደንግጦ ‹‹የሚያሸንፍልኝ ቢኖር ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ›› ብሎ ተናገረ፡፡ አትናስዮስ የተባለ መሰርይ አንዲትን ላም በጆሮዋ ሲያንሾካሹክባት ለሁለት ተሰንጥቃ ስትሞት ለንጉሡ አሳየውና ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲሚያሸንፍ ምልክት አሳየ፡፡ ንጉሡም ያሸንፍልኛል ብሎ ደስ አለው፡፡ መሰርይውም ሆድ በጥብጦ አንጀት ቆራርጦ የሚገድል መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት እንዲጠጣው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፡፡ በዚህም ጊዜ ጠንቋዩ ማረኝ ብሎ ከእግሩ ሥር ወደቀ፡፡
+
ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በመንኰራኩር አስፈጭቶ ከትልቅ ጉድጓድ ጥሎት ደንጊያ ዘግቶበት አትሞበት ሄደ፡፡ ጌታችንም የተፈጨውን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ በእጁ ዳስሶ ፈውሶታል፡፡ ወደ ከሃዲውም ንጉሥ ተመልሶ ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› በማለት መሰከረ፡፡ ንጉሡም ዳግመኛ በብረት አልጋ አስቸንክሮ ከበታቹ እሳት አነደደበት ነገር ግን እሳቱ ደሙ ሲንጠባጠብበት ጠፍቷል፡፡ ጌታችንም ፈወሰው፡፡ ከዚህም በኋላ ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ‹‹ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አሳየኝ›› ቢለው የለመለሙትን ዕፅ አድርቆ፣ የደረቁትን ደግሞ አለምልሞ፣ ከሞቱ 430 ዓመት የሆናቸውን ሙታንን አስነሥሰቶ አሳይቶታል፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ልቡ ክፉ ነውና በርኃብና በጽም ይሙት ብሎ ምንም ከሌላት መበለት ቤት አሳስሮታል። እርሷም የሚቀመስ ስትፈልግ ቤቷን በእህል አትረፍርፎ የታሰረበትን ግንድ ማለትም የቤቱን ምሰሶ አለምልሞታል፡፡ ልጇም ጆሮው የማይሰማ ነበርና ፈወሰላት፡፡ መበለቲቷንም ከነልጆቿ አጥምቆአቸው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከእስራቱ ፈትቶት ተመልሷል፡፡
ዳግመኛም ንጉሡ ዱድያኖስ ጭፍሮቹን ‹‹በመንኰራኩር ፈጭታችሁ አጥንቱን ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ ወስዳችሁ ዝሩት›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥጋ በመንኰራኩር ፈጭተው ወስደው በተራራው ላይ ቢረጩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣ ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ ‹‹ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣ ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር›› እያሉ አመስግነዋል፡፡ አሁንም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣውና ሥጋውን ፈጭተው በተራራም ላይ ሥጋውን በትነውት ወደ ንጉሡ የሚመለሱትን ወታደሮች በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ ደረሰባቸውና ‹‹ቆዩኝ ጠብቁኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እጅግ ደንግጠው ይህ እንዴት እንደሆነ ሲጠይቁት ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› አላቸው፡፡ ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠው ከእግሩ ስር ወድቀው ይቅር በለን ብለው በአምላኩ እንደሚያምኑ መሰከሩለት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከመሬት ላይ ውሃ አመንጭቶ በጸሎት ጌታችንን ቢጠይቅ ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ አጥምቋቸዋል፡፡ እነርሱም በንጉሣቸው ፊት ሄደው ስለጌታችን በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐፅሙ ተቃጥሎ አጥንቱ ተፈጭቶ በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የተበተነው በዛሬዋ ዕለት ነው፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን፤ የዓሥራት አገሩን ቅድስት ኢትዮጵያን ይጠብቅልን፡፡
#ምንጭ፡ ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
፠፠፠
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የወለድ የመንፈስ ቅዱስ ልባቸው አብ ሆይ ላንተ ሰላምታ ይገባሃል፡፡
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የአብ ፤ የመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ወልድ ሆይ ላንተ ምስጋና ይገባሃል፡፡
+ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድመህ የነበርክ ዛሬም ያለህ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የአብና የወልድ ሕይወታቸው እስትንፋሳቸው መንፈስ ቅዱስ ሆይ ላንተ ሰላምታ ይገባሃል፡፡
+ የፀጋው ብዛት የማይታወቅ: ከዋክብት የሚያመሰግኑት በስማቸውም የሚጠራቸው: ጌታችን አምላካችና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሥጢሩን ይግለጽልን: ክብር ምስጋና ይግባው።
ወ ስ ብ ሐ ት ለ እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር
ወ ለ ወ ላ ዲ ቱ ድ ን ግ ል
ወ ለ መ ስ ቀ ሉ ክ ቡ ር
†† † † ††
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
#ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ
እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የዕረፍቱ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን !!!
" እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው።"
መዝ.፷፯፥፴፭ /67፥35/
✝️ ገና በሃያ ዓመት ዕድሜው የአባቱን መዓረግ ለመቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ በሄደ ጊዜ ንጉሡ ሕዝቡ ጣኦት ያመልክ ዘንድ ያስገድድ ስለነበረ በንጉሡ ሥራ አዘነ
✝️ በንጉሡ ሥራ የተናደደው ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለውን ንብረት ሸጦ ለድሆች ሰጠ፣ ከባርነትም አወጣቸው
✝️ በኢየሱስ ክርስቶስ ታምኖ ክርስትናውን ጠብቆ ለጣኦት መሰግድን አሻፈረኝ አለ
✝️ በዚህም ብዙ መከራና ስቃይ ደረሰበት፤ በብዙ ሕማምና ስቃይ አለፈ፤ በተደጋጋሚም ስጋውን ገደሉ
✝️ የክብር ጌታ፣ የታመነለት አምላክም ደጋግሞ አስነሳው
✝️ ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለው ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕረፍቱ ሚያዚያ ፳፫ ቀን ሆነ
የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በረከትና ምልጃ ይደርብን። አሜን።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የዕረፍቱ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን !!!
" እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው።"
መዝ.፷፯፥፴፭ /67፥35/
✝️ ገና በሃያ ዓመት ዕድሜው የአባቱን መዓረግ ለመቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ በሄደ ጊዜ ንጉሡ ሕዝቡ ጣኦት ያመልክ ዘንድ ያስገድድ ስለነበረ በንጉሡ ሥራ አዘነ
✝️ በንጉሡ ሥራ የተናደደው ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለውን ንብረት ሸጦ ለድሆች ሰጠ፣ ከባርነትም አወጣቸው
✝️ በኢየሱስ ክርስቶስ ታምኖ ክርስትናውን ጠብቆ ለጣኦት መሰግድን አሻፈረኝ አለ
✝️ በዚህም ብዙ መከራና ስቃይ ደረሰበት፤ በብዙ ሕማምና ስቃይ አለፈ፤ በተደጋጋሚም ስጋውን ገደሉ
✝️ የክብር ጌታ፣ የታመነለት አምላክም ደጋግሞ አስነሳው
✝️ ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለው ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕረፍቱ ሚያዚያ ፳፫ ቀን ሆነ
የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በረከትና ምልጃ ይደርብን። አሜን።
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
🔴 እንደ አባቶቼ አምናለሁ || እመቤታ...
ፈውስ መንፈሳዊ ጣና ቅ/ቂርቆስ ፬ መጻሕፍተ ጉባኤ ሚዲያ Fews Menfesawi
✝እንደ አባቶቼ አምናለሁ✝
ድንግል ማርያም ቤዛዊት ናት
Size:-67.5MB
Length:-1:12:55
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
ድንግል ማርያም ቤዛዊት ናት
Size:-67.5MB
Length:-1:12:55
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ለመቀላቀል 👉 @ortodoxtewahedo
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ተስፋ የምናደርጋት ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን ፤ እንሞትባታለን ፤ በእግዚአብሔር ፍቃድ እንነሣባታለን "
ሃይማኖተ አበው
እንቁ መምህራችን የሆኑት እዮብ ይመኑ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ናለድ ሊንክ ይግቡ❤️
የይቱብ ቻናላችን ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
ሃይማኖተ አበው
እንቁ መምህራችን የሆኑት እዮብ ይመኑ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ናለድ ሊንክ ይግቡ❤️
የይቱብ ቻናላችን ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9