Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
📚👉መናፍቃን ከሚያነሷቸው 3 ጥያቄዎች መካከል⁉️
1)የጌታችን እኔ የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለበት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው። አሁኑኑ ይቀላቀሉ በማርያም ❗️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
👇👇👇
🔔
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ስብከት⛪️
🤗ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🤗
❤️ትምህርቱን በይቱብ❤️
ከታች ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇🏽👇🏽
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
1)የጌታችን እኔ የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለበት።
2)የጌታችን እናት አልተነሳችም
3)ኢየሱስ ክርስቶስ አማላጅ ነው።
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት መልስ የሚያገኙበት ቻናል ነው። አሁኑኑ ይቀላቀሉ በማርያም ❗️
👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲ █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
👇👇👇
🔔
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ስብከት⛪️
🤗ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🤗
❤️ትምህርቱን በይቱብ❤️
ከታች ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇🏽👇🏽
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓
እኒህ ሦስቱ:-
፩. የተሸከሙት ሸክም ያላጎበጣቸው
፪. የመከራ ቀን ጥብዐታቸው
፫. መከራውን ያለፉበት ጥበባቸው
፬. ለሲኖዶሳዊ ልዕልና ተጋድሏቸው
እናት ቤተ ክርስቲያንን በጃት!
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
፩. የተሸከሙት ሸክም ያላጎበጣቸው
፪. የመከራ ቀን ጥብዐታቸው
፫. መከራውን ያለፉበት ጥበባቸው
፬. ለሲኖዶሳዊ ልዕልና ተጋድሏቸው
እናት ቤተ ክርስቲያንን በጃት!
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
#ሐዋርያት ፳፥፳፰
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
አባ ሳዊሮስን በአጭሩ - ግቡና መርምሩ
+ + + + +
ባለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት ቤተክርስቲያን መከራ በምትቀበልባቸው ወቅቶች፣ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ስታልፍ... አንድ አይነት አሻራ ወይም አንድ አካል ከሁነቶቹ ጋር ተያይዞ ሲነሳ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሚነድ እሳት ጀርባ ከሚጨስ ጭስ ጀርባ ክብሪት እጃቸው ላይ የሚገኝ ሰው። ይህ አጋጣሚ ብቻ ለመሆኑ ግራ ያጋባኛል። እስኪ ጥቂት አጋጣሚዎችን እናንሳ፦
👉 ዘጠናዎቹ መጨረሻ የሚሊንየሙ መጀመሪያ ቤተክርስቲያንን ሊውጥ የመጣው ተሐድሶ ልባችንን በእሳት ሲለበልበው በነበረበት ወሳኝ ወቅት... እሳቸው ከሌሎቹ አባቶች በልዩነት የተሐድሶዎችን የቴሌቪዥን ፕሮግራም (የታኦሎጎስ)፣ የአደራሽ (የቦሌ ፋና ፓርክ) ገባኤያቸውን ሲባርኩ ነበር!
👉 በየ ሀገረ ስብከቱ የቤተክርስቲያንን ቀኖና የጣሱ የተሐድሶ አራማጆች ሲታገዱና ሲወገዱ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ግን እነዚሁ አራማጆች ያለ ማንም ከልካይ በአውደ ምህረት ላይ ሲፈነጩ... እሳቸው በግልጽ ማንም እንዳይነካቸው ከለላ ይሰጡ ነበር!
👉 ቤተክርስቲያን አንድነቷን ተነጥቃ በሕገወጥ መንገድ "የኦሮሚያ ቤተክህነት" የሚባል አካል ሲመሰረት... ከነ ቀሲስ በላይ ጀርባ እርሳቸው ነበሩ!
👉 የቤተክርስቲያንን መሠረት ያናጋው፣ ልብንም ያቆሰለው መፈንቅለ ሲኖዶስና መፈንቅለ ፓትርያሪክ ሙከራ ሲደረግ፣ ያ የጫካ ውስጥ የሕገወጥ ሹመት ሲካሄድ... አቡነ ሳዊሮስ ከዋነኛ ተዋናዮቹ መካከል ዋነኛው ሰው ነበሩ!
👉 አንዳንድ አባቶች መንበረ ሰላማ በሚል ሽፋን ከእናት ቤተክርስቲያን ህጋዊ ሲኖዶስ ሲለዩና ሲገነጠሉ... እሳቸው መቀሌ ተጉዘው "በርቱ!" የሚል የማበረታቻ መልእክት ያስተላለፉ ሰው ነበሩ!
👉 በተደጋጋሚ በገንዘብ የኑፋቄ እንቅስቃሴዎችን በቤተክርስቲያን ላይ ከሚያደርገው ጸጋዬ ሮቶ (ፍኖተ ጽድቅ) ጀርባ... አለምገና ሰበታ ላይ ባለው ኢንቨስትመንት ተጠቅሞ ቤተክርስቲያንን ሲያደማ ከለላው እሳቸው ነበሩ!
👉 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቤተክርስቲያንን ህልውና ለመጋፋት በሚመስል መልኩ በክልል ደረጃ ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጪ የሐይማኖት ጉባኤ አደረጃጀት ሲፈጥር... እሳቸው ከጀርባ ነበሩ! ከፍ ብሎም የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖቶ ሰብሳቢ ሆነዋል!
👉 እነሆ ብልጽግና ጥቅሙን የሚያስከብርለት የቤተክህነት ተሿሚ ሲሻ እሳቸው እጩ ስርአስኪያጅ ሆነው ብቅ ብለዋል።
ምንግዜም ቤተክርስቲያን ላይ ፈተና ሲመጣ እሳቸው ከጀርባ አሉ።
....
በብጹእ አባታችን በጎ በረከቶት ይደርብን አባታችን ይሄ ሁሉ አጋጣሚ ይሆን? እላለሁ፤
እርሶ ከወ/ር እጅጋየሁ ጀርባ ነበሩ፣ የበጋሻውም ከለላ ነበሩ፣ ቤተክርስቲያን ከሚፈትኑ ንኡስ ብሔርተኞችም አጋር ነበሩ፣ ከቀሲስ በላይና ከኃይለ ሚካኤል ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ቤ/ክህነት ምስረታ ላይ ቡራኬ ሰጪ ነበሩ፣ ቀጥሎም የቤተክርስቲያንን ህልውና ተጋፍተው በወሊሶ ጫካ መነኮሳትን ሊያጰጵሱ ሲሞክሩ ነበር፣ ቀጥሎም የፕትርክና ልብስ አሰፍተው መፈንቅለ ፓትርያርክ ሲያደርጉ ነበረ፣ ቀጥሎም የመንበረ ሰላማ ተገንጣዮቹን አይዟቹህ ሊሉ በአካል ሄደው ነበረ፣ ብልጽግና ቤተክርስቲያን ባሳነሰበት መድረክ ሁሉ እርሶ አሉ፣ አሁን ከስርአተ ቤተክርስቲያን ባፈነገጠ ሁኔታ በ5ኪሎ የ4ኪሎ ፖሊት ቢሮ ለመሆን የስርአስኪያጅነት ቅስቀሳ እያስደረጉ ነው.... አባታችን ለቤተክርስቲያን እየጠቀምኳት ነው ብለው ያምናሉ?
...
Maryamawit Henok Lemessa
+ + + + +
ይኽም ኾኖ ሲኖዶስ የጸሐፊነት ዕድል ሰጥቷቸው ነበረ። ያኔ ያጠፉት ብዛት ቀላል አልነበረም። ከሲኖዶሱ አባላት አንድም ጊዜ ወይ በጸሐፊነት ወይ በሥራ አስኪያጅነት ያላገለገሉ ሞልተዋል። ወደዚያ ማማተሩ ይሻላል።
+ + + + +
ባለፉት ሁለት አስርተ ዓመታት ቤተክርስቲያን መከራ በምትቀበልባቸው ወቅቶች፣ በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ስታልፍ... አንድ አይነት አሻራ ወይም አንድ አካል ከሁነቶቹ ጋር ተያይዞ ሲነሳ መስማት የተለመደ ሆኗል። ከሚነድ እሳት ጀርባ ከሚጨስ ጭስ ጀርባ ክብሪት እጃቸው ላይ የሚገኝ ሰው። ይህ አጋጣሚ ብቻ ለመሆኑ ግራ ያጋባኛል። እስኪ ጥቂት አጋጣሚዎችን እናንሳ፦
👉 ዘጠናዎቹ መጨረሻ የሚሊንየሙ መጀመሪያ ቤተክርስቲያንን ሊውጥ የመጣው ተሐድሶ ልባችንን በእሳት ሲለበልበው በነበረበት ወሳኝ ወቅት... እሳቸው ከሌሎቹ አባቶች በልዩነት የተሐድሶዎችን የቴሌቪዥን ፕሮግራም (የታኦሎጎስ)፣ የአደራሽ (የቦሌ ፋና ፓርክ) ገባኤያቸውን ሲባርኩ ነበር!
👉 በየ ሀገረ ስብከቱ የቤተክርስቲያንን ቀኖና የጣሱ የተሐድሶ አራማጆች ሲታገዱና ሲወገዱ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ግን እነዚሁ አራማጆች ያለ ማንም ከልካይ በአውደ ምህረት ላይ ሲፈነጩ... እሳቸው በግልጽ ማንም እንዳይነካቸው ከለላ ይሰጡ ነበር!
👉 ቤተክርስቲያን አንድነቷን ተነጥቃ በሕገወጥ መንገድ "የኦሮሚያ ቤተክህነት" የሚባል አካል ሲመሰረት... ከነ ቀሲስ በላይ ጀርባ እርሳቸው ነበሩ!
👉 የቤተክርስቲያንን መሠረት ያናጋው፣ ልብንም ያቆሰለው መፈንቅለ ሲኖዶስና መፈንቅለ ፓትርያሪክ ሙከራ ሲደረግ፣ ያ የጫካ ውስጥ የሕገወጥ ሹመት ሲካሄድ... አቡነ ሳዊሮስ ከዋነኛ ተዋናዮቹ መካከል ዋነኛው ሰው ነበሩ!
👉 አንዳንድ አባቶች መንበረ ሰላማ በሚል ሽፋን ከእናት ቤተክርስቲያን ህጋዊ ሲኖዶስ ሲለዩና ሲገነጠሉ... እሳቸው መቀሌ ተጉዘው "በርቱ!" የሚል የማበረታቻ መልእክት ያስተላለፉ ሰው ነበሩ!
👉 በተደጋጋሚ በገንዘብ የኑፋቄ እንቅስቃሴዎችን በቤተክርስቲያን ላይ ከሚያደርገው ጸጋዬ ሮቶ (ፍኖተ ጽድቅ) ጀርባ... አለምገና ሰበታ ላይ ባለው ኢንቨስትመንት ተጠቅሞ ቤተክርስቲያንን ሲያደማ ከለላው እሳቸው ነበሩ!
👉 የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቤተክርስቲያንን ህልውና ለመጋፋት በሚመስል መልኩ በክልል ደረጃ ከቤተክርስቲያን እውቅና ውጪ የሐይማኖት ጉባኤ አደረጃጀት ሲፈጥር... እሳቸው ከጀርባ ነበሩ! ከፍ ብሎም የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖቶ ሰብሳቢ ሆነዋል!
👉 እነሆ ብልጽግና ጥቅሙን የሚያስከብርለት የቤተክህነት ተሿሚ ሲሻ እሳቸው እጩ ስርአስኪያጅ ሆነው ብቅ ብለዋል።
ምንግዜም ቤተክርስቲያን ላይ ፈተና ሲመጣ እሳቸው ከጀርባ አሉ።
....
በብጹእ አባታችን በጎ በረከቶት ይደርብን አባታችን ይሄ ሁሉ አጋጣሚ ይሆን? እላለሁ፤
እርሶ ከወ/ር እጅጋየሁ ጀርባ ነበሩ፣ የበጋሻውም ከለላ ነበሩ፣ ቤተክርስቲያን ከሚፈትኑ ንኡስ ብሔርተኞችም አጋር ነበሩ፣ ከቀሲስ በላይና ከኃይለ ሚካኤል ጀርባ ሆነው የኦሮሚያ ቤ/ክህነት ምስረታ ላይ ቡራኬ ሰጪ ነበሩ፣ ቀጥሎም የቤተክርስቲያንን ህልውና ተጋፍተው በወሊሶ ጫካ መነኮሳትን ሊያጰጵሱ ሲሞክሩ ነበር፣ ቀጥሎም የፕትርክና ልብስ አሰፍተው መፈንቅለ ፓትርያርክ ሲያደርጉ ነበረ፣ ቀጥሎም የመንበረ ሰላማ ተገንጣዮቹን አይዟቹህ ሊሉ በአካል ሄደው ነበረ፣ ብልጽግና ቤተክርስቲያን ባሳነሰበት መድረክ ሁሉ እርሶ አሉ፣ አሁን ከስርአተ ቤተክርስቲያን ባፈነገጠ ሁኔታ በ5ኪሎ የ4ኪሎ ፖሊት ቢሮ ለመሆን የስርአስኪያጅነት ቅስቀሳ እያስደረጉ ነው.... አባታችን ለቤተክርስቲያን እየጠቀምኳት ነው ብለው ያምናሉ?
...
Maryamawit Henok Lemessa
+ + + + +
ይኽም ኾኖ ሲኖዶስ የጸሐፊነት ዕድል ሰጥቷቸው ነበረ። ያኔ ያጠፉት ብዛት ቀላል አልነበረም። ከሲኖዶሱ አባላት አንድም ጊዜ ወይ በጸሐፊነት ወይ በሥራ አስኪያጅነት ያላገለገሉ ሞልተዋል። ወደዚያ ማማተሩ ይሻላል።
አይደረግም ‼️
የቤተ ክርስቲያን የሴራ ፖለቲካ አስፈፃሚ እንድትሆን መከራዋ እንዲበዛ ካልተፈለገ በስተቀር አባ ሳዊሮስን በየትኛው መልካም ስራው ይመረጣል ኸረ እረፉ ነገ የምትቆጩበትን ስራ ዛሬ አትስሩ እባካችሁ አባቶች የምእመናን እንባ አይገዳችሁም ወይ ?
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
የቤተ ክርስቲያን የሴራ ፖለቲካ አስፈፃሚ እንድትሆን መከራዋ እንዲበዛ ካልተፈለገ በስተቀር አባ ሳዊሮስን በየትኛው መልካም ስራው ይመረጣል ኸረ እረፉ ነገ የምትቆጩበትን ስራ ዛሬ አትስሩ እባካችሁ አባቶች የምእመናን እንባ አይገዳችሁም ወይ ?
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
🙏ከሹመቱ ምርጫ በፊት የህንፃው ምረቃ ጥድፊያ
👉በቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ በአሁኑ በሸገር ሀገረስብከት ስር የሚገኘው የገላን ጉዳ ክፍለ ከተማ የነበረ ህንፃ ግንቦት 10 , 2017 ዓ.ም እንደሚመረቅ የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል ፦
👉በዚህ ምርቃት ላይ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ለጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ ሹመት ድጋፍ ለማግኘት ሆን ብለው ይህንን ቀን የመረጡ መሆኑን የመረጃ ምንጮቻችን በመረጃውን በማድረስ ፣
👉በዚህ ምርቃት ላይ በርካታ ጳጳሳት እንደተጠሩ ፣ብሎም በዚህ ምርቃት ላይ ለሚገኙ አባቶች ስጦታ የብር መስቀል እጅ መነሻ እና በቂ መስተንግዶም እንደተዘጋጀ እንዲሁም የዚህ ዝግጅት ዋና እስፖንሰር ፣ የፍኖተ ጽድቅ ባለቤት አቶ ጸጋዬ መሆናቸውን የመረጃ ምንጮቻችን ለኢትዮ ቤተሰብ አድርሰውናል ፣
👉እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት ከዚህ ቀደምም በአባ ሳዊሮስ ጋባዥነት የተከናወነ ሲሆን ፣ ይህ መርሀግብር ጳጳሱ እና ግብራበሮቻቸው ላሰቡት የቡድን የምርጫ ቅስቀሳ ይረዳቸው ይሆን? ዝርዝሩን በመደበኛ መርሀግብራችን ይጠብቁን ፦
ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ
ምንጭ 👉 ኢትዮ ቤተሰብ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
👉በቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ በአሁኑ በሸገር ሀገረስብከት ስር የሚገኘው የገላን ጉዳ ክፍለ ከተማ የነበረ ህንፃ ግንቦት 10 , 2017 ዓ.ም እንደሚመረቅ የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል ፦
👉በዚህ ምርቃት ላይ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ለጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ ሹመት ድጋፍ ለማግኘት ሆን ብለው ይህንን ቀን የመረጡ መሆኑን የመረጃ ምንጮቻችን በመረጃውን በማድረስ ፣
👉በዚህ ምርቃት ላይ በርካታ ጳጳሳት እንደተጠሩ ፣ብሎም በዚህ ምርቃት ላይ ለሚገኙ አባቶች ስጦታ የብር መስቀል እጅ መነሻ እና በቂ መስተንግዶም እንደተዘጋጀ እንዲሁም የዚህ ዝግጅት ዋና እስፖንሰር ፣ የፍኖተ ጽድቅ ባለቤት አቶ ጸጋዬ መሆናቸውን የመረጃ ምንጮቻችን ለኢትዮ ቤተሰብ አድርሰውናል ፣
👉እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት ከዚህ ቀደምም በአባ ሳዊሮስ ጋባዥነት የተከናወነ ሲሆን ፣ ይህ መርሀግብር ጳጳሱ እና ግብራበሮቻቸው ላሰቡት የቡድን የምርጫ ቅስቀሳ ይረዳቸው ይሆን? ዝርዝሩን በመደበኛ መርሀግብራችን ይጠብቁን ፦
ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ
ምንጭ 👉 ኢትዮ ቤተሰብ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
👑 ስለ ንጉስ ቴዎድሮስ 🤴
🩸 ትንቢት የተነገረለትን ንጉስ የቴዎድሮስ የሚነሳበት አስደናቂና ምስጢራዊ ስፍራ
🩸 እውነት ትንቢት የተነገረለት ንጉስ ቴዎድሮስ ይመጣል ?
🩸 በፍካሬ ኢየሱስና በገድለ ፊቅጦር ስለ ትንቢታዊው ንጉስ ቴዎድሮስና ተጽፎ ይገኛል
🩸 የየረር ተራራ አስገራሚ ምስጢሮች
ለእነዚህ ጥያቂዎች መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
እዚህ ጋር ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
🩸 ትንቢት የተነገረለትን ንጉስ የቴዎድሮስ የሚነሳበት አስደናቂና ምስጢራዊ ስፍራ
🩸 እውነት ትንቢት የተነገረለት ንጉስ ቴዎድሮስ ይመጣል ?
🩸 በፍካሬ ኢየሱስና በገድለ ፊቅጦር ስለ ትንቢታዊው ንጉስ ቴዎድሮስና ተጽፎ ይገኛል
🩸 የየረር ተራራ አስገራሚ ምስጢሮች
ለእነዚህ ጥያቂዎች መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
እዚህ ጋር ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
Forwarded from 🟢ናታኒም ፖሮሞሽን🟢
📌 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?
📌 ሊቀ መዝሙራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📌 ሊቀ መዝሙራን ይልማ ኃይሉ
📌 ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
📌 ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
📌 ዘማሪ ምርትነሽ ጥላሁን
📌 ዘማሪት አቦነሽ አድነው
እና የሌሎችንም ...........
የዘማሪዎችው መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር Join የሚለውን ንኩት 🔻🔻🔻
👇👇👇
https://www.tg-me.com/+2ua4-eAbNTI1MTRk
https://www.tg-me.com/+2ua4-eAbNTI1MTRk
📌 ሊቀ መዝሙራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📌 ሊቀ መዝሙራን ይልማ ኃይሉ
📌 ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
📌 ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
📌 ዘማሪ ምርትነሽ ጥላሁን
📌 ዘማሪት አቦነሽ አድነው
እና የሌሎችንም ...........
የዘማሪዎችው መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር Join የሚለውን ንኩት 🔻🔻🔻
👇👇👇
https://www.tg-me.com/+2ua4-eAbNTI1MTRk
https://www.tg-me.com/+2ua4-eAbNTI1MTRk
ተመሰጌን
የበፊቱ ፓስተር የአሁኑ ባለማዕተብ ተሙ!
ለ34 ዓመት በፕሮቴስታንት ውስጥ ቆይቷል
ለአንድ አመት በጥሞና ቆይቷል። ለ interview ሲጠየቅ እራሱ መጀመሪያ ክርስትናን ልኑረው ነው መልሱ።
ተሙ ሁለት ቸርች ከነምዕመኑ ያስጠመቀ ጀግና ነው።
ክርስቶስ ስለበራልኝ ነው ወደ ኦርቶዶክስ የመጣሁት በማለት መስክሯል። እንዲህ በማለት.......
"ፕሮቴስታንት ጋር አብዛኛው ጊዜ ቸርች የግለሰብ ነው ነገር ግን እውነተኛ ቸርች የግለሰብ ሳይሆን የክርስቶስ ነው ።
እሮብ እኮ ፓስተር እከሌ ይመጣል ተብሎ ይኬዳል ስለዚህ ህዝቡ የሚሄደው ነቢይ ደመቀን ወይም ኢዩ ጩፋን ለመቀበል እንጂ ኢየሱስን ለመቀበል አይደለም።
አሁንም መምጣት የሚፈልጉ አሉ ነገር ግን እንደሚታወቁ ደሞዝ ይከፈላቸዋልና ስንወጣ ምን እንሆናለን ነው የሚይአሳስባቸው።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በጀት መድባ ትልቅ ሥራ ብትሰራ ደስ ይለኛል። ምክንያቱም ከመጡ ቸርቻቸውን ዘግተው ነው የሚመጡት ሌላ ስራ የላቸውም።
የፕሮቴስታንት ቸርች ጭስ አልባ ኢንዱስትሪ ነው።
ብዙኦች ገና ይመጣሉ ትዝታው እራሱ ይመጣል አይታችሁት እንደሆነ የእሱ ትችት የክርስቶስ ትምህረት ላይ ሳይሆን በግለሰብ ነው። ኦርቶዶክስ ደግሞ በግለሰብ አትለካም እኛ ሰዎች ደካማ ነን አንድ ጳጳስ ፣ አንድ ቄስ ሳተ አንድ ዲያቆን ተሳሳተ ማለት ኦርቶዶክስ ተሳሳተች ማለት አይደለም።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ወጣቶች ጀግና ናቸው፣ ዘመዴ፣ ወገኔ የምላቸው የበፊት ጓደኞቼ ሁሉ የእግዚአብሔር ሰላምታ እራሱ ሲነፍጉኝ ኦርቶዶክሳዊያን ግን በፍቅር ወደ እውነተኛው የክርስቶስ ህብረት እንድጨመር ምክንያት ሆኖዉኛል"
በማለት ገልጿል። በርታ! 💪
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
የበፊቱ ፓስተር የአሁኑ ባለማዕተብ ተሙ!
ለ34 ዓመት በፕሮቴስታንት ውስጥ ቆይቷል
ለአንድ አመት በጥሞና ቆይቷል። ለ interview ሲጠየቅ እራሱ መጀመሪያ ክርስትናን ልኑረው ነው መልሱ።
ተሙ ሁለት ቸርች ከነምዕመኑ ያስጠመቀ ጀግና ነው።
ክርስቶስ ስለበራልኝ ነው ወደ ኦርቶዶክስ የመጣሁት በማለት መስክሯል። እንዲህ በማለት.......
"ፕሮቴስታንት ጋር አብዛኛው ጊዜ ቸርች የግለሰብ ነው ነገር ግን እውነተኛ ቸርች የግለሰብ ሳይሆን የክርስቶስ ነው ።
እሮብ እኮ ፓስተር እከሌ ይመጣል ተብሎ ይኬዳል ስለዚህ ህዝቡ የሚሄደው ነቢይ ደመቀን ወይም ኢዩ ጩፋን ለመቀበል እንጂ ኢየሱስን ለመቀበል አይደለም።
አሁንም መምጣት የሚፈልጉ አሉ ነገር ግን እንደሚታወቁ ደሞዝ ይከፈላቸዋልና ስንወጣ ምን እንሆናለን ነው የሚይአሳስባቸው።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በጀት መድባ ትልቅ ሥራ ብትሰራ ደስ ይለኛል። ምክንያቱም ከመጡ ቸርቻቸውን ዘግተው ነው የሚመጡት ሌላ ስራ የላቸውም።
የፕሮቴስታንት ቸርች ጭስ አልባ ኢንዱስትሪ ነው።
ብዙኦች ገና ይመጣሉ ትዝታው እራሱ ይመጣል አይታችሁት እንደሆነ የእሱ ትችት የክርስቶስ ትምህረት ላይ ሳይሆን በግለሰብ ነው። ኦርቶዶክስ ደግሞ በግለሰብ አትለካም እኛ ሰዎች ደካማ ነን አንድ ጳጳስ ፣ አንድ ቄስ ሳተ አንድ ዲያቆን ተሳሳተ ማለት ኦርቶዶክስ ተሳሳተች ማለት አይደለም።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ወጣቶች ጀግና ናቸው፣ ዘመዴ፣ ወገኔ የምላቸው የበፊት ጓደኞቼ ሁሉ የእግዚአብሔር ሰላምታ እራሱ ሲነፍጉኝ ኦርቶዶክሳዊያን ግን በፍቅር ወደ እውነተኛው የክርስቶስ ህብረት እንድጨመር ምክንያት ሆኖዉኛል"
በማለት ገልጿል። በርታ! 💪
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ዜኖኩ ጽድቀከ
♡የመዝሙር ግጥሞች♡
ዜኖኩ ጽድቀከ ወነገርኩ አድኅኖተከ
ከሠትኩ ቃላቲከ ለሕዝብከ ኢትዮጵያ(፪)
በጸጋሁ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ
አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ(፪)
ቃላትህን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ገለጥኩ
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አስተማርኩአቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ግሩኙን ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedoo
#ለሃሳብ አስተያየት
@Orthodox_tewahedo_Bot
ከሠትኩ ቃላቲከ ለሕዝብከ ኢትዮጵያ(፪)
በጸጋሁ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ
አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ(፪)
ቃላትህን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ገለጥኩ
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አስተማርኩአቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ግሩኙን ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedoo
#ለሃሳብ አስተያየት
@Orthodox_tewahedo_Bot
መላእክት ምስጋናቸው እረፍታቸው ፣እረፍታቸው ምስጋናቸው ሆኖ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ያመሰግናሉ፡፡
ቤተክርስቲያንም አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድረግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት የሚመሰገንበትን የምስጋና ሥርዓት ዘርግታለች፡፡
ሕያው እግዚአብሔር የአዳም ልጆች በመላእክት ምስጋና
እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምስጋና ይማር
ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መረጠ፡፡
ማህሌታዊው ቅዱስ ያሬድ የመላእክት የምስጋናውን እንጀራ
ያበላን የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ እንቁ ነው።
በረከቱ ይደርብን!
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
ቤተክርስቲያንም አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድረግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት የሚመሰገንበትን የምስጋና ሥርዓት ዘርግታለች፡፡
ሕያው እግዚአብሔር የአዳም ልጆች በመላእክት ምስጋና
እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምስጋና ይማር
ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መረጠ፡፡
ማህሌታዊው ቅዱስ ያሬድ የመላእክት የምስጋናውን እንጀራ
ያበላን የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ እንቁ ነው።
በረከቱ ይደርብን!
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#11 የቅዱስ ያሬድ በዓል]
#በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ (ይሥሐቅ) እናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) ሲባሉ የተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላረፈ፤ እናቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምረው ለአባ ጌዴዎን ሰጠችው፡፡ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዴዎን ይቈጣው ነበርና ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ፤ ከዐዘኑም ብዛት የተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሽ ትል ከዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጨረሻም በጭንቅ ከዛፉ ላይ ሲወጣ በማየቱ እግዚአብሔር በዚኽች ታናሽ ፍጥረት እንዳስተማረው በመረዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡
“ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህረ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ” ይላል ከዚኽ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኾኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጨረስ ዲቁናን ተሾመ፤ እስከ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በከፍተኛ ድምፅ የመዝሙር ማሕሌት አልነበረም፤ እግዚአብሔርም ለዚኽ አባት የመላእክትን ዝማሬ ሊያሳየው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ የኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን የምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡
ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደረሰ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገብቶ፡- “ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ” (ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም ለሙሴ የድንኳኑን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ አሳየው) ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ከሰማይ መላእክት አገኘኹት፣ በማለት አርያም በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡
ይኽነኑ ድርሳነ ዜማ የጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብረ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስከትል መኳንንቱ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተከትለው እየተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኼድ በተመስጦ ሲሰሙት ውለዋል፡፡
ቅዱስ ያሬድ ዐምስት የዜማ መጻሕፍትን የደረሰ ሲኾን እነርሱም
፩ኛ) ድጓ ፪ኛ) ጾመ ድጓ
፫ኛ) ምዕራፍ ፬ኛ) ዝማሬ ፭ኛ)መዋሥዕት ናቸው፡፡
እነዚኽንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሦስት የዜማ ስልቶች ማለት በግእዝ፣ በዕዝል፣ በአራራይ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ “ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብረ መስቀል ወእንዘ ያጸምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተከለ በትረ ኀጺን ውስተ መከየደ እግሩ ለያሬድ” ይላል፤ ከዕለታት ባንዳቸው ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብረ መስቀል ሳያውቁት ልባቸው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ የብረት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታል፤ ከእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስከሚፈጽም ድረስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡
ንጉሡም የደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጦ ቅዱስ ያሬድን “የደምኽ ዋጋ የፈለግኸውን ንገረኝ” አለው፤ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኼድ እንደኾነ ነገረው፤ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡
“ወእምዝ ቦአ ያሬድ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቦተ ጽዮን” ይላል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት በመቆም የአንቀጸ ብርሃንን ምስጋና ከመዠመሪያው እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኽል ከምድር ከፍ ከፍ አለ፤ ከዚኽ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ገዳም ሲኼድ የአኲስም ጽዮን ካህናት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት ርሱም እጅግ ባማረ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ከፍ አድርጎ “ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትረ ምስለ ኲልክሙ” (በኹሉ ላይ ጸንታ የምትኖር የእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ከኹላችኊ ጋር ትኑር) ብሎ የስንብት መዝሙርን ዘመረ፤ ካህናቱም ይኽነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡
በትርጓሜ ቅዳሴ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቦታ ተሰውሮ ጸዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቤታችን ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬምን የብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኤፍሬም ውዳሴዬን፤ ሕርያቆስ ቅዳሴዬን ነግራችኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድረስልኝ ብላ ነግረውት በዜማ ደርሶታል፤ ይኽም ሊታወቅ ሥረይ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል፡፡
ርሱም ጸዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማረ መላእክት ዘወትር እየጐበኙት በጾም በጸሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጸንቶ ኖረ፤ በመጨረሻም ጌታችንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጾለት “ኦ ፍቁርየ ቀዳሚኒ በከመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍከ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር... ” (ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኽ ይኽነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊልና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል” ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት በክብር ዐረገ፡፡ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቦት ዐሥራ አንድ ነው፡፡
ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ፦
“ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጼ እንተ አዕረገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ረዋጼ ለትምህርተ መጽሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጼ በብዙኅ ጻማ ዘአልቦ ሑጻጼ*መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ የዐርግ ዕጼ”
(የመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳረገ ለኾነ፤ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶ፤ ኰብልሎ ከኼደበት መጻሕፍትን ለመማር የተመለሰ ለኾነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል) በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ፡-
“ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ፤
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ
ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ”፡፡
(የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡
[የጽሑፉ ምንጭ፡- አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የደረሰው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ የተጻፈ፤ ከገጽ 232-235]፡፡
የቅዱስ ያሬድ በረከት ይደርብን፤ እናንተም ይኽነን ሊቅ አወድሱት።
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ (ይሥሐቅ) እናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) ሲባሉ የተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላረፈ፤ እናቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምረው ለአባ ጌዴዎን ሰጠችው፡፡ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዴዎን ይቈጣው ነበርና ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ፤ ከዐዘኑም ብዛት የተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሽ ትል ከዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጨረሻም በጭንቅ ከዛፉ ላይ ሲወጣ በማየቱ እግዚአብሔር በዚኽች ታናሽ ፍጥረት እንዳስተማረው በመረዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡
“ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህረ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ” ይላል ከዚኽ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኾኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጨረስ ዲቁናን ተሾመ፤ እስከ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በከፍተኛ ድምፅ የመዝሙር ማሕሌት አልነበረም፤ እግዚአብሔርም ለዚኽ አባት የመላእክትን ዝማሬ ሊያሳየው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ የኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን የምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡
ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደረሰ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገብቶ፡- “ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ” (ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም ለሙሴ የድንኳኑን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ አሳየው) ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ከሰማይ መላእክት አገኘኹት፣ በማለት አርያም በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡
ይኽነኑ ድርሳነ ዜማ የጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብረ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስከትል መኳንንቱ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተከትለው እየተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኼድ በተመስጦ ሲሰሙት ውለዋል፡፡
ቅዱስ ያሬድ ዐምስት የዜማ መጻሕፍትን የደረሰ ሲኾን እነርሱም
፩ኛ) ድጓ ፪ኛ) ጾመ ድጓ
፫ኛ) ምዕራፍ ፬ኛ) ዝማሬ ፭ኛ)መዋሥዕት ናቸው፡፡
እነዚኽንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሦስት የዜማ ስልቶች ማለት በግእዝ፣ በዕዝል፣ በአራራይ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ “ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብረ መስቀል ወእንዘ ያጸምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተከለ በትረ ኀጺን ውስተ መከየደ እግሩ ለያሬድ” ይላል፤ ከዕለታት ባንዳቸው ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብረ መስቀል ሳያውቁት ልባቸው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ የብረት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታል፤ ከእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስከሚፈጽም ድረስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡
ንጉሡም የደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጦ ቅዱስ ያሬድን “የደምኽ ዋጋ የፈለግኸውን ንገረኝ” አለው፤ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኼድ እንደኾነ ነገረው፤ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡
“ወእምዝ ቦአ ያሬድ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቦተ ጽዮን” ይላል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት በመቆም የአንቀጸ ብርሃንን ምስጋና ከመዠመሪያው እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኽል ከምድር ከፍ ከፍ አለ፤ ከዚኽ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ገዳም ሲኼድ የአኲስም ጽዮን ካህናት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት ርሱም እጅግ ባማረ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ከፍ አድርጎ “ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትረ ምስለ ኲልክሙ” (በኹሉ ላይ ጸንታ የምትኖር የእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ከኹላችኊ ጋር ትኑር) ብሎ የስንብት መዝሙርን ዘመረ፤ ካህናቱም ይኽነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡
በትርጓሜ ቅዳሴ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቦታ ተሰውሮ ጸዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቤታችን ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬምን የብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኤፍሬም ውዳሴዬን፤ ሕርያቆስ ቅዳሴዬን ነግራችኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድረስልኝ ብላ ነግረውት በዜማ ደርሶታል፤ ይኽም ሊታወቅ ሥረይ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል፡፡
ርሱም ጸዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማረ መላእክት ዘወትር እየጐበኙት በጾም በጸሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጸንቶ ኖረ፤ በመጨረሻም ጌታችንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጾለት “ኦ ፍቁርየ ቀዳሚኒ በከመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍከ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር... ” (ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኽ ይኽነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊልና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል” ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት በክብር ዐረገ፡፡ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቦት ዐሥራ አንድ ነው፡፡
ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ፦
“ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጼ እንተ አዕረገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ረዋጼ ለትምህርተ መጽሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጼ በብዙኅ ጻማ ዘአልቦ ሑጻጼ*መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ የዐርግ ዕጼ”
(የመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳረገ ለኾነ፤ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶ፤ ኰብልሎ ከኼደበት መጻሕፍትን ለመማር የተመለሰ ለኾነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል) በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ፡-
“ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ፤
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ
ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ”፡፡
(የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡
[የጽሑፉ ምንጭ፡- አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የደረሰው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ የተጻፈ፤ ከገጽ 232-235]፡፡
የቅዱስ ያሬድ በረከት ይደርብን፤ እናንተም ይኽነን ሊቅ አወድሱት።
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች
፠ ጥዑመ ልሳን፤
፠ የሱራፌል አምሳያ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤
፠ መዓርዒረ ዜማ፤
፠ ካህን (ካህነ ስብሐት)
፠ ማኅሌታይ፤
፠ መዘምር ዘበድርሳን፤
፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት)
፠ ዓርከ ሊቃውንት፤
፠ ደራሲ፤
፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ)
፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤
፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ
፠ ልዑለ ስብከት፤
፠ ሰማዕት፤
፠ ባሕታዊ፤
፠ መናኝ
፠ የዜማ አባት፤
፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡
፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ::
፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ
፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ::
፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ::
፠ አእምሮው የመጠቀ፤
፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤
፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …...
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
፠ ጥዑመ ልሳን፤
፠ የሱራፌል አምሳያ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤
፠ መዓርዒረ ዜማ፤
፠ ካህን (ካህነ ስብሐት)
፠ ማኅሌታይ፤
፠ መዘምር ዘበድርሳን፤
፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት)
፠ ዓርከ ሊቃውንት፤
፠ ደራሲ፤
፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ)
፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤
፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ
፠ ልዑለ ስብከት፤
፠ ሰማዕት፤
፠ ባሕታዊ፤
፠ መናኝ
፠ የዜማ አባት፤
፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡
፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ::
፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ
፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ::
፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ::
፠ አእምሮው የመጠቀ፤
፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤
፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …...
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
ዜኖኩ ጽድቅከ ወነገርኩ አድህኖትከ ከሰትኩ ቃላቲከ ለህዝበ ኢትዮጲያ(፪)
# ግንቦት_11
በምድር ሁኖ በሰማያዊ ቋንቋ የሚናገረው አልቦ እምቅድሜከ ወአልቦ እምድህሬከ ከአንተም በፊት ከአንተ በኋላ አንተን የሚመስል የለም የተባለለት ብቸኛው የኪሩብም ደቀ መዝሙር ቅዱስ ያሬድ የመሰወር በዓሉ ነው በረከቱ ይደርብን
ዜኖኩ ጽድቅከ ወነገርኩ አድህኖትከ ከሰትኩ ቃላቲከ ለህዝብከ ኢትዮጲያ(፪)
በጸጋሑ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
+++ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ ቃላትህን ለኢትዮጲያ ሕዝብ ነገርኩ(፪)
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አስተማርኳቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
በመጨረሻም እግዚአብሔር ለቅዱስ ያሬድ ቃልኪዳን ገብቶለታል
ዝክረ ቅዱስ ያሬድ
'ብፁዕ ውእቱ ዘገብረ ተዝካረከ...አነ እሁቦ ሕይወተ ዘለዓለም ወአወርሶ መንበረ ክብር' ይቤሎ እግዚአብሔር ለያሬድ ካህን
እግዚአብሔር ለካህን ያሬድ እንዲህ ብሎታል 'ተዝካርህን ያደረገ ንዑድ ነው ክቡር ነው... የዘለዓለም ሕይወትን እሰጠዋለሁ መንግሥተ ሰማያትንም አወርሰዋለሁ' በምልጃው ያስበን
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
# ግንቦት_11
በምድር ሁኖ በሰማያዊ ቋንቋ የሚናገረው አልቦ እምቅድሜከ ወአልቦ እምድህሬከ ከአንተም በፊት ከአንተ በኋላ አንተን የሚመስል የለም የተባለለት ብቸኛው የኪሩብም ደቀ መዝሙር ቅዱስ ያሬድ የመሰወር በዓሉ ነው በረከቱ ይደርብን
ዜኖኩ ጽድቅከ ወነገርኩ አድህኖትከ ከሰትኩ ቃላቲከ ለህዝብከ ኢትዮጲያ(፪)
በጸጋሑ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
+++ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ ቃላትህን ለኢትዮጲያ ሕዝብ ነገርኩ(፪)
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አስተማርኳቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
በመጨረሻም እግዚአብሔር ለቅዱስ ያሬድ ቃልኪዳን ገብቶለታል
ዝክረ ቅዱስ ያሬድ
'ብፁዕ ውእቱ ዘገብረ ተዝካረከ...አነ እሁቦ ሕይወተ ዘለዓለም ወአወርሶ መንበረ ክብር' ይቤሎ እግዚአብሔር ለያሬድ ካህን
እግዚአብሔር ለካህን ያሬድ እንዲህ ብሎታል 'ተዝካርህን ያደረገ ንዑድ ነው ክቡር ነው... የዘለዓለም ሕይወትን እሰጠዋለሁ መንግሥተ ሰማያትንም አወርሰዋለሁ' በምልጃው ያስበን
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo