Telegram Web Link
Audio
ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው
         በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር


🕹 #ጊዜ_አጠቃቀም

👍 #የጊዜ_አጠቃቀም_ጥቅሞች

🔸የጊዜ አጠቃቀም ጥቅሞች እንደየሰው ቁጥራቸው ሊጨምርና ሊያንስ ይችላል፡፡ እዚህም ጋር የሚከተሉት ሦስት ዋና ዋና ጥቅሞች ቀርበዋል፡፡

1⃣ በሌሎች ዘንድ የሚኖረን ተቀባይነት ከፍ ይላል


🔹አገልጋዮች ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊ ቁርኝት የሚጠበቅብን በመሆኑ የጊዜ አጠቃቀሙን መጀመርና መልመድ በምናደርገው ግንኙነት የሚጠበቅብንን በጊዜው እንድናከናውን ይረዳናል፡፡

🔸በዚህም በሰዎች ዘንድ የተግባር ሰው፣ ቃል አክባሪ፣ ትጉህ፣ ወዘተ የእኛ መገለጫዎች ይሆናሉ፡፡

🔹እነዚህ እሴቶች ደግሞ በመንፈሳዊውም ሆና ዓለማዊው እንቅስቃሴያችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጉልናል፡፡

2⃣ የተመጣጠነ ሕይወት እንድንመራ ያስችለናል

🔸የጊዜ አጠቃቀምም በመንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቋማችን የተመጣጠነ እንዲሆን ይረዳናል፡፡

3⃣ ውጤታማነታችን ያሳድጋል

🔹ውጤታማነት ሲለካ ሥራው መሠራቱ ብቻ ሳይሆን የሚታየው ሥራው የፈጀውም ጊዜ አንዱ መለኪያ በመሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ይገባል፡፡

🔸ጊዜያችን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ በሁሉም ረገድ በትንሽ ጊዜ ብዙ ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡

#ማጠቃለያ

❇️ጊዜ ሀብት ነው፤ እንዲሁም ጊዜ ለእያንዳንዳችን እኩል የተሰጠን ሀብት ነው፤ በመሆኑም እያንዳንዳችን አጠቃቀሙን ተረድተን ይህን ሀብታችንን ለውጤታማነት ልናውለው ይገባል፡፡

❇️ምንም እንኳ ጊዜ ሀብት ቢሆንም አጠቃቀሙን ካላወቅንበት፣ ሀብትነቱን ካልተረዳን ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡

👌ይህም ማለት ጊዜ ካወቅንበት እና ከሠራንበት የሚጠቅመን ሲሆን ካላወቅንበት ግን ምንም ጥቅም የለውም፡፡

❇️ጊዜ ለሁላችን እኩል የታደለ ሀብት ቢሆንም ጠቀሜታው ግን ለሁላችን እኩል አይደለም፡፡

👌ምክንያቱም የጊዜን ሀብትነት ተረድተው በአግባቡ የተጠቀሙበት ውጤት ሲያገኙበት ይህንን ያልተረዱ ግን ተጠቃሚ አይሆኑም፡፡

❇️ጊዜ ለእያንዳንዷ እንቅስቃሴአችን አስፈላጊ እና ጠቃሚ ሀብት በመሆኑ ትኩረትን ይሻል፡፡

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

📌ምንጭ
↪️ @Tewahedo12 Channel




🙏 ሼር ማድረግ አይርሱ 🙏

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን

📩Coment- @YeBiruk
- @Samiabush

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማታረጅ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትታደስ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትጠፋ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትለወጥ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትሻሻል


📖በክርስቶስ ደም የተመሰረተች እውነተኛ ዘላለማዊ ሕይወት ናት ከድንግል ማርያም ፍቅር ከተዋህዶ ማዕድ አይለየን

📖አሜን ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር
በዚህ ወቡ በሆነች ሐይማኖት እስከዘላለም ያፅናን።

#አሜን
#አሜን
#አሜን

#share #share #share

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

📖ቅጠል ረግፎ ቅጠል እንደሚተካው ሁሉ ሰው ወድቆ ሰውን ያኖራል።

📖እኛም ይሄው ነን ይህ ነው ታሪክና ሂደታችን ኑሮና ይህ ህይወታችንን እየወደቁ ያኖሩን እየሞቱ ያተረፉን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት ላንዳችን ህይወት ነው በዚህ መንገድ ነው እየተተካካን የተጓዝነው

📖በዚህ ሂደት ነው ሰው ለመሆን የተንገዳገድነው እየሞቱ ያኖሩን እየወደቁ ያተረፉን የህይወት ቀብድ የተከፈለብን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት የሌላችን ህይወት ነውና የተከፈለልንን ዋጋ ላለማባከን

📖 በእምነት በእውነትና በፅናት በመኖር ህሊናችንን እናሳርፈው።

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
👉 ትዝታው ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ እና ከቤተክርስቲያን ጋር ባለው ግንኙነት ዙሪያ የተነሱት ስጋቶች፣ በተለይም የሕግ ክፍል ሚና ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።

የቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል ሚና እና ተጠያቂነት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል፣ ልክ እንደማንኛውም ተቋም የሕግ ክፍል፣ የቤተክርስቲያኗን ሕጋዊ መብቶችና ጥቅሞች የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት። ይህ የሚያጠቃልለው፡-
የቤተክርስቲያኗን ስም መጠበቅ: ማንኛውም የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም የሚጎዳ፣ የሚያጠለሽ ወይም ውሸት የሚያሰራጭ አካል ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ።
ንብረት ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን ንብረቶች (ሕንፃዎች፣ መሬቶች፣ ቅርሶች፣ ገንዘብ ወዘተ) ከሕገ-ወጥ ወረራ፣ ብዝበዛ ወይም ጉዳት መጠበቅ።
የአስተምህሮ ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን አስተምህሮ የሚጻረሩ ወይም ምእመናንን የሚያደናግሩ ድርጊቶችን ሕጋዊ በሆነ መንገድ መከላከል (ይህ ግን የሃይማኖት ነጻነትን የማያደናቅፍ መሆን አለበት)።
ውሎች እና ስምምነቶች: ቤተክርስቲያን የምትገባባቸውን ማንኛውንም ውሎች እና ስምምነቶች ሕጋዊ ገጽታ ማረጋገጥ።
የውስጥ ክርክሮች: በቤተክርስቲያኗ አባላት ወይም አካላት መካከል የሚፈጠሩ የሕግ ጉዳዮችን መፍታት።
"ቤተክህነቱ የሕግ ክፍል ነፍስ አለው?" የሚለው ጥያቄ
ይህ ጥያቄ ቤተክርስቲያን እንደ ተቋም ለሚያጋጥሟት ችግሮች ምላሽ የመስጠት ፍጥነት እና ብቃት ላይ ያነጣጠረ ነው። "ነፍስ አለው?" ሲባል፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ንቁ፣ ብቁ እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም አለው ወይ? የሚል ጥያቄን ይዞ ይመጣል።
ተቋማዊ ሕይወት: ማንኛውም ተቋም (እንደ ቤተክርስቲያን) የራሱ ሕግና ሥርዓት ያለው አካል ሲሆን፣ የሕግ ክፍሉም ይህንን ሥርዓት በሕይወት ለማቆየትና ለማንቀሳቀስ ቁልፍ ሚና አለው። ስለዚህ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ "ነፍስ" ወይም "ሕይወት" አለው ሊባል ይችላል።
ተግባራዊ ችግሮች: ሆኖም በተግባር ግን እንደ ማንኛውም ትልቅ ድርጅት፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍልም ቢሮክራሲ፣ የሀብት እጥረት፣ የሰው ኃይል ውስንነት ወይም የውሳኔ አሰጣጥ መዘግየቶች ሊያጋጥሙት ይችላሉ። እነዚህ ችግሮች "ነፍስ የለሽ ሬሳ" አስመስለው ሊያቀርቡት ይችላሉ።
ትዝታው እና የቤተክርስቲያን መልካም ስም ጉዳይ
ትዝታው በኢትዮጵያ ውስጥ በቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሲያቀርባቸው የነበሩ አስተያየቶች በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ እንደሆኑ ይታወቃል። የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም አጠፋተዋል የሚል ቅሬታ ካለ፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ይህንን ቅሬታ መርምሮ በሕግ አግባብ ክስ መመስረት የሚችልበትን ሁኔታ ማየት አለበት።
ማስረጃ ማሰባሰብ: "ብዙ ማስረጃ አለ" ተብሎ እንደተጠቀሰው፣ የሕግ ክፍሉ መጀመሪያ እነዚህን ማስረጃዎች በጥንቃቄ ማሰባሰብ፣ ማደራጀት እና ሕጋዊ ክብደት እንዳላቸው ማረጋገጥ አለበት።
የክሱ ዓይነት: ክሱ የስም ማጥፋት (defamation)፣ የሐሰት ወሬ ማሰራጨት ወይም ቤተክርስቲያኗን የሚያጎድፍ ሌላ ሕገ-ወጥ ድርጊት ሊሆን ይችላል።
የፍጻሜ አደራረስ: "ሬሳ የሕግ ክፍል ክስ ቢከስም ለፍጻሜ አያደርስም!" የሚለው አስተያየት የሕግ ክፍሉን አቅም መፈተሽ ነው። ክሱ ለፍጻሜ ለመድረስ ጠንካራ የሕግ መሠረት፣ በቂ ማስረጃ፣ ብቁ የሕግ ባለሙያዎች እና የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ፍቃደኝነትና ድጋፍ ያስፈልገዋል። ያለዚህ ድጋፍ፣ ሕጋዊ ሂደቶች ቀርፋፋ ሊሆኑ ወይም ሙሉ በሙሉ ሊዳክሙ ይችላሉ።

የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል በሕግ ፊት ስልጣን ያለው አካል ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኗን መብቶች ማስጠበቅ የሕግ ግዴታው ነው። ትዝታው በቤተክርስቲያኗ ላይ ጉዳት አድርሷል ተብሎ ከታመነ፣ የሕግ ክፍሉ ያሉትን ማስረጃዎች ተመልክቶ ሕጋዊ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው። ሆኖም የሕግ ሂደቶች ውስብስብ እና ጊዜ የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ውጤታማ ለመሆን ጠንካራ የሕግ አቅም እና ተቋማዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያኗ ምን አይነት እርምጃ ትወስዳለች ብለው ያስባሉ?
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
መ/ር አክሊል

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ አክሊልዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ በቤተ ክርስቲያን ደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።

Mk tv ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር በደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።

ሰኔ 4/2017 ዓ/ም በድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት በተከናወነው የዕውቅናው መርሐ ግብር ላይ የምስጋና ወረቀትም ዶክተሩ የሚመሩት አመልድ ኢትዮጵያ ለአበረከተው አስተጽኦ ከቤተ-ክርስቲያን ደን ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ተበርክቶለታል።

ሽልማቱ የሰጡት በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በደራ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኙ የስድስት አብያተ ክርስቲያናት እና የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተወካዮች ናቸው።

የአብያተ ክርስቲያናቱ ተወካዮች እንደገለጹት በዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የሚመራው አመልድ ኢትዮጵያ በአካባቢያችን ለሚገኙ ጥንታዊ ገዳማት እና አድባራት ተፈጥሮአዊ ደኖቻቸው እና ይዞታቸወ እንዲጠበቅ፣ ኅብረተሰቡን በማስተባበር አጥራቸው እንዲታጠር እና በአካባቢው ለሚገኙ ድሃ ማኅበረሰቦች የኑሮ ማሻሻያ ድጎማ በማድረግ ያደረገውን ተግባራት አውስተው ተወካዮቹ ምሥጋና አቀርበዋል፡፡

የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዓለማየሁ ዋሴ (ፒ.ኤች.ዲ) እንደተናገሩት ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሮጀክት ተጠቃሚዎች መካከል ምስጋና ያቀረቡ መሆናቸውን አውስተው፣ በቀጣይ የቤተ-ክርስቲያን ደንን መሠረት ያደረገ የመልክዐ- ምድር መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ሥራ በሌሎች ቦታዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በአካባቢው የተሠራው ሥራ ዉጤታማ መሆኑን አድንቀዋል፡፡

ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በቤተክርስቲያን የደንና ብዝኃ ሕይወት ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በማካሄድ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ግንዛቤ መፍጠር የቻሉ ሲሆን እመጓ፣ መርበብት እና ዝጎራ በተባሉት መጽሐፎቻቸውም አንቱታን ያተረፉ መሆናቸው ይነገርላቸዋል።

©የዘገባው ምንጭ አመልድ ኢትዮጵያ ነው።

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Forwarded from Ⓢ ⓙⓇ ️ ️️
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።

ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::

#መልካም እለተ ይሁንልን

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

ለመቀላቀል ➟ @weludebirhane

ለአስተያየት ➟ @weludebirhane_bot

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼.
የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት መታሸጉን ተከትሎ አባላቱ ቅሬታቸውን ገለጹ !

ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ሀገረ ስብከት ካሉት ቀደምት እና አንጋፋ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የአሰላ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት በደብሩ ሰበካ ጉባኤ አማካይነት መታሸጉን የሚዲያችን የመረጃ ምንጮች ለሚዲያ ክፍላችን መረጃውን አድርሰውናል። ይህንንም ተከትሎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

በሚያዝያ 08/2017 ዓ.ም በሰበካ ጉባኤ በቁጥር አካ/ደመ/መዓ/ቤክ/ሰጉ/0320/17 በተጻፈ ደብዳቤ የሰ/ት/ቤቱን ሊቀመንበርና የሕጻናት ክፍል መምህር ዲ/ን አበበ ይልማን ከሥራና ከሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢነት ማገዳቸውን በመግለጹ ሰንበት ት/ቤቱ በቀን ምልዓተ ጉባኤ አድርጎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሊቀ መንበር የታገደበትን ውሳኔ ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በደብዳቤ ለወረዳው ቤተክህነት እና ለወረዳው ሰ/ት/ቤት አንድነት አስገብቶ አፋጣኝ ምላሽ ባለማግኘቱ በድጋሚ ለወረዳ ቤተ ክህነቱ በቀን 16/08/2017 ዓ.ም የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቶ ፤ የወረዳው ቤተክህነት ጉዳዩን ተመልክቶ ሊቀ መንበሩ አለአግባብ መታገዱንና የሰ/ት/ቤቱን መብት የነካ ተግባር መሆኑን ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በቁጥር 97/2017 በቀን 17/08/2017 ዓ.ም እገዳው እንዲነሳ ደብዳቤ መጻፉን ለሚዲያችን አስረድተዋል።

ሆኖም ግን ሰበካ ጉባኤው ተፈጻሚ የወረዳ ቤተ ክህነቱን ትዕዛዝ ባለመቀበሉ በ25/09/2017 ለብፁዕ አቡነ ያሬድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል ጠቅሰው ያስገቡት ደብዳቤ ምላሽ ሳይሰጣቸው ሰንበት ትምህርት ቤቱ በግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ታሽጎ አገልግሎት መስጠት ማቆሙን ሚዲያችን ለማወቅ የቻለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ የተላኩ ልዑካን በተገኙበት የታሸገው የሰንበት ት/ቤት ሂሳብ ነክ እና አባላት ቁጥርን ከያዘው ሳጥን ባሻገር ሌላው የታሸጉት ተከፍተው ሰ/ት/ቤቱ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ደብዳቤ ጽፎ ቢልክም ሰበካ ጉባኤው የታሸገውን ለመክፈት ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ለመረዳት ችለናል

ይህንን አስመልክቶ የሚዲያ ተቋማችን የካቴድራሉን አስተዳዳሪ አባ ፍቅረ ሥላሴን በተደጋጋሚ ደውሎ ለማነጋገር ቢሞክርም ሐሳባቸውን በስልክ ለማጋራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሐሳባቸውን ማካተት ያልቻልን ሲሆን ፤ በተጨማሪም የወረዳው ሊቀ ካህናት እና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴን ለማግኘት ያደግረነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል።

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ !

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት
የሕግ አገልግሎት መምሪያው ከሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ
ኮሚቴ ጋር በመሆን አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተ።

የቤተክርስቲያናችን ሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ የምርመራ መዝገቡ መብቱ ለሚፈቅድለት የዐ/ሕግ ዘርፍ እንዲተላለፍለፍ ጠይቋል።

በወንጀል ተጠርጣሪ /ተከሳሽ - አቶ ትዝታው ሳሙኤል
ተጠርጣሪ /ተከሳሹ ነዋሪነቱን በውጪ ሃገር በማድረግ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣
ለመስደብ እና የምዕመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በመጠቀም ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣ በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን <<ግብረ ሰዶማውያን ናቸው>> በማለት፣እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን <<የመተት እና ጠንቋይ ቤት ናት >>በማለት፣ሲቀሰቅስ የቆየ መሆኑን የገለጸው መምሪያው ግለሰቡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የፀሎት፣የታሪክ ፣የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን <<ድውያን መጽሐፍት ናቸው መጥፋት አለባቸው>>ማለቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅድስናየምታ
ከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን << ጣኦታትና ጣኦት አምላኪ>> ናቸው በማለት ግለሰቡ የፈጸመውን የወንጀል አድራጎት በመጥቀስም ክስ መስርቶበታል።
2025/07/01 14:47:14
Back to Top
HTML Embed Code: