Telegram Web Link
#ያንተን ስራ ያንተን ክብር ፣
ማን ይመራመር ።
እግዚአብሔር ምን ይበል እኛ ቅጥ ብናጣ ፣
በስምንተ ሺ በቀጠሮ መጣ።

ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇
@Ortodoxtewahedo
3
የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል ።

ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ።

"ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር ! እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።

አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
👍166
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ፦

1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤
2. ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤
5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሚኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤
6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤
7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤
8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።

መረጃው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘ ነው።


@Ortodoxtewahedo
😢13👍43
ሻሸመኔ እና መሃል አዲስ አበባ ላይ እርሳቸው በለኮሱት እሳት ምክንያት በጥይት ለተቆሉ ምዕመናንን ጸጸት ወይም ሀዘኔታ አላሳዩም።

ላፈረሱት ቅኖና ፣ ለተዳፈሩት ክብር ፣ለፈጸሙት የስርዓት ህጸጽ ይቅርታ አልጠየቁም። ይልቁንስ ዛሬም ድረስ ትክክል እንደሆኑ ይሰማችዋል።

ከክርስቶስ ይልቅ ዘር እና ቋንቋቸውን አሳይተው በሥጋ ዋሻ የተጠለሉት የሌላ ቤተ እምነት ተከታይ የሆኑ ጭምር እንዲከተሏቸው ፊት ለፊት ቆመዋል።

ወጥቼበታለው ካሉት ዘር በእምነታቸው ብቻ ካህናት አባቶች እና ምዕመናንን እየተለቀሙ ሲገደሉ አንድ ቀንም -ስለልጆቼ- ብለው ቃል አላወጡም።

እርሳቸው ስርዓት ማፍረስ ትክክል እንደሆነ ፣ አመጸነት አዋጭ እንደሆነ በገለጡት ቤተክርስቲያን ውስጥ ቀጣይ 3 ዓመት ምን እንደሚከሰት እንግዲህ እናያለን።

እንግዲህ ምን እንላለን ? መንፈስቅዱስ የዘገዬ ቢመስልም በእውነት ይፈርዳል!!!

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
👍12🙏3
አልተገለገላችሁም አገለገላችሁን እንጂ !

ብጹአን አባቶች ብጹዕ አቡነ አብርሃም እና ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ
በረከታችሁ ይደርብኝ ። ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለከፈላችሁት ተጋድሎ ውለታን የማርሳ የታመናችሁለት ኢየሱስ ክርስቶስ አሁንም ባላችሁ ኃላፊነት ብርታቱን ይስጣችሁ ።

በተለይ ብጹዕ አቡነ አብርሃም ለአስራ አንድ ዓመታት ደብራችንን በአስተዳዳሪነት ባገለገሉበት ወቅት የነበርዎትን መንፈሳዊነት እና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዕድገት ያሳዩትን ትጋት እንኳን እኛ ምዕመናን ማንም የሚመሰክረው ሃቅ ነው ።

አንዳንድ ያልታደሉ ሰዎች ሹመትን ይገለገሉበታል የታደሉት ደግሞ በዓላማ እና በጽናት በቆራጥ መንፈሳዊነት ጭምር መንጋውን ያገለግሉበታል ። ለዚህ ምሳሌ ስለሆናችሁን እንደ ልጅነቴ ዝቅ ብዬ ባላመሰግናችሁ ያጸናችሁ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይቅር አይለኝም ።

በምትካችሁ ለተሾማችሁት ት ብጹዐን አባቶች መልካም የኃላፊነት ጊዜ ይሆንላችሁ ዘንድ ምኞታችንም ጸሎታችንም ነው ።

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
18👍2🔥1
ለቅድስት ቤተክርስቲያን ላደረጉት መንፈሳዊ ተጋድሎ ለከፈሉት መስዋዕት ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁሌም ስትዘክረው ትኖራለች

አባታችን አቡነ ጴጥሮስ ክብር ይገባቸዋል 🙏


#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
🥰18🔥4
የቆያችኋባቸው መናብርት ከእናንተ በፊት በተራ የሚዳረሱና ማንም ጉዳይ የማይላቸው "የዙር ወንበሮች" ነበሩ። ከእናንተ በኋላ ያ ተቀይሯል። በገሐድም፣ በኅቡዕም፣ በመልከ ብዙ ግንባር (alliance) ከያዛችሁት ርቱዕ መንገድ እንድትናጠቡ የሚደረገውን ያልታዘብን አይደለንም። ያልተደረብንላችሁ እውነት ተደራቢ ስለማትሻ ነው። ባሰባችሁበትና ባሰብነው ልክ ተቋሙን ለመለወጥ እንዳልቻላችሁ እናውቃለን። ያንን የኃላፊነት ቀንበር ግን ብቻችሁን አትሸከሙትም። እንጋራችኋለን። በሦስት ዓመት የሠላሳ ዓመት ሰቆቃ የሚመዝን ድካም ውስጥ እንደ ነበራችሁ እንረዳለን። በዚህም "አባቶቻችን" ስንል አናፍርባችሁም። እናመሰግናለን። ቤተ ክርስቲያን ታመሰግናችኋለች።

ለቅድስት ቤተክርስቲያን ላደረጉት መንፈሳዊ ተጋድሎ ለከፈሉት መስዋዕት ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁሌም ስትዘክረው ትኖራለች


#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
25👍2
የብልጽግናው ዋና ሴራ አስኪያጅ ባለሙሉ ሥልጣን ሆኖ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተቀምጧል፡፡ በመጨረሻም ሰዎቹ እንደፎከሩት፣ እንደቀሰቀሱት ቤተ ክርስቲያንን ከነሁለንተናዋ ተረክበዋል፡፡ ያ ሁሉ ግርግር፣ ያሁሉ እስር፣ ያ ሁሉ ቅስቀሳ ለዚህ ነበር፡፡

የኢትዮ ፎረሙ ዘገባ ወገባቸውን የመታው፣ ሴራቸውን ቀድሞ ያጋለጠባቸው ለዚህ ነበር፡፡ ያንን ሲያጣጥሉ የነበሩ የቤተ ክርስቲያን ሰዎች አሁን እርማቸውን ያውጡ፡፡ ሁኔታዎችን ባለመረዳት ጭምር ቤተ ክርስቲያናቸውን አዘናግተዋታልና፡፡ አሳዛኞች፡፡

ቤተ ክርስቲያንን ለመክፈል ቀንደኛ የነበረውን ሰው፣ 'መክፈል ምን ይሠራልሃል፣ ገብተህ ሙሉውን ተረከብ እንጂ' በሚለው የብልጽግና ፈሊጥ ምክንያት ይኸው በቦታው ላይ አስቀምጠውታል፡፡ አሁን ከልካይም፣ ተቆጭም ገልማጭም፣ አምቢ ባይም የላቸውም፡፡ የፈለጉትን የሚሹትን የሚያደርጉበትን ሥልጣን ይዘዋል፡፡ ምክትላቸው ቄስ በላይ ገንዘብ ሠርቆ ታሠረባቸው እንጂ ያኔ ጀምረው ያቀዱት ይኸንን ሙሉ ወረራ ነበር፡፡

ቦታውን የፈለጉት ለቤተ ክርስቲያን ሥራ ሊሠሩላት ሳይሆን ሊሠሩባት፣ ቤተ ክርስቲያንን ሊያዋርዷት፣ ሊዘርፏት፣ ሊቀሟት ነው፡፡ ለብልጽግናም ሰጥ ለጥ ብላ እንድትገዛ ለማድረገ ነበር፡፡ አሁን ቤተ ክርስቲያ በገጣባ አህያ ተወራለች፡፡ ጫካ ሄዶ ሲኖዶስን ከከፈለ ሰው በላይ በክርስትናው ገጣባ አህያ ከየትም አይገኝም፡፡ ገጣ አህያ ደግሞ ጠባዩን ባለፈው አስረድቻለሁ፡፡ ክህደቱ፣ ሸፍጡ፣ ዘረኝነቱ ያመረቅዝበታል እንጂ የሚድንበት አንዳች እድል የለውም፡፡ በድለዳል፣ በጨርቅ ወዘተ ብታለባብሰው የሚሆን አይደለም፡፡

አሁን ያ ጸጉሩ መሸበቱን ለማየት ቆራጩን ሲያጣድፈው ለነበረው ሰው 'ሲወድቅ ልታየው ምን ያስቸኩልሃል እንዳለው' ቤተ ክርስቲያንም ጸጉሯን ተላጭታ፣ ሸበቶውን በግላጭ ፊታችን ወድቆ አየነው፡፡ መልኳ ተቀየረ፣ ያለ ተቆርቋሪ ቀረች፣ አሳልፋ ተሰጠች፣ ሲሞናዊነት ዐይኑን ጨፍኖ መላዋን ወረራት ማለት ነው፡፡

አሁን ቤተ ክርስቲያን የሚጠበቃትን የተጠናከረ ስደት፣ ሊሆንባት የታቀደውን፣ ማንንም መጠየቅ አያስፈልገንም፣ ራሳችን ፊት ለፊታችን መከራዋን ሲገለጥ አየነው፡፡ ሳዊሮስ መከራ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ሳዊሮስ አሳልፎ ሻጭ ነው፡፡ የምናውቅለት ታሪኩ ይኸ ነው፡፡

አሁን ያኔ 'ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር እርስዎ እኮ ቤቱን ትተውታል፣ እስከዛሬ እኮ እንዲህ አልነበረም' ያለውን ቃል ለመፈጸም፣ ቤተ ክርስቲያንን ለብልጽግና አሳልፎ የሚሰጥበትን ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡

በኦሮሚያ የሚደረግ የቤተ ክርስቲያን ስደት፣ በዐዲስ አበባ የሚደረግ የቤተ ክርስቲያን ወረራ ያለማንም ተቆጭና ገልማጭ ያስፈጽሙታል፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር ከላይ እስከ ታች፣ ከታጠቀ ኃይል እስከ ስለላ መረብ ተብትበው ተቆጣጥረውታል፡፡ 'ምንም አታመጡም እንዳሉት' አድርገውታል፡፡

አሁን ሁሉም በእጃቸው ነው፣ ዛሬ ደግሞ በጻዕር ላይ የነበረውን ጠቅላይ ቤተ ክህነትንም ፈጽመው ገድለውታል፡፡ ያንን ያደረጉት ደግሞ 'በመንፈስ ቅዱስ ይመራሉ' የተባሉት አባቶች ሲሆኑ በመንፈስ ቅዱስ መመራታቸውን ትተው እነ ከድር በጠቆሟቸው መሠረት የእነ ከድርን አባት የቤተ ክርስቲያኒቱ ሥራ (ሴራ) አስኪያጅ አድርገው መርጠዋል፡፡

በእኔ በኩል ቤተ ክርስቲያኔን የተቀማሁት ዛሬ ነው፣ ዛሬ የግመሉን ወገብ የሰበረው የመጨረሻው በትር ቤተ ክርስቲያን ላይ አርፎል አይቸዋለሁ፡፡ ምእመናን ሰሚ እንደሌላቸው፣ ጠላት ደግሞ የፈለገውን ነገር የማድረግ አቅሙን ያሳዩበት ነው፡፡ ሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን ሊቀሙን ባይችሉም፣ የሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን ማሳለጫ የሆነችውን የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያንን መዋቅር ያላቸውን ኃይል ተጠቅመው ከምእመናን መቀማት የቻሉበት ቀን ተደረጎ ይወሰዳል፡፡

አሁን ውሉ ወደማይታወቅ፣ እጅግ በሚያሳስብ ጨለማ ተወርውረናል፣ መዋቅሩም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወድቋል፡፡

ዳሩ ግን ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን ትንሣኤ ይኖራት ይሆን? ለዚህስ የሚረባረቡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ይኖሩ ይሆን? ምእመናን ሰፊ ትግል ይጠይቀናል፡፡ ይኸንን ችላ ብለን የተውን እንደሆነ፣ በመዋቅሯ ሽባነት ስደት፣ ፈተና፣ የመንጋ ነጠቃ መከራ ስትቀበል የቆየችው የነበረችው ቤተ ክርስቲያን፣ አሁን ደግሞ በቅሰጣ ባልሆነ ነገር ግን በሁለንተናዊ ነጠቃ ሙሉ በሙሉ ልናጣት የምንችልበት አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡

አሁን ድርሻው የምእመናን ነው፡፡ እለ ከድር በመረጡላቸው፣ ፖለቲከኞች እንደፎከሩት ባስቀመጡላቸው ሰው ሴራ አስኪያጅነት እየተመሩ ቀጣዩን ሦስት ዓመታት ቤተ ክርስቲያናቸውን በማፍረስ ይተባበራሉ? ሰውየውም ቃል እንደገቡት ቤተ ክርስቲያኗን ከነሁለንተናዋ ለብልጽግና ሲያስረክብ ዝም ብለው ያዩ ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች በቀጣይ የሚታዩ ይሆናሉ፡፡

ሰፊ ትግል፣ ሰፊ ርብርብ የሚጠይቅበት ወቅት ላይ ወድቀናል፡፡ አሁን መተኛት እንኳን የሚቻለው በአንድ ዐይን ብቻ ይሆናል፡፡ አሁ ይሉኝታ ሊኖር አይገባም፣ አሁን የውጭና የውስጥ የሚባል ጠላት ቀርቷል፣ አሁን ያለው የውስጥ ጠላት ሆኗል፡፡ የውጩም ከነመሣሪያው ውስጥ ገብቶ ተጠቃሏል፡፡

ትግሉም ዋጋ የሚያስከፍል ዋጋም የሚያሰጥ ነው የሚሆነው፡፡

አንቺ ቤተ ክርስቲያን መጽናኛ ይስጥሽ!
👍1714
#like#share
ወደደንም ጠላንም እኝህ አባት የብዙ ኦሮቶዶክሳዊያን ስማእታት ደም በእጃቸው አለ ። ammatanis Amanuu baataniAbbaan keenyi kun Dhigga wareggamtoottaa Harka isaani irra jira.
👍13😢43
ዲ/ን ዶር ቴዎድሮስ በለጠ ከአንድ ዓመት የጽሙና ጊዜ በኋላ ቀሪ ጊዜያቸውን በምንኩስና ሕይወት ለመኖር ጉዞውን ጀምረዋል። አባ ክፍለ ሥላሴም እንደ ተባሉ ምንጮች ገልጠዋል። የአበውን ጸጋ ሰጥቶ ያጽናልን
“ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤” 1ኛ ቆሮ 7፥32

ምንጭ፦ማ/ሚድያ

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
👍26🙏139🥰6
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የብርሃን እናት ነሽና /፪/
ለምኝልን ድንግል /፪

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
12👍9🙏1
ዲ/ን ፈለገ አትናቴዎስ

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ፈለገዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
👍2813🔥2
‘‘እኔና ልጄ ሰግደን እንመለሳለን‘‘ ...
EOTC Germany Archdiocese የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
እኔና ልጄ ሰግደን እንመለሳለን
  
           
Size:-54.4MB
Length:-58:44

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
6👍5
የቅዱስ ሲኖዶስ  መግለጫ

ግንቦት ፳/፳፻፲፯ ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ አካሂዷል፡፡
የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና እድገት፣ ለሀገር ሰላምና መረጋጋት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋትና ለመንፈሳዊ ልዕልና ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ መስጠት፣ምትክ ለሌለው የሰው ልጅ ሕይወት ባለአደራ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ሰላም ያለማቋረጥ መጸለይ፣ ጸሎተ ምሕላ ማወጅ፣ የሰላምና የአንድነት ጥሪ ማስተላለፉ እንደተጠበቀ ሆኖ ለሰላምና ለአንድነት ልዩ ትኩረት ሰጥተው ሁሉን አቀፍ ሥራ የሚሠሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ” በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
ኮሚቴውም ዘላቂ ሰላምንና አንድነትን ለማስፈን፣ የዜጎችን ሕይወት እየነጠቀ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥረት እንዲያደርግ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ባካተተ መልኩ በየደረጃው የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና፣ ውይይቶችንና የጥናት መድረኮችን እንዲያዘጋጅ፤ አፈጻጸሙንም በየሦስት ወሩ ለቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት እንዲያደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

@ortodoxtewahedoo
4👍2
2025/07/13 01:39:42
Back to Top
HTML Embed Code: