╔══════════════════╗
ኢስላማዊ መንግስት መመስረትን ለምን ይፈሩታል
╚══════════════════╝

ኢስላማዊው መንግስት የሙስሊሙን ሃብት፣ መሬት እና ክብርን ከጥቃት ስለሚከላከል።

የዑመር ፍትህ፣ የኻሊድ ኢብኑል-ወሊድ ጀግንነት፣ የኢብኑል-ሃይሰም ዕውቀት የጃቢር ኢብኑ ሐያን ጥበብ የሙሐመድ አል-ፋቲህ ጀግንነት ዳግም እንዳይመለስ ስለሚፈሩ።

አሜሪካ የተዋረደች ሆና ግብርን ለሙስሊሞች ስለምትከፍል። ፈረንሳይ የሙስሊሞችን ኃይል በመፍራት አንገቷን ደፍታ ስለምትኖር።

አንድም የአውሮፓዊያን መርከብ በሙስሊሞች ፈቃድ እንጂ የሜዲትራኒያንን ባህር ማቋረጥ ስለማይችል።

ሞንጎሊያውያን እና ፋርሳውያን፣ አረቦች እና ቱርኮች፣ በርበሮች እና አፍሪካውያን፣ ሕንዳውያን እና አፍጋኒስታኖች ሁሉም ዘሮች በእስልምና ተሳስረው እርስ በርሳቸው የሚደጋገፉ ለወንድሞቻቸው ክብር የሚፋለሙ ወንዶች ስለሚሆኑ።

ኢስላማዊ መንግስት ባለበት ክፋት፣ ጥመት፣ እኩይ ተግባር፣ ፀያፍ ድርጊት፣ የሙስና መስፋፋት፣ የላሸቀ ሥነ ምግባርን ለማስፋፋት እድሉን ስለማያገኙ።

የሶሺዮሎጂ መስራቹ የኢብኑ ኸልዱን ጥበብ፣ በሂሳብ ሊቁ የአል-ኸዋሪዝሚ ብልህነት፣ የአል-ጀዘሪ ፈጠራዎች እና የኢብኑ ሲናን የህክምና ሊቅነት ዳግም ተመልሶ በተሻለ መልኩ በሙስሊሞች እጅ ይገባል ብለው ስለሚሰጉ።

አሜሪካዊው ቶማስ ፓይን በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር:-
"አሁን ሁኔታው ሁሉ ​​ተለውጧል ሙስሊሞቹ በመዳፋችን ውስጥ ገብተዋል ግና ያለፈ ታሪካቸው እንደገና ሊከሰት ይችላልና ጥንቃቄ ያሻል"

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
╔════════════╗
ወተት ነጋዴው ኢማም ሶትጆ
╚════════════╝

ከአንደኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ዓለምን ያንቀጠቀጠው ታላቁ የዑስማኒያ ኺሊፋ በውስጥ መናፍቃንና በጣላቶቹ ሴራ ከወደቀ ወዲህ የፈረንሣይ ኃይሎች ደቡብ ቱርክ "ካህራማማራስ" ግዛትን ተቆጣጠሩ። በወቅቱ ሁሉም ሙስሊም ሴቶች የሚለብሱት ኒቃብ ነበር። ኒቃብ የኢስላም መገለጫ፣ የክብራቸው ማረጋገጫ፣ የውበት ማጌጫ ነበር።

አንድ ፈረንሳዊ ጄኔራል ኒቃብ ለብሰው በመንገድ ዳር የሚጓዙ ሶስት ሴቶችን ተመለከተ። ውስጡ በገነ ኢስላም ዛሬም አለ ሲል ተብከነከነ። ሊያጠፉት የቋመጡት ኢስላም በመኖሩ ልፋቱ ከንቱ የሆነ ያህል ተሰማው።

"ኸሊፋው ተወግዷል አሁን በፈረንሣይ አገዛዝ ሥር ናችሁና ኒቃባችሁን አውልቁ" በማለት አዘዛቸው። ሴቶቹ ኒቃባቸውን ከማውለቅ በያዘው ጥይት ተበሳስተው ነፍሳቸውን መሰዋትን መረጡ። በኒቃባቸው ምክንያት ሸሂድ ሆነው ጌታቸውን መገናኘትን ተመኙ።
በዚህ መሐል ከወታደሮቹ መካከል አንዱ የአንዷን ኒቃብ ለማውለቅ እጁን ዘረጋ። ይህን ክስተት ይመለከት የነበረ "ኢማም ሶትጆ" የተባለ ወተት ነጋዴ ሙስሊም ሴቶቹ ላይ የተጋረጠውን ጥቃት ለመከላከል የፈረንሳዩ ወታደር ላይ እንደተቆጣ ነብር ዘሎ ተጠመጠመበት። ከጄኔራሉ ሽጉጡን ነጥቆ ገደለው። ስለሙስሊም ሴቶች ክብር ሲል ጠላታቸውን ገድሎ በነጠቀው የፈረንሳይ ጀነራል ሽጉጥ አጅቦ ቤት አደረሳቸው።

በዚህ ክስተት ምክንያት በካህራማማራስ ከተማ ውስጥ ግዙፍ አብዮት ፈነዳ። ፈረንሳውያንን በማባረር ከተማዋን ከጸያፍ ድርጊታቸው ነፃ አወጡ።
ከተማዋ በኢማም ሶትጆ ስም አሸብርቃ ዋለች። የተሸፈነች ሙተነቂብ ሴት መሬት የወደቀ የፈረንሳይ ጄኔራልና ኢማም ሶትጆ ሽጉጥ አነጣጥሮ ሲገድለው የሚያሳይ ምስል በከተማው አደባባይ ላይ ተተከለ። የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በስሙ ተሰየሙ። ታሪክ የማይረሳው ጀግና ሲሉ እስከ አሁንም ያስታውሱታል።

አላህ መልካም ስራውን ይቀበለው።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከናፋቂዎች ገጠመኝ
የሼኽ ኻሊድ አርራሺድ አማርኛ ትርጉም ዳዕዋ
╔════════════════╗
ካፉር አል-ኢኽሺዲ
(ከባርነት እስከ የሙስሊሞች መሪ ኸሊፋነት)
╚════════════════╝

ጥቁር ጀንደረባ ነው። አጭርና ወፍራም፣ አስቀያሚ መልከ ጥፉ መልኩ መስህቦቹን አሳጥተውታል። የታችኛው ከንፈሩ የተገለበጠ፣ የተወላገዱ እግሮች ባለቤት ነው። ቀርፈፍ ያለ እግሮቹ ሰውነቱን መሸከም ይከብዳቸዋል። ካፉር አል-ኢኽሺዲ ይባላል።
በኑባ የባርያ ገበያ ተሽጦ ወደ ግብፅ ጉዞውን ጀምሯል። እጁ በሰንሰለት አብሮ ወደተጠፈረው ባርያ ዞሮ ስለ ወደፊት ምኞቱ ጠየቀው በርሀብ ሆዱ እየጮኸ የነበረው ሰው እንዲህ ሲልም መለሰለት "በፈለግኩበት ጊዜ የፈለኩትን መብላት እንድችል ምግብ ሰሪ ብሆን እመርጣለሁ" አለ።
እሱም በተራው ካፉር ኢኽሺዲን ስለምኞቱ ጠየቀው "የዚህች ሀገር ባለቤት መሆን እመኛለሁ" ሲል ካፉር መለሰ። ለገበያ የቀረበ ባሪያ ሻጮቹን ለመምራት አሰበ። በሰዎች እየተገዛ የሚሸጥ ኒያውን ከፍ አድርጎ የመሪነት ዙፋኑ ላይ ተደላድሎ ህዝብን ሲመራ በሐሳብ ነጎደ። በተንፈላሰሰና በወርቅ በተጌጠ አልጋ ላይ ተኝቶ ሀገሩን በፍትህ ሲያስተዳድር በዓይነ ህሊናው ታየው። "ይህንን ሀገርና ህዝብ ማስተዳደርን እመኛለሁ" ሲልም በእርግጠኝነት ተናገረ።
ካፉር ኢኽሺዲ ለአንድ የዘይት ነጋዴ ተሸጠ። ሰውየውም በተለያዩ ስራዎች ላይ አሰማርቶ ጉልበቱን በዘበዘው። ለዘይት አገልግሎት የሚሆን እህል አጭዶና አዘጋጅቶ፣ በእግሩ እየረገጠ የጨመቀውን ዘይት በማሰሮ ሞልቶ በትከሻው ላይ ይጭንና በየመንገዱ እያዞረ ለፈላጊዎች ይሸጣል። ዘይት በነካካው እጆቹ እሳት እያቀጣጠለ ምግብ ያበስላል። አረፍ ብሎ የሚተኛውም መሬት ላይ ነው። ፍራሽም ሆነ ምንጣፍ አያውቅም። ከዚህ የእለት ተእለት ተግባር በተጨማሪ የአሳዳሪው ዘርፈ ብዙ መከራዎች እየተፈራረቁበት ችግሮችን ለመጋፈጥ የሚያስችለውን ጥንካሬ አላበሰው። በእርግጥም ጠንካራ ሰው አደረገው።
ዘይት ነጋዴው የበለጠ ትርፍ ያመጣ ዘንድ መህሙድ ቢን ወህብ ለተባለ በስነ ፅሑፍ ለመጠቀ ሰው ሸጠው። ከዘይት ፍሳሾች እጆቹን አፅድቶ የንባብና የፅሑፍ መንገድን ተቀላቀለ። ከፊደልና ከወረቀት ጋር ተፋጠጠ።
በወቅቱ ግብፅን ያስተዳድር የነበረው የአባሲያ ኸሊፋ በሺዐ ፋጢሚያ ኢንፓየር ላይ ድልን ተቀዳጅቶ ሙሐመድ ቢን ጠግጅ የተባለን ቱርካዊ ወጣት የሾመበት ወቅት ነበር።
ካፉር ኢኽሺዲ የፅሑፍ ትምህርቱ ላይ ጎብዟል። ቋንቋም አቀላጥፎ ይናገራል። አሳዳሪው ከግብፁ ገዥ ጋር ወዳጅ ነበር። ታዲያ አንድ ቀን ካፉርን ለግብፁ ገዢ ውድ እቃ በመጠቅለያ አሸብርቆ ስጦታን ያደርስ ዘንድ ላከው። ካፉር ወደ ቤተ መንግስቱ አምርቶ ስጦታውን አስረከበ። የግብፁን መሪ ቀልብ ገዛ። ይሸጥ ይሆን በማለት ጓደኛውን ጠየቀ። ልቡ የተማረከበትን ሰው ወዳጁ በስጦታ አበረከተለት።
ካፉር የቤተ መንግስት ህይወት የተመቸው ይመስላል። በደስታ ያጣጥማት ይዟል። በመላላክና ስራዎች ላይ በመጠመዱ በጣም ቀሎታል። ቤተ መንግስቱ እንዳሻው የሚቦርቅበት ሥፍራም ሆኖ ዓመታት ነጎዱ። የግብፁ ገዢም ወደማይቀረው ሞት ተጓዘ። ኡንጆር የተባለ ትንሽ ልጅ ነበረው። አገልጋዩ ካፉርን ለልጁ እንደ ጠባቂ አድርጎ ሾሞታል። የትንሹ ልዑል ጠባቂ ሆኖ ኃላፍትናውን ተቀብሏል። ኦንጆር ከሁለት አመት በኋላ የአባቱን መንገድ ተከተለ። ወንድሙ አሊ አሚር ተደርጎ ተሾመ። የግብፅ ሰዎች በእርሱ ላይ አደሙ። ከመዝናናት አሊያም ከሰላት በስተቀር ምንም ሥልጣን እንዳይኖረው ተደርጎ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ የቁም እስረኛ ሆነ።
አሊም ቀነ ቀጠሮው ደርሶ አፈር ለበሰ። ካፉር አል-ኢኽሺዲ ራሱን የግብፅ መሪ አድርጎ ሾመ። "ኢኽሺዲያ ሥርወ መንግስትን" መሰረተ። የኢስላም ጠላቶች በጀግንነቱ የተነሳ ጥቁሩ ዲንጋይ እስካልጠፋ ግብፅን ማሸነፍ አንችልም እስከማለት ደረሱ።
በካፉር አል-ኢኽሺዲ ወይም በኢኽሺዲያ ስርወ መንግስት ዘመን የገንዘብ ባለቤቶች ዘካ የሚቀበልላቸው ሰው እስከመያገኙ ድረስ ድሆች ከከተማዋ ጠፉ። ሻምና ግብፅ በዓውደ ጥበብ የበለፀገ ዘመንን ኖሩ። ከአራት መቶ ሺህ በላይ ጠንካራ ሠራዊትን መልምሎ ጦሩን አደራጀ። ውብ የአትክልት ሥፍራን ገንብቶ በማራኪ መስህቦቿ ነዋሪዎቿን አጀብ የምታሰኝ ከተማ አደረጋት።
ሷሊሆችን የሚወድ፣ ለኃይማኖቱ ቀናኢ ሰው ነበር። በየሳምንቱ ረቡዕ ከመሻኢኾች ጋር ተቀማምጦ ከማይጠገብ አንደበታቸው ጥበብ ከተሞላው ዕውቀታቸው ይቀስማል። የኢስላም ሊቃውንቶችን፣ ጸሐፊዎችና ባለቅኔዎችን በእጅጉ አከበረ። ወደራሱም አስጠጋቸው። 23 ዓመታት ግዛቱን በፍትህ ሞልቶ፣ በኢስላማዊ ስነምግበር የታነፀ ትውልድን አፈራ። ግብፅን በኢልም ያበበ በአዛን ያሸበረቀ ከተማ አደረጋት።
አላህ ይዘንልህ ያ በጠል

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
╔════════════════╗
ዐብዱላሂ ጋሊብ አብደላህ አል-በርጉሲ
╚════════════════╝

"እርሱ ማስተር ማይንዳችን ነበር" በማለት የፍልስጤም ሙጃሂዶች ያንቆለጳጵሱታል። የእስራኤሉ የስለላ ተቋም "ሞሳድ" "ባለጥላው መሪ!" በማለት ይጠራዋል። እስራኤላውያንን ቁም ስቅል ያሳየ፣ ጭንቅላቱን በሚገባ የተጠቀመ የጦር ሊቅ፣ የሞሳድ ኤጀንቶችን ያደናገረ ጀግና የጦር መሪ እንደነበር ራሳቸው ይመሰክራሉ።
ፅዮናዊቷ እስራኤል የአን ነክባን ጥቃት በሰነዘረችበት ጊዜ ነበር የጂሃድ እንቅስቃሴውን በይፋ የተቀላቀለው። ዳር-ያሲን የምትባል ከኢየሩሣሌም አቅራቢያ የምትገኝ ፀጥተኛ መንደር ላይ ከበባ አድርገው ዕድሜና ፆታ ሳይለዩ ፊት ለፊት ያገኙትን ሁሉ በጥይት ቆሉት፡፡ በስለትና በመጥረቢያ ጨፈጨፉት፡፡ ለማምለጥ የሚሞክረውን መግቢያ መውጫውን ዘግተው በመጠበቅ ደፉት፡፡ 256 ነዋሪዎች ላይ ጭፍጨፋ አድርገው አንድም እንዳልተረፋቸው እርግጠኛ ሲሆኑ ቤት ንብረቱ ላይ የፍየልና የግመል ማደሪያ፣ የጥራጥሬ ማከማቻ ሳይቀር እሣት ለቀቁበት፡፡ ፍልስጤማውያን ይህን ቀን ´አን-ነክባ’ ይሉታል፡፡ በታላቅ ምሬትም ያስታውሱታል፡፡ የኃዘንና የዕልቂት ቀን ማለት ነው፡፡
አብደላህ አልበርጉሲ በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ከደቡብ ኮሪያ በማእረግ ተመርቋል። በጁዶ ካራቴ ከፍተኛ ማዕረግን አጊኝቷል። ተቀጣጣይ ፈንጅዎችን መስራት ለሱ ምግብ እንደማብሰል ቀላል ነው። በኮምፒውተር ሃኪንግ ኤክስፐርት ነው። ከዛሬ ሀያ አመታት በፊት ነበር በጠቅላይ ሚኒስትር ናታንያሁና በእስራኤል ቱባ ባለስልጣናት በተመራ ኦፕሬሽን በመናፍቃን ጥቆማ በቁጥጥር ስር የዋለው።
እጃቸውም እንደገባ በደስታ ፈነደቁ። ውስኪያቸውን እየተራጩ እርስ በርስ እንኳን ደስ አላችሁ ተባባሉ። በመጠጥ ሰክረው በደስታ ስሜት ተናጡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ናታንያሁ በዚያው ለሊት ለሚስታቸው በቀጥታ ደውለው እንዲህ በማለት እንደተናገሩ ጋዜጦች ከተቡ
"አስቸጋሪውና የሙጃሂዶቹን ማስተር ማይንድ፣
ባለ ጥላውን መሪ ያዝነው!.. አዎ በትክክል ይዘነዋል! እርሱ መሆኑንም አረጋግጠናል.." በማለት ደስታቸውን እየፈነጠዙ ለሚስታቸው አጋሯት።
67 ጊዜ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል። 5200 ዓመታት በእስር እንዲያሳልፍም ተወስኖበታል። እግርና እጁ ተጠፍሮም ለአመታት ብቻውን ጨለማ ቤት አሳልፏል። ጭካኔ የተሞላበት ስቃይንም አስተናግዷል። ሚያዝያ 2012 ለ28 ቀናት ባካሄደው የእስር ቤት የረሃብ አድማ ሁሉም እስረኞች እንዲፈቱ ምክንያት ሆኗል። በእርግጥም እሱ ስለኢስላምና ሙስሊሞች ሲታገል የኖረው ሕይወቱን ለስቃይ የዳረገው ዐብደላህ አልበርጉሲ ነው።

ከቤተሰቡ ተገሎ በእስር ቤት ስቃይ መማቀቅ ከጀመረ ዘንድሮ ሀያ አመቱን ይዟልል። አላህ ከግፈኞች ነጃ ይበለው።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
╔══════════════════╗
ታሪክን ቢያድበሰብሱትም እውነታው ግን ይህ ነው
╚══════════════════╝

ከቡና ሲኒ .. እስከ ጥርስ መፋቂያ .. ከሆስፒታል .. እስከ ዩኒቨርሲቲ .. ከኦፕራሲዎን እስከ ችግኝ ማቆያ .. ከኬሚስትሪ እስከ ፊዚክስ፣ ከሰርጓጅ መርከብ እስከ ሚሳኤል .. ፓምፖችን፣ ሞተሮችን፣ ሰዓቶችን፣ ሻምፖ፣ ብዕር .. የሂሳብ ቁጥሮች .. ገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶች፣ ባንክ ቤቶች .. ኢስላማዊ ፈጠራዎች ናቸው። የዘመናዊ ሳይንስ የስኬት ውጤት የሙስሊሞች ነበር።
የደም ዝውውርን ያገኘና በሰው አካል ላይ የአስከሬን ምርመራን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስጀመረው ሙስሊም ነበር “ኢብኑ አን-ነፊስ” ይባላል።
የዓለምን ካርታ የቀረፀው የመጀመሪያው ሰው “ሙሐመድ ኢድሪስ” ይሰኛል።
የአልጀብራን ሳይንስ የፈለሰፈ፣ የዘመናዊ የሂሳብ ደንቦችን የመሰረተ የመጀመሪያው ሰው “ኸዋሪዝም” ይባላል።
“አል-ቡሩኒ” በሳይንሳዊ ጥናት የስበት ኃይልን ያጠና የመጀመርያው ሙስሊም ሳይንቲስት ነበር።
የአተሞችን እና የኒኩለር ፍንዳታ ሳይንስን ያገኘ የመጀመሪያው ሰው ጃቢር ቢን ሀያን ይሰኛል።
ኢብን ኸልዱን ሶሺዮሎጂን ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው ሙስሊሙ ሊቅ ነበር።
ጆሴፍ ኬፕ “The Civilization of Muslims” በሚለው መጽሐፉ ገጽ 31 ላይ (ሙስሊሞች በስፔን እንዳሸነፉት በአውሮፓ አሸንፈው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ካለንበት አምስት መቶ ዘመናት ወደፊት እንቀድም ነበር) ይላል።
በፊዚክስ ዘርፍ የኖቤልን ሽልማት ያገኘው ፈረንሳዊው ሳይንቲስት ፒየር ኩሪ እንዲህ ይላል:-
"ከአንደሉስ ምድር በሙስሊሞች እጅ የተፃፉ ሠላሳ መጽሐፍትን አገኘን። እነዚህ መፅሐፍትም አቶምን ለመከፋፈል አስቻለን። ከተቃጠሉት ሚሊዮን መጻሕፍት ውስጥ ግማሾቹ ቢኖሩ ኖሩ ዛሬ በጠፈር ጋላክሲዎች መካከል እንገኝ ነበር"
በእስልምና ኺላፋ ወርቃማ ዘመን አውሮፓውያን ከሙስሊም ሊቃውንቶች ትምህርትን ለመቅሰም ወደ ባግዳድ፣ ካይሮ፣ ቤጃያ፣ ማርኬሽ፣ ቱኒዝ፣ ኮርዶባ እና ሴቪል በእግራቸው ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አቆራርጠው ይጓዙ ነበር።
አላህ በእስልምና ክብርን ሰጥቶናል እኛ ግን እስልምናን በተግባር ከመኖር ተዘናጋን። ውርደትንም ተከናነብን።

ኢስላም የሚኖሩት እንጂ የሚያወሩት እምነት አይደለም

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
╔═══════════╗
የአሊሟ ሴት ገጠመኝ
╚═══════════╝

የሸይኽ ሰኢድ ኢብኑ ሙሰዪብን የዕውቀት ገበታን ያዘወትራል። በረሀውን አቆራርጦ በብርድ በቁሩ፣ በሙቀት በግለቱ አንገቱን ሰበር አድርጎ ጆሮውን ቀስሮ ከማዕዱ ይቋደሳል። አቡ ወዳአ ሲሉም ይጠሩታል።
የጀነቱ ጨፌ ከሚቀጠፍበት ሥፍራ ለሁለት ወራት ከራቀ በኋላ ወደ ዒልም ገበታው ዳግም ተመለሰ።
ሰላምታን ከኡስታዙ ጋር ተለዋወጠና የናፈቀውን ትምህርት መከታተል ጀመረ። ደርሱ እንዳበቃ በምን ምክንያት እንደቀረ ለምንስ ሳይናገር እንደጠፋሁ ሸይኹ ጠየቁ። ባለቤቴ ሞታብኝ ሀዘን ላይ መቆየቱን አብራርቶ አስረዳቸው።
ሰው ከበዛበት ቦታ ገለል አድርገው ወሰዱትና እንዲህ በማለት ጠየቁት፦
"አዲስ ሚስት ለማግባት አላሰብክምን?!"
"ለኔ አይነቱ የቲም ሆኖ ላደገ፣ ድሃ ሆኖ ለኖረ ልጁን የሚድር ማን አለ?! ወላሒ አሁን ከሁለት ዲርሃም ሀብትም ሆነ ንብረት የለኝም" በማለት መለሰላቸው።
"ልጄን እድርልሀለው" አሉት።
ታላለቅ ባለስልጣናት ልጃቸውን ጠይቀው አልድርም ማለታቸውን ያውቃልና ይህን ቃል ሲሰማ ምላሱ ተኮላተፈ። ተንተባተበ።
"የችግር ህይወቴን አውቀው ልጅዎን ሊድሩኝኝ?" በማለት በተደናገጠና በተቆራረጠ ድምፅ ጠየቀ።
"አዎ! ልጄን እድርልሃለው ኃይማኖቱና ሥነምግባሩ ያማረ ሰው ካገኘን ልጃችንን እንድንድር እስልምና ያዘናልና አንተ ደግሞ በሥነ ምግባርህ ትሁትን አደብ ያለህ መልካም ሰው ነህ" በማለት መለሱለት።
ለምስክርነት የሚሆኑ ሁለት ሰዎችን ጠሩና ያለችውን ሁለት ዲርሀም መህር አድርገው ኒካሁ ታሰረ።
ከድንጋጤና ከደስታው ብዛት የተነሳ የሚናገረውን ማወቅ ተሳነው። ከተቀመጠበት ብድግ አለ። ቀኑን ፆመኛ ስለነበር መስጂድ ገብቶ የመግሪብ ሰላት ሰገደና ወደ ቤቱ አቀና። ልጅቱን ሳያውቃትና ሳያያት መቀበሉ ገርሞት አንገቱን ነቀነቀ።
ትርክቱን ለባለታሪኩ እንተውለት
"ቤት እንደገባሁ ፋኖሴን አብርቼ የማፈጥርበትን ዘይትና ዳቦ አቀረብኩ። አንድ ሁለት እንደጎረስኩ የቤቴ በር ተንኳኳ። "ማነው?" በማለት ከበሩ ኋላ የቆመውን ሰው ማንነት ለማጣራት ጠየቅኩ። "ሰዒድ" የሚል ምላሽ ሰማሁ። በአላህ እምላለሁ!ሰዒድ በሚል መጠሪያ የማውቃቸውን ሰዎች ሁሉ ሳስብ ኡስታዜ ሰዒድ ኢብኑ ሙሰዪብ ይሆናል ብዬ ፈፅሞ አላሰብኩም። አርባ ዓመታትን ሙሉ ቤቱ ወይም መስጂድ እንጂ ሌላ ቦታ ታይቶ አይታወቅም። አወለሰፍ እንጂ የሰውን ጀርባ እያየ ሰግዶ አያውቅም። በሩን ከፈትኩ ከፊት ለፊቴ ኡስታዜ ቆሟል። ደነገጥኩ። "ልጁን ለኔ አይነቱ መናጢ ድሃ በመዳሩ ተፀፅቶ ሀሳቡን ሊቀይር ነው የመጣው ብዬ አሰብኩ "ያ አባ ሙሐመድ! እዚህ ድረስ በመምጣት ለምን ደከምከ ሰው ልከህ ብታስጠራኝ እመጣ ነበር" አልኩትና ወደ ቤት እንዲገባ ጋበዝኩት።
"ዛሬ መምጣት ያለብኝ እኔ ነኝ። የመጣሁትም ልጄ ሚስትህ ሆናለችና እሷ አባቷ ቤት ብቻዋን አንተም በቤትህ ያለ አጫዋች ስለሷ እያሰብክ ብቻህን መሆንህን ጠልቼ ይዣት መጥቻለሁ" አለና ከጎኑ ወፈቆመችው መልከ መልካም እንስት ዞሮ "ልጄ ሆይ! በአላህ ስምና ረድኤት ወደ ባልሽ ቤት ግቢ" በማለት የአባትነት ትዕዛዙን አስተላለፈ። ከሐያእዋ የተነሳ ወደኔ ስትራመድ ቀሚሷ አደናቅፏት ልትወድቅ ተቃረበች።
አባቷን አንኳ በስርአት ሳልሰናበት እየተጣደፍኩ ወደ ውስጥ ዘለቅኩ። ድህነቴ ስላሳፈረኝ የፋኖሱን ብርሃን አደብዝዤ ዳቦና ዘይቱን አልጋ ስር ደበቅኩት።
የቤቴ ጣራ ላይ ወጥቼ "ሰዒድ ኢብኑል ሙሰዪብ ልጁን ዳረኝ ቤቴ ድረስም ይዞልኝ መጣ" ብዬ ከፍ ባለ ድምፅ አዋጅ አልኩ። ከጎረቤቶቼ መካከል አንዲት አሮጊት በመስኮት በኩል አንገቷን ብቅ አርጋ እንዲህ አለችን፦
"አንተ ሰው! ለመሆኑ የምትናገረውን ታውቃለህ? ሰዒድ ልጁን ድሮህ ከቶውንም ቤትህ ድረስ ይዞልህ ሊመጣ? እሷ እንኳን ላንተ ለድሃው ለታላቁ መሪ ልጅ ወሊድ ቢን አብዱልመሊክ እምቢ ተብላለች ውበቷስ ቢሆን ላንተ ለደሃውማ አትገባም"
"ግቡ ቤቴ ናት ያለችው ተመልከቷት እውነተኛነቴን ታረጋግጣላችሁ" አልኳት።
ከአዲሷ ሚስቴ ጋር የጫጉላ ቆይታዬን ጨርሼ ወደ ቀድሞው የዕውቀት ገበታ ዒልምን ለመቋደስ ስነሳ "አንተ የዓይኔ ማረፊያ የቤቴ ሙሶሶ ባሌ ሆይ! አባቴ ጋር ያለው እውቀት ሁሉ እኔም ጋር አለና ቁጭ ብለህ ቅራ" በማለት በጆሮዬ ሹክ አለችኝ።
ቁርአንን በቃሎ የሸመደደች። የረሱልን ﷺ‎ ሐዲስ የሐፈዘች የጌታዋን ቃል አክባሪ፣ የተማረችውን ዕውቀት ተግባሪ፣ አላህን ፈሪ የባሏን ሀቅ ጠባቂ መልከ መልካምና እጅግ ቆንጆ እንስት ሆና አገኘኋት።

አሚን በሉ ልመርቃችሁ!
የእስልምና አኽላቅን የተላበሰች፣ ልጆቻችሁን በጀግንነት አሳድጋ ለቆራጥ አላማ የምታዘጋጅ እንስትን አላህ ይወፍቃችሁ።
ሴቶችዬ በኢማን የበለፀገ በተግባር የጎለበተ እንደ ሰላሐዲነል አዩቢ አባት ልጆቻችሁን የሚያንፅ ባል ይስጣችሁ።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ አድራሻችን ነው ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
ጀግናን ላስተዋውቃችሁ ፕሮግራም ቁጥር 1

ሞት የተፈረደባቸው ኢትዮጵያዊው ሙጃሂድ

. . . የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ፈርጥ፣ የጀግኖች ተምሳሌትና ወደር የሌላቸው ተፋላሚ ናቸው። ስለ ጀግንነታቸው አፄ ኃይለሥላሴ ሳይቀሩ መስክረውላቸዋል "የዚህ ቃልቻ ድፍረት ሰላም ነሳኝ" ሲሉም ተናግረዋል . . .
ሙሉ ታሪካቸውን አሰናድቼ ወደእናንተ አቅርቤዋለሁ። ሊንኩን በመጫን ይከታተሉ።

https://youtu.be/eVppvJIh4h4
https://youtu.be/eVppvJIh4h4

ተመሳሳይ ትምህርቶችን ለማግኘትም ሰብስክራይብ በማድረግ ከታሪኩ ይቋደሱ።

ሼር በማድረግ በጣቶቻችሁ አጅርን ሸምቱ
የብሪታኒያው ንጉስና የሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በሱልጣን ሱለይማን አልቃኑኒ ዘመን ደማስቆን ለመጎብኘት ፈቃድ ጠየቁ። ከአራት ወራት በኋላ ያለ አጃቢ ወታደርና ያለ ጫማ በባዶ እግራቸው ደማስቆን እንዲጎበኙ ተፈቀደላቸው።
የብሪታንያው ንጉስ ጫማውን ለምን እንደሚያወልቅ ጠየቀ። ሱለይማን አልቃኑኒም እንዲህ በማለት መለሰ "ይህ የተባረከ ምድር የረሱል ባልደረቦች የተቀበሩበትና በከበረ እግሮቻቸው የረገጡት መሬት ነው። በሱለይማን አልቃኑኒ የንግስና ዘመን በነጃሳ እግሮቻችሁ ገብታችሁ ታሪክ የሚወቅሰኝን ተግባር እንድፈፅም ትሻላችሁን? በጌታዬ ይሁንብኝ ከፀሀይ መውጫ እስከ ፀሐይ መግቢያ በባዶ እግራችሁ ትጎበኛላችሁ እንጂ ከነ ነጃሳችሁማ ወደ ከተማው አትገቡም"

ምንጭ:-
كتاب سكون الليل
╔═══════════════╗
ከ ሡልጣን ሱለይማን አልቃኑኒ
ለ ፈረንሳዩ ንጉስ የተፃፈ ደብዳቤ
╚═══════════════╝

በታላቁ ሱልጣን ሱለይማን አልቃኑኒ የአመራር ዘመን በፈረንሳይ ውስጥ ወንዶች ከሴቶች ጋር እየጨፈሩ ነው የሚል ዜና ኸሊፋው ጆሮ ዘንድ ደረሰ። በንዴት በግኖ ደብዳቤን ፃፈ። ወደ ፈረንሳዩ ንጉስም ላከ፡፡
"በሀገራችሁ ያሉ ሀፍረት የሌላቸው ወንዶችና ሴቶች በሰዎች ፊት ተቃቅፈው እየጨፈሩ እንደሆነ ሰምቻለሁ። ሀገራችሁ ከእኛ ድንበር ጎን ስላለች ይህ ጋጠወጥ ስነምግባር ወደእኛም ሊዛመት ይችላልና መልዕክቴ እንደደረሰህ በፍጥነት ይህን እርኩስ ተግባር አስቁም አለዚያ እኔው ዘምቼ ለማጥፋት ወደናንተው ሀገር እመጣለሁ"
ከዚህ ደብዳቤ በኋላ ጭፈራው በፈረንሳይ ውስጥ ለመቶ ዓመታት ሙሉ በምስጢርና በድብቅ ይከወን እንደነበረ የኦስትሪያው ታሪክ ጸሐፊ ሀመር ዘግቧል፡፡
ሱለይማን የአመራር ብቃቱ በታሪክ ድርሳናት ተገልፀዋል። ራሱ ውጊያ ውስጥ እየገባ ከጠላቶቹ ጋር በሠይፍ ይዋጋ ነበር። ወታደሮቹን ሁሉ በውጊያ ውስጥ ይቀሰቅሳቸዋል።
"እናንተ ዘማች ታጋዮች ሆይ! የአላህ ወታደር ሁኑ። ጠንክሩ በርቱ። ለዲናችሁም መስዋዕት ክፈሉ። ከፊት ለፊታችሁ ጀነትንና ሑረል ዓይንን አድርጋችሁ ተዋጉ" እያለ ይመክር ነበር።
ማንኛውም ድርጊቱን የሚከውነው በእስልምና ድንጋጌዎች ሥር ነው። ሸሪዓን በጣም ተግባራዊ ያደርጋል። ኢስላም የሚያዘውን ማንኛውንም ነገር እሱ መጀመሪያ ተግብሮ ህዝቦቹ እንዲተገብሩ ያደርጋል። በእሱ ግዛት ያሉ ሙስሊም ያልሆኑ የሌላ ኃይማኖት ተከታዮች በደልም ሆነ ግፍ አይደርስባቸውም። መመሪያው ሐቅና ፍትህ ብቻ ነው።
በግዛቱ ውስጥ ፍትህ እንዲነግስ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋል። በየጊዜው ከተለያዩ አካባቢዎች ዑለማኦች ግዛቱን እንዲጎበኙና የፍትህ መጓደል ካለ መረጃ እንዲያቀርቡለት ያደርግ ነበር። በተለይ ወደ ገጠር ክልሎች እየሄደ የፍትህ ይዞታውን ይመለከታል። ፍትህ ተጓደለብን የሚሉ ሰዎችን በግንባር ያደምጣቸዋል። መፍትሔም ይሰጣቸዋል።
በለሊት ሰዓት በከተማ ውስጥ እየተዘዋወረ ይመለከታል። የሰውን ችግር በመጠየቅ ችግራቸውን ይፈታል።
"ኢስላምን ማገልገል ፍላጎቴ ነው። በክህደት መንገድ ላይ ያሉ ታጋዮች ድልን እንዲጎናፀፉ አልፈቅድም። በገንዘቤና በሕይወቴ አላህን መገዛት የምንጊዜም ትግሌ ነው። ከአላህ የሆነ ድልን ተጎናፅፌ ትልቁን ኢስላማዊ ስርወ መንግስትን ማጠናከር ምኞቴ ነው" ይል ነበር።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንታችን ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
የረሱል ኒካህ ዕለት
══════════════

የሙሽሪት እና የሙሽራው አጎቶች ተሰባስበው ወጉን ሊጀምሩ እርስ በርስ እየተያዩ ነው። የሙሽራው አጎት የሆነው አቡ ጣሊብ ከመሐል ብድግ ብሎ ቆመ።
ስፍራው ላይ የታደሙት ሰዎች አቡ ጣሊብ ለመናገር እንደቆመ ሲረዱ ፅሞናን አሰፈሩ። አቡ ጣሊብም ንግግር ጀመረ፦ "የኢብራሂም ዝርያዎች እና የኢስማዒል ፍሬዎች ያደረገን ጌታ የክብርነት ቤቱ ጠባቂያዎች እና የጎብኚዎቹም ተቀባይ ስላደረገን ጌታችንን እናመሰግናለን። በመቀጠል ይህ የወንድሜ ልጅ ምንም እንኳ ደሃ ቢሆንም ከመካ ቁረይሽ ወጣቶች ብታነፃፅሩት ብጤ የሌለው ሲሆን በልግስናም፣ በትህትናም፣ በክብርም ማንም አይስተካከለውም። ባለ ፀጋነት እንደሆን የቀን ጥላ ማታ ጠፊ ነው። ልጃችን ልጃችሁን የከጀለ ሲሆን ልጃችሁም ልጃችንን ከጅላለች እና የሻችሁን የመህር ተመን ወስኑ ከፋዩ እኔ ነኝ" ብሎ የሽምግልና ሂደቱን አስጀመረ።

የሙሽሪት አጎት እሷን ወክሎ ሊድራት ከተሰየመበት መንበር ተቀምጦ እንዲህ አለ፦ "ባወሳኋቸው ፀጋዎች ሁላ ለጌታችን ምስጋና ይገባው። የመላው አረብ በላጮች ስላደረገንም እያመሰገንን እናንተም በኑ ሀሺሞች የዐረብ ሁላ ቁንጮ መሆናችሁን እንመሰክራለን። እኛም ከናንተ በሚያስተሳስረን የዝምድና ገመድ ለመተሳሰር ከጅለናል" ብሎ ሽምግልናውን ተቀበለ።
ንግግሩን ቀጠለ። በስፍራው ወደታደሙ የቁረይሽ ነገዶች ፊቱን አዙሮም፦ "እናንተ የቁረይሽ ነገዶች ሆይ! እኔ ኸዲጃ ኹወይሊድን ለሙሐመድ ዐብዱላህ የዳርኩ ስሆን እናንተም ምስክር ሁኑ" ብሎ ለኸዲጃ የአለማቱን ክብረት ሸለማት።

ይኼኛው የረሱል (صلى الله عليه وسلم) ሰርግ ቢያመልጠንም ነገ በአኪራ በጀነት እልፍኞች ውስጥ የሚደገሰውን ሰርጋቸውን በክብር እንድናጅባቸው አላህ ይወፍቀን።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንታችን ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
የወጣቱ ኦታ ቤንጋ ታሪክ
╚═══════════════╝

በ1883 በደኖች በተከበበው ሀገረ ኮንጎ ሞቡቲ በተሰኘ መንደር ውስጥ ኦታ ቤንጋ የተባለ ብልህ እና ደስተኛ ወጣት ተወለደ። በአካባቢው ቋንቋ ጓደኛ እንደማለት ነው።
ሀገረ ኮንጎ በንጉሥ ሊዮፖልድ በጭካኔያዊ ትዕዛዙ በርካቶችን የሚገልበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን በእልቂቶች የታወቀ እና በአገሬው ተወላጅ ሕዝብ ላይ የበዙ ግድያዎች የተፈራረቁበት ነበር።
ኦታ ቤንጋ በልጅነት ዕድሜው አግብቶ ሁለት ልጆችን አፍርቶ ኑሮውን ይገፋው ይዟል። በአንድ ወቅት በሀያኛው ዕድሜ ውስጥ ሳለ ሪዝቅን ፍለጋ ለአደን ወጥቶ የከሰባትን ይዞ ወደ ቀዬው ሲመለስ መንደሩ በእሳት ነዶ ወድሟል። ሚስትና ሁለት ልጆቹን ጨምሮ አብዛኛው የቀዬው ነዋሪ ሞቷል። በፈረንጅ ተመራማሪዎች ቦታው ተከቧል።
ገና ከመድረሱ እጅና እግሩ በሰንሰለት ተጠፍሮ ከኋላ እየተገረፈና እየተነዳ በባርነት ይሸጥ ዘንድ ወደ አውሮፓ ምድር በባዶ እግሩ ጉዞውን ጀመረ።
በዚህ መሐል ነበር በሴንት ሉዊስ ከሚገኘው የሉዊዚያና የግዢ ኤክስፖሲሽን ጋር ውል የነበረው አሜሪካዊው ተመራማሪ ሳሙኤል ፊሊፕስ ቨርነር የተመለከተው። የዝግመተ ለውጥን ፅንሰ-ሀሳብ ለማረጋገጥ ምርምር እያደረገ የነበረበት ወቅት ነበር። የሉዊ ወርልድ ፒግሚዎችን ለማሳየት እጅግ የጠለቀ ፍላጎትና እንቅስቃሴ ነበረው። በተለይም በአፈ ታሪክ የሰው ልጅ የዝግመተ ለውጥ ሚዛን መሠረት ከቺምፓንዚዎች ከጎሬላዎችና ከኦራንጉተኖች ጋር በጣም ቅርብ ነው ይባልበት የነበረበት ዘመን ነው።
ኡታ ቤንጋ ቁመቱ አንድ ሜትር ተኩል ነው። ሳሙኤል ፊሊፕስ ቨርነር ሲመለከተው በጣም አጭር ሆኖ አገኘው። በእጅጉም ተገረመ። አልባሳትንና ጨውን ከፍሎ ከገዛው በኋላ ምርምሩን ለማድረግ ይረዳው ዘንድ ወደ አሜሪካ ይዞት ሄደ።
ቤተሰቡን፣ ሚስቱን እና ሁለት ልጆቹን በማጣቱ ከደረሰበት አሳዛኝ ሁኔታ ገና ያላገገመው ወጣት ኦታ ቤንጋ እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1904 በሴንት ሉዊስ አንትሮፖሎጂካል ኤግዚቢሽን የሰው ልጅን ዝግመተ ለውጥ ታሪክ ለማሳየት በሚል በሳጠራ ውስጥ ተከልሎ ለማህበረሰቡ ክፍት ሆነ።
እ.ኤ.አ. በ1906 ከሁለት ዓመት በኋላ በኒው ዮርክ ወደሚገኘው ብሮንክስ ዙ መካነ እንስሳ አዘዋወረው። ሰዎች በተፈጥሮ ተደንቀው እንዲመለከቱት በዛፎችና በአጥሮች በተከለለ እንደ አንበሳ ግቢ በመሰለ ትናንሽ ዛፎች ባሉበት ስፍራ እንዲዘዋወርና እንዲንቀሳቀስ ተፈቀደለት።
አጭር ቁመቱና የጠቆረ መልኩ አግራሞትን ጭሮ ጎብኚዎች እሱን ለማየት እንዲጓጉና እንዲረባረቡ አደረጉት።
ይበልጥ የቱሪስትን መስህብ ይስብ ዘንድ ዝንጀሮዎች ወደሚኖሩበት የእንስሳት መካነ አራዊት ወሰዱት። በዚህ ጊዜ ነበር ኦታ ቤንጋ ሁኔታቸውን የተረዳው። ከጦጣዎች፣ ቺምፓንዚዎች እና ከጎሬላዎች ጋር “የጥንት የሰው ዘር አባት” በሚል ስያሜ ፓርኩ ለጎብኚዎች ክፍት ሆነ።
በወቅቱ የፓርኩ ዳይሬክተር የነበረው ዶ/ር ዊሊያም ሆርናዳይ በዚያ ስፍራ ይህን ልዩ ፍጡር በማግኘታቸው ምን ያህል እንደኮሩ ተናገሩ፡፡
ኦታ ቤንጋ እስከ 32 ዓመት ዕድሜው ድረስ እንደ ሰው ሳይቆጠር በፓርክ ውስጥ እየተጎበኘ አሳለፈ። የወደፊት ህልሙ ጨልሞ በሳጠራ ውስጥ ኑሮን መግፋት ተያያዘው።
ቀፎው ውስጥ እንደ እንሰሳ የመኖርን ጭንቀት መቋቋም ተሳነው። እ.ኤ.አ. መጋቢት 20 ቀን 1916 “እኔ የተከበርኩ የሰው ዘር ወንድ ነኝ ...” የሚል መልዕክትን አስፍሮ ራሱን አጠፋ። ከአንድ ጠባቂ ሽጉጥ ቀምቶ ልቡን በጥይት መቶ ራሱን ገደለ።

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
ወንዶቹ እንዲህ ነበሩ

ዑመር ሙኽታር በችሎት ፊት ቀርበው ከዳኛው ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

ዳኛው - ከጣሊያን ጋር ተዋግተሀል?
ዑመር ሙኽታር - አዎ
ዳኛው - ሰዎችስ እንዲፋለሙ አነሳስተሀል?
ዑመር ሙኽታር - አዎ
ዳኛው - በዚህ ተግባርህ የሚከተልህን ቅጣት ታውቃለህ?
ዑመር ሙኽታር - አዎ አውቃለሁ
ዳኛው - ከጣሊያን ጋር ስንት ዓመታትን ተዋግተሀል?
ዑመር ሙኽታር - ከ 20 ዓመታት በላይ
ዳኛው - ቅጣትህ ሞት መሆኑንስ ታውቃለህ?
ዑመር ሙኽታር - በሚገባ አውቃለሁ
ዳኛው - ይህ መጨረሻህ በመሆኑ አዝናለሁ
ዑመር ሙኽታር - ይህ ሕይወቴን የማጠናቀቅበት በጣም ጥሩው መንገድ በመሆኑ እደሰታለሁ
ዳኛው - ሙጃሂድ ጓደኞችህ የጂሃድ ትግላቸውን እንዲያቆሙ ደብዳቤን ጻፍና በምህረት ልልቀቅህ
ዑመር ሙኽታር - በየሰላቱ ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ እና ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ መሆናቸውን የምትመሰክረው ጣቴ ባጢልን መፃፍ ከቶ እንዴት ይቻላታል?

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
አናቶሊ አንደርቡክ
╚═══════════════╝

ኢስላምና ሙስሊሞችን በእጅጉ ይጠላ ነበርና ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ያለውን አቅም ሁሉ አሟጦ ተፋልሟል። ሙስሊሞችን ሲያይ በንዴት በግኖ ዓይኑ ይቀላል። ሙጃሂዶችን እያሳደደና ዋሻቸው ድረስ እየዘለቀ ብዙ ኳትኗል። ኃይማኖት የሌለው ከንቱና የባከነ ሰው ነበር። ሙስሊሞችን በመግደል እና በማጥፋት ይፀድቅ ይመስል አምርሮ ተዋግቷል። ያደገው ጫካ ነው። የሰብአዊ እሴቶችን ትርጉም አያውቃቸውም።
የተወለደው በአዘርባጃን ከተማ በባኮ አውራጃ ነው። ቤተሰቦቹ በማርክስ እና በሌኒን አምላክ የለሽ ሀሳቦች ያምኑ ነበር። ይህም በአስተሳሰቡ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖን በማሳደር እስልምናን እና ሙስሊሞችን እንዲጠላ አደረገው።
የሶቪዬት ህብረትን ጦር ተቀላቅሎ የጄኔራልነት ማዕረግን ተቆናጠጠ። ጊዜው የሶቪዬት ኮሚኒስት ኃይሎች የሙስሊሞችን ሀገር አፍጋኒስታንን የወረሩበት ወቅት ነበር። የጦርነት ነጋሪቱ ከተጎሰመበት ዕለት ጀምሮ ከ1979 እስከ 1989 መጨረሻ ድረስ እየተዋጋና እያዋጋ እየገደለና እያሳሰረ አስር አመታትን አሳልፏል።
ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የሆነ እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ ሙስሊሞችን በመግደል እና በማሰቃየት የበዙ ሙጃሂዶች በእጁ ሸሂድ ሆነዋል።
የሩሲያ ጦር በጥንካሬው እና በጦር መሣሪያ የበላይነትን ቢቀዳጅም ጥቂት ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ሙጃሂዶች በቀላልና ባረጁ መሣሪያዎች ፊት ለፊት መጋጠማቸው የአናቶሊን ትኩረት ሳበ።
እነዚህ ሰዎች ቁጥራቸው አናሳ፣ መሳርያቸው ያረጀ ሆኖ ሳለ ይህን ያህል ብዛት ባለውና በዘመናዊ መሳርያ የደረጀ ኃይል ፊት እንዴት ይፀናሉ?! በጥንካሬ፣ በድፍረት እና በጀግንነት እንዴት ይዋጋሉ?! በማለት ራሱን ይጠይቅ ጀመር። በቆራጥነት ለመፋለም የሚያነሳሳቸው የተደበቀ ኃይል እንዳለም በአዕምሮው አሰላሰለ። እስልምና በልብ ውስጥ ተዘርቶ በእምነት ፅናት አብቦ በስነምግባር ላይ የሚፈካ ውስጣዊ ኃይል ነው።
ታዲያ ከቀናቶች በአንደኛው የአላህ ቀን ከጠንካራው የጦርነት መስክ ውሎ በኋላ ጄኔራል አናቶሊ እየተዟዟረ የሩስያውያንን አስከሬን ተመለከተ። አካላቸው ተነፋፍቶ ሰውነታቸው አፍንጫን የሚሰነፍጥና የሚሸት ሆነው አገኛቸው። በተቃራኒው ወደ ሙስሊሞች ጀናዛ አይኑን አዞረ ሳይበላሽ እና ጥርሳቸው የተፈለቀቀ ጥጥ መስሎ ፈገግታን ከፊታቸው እየረጩ ተመለከተ።
ይህ ቅጽበት በሕይወቱ ውስጥ ትልቅ የለውጥ ጉዞን እንዲጀምር አደረገው። ያየውን ምስጢር ይመረምር ጀመር። ስለ ሃይማኖቶች ማንበብ ጀመረ። በተለይም ስለእስልምና በጥልቅ ለማወቅ ጓጓ።
ታሪኩን በአንደበቱ እንዲህ ያወጋናል:-
"ግቤ የሙስሊም ኃይሎችን ማቃጠልና ማጥፋት ነበር ... እስረኞቻቸውን ጭካኔ በተሞላበት መልኩ አሰቃያቸዋለሁ ... የቻልኩትንም እገላለሁ። ዘመናዊ መሳሪያን ታጥቀን ተዋጋናቸው። አዳዲስ መሳርያዎችን ሳይቀር ሞከርንባቸው። ከአየርም ከመሬትም አጠቃናቸው። እጅግ ይገርማሉ እውነትም ከፈጣሪ የሚታገዙ የአላህ ወታደሮች ነበሩ። ሚዳቆን እንኳ ማደን የማይችል ጠመንጃዎችን ብቻ ነበር የታጠቁት። ግና ወታደሮቼ ከፊታቸው እየሸሹ ሲፈረጥጡ በዓይኔ ተመልክቻለሁ። ለዚህ አለም ያላቸው ንቄትና ከጌታቸው ጋር የነበራቸው ጠንካራ ግንኙነት እምነቴ ላይ ጥርጣሬን ፈጠረ። ሩሲያኛ የሚናገሩ እስረኛ ሙጃሂዶችን እንዲያመጡልኝ ወታደሮቼን አዘዝኳቸው። እኔ ዘንድም አመጧቸው። በሩሲያኛ አናገርኳቸው። እነሱም እስልምናን እቀበል ዘንድ ጋበዙኝ። ስለ እስልምና ያለኝ አመለካከት ቀስ በቀስ ተለወጠ። በጥልቅ ማንበብ ጀመርኩ። ጓደኞቼ የተቃወሙኝን ውሳኔ እስክወስን ድረስ ስለ ሁሉም ሃይማኖቶች ማንበቤን ቀጠልኩ። በመጨረሻም እስልምናን በይፋ ተቀበልኩ። በሐቅ መንገድ ላይ ለመጓዝም ወሰንኩ። አመራሮቼ ውሳኔዬን እንድቀይር ለማሳመን ያደረጉትን ሙከራ ተቋቁሜ ባለቤቴና ልጆቼን አሰለምኩ። አላህ ያለፈውን ወንጀሌን ይምረኝም ዘንድ ሰዎችን ወደ አላህ መንገድ ለመጣራት ጉዞ ጀመርኩ። በህይወት እስካለሁም በአንድ መስጂድ ሙአዚን ሆኜ ለመኖር ወሰንኩ"
ለእስልምና መስህብ ራሱን በመስጠት ከግትር ተዋጊነት ወደ ሙአዚንነት መለወጡ ሂዳያ በአላህ እጅ መሆኑን እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ። አላህ ተውበቱን ይቀበለው

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
አቡ ሚህጀን አስ-ስቀፊ
╚═══════════════╝

የተዋጣላት ጀግና ተዋጊ ነው። በየጦር ሜዳው የካፊርን አንገት ቀንጥሶ ከአፈር ጋር በመቀላቀል ይታወቃል። የአላህንና የነቢዩን ጠላት በማሸበር ወደር ያልተገኘለት ጀግና ነው። ወደ ጦር ሜዳ ሲገባ ጭንቅላቱ ላይ የሚጠመጥማትን ቀይ ጥምጥም የተመለከተ ከሐዲ በፍርሐት ይርዳል።
ግና አንድ መሰረታዊ ችግር ግን ነበረበት። ሁሌም ይጠጣል። ጭንብስ ብሎ ይሰክራል። የአላህን ህግ በተደጋጋሚ እየጣሰ አስቸግሯልና በአደባባይ ብዙ ጊዜ ተገርፏል። ከዚህ ተግባሩ ባለመላቀቁ በእግረ ሙቅ ተጠፍሮ በግዞት ወደ እስር ቤት ተወርውሯል።
ዕለቱ የቃዲሲያ ዘመቻ እየተደረገ የነበረበት ወቅት ነበር። አቡ ሚህጀን የታሰረው ጦርነቱ ከሚካሄድበት ቦታ ብዙም አይርቅም። የፈረሶችን ማሽካካት የሰይፍ ግጭቶችና የተክቢራ ድምፆችን ሲሰማ መታሰሩን አምርሮ ጠላ። ከተጋጋለው ጦር ገብቶ የአላህን ጠላቶች አንገት በሠይፍ መሸልቀቅን በእጅግ ናፈቀ። ከአይኖቹ እንባን እያረገፈ ውስጡ ክፉኛ ተረበሽ። የጂሃድ ናፍቆት እንደነበልባል እያንገበገበ አላስችል ቢለው የታሰረበትን ክፍል በር ደብድቦ ለጦር መሪው ሚስት መልዕክትን ላከ። እንዲህም አላት "ካቴናዬ ተፈቶ የጦር መሳሪያና ፈረስ አዘጋጅተሽ የናፈኩትን ጂሃድ እንድካፈል አድርጊኝ። ከካፊር መሐል ገብቼ እፋለም ዘንድ እርጂኝ። በህይወት ከተረፍኩ ራሴ መጥቼ የእስር ቤቱን በር በላዬ ላይ እከረችማለሁ" አላት።
የጦር መሪው ሚስት ፈረስና ሠይፍ ሰጥታ ለቀቀችው። አቡ ሚህጀን ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ ከጦር ሜዳው መሐል ሰፈረ። ካፊሮች የበላይነትን ለመቆጣጠር ቀርበዋል። የሙስሊሙ ጦር ተዳክሟል። በዚህ ቅፅበት አቡ ሚህጀን ከመሐላቸው ተከሰተ። አንዱን በአንዱ ላይ አነባበረ። ድል ወደ ሙስሊሞች ማዘንበል ጀመረ። የካፊርን ደም የተጠማው አቡ ሚህጀን የአላህንና የሙስሊሙን ጠላቶች አረገፋቸው። ከፊቱ የቀረበ የጠላት ጦር አንገቱን ቀንጥሶ መሬት ላይ እየጣለ፣ ከፊቱ ያገኘውን የኢስላም ጠላት እየገነዳደሰ ወደመሐል ገሰገሰ።
የጦር መሪው ሰዕድ የዚህን ተዋጊ ስራ ይመለከታል!! እንዲህ በፅናት የአላህን ጠላቶች አመድ የሚያደርገው ማን ነው ሲል ጠየቀ። የሚያውቀው ሰው ጠፋ። አቡ ሚህጀን ነው እንዳልል እሱን አስሬዋለሁ አለ።
ጦርነቱ በሙስሊሞች ድል አድራጊነት መጠናቀቁን የተመለከተው አቡ ሚህጀን ተመልሶ ወደ እስር ቤቱ ገባና እነዛን በጦርነት የደከሙ እግሮቹንና እጆቹን በካቴና ጠፍሮ አሰራቸው። ሰዕድ ወደ ቤት ሲመለስ ሚስቱ ዛሬ ውጊያ እንዴት ነበር በማለት ጠየቀችው።
ሰዕድም መጀመሪያ የሽንፈት ማቅ ልንከናነብ ቀርበን ነበር። አላህ ግን ሳናስበው አንድ ልዩ የሆነ የጦር ተዋጊ ላከልንና ያ የመነመነ የድል ተስፋ ወደእኛ ተቀልብሶ ለማሸነፍ በቃን። አቡ ሚህጀንን አስሬው ባልሄድ ኖሮ ያ ጀግና ተፋላሚ እሱ ነው ብዬ እጠረጥር ነበር። የጦር ስልቱ የእሱን ይመስላል በማለት ተናገረ።
ሚስቱም በአላህ ይሁንብኝ እራሱ አቡ ሚህጀን ነው ብላ የተከሰተውን አስረዳችው። በሁኔታው በእጅጉ የተደሰተው ሰዕድ አቡ ሚህጀንን አስጠርቶ ከዛሬ ጀምሬ አልገርፍህም። አላስርህም በነፃ ለቅቄሀለው አለው።
አቡ ሚህጀንም እንግዲያውስ እኔም ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣም አልሰክርም በማለት መለሰ።

ረድየላሁ አንሁም አጅመዒን

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
ኢብኑ ባቱታ በዘመናቸው ስላስገረማቸው ጥቁር አፍሪካውያን ሙስሊሞች እንዲህ ሲሉ ያወጉናል

"በሀገራቸው የፍትሕ መጓደል አይስተዋልም። ከበደል ፍፁም የራቁ ናቸው። አገራቸው ደህንነቱ የተጠበቀ ነውና ነዋሪው በሌባም ሆነ በአስገድዶ ደፋሪ ጥቃት ይደርስብኛል ብሎ አይሰጋም።

ጁሙዐ ጁሙዐ በጊዜ ወደ መስጂድ ካላመሩ መስገጃ ቦታም አይገኝም። የዘንባባ ዛፍ ከሚመስሉ ፍሬ ከሌለው የዛፍ ቀንዘሎች የተሠሩት ምንጣፎቻቸውን ዘርግተው የተሰደረ ብሎኬት ይመስላሉ። የሚያማምሩ ነጫጭ ልብሶቻቸውን ለብሰው ከመስጂዱ ይታደማሉ።

ታላቁን ቁርአን ይሐፍዙ ዘንድ ልጆቻቸውን ይመክራሉ። በቃላቸው እስኪሸምዱትም በካቴና ተጠፍረው ይታሰራሉ።

በአንድ ኢድ ቀን ወደ ሀገሪቱ ቃዲ ዘንድ ለዚያራ አመራሁ። ልጆቹ በካቴና ታስረዋል። እጅና እግራቸው ተጠፍሯል። ለምንድነው በዒድ ቀን የታሰሩት? ብዬ ጠየቅኩት። እርሱም:- ቁርአንን በቃላቸው አልሸመደዱምና በቃላቸው እስኪሐፍዙ በዚህ መልኩ ተጠፍረው ይታሰራሉ አለኝ።

በሌላ ጊዜም ግርማ ሞገስን የተላበሰ ወጣት በተቀመጠበት ቦታ አለፍኩ። ያማረ ልብስ ለብሷል። በእግረ ሙቅ እግሮቹ ተከርችሞባቸዋል። በከባድ ሸምቀቆ ታስሯል። ምን አድርጎ ነው? ሰው ገድሎ ነውን? ስል ጠየቅኩ። ተጠያቂው ንግግሬን ተረድቶ ነበርና ፈገግ አለ "ቁርአንን በቃሉ እስኪሸመድድ ነው የታሰረው" በማለት መለሰልኝ።

═════════════════
ምንጭ:-
ابن بطوط "تحفة النظار في غرائب الأمصار وعجائب الأسفار" او كما يعرف بكتاب "رحلة ابن بطوط".
═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
ኢብራሂም አወድ ኢብራሂም አል-በድሪ
(አቡበክር አልባግዳዲ) ክፍል 1
╚═══════════════╝

እንደ አውሮፓውያን የዘመን ቀመር በ1971 ከባግዳድ በስተሰሜን አቅጣጫ በምትገኘው ሳማራ ከተማ ውስጥ ወንድ ልጅ የመወለዱ ብስራት ተሰማ። ኢብራሂም በመባልም ተሰየመ። የጎልማሳነት ጊዜውን በባግዳድ ከተማ በማሳለፉ በትግል መስክ ላይ ያገኙት ጓደኞቹ አቡበከር አልባግዳዲ በማለት ይጠሩታል።
ወደ ኢራቅ ከተማ ባግዳድ ከመዘዋወሩ በፊት የልጅነት እና የወጣትነት ጊዜውን በሰማራ ከተማ አሳልፏል። ወደ አል-ታጂ መንደር ተዛውሮ የመጀመሪያ ዲግሪውንና ማስተርሱን በእስልምና ሳይንስ ዘርፍ አግኝቷል። በዚያው ዩኒቨርሲቲ በእስልምና ሕግ የዶክትሬት ዲግሪውን ከባግዳድ ዩንቨርስቲ ይዟል። ከሳዳም ሁሴን ዩኒቨርሲቲ በቁርአን ጥናት ፒኤች ዲግሪም አለው።
በአካባቢው በሚገኝ መስጂድ ውስጥ ልጆችን ቁርአን ከማስተማር በቀር ዝምተኛ ሰው እንደነበር አብሮ አደጎቹ ይናገራሉ። ኢማም ሆኖ በሚያሰግድበት መስጂድ ውስጥ እያደረ ለአስራ አራት አመታት ኖሯል። ከእግር ኳስ ሜዳም አይጠፋም። እጅግ ጎበዝ ተጫዋች ነው። ማጠፍ ይወዳል። ያንቀረቅባል። በኳስ ይራቀቃል። ጎበዝ አጥቂም ነበር።
በአቡ ሙስዓብ አዝ-ዘርቃዊ የሚመራውን የጂሃድ እንቅስቃሴ ገና በአፍላ ዕድሜው ነበር ተቀላቀለው። በአንባር ግዛት ውስጥ በአላህ መንገድ ካገኛቸው ጓደኞቹ ጋር በመሆን ከአላህ ጠላቶች ጋር ውጊያ ማድረግ ጀመረ።
በአሜሪካ ወታደሮችም ተማርኮ በስራ በሚገኘው ቡካ እስር ቤት ውስጥ ለአራት ዓመታት ቆይቷል። አብረውት ከታሰሩ የአልቃኢዳ አባላት ጋር ተገናኝቶ የጂሃድ እንቅስቃሴውን ለማስፋት ተመለመለ። ከእስር እንደወጣም በሀገረ ኢራቅ ከአሜሪካ ወታደሮች ጋር በዘርቃዊ ትዕዛዝ ሥር ሆኖ ለዓመታት ተዋግቷል።
እ.ኤ.አ. በ2011 በፕሬዝዳንት በሽር አል አሳድ ላይ የሶሪያ አብዮት በተቀሰቀሰ ጊዜ የአል-ቃዒዳ ክንፍ በሶሪያ ይመሰረት ዘንድ አቡ ሙሐመድ አል-ጁላና መሪ ተደርጎ ወደ ሶሪያ ተላከ። የኑስራ ግንባርን መስርቶ መፋለም ጀመረ። እጅግ ጀግኖች ከቆሙበት ቦታ የማይነቃነቁ ሲል ጠላት በአንደበቱ መስክሮላቸዋል።
እንደ አውሮፓ የዘመን ቀመር ሚያዝያ 9 ቀን 2011 አቡበከር አል-ባግዳዲ የድምፅ ቅጂ ለቀቀ። በሶሪያ ውስጥ የሚገኘው ጀብሃተ ኑራ የኢራቅ ኢስላማዊ መንግሥት ንቅናቄ መሆኑን በመግለጽ ከ“ጀብሃተ ን-ኑስራ” ጋር ማዋሃዱን አስታወቀ። “የኢራቅ እና የሻም ኢስላማዊ መንግሥት” ብሎም ሰየመው።
በሶሪያ ያለው የአል-ጁላና ተጽዕኖ እየጨመረ በመምጣቱ እና የኢራቅ ኃይሎችን ለማዋሃድ የተሰጠውን ፈትዋ ባለመቀበሉ የወቅቱ የአልቃኢዳው መሪ አይማን አል-ዘዋሂሪ ወደ አል-ኑስራ ግንባር ጦር እንዲያዘምት ጥያቄ አቀረበ "ከቶ እንዴት ወንድሞቼ ላይ አፈሙዜን አዞራለሁ በየትኛውስ አቅሜ ወንድሞቼን እወጋለሁ" በማለት አይመን አልዘዋሂሪ ተቃወመ። አልባግዳዲ በሰሜናዊና በምስራቅ ሶሪያ ውስጥ እንቅስቃሴውን በማስፋፋት ራሱን ከአልቃኢዳ የጂሃድ ቡድን አገለለ። ኦሳማ ቢን ላደን በህይወት ሳለ ሻምና ኢራቅ ላይ ለሾመው ለቅርብ ወዳጁ ለአይመን አል-ዘዋሂሪ ቃልኪዳን ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀረ። ከኦሳማ ቢን ላደን ሞት በኋላ ለአይመን አል-ዘዋሂሪ ቃሉን ያልሰጠ ብቸኛም ሰው ነበር።
እንቅስቃሴውን በማስፋፋት የበዙ የሶሪያ ከተሞችን ወደራሱ ጠቀለለ። የነዳጅ ማመንጫዎችን በመቆጣጠር የበዙ ገንዘቦችን መሰብሰብ ቻለ።
አቡበከር አል-ባግዳዲ ጁሙዓ ሐምሌ 4 ቀን 2014 በሞሱል ከተማ በታላቁ መስጂድ ሚንበር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ታየ። ኢስላማዊ ኺላፋ መመስረቱንና አቡበከር አል-ባግዳዲ በሁሉም ቦታ የሙስሊሞች ኢማምና መሪ መሆኑን በይፋ አስታወቀ። ለእሱ የታማኝነት ቃላቸውን እንዲሰጡ በዓለም ዙሪያ ላሉ የጂሃድ ቡድኖች ጥሪውን አስተላለፈ። “የኢራቅና የሻም ኢስላማዊ መንግሥት” የሚለው ስም ተሰርዞ “ደውለቱል ኢስላሚያ” ተብሎ እንዲጠራ ወሰነ።
አሜሪካ ምትሀታዊና የማይታይ ስትል ትገልፀዋለች። እሱን ለመያዝ የበዙ ልፋቶችንና ጥረቶችንም አድርጋለች። በራሷና በበርካታ ሀገር ሰላዮች ታግዛ ያገኘቻቸውን መረጃዎች ተንትናና አጠናቅራ እንደ ቅዠት ታይቶ የሚጠፋባት አቡበከር አልባግዳዲ መገኘቱን ኤፍቢአይ አስታወቀ።
የአሜሪካ ባለመንታ ቀዛፊ CH47 ሄሊኮፕተሮች ኢራቅ ከሚገኘው የአየር መደብ ከምሽቱ 5:00 በፊት በረራ ጀመረዋል። በረራው አንድ ሰዓት የሚፈጅ ሆኖ በኢራቅ፣ በሶሪያ፣ በቱርክ የአየር ክልልሎች የሚያልፍ ነበር። ሄሊኮፕተሮቹ ከ80-100 የሚገመቱ የዴልታ ፎርስ አባላትና ኮማንዶዎችን አሳፍረዋል። የዴልታ ኃይል የሚባለው የአሜሪካ ጦር በ1970ዎቹ መጀመሪያ ሙስሊም ሙጃሂዶች እየበዙ መሄዳቸውን ተከትሎ እነሱን ለማጥቃት እንዲቻል የተቋቋመ በአሜሪካ የማእከላዊ እዝ ስር የተደራጀ ልዩ ኃይል ነው።
ይ - ቀ - ጥ - ላ - ል
═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
ኢብራሂም አወድ ኢብራሂም አል-በድሪ
(አቡበክር አልባግዳዲ) ክፍል 2
╚═══════════════╝

ኮማንዶዎቹ የጨለማ መዋጊያ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ሮኬቶችና ሚሳይሎች ውሾችና ሮቦቶችን ጭምር ጭነዋል። የበረራ ግዳጃቸው በሰሜን ምዕራብ ሶሪያ በምትገኘው የባሪሻ መንደር እንደሆነም አውቀውታል። የተመረጡት የዴልታ ኃይል አባላት ከሁለት ሳምንታት በፊት ጀምሮ ልዩ ወታደራዊ ልምምድ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ሄሊኮፕተሮቹ የሞት መልዕክተኛ ይመስል ወደ በሪሻ መንደር በረሩ። ጥቅምት 15 ቅዳሜ ምሽት 5:00 ሰዓት ግድም ሄሊኮፕተሮቹ ሞተራቸውን ሲያሞቁ አሜሪካ ለቱርክ ለሩሲያ ለሶሪያና ለኢራቅ በአየራችሁ ክልል ላይ እየበረርን ነውና እንድታውቁት የሚል መረጃ እያስተላለፈች ነበር። ሄሊኮፕተሮቹ የጦር መሳሪያ ጭነው ዝቅ ብለው በሚበሩበት ወቅት ያለእነዚህ ሀገሮች ፍቃድ ማለፍ አስቸጋሪ ነበር። ትራምፕም እነዚህን ሀገሮች እግዜር ይስጣቸው ሲሉ አመስግነዋቸዋል።
በሪሻ በሰሜን ምዕራብ የምትገኝ ትንሽ መንደር ናት። በአይኤስ ይዞታ ስር ቆይታ በኋላ የበሽር መንግስት ተቃዋሚ በሆነውና በአሜሪካ በሚደገፈው የሶሪያ ዲሞክራቲክ ጥምር ኃይሎች ይዞታ ስር ወድቃለች። ኩርዶችም በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ። ወታደሮቹ በሪሻ መንደር ደርሱ። በምዕራብ በኩል የሚገነጠለው አቧራማ መንገድ 5 ኪ.ሜ ፈንጠር ብሎ ከተሰራው ግንብ ቤት ያደርሳል። በጥብቅ ግንብ ቤት የተስራው ሰፊው ቤት በረጅም አጥር ተከቧል። ከቤቱ ጋር ተያይዞ የመሬት ውስጥ ዋሻ ተቆፍሯል። ከግንቡ ወጥቶ ወደ ዋሻው በመተላለፍ ከአየር እና ከሌላ ጥቃት ለመመከት እንዲቻል ታስቦ የተሰራ ነው። የባሪሻ መንደር ሰዎች ጭልል ባለ በረሃ ለፀሀይ የማይስብ አይነት ሆኖ በተሰራው ግንብ ቤት ውስጥ ማን እንደሚኖር አያውቁም።
የባሪሻ ምሽት ጨለማውን አንግሶ ፀጥ ባለበት ሰዓት ስምንቱ ሄሊኮፕተሮች አየሩን እየሰነጠቁ ወደዚያች መንደር እየገሰገሱ ነበር። የአሜሪካ ርዕሰ ብሄር መቀመጫ በሆነው የኋይት ሃውስ ቤተመንግሥት አነስተኛ ክፍል ውስጥ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከምክትላቸው፣ ከመከላከያ ሚንስትራቸውና ከጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጋር ተቀምጠው የሄሊኮፕተሮቹን በረራ ይከታተላሉ። በረቀቀ ቴክኖሎጂ ምስልና ድምጽ በሚያሰራጨው መሳሪያ ዘመቻውን ፊልም እንደማየት አይነት በትኩረት እየተከታተሉ ነበር። ዕለቱ ለነርሱ የቁርጥ ቀን ስለሆነ አይናቸውን ሳይነቅሉ የሚሆነውን ሁሉ ይከታተላሉ። ሄሊኮፕተሮቹ በተዋጊ ጀቶችና በጦር መርከቦች ሽፋን ተሰጥቷቸዋል።
ወደ ግቢው ደርሰው አዘቅዝቀው መውረድ ሲጀምሩ ግቢውን ከሚጠብቁ ታጣቂዎች ጥይት ተቀበላቸው። አሜሪካኖቹ የፈሪ ዱላ አፀፋዊ ምላሽ ሰጡ። በሄሊኮፕተሮቹ ላይ የተጫኑት ሮኬቶች ሲተኮሱ ግቢው በፍንዳታ ተሞላ። በዋናው መዝጊያ በር በኩል ልዩ ጥበቃና የፈንጂ አጥር ሊኖር ይችላል ብለው ስለገመቱ በኋላ በኩል አጥሩን ደረመሱና ወደ ውስጥ ዘለቁ። ልዩ ኮማንዶዎቹ ለዚህ ግዳጅ ያሰለጠኗቸውን ውሾች ይዘው አቡበከር አልባግዳዲ አለ ብለው በጠረጠሩት ክፍል ለመድረስ ተጣደፉ። ግቢውን የሚጠብቁት አጃቢዎችም በአልሞ ተኳሾች ተገለው ከጌታቸው ጋር ተገናኙ። በተኩሱ መካከል አቡበከር አልባግዳዲ ፈንጂ የተጠመደበትን ሰደርያውን ለብሶ በዋሻው ስር ጉዞ ጀመረ። ወታደሮቹ ወደ ዋሻው የዘለቀውን ሰው ከአነፍናፊ ውሾቻቸው ጋርና ፓውዛ በተገጠመላቸው አልሞ ተኳሾች ጋር ተከትለውት ገቡ። ከዋሻው ውስጥ መሬት የሚንጥ ድምጽ ያለው ፈንጂ ዋሻውን የላይኛውን ወደታችኛው እስኪገለባበጥ ድረስ አደበላለቀው። አቡበከር አልባግዳዲ ራሱ ላይ ባጠመደው ፈንጂ ራሱን ገደለ። በተኩሱ ልውውጥ እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልተነገረ ተዋጊዎች ሞተዋል። አራት ሴቶችም ተገድለዋል። ኮማንዶዎቹ አካባቢውን ሲመረምሩ ለ2:00 ሰዓት ያህል ቆይተው ወደነበሩበት ለመመለስ ተዘጋጁ። ሲመለሱ ያን ቤትና አጥር ምን ላይ ነበር ተብሎ ደብዛው እስኪጠፋ ድረስ በሚሳኤል አወደሙት። አንዳችም ምልክት ሳይቀር የተደለደለ መሬት አደረጉት። ይህን ማድረጋችን ተከታዮቹ እንደ እምነት ቦታ አድርገው እንዳይዙት ነው በማለት ጀነራል ኬንዝ ተናግረዋል። አንድ አነፍናፊ ውሻ ጉዳት በማስተናገዱም ፕረዝዳንት ትራምፕ የቆሰለውን ውሻ በትዊተር ገጻቸው ፎቶግራፉን ለጥፈው ጀግና ሲሉ አወደሱት።
ለዘጠኝ አመታት ሲፈለግ የነበረው በተለይም ባለፉት ስድስት አመታት ከአፍሪካ እስከ አውሮፓ የሚኖሩትን ህዝቦች በእስልምና ሸሪዓ አስተዳድራለሁ በሚል መርሁ የሚታወቀው፣ የሶርያና የኢራቅ ግዛቶች ሉአላዊ የአገር ኸሊፋ ነኝ በማለት ያወጀው አቡበከር አልባግዳዲ በዚህ አይነት መልኩ ህይወቱ መደምደሙን በርካቶች ዘግበውታል።
የአይኤስ አዲሱ መሪ ኢብራሂም አልሐሺም እንደሚሰኝ እና ሁሉም ሙስሊሞች ታማኝነታቸውን እንዲያረጋግጡለት ቃል አቀባዩ ተናግረዋል። ስለ ሐሺም ማንነትና ስላለፈው ተግባሩ ግን ዝርዝር መግለጫን አልሰጡም።
አላህ መልካም ስራውን ይቀበለው ያለፈ ወንጀሉንም ይማረው
ተ - ፈ - ፀ - መ

═════════════════
ይህ የዩቱዩብ ፔጄ ነው ሰብስክራይብ አድርገው የጀግኖችን ታሪክ ይከታተሉ
👇👇
https://youtube.com/channel/UCPgxFIQ_qZ2XHM1di_y_xoA

ይህ ደግሞ የቴሌግራም አካውንቴ ነው
👇👇👇
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
═════════════════
ለሌሎችም ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን እናስፋ
╔═══════════════╗
Like Comment Share
ኢኽላስ - ታማኝነት - ትጋት - ስኬት
╚═══════════════╝
╔═══════════════╗
ማጄላንና ታላቁ ሙጃሂድ ላቡ ላቡ
╚═══════════════╝

ልጅ ሳለን ስለማጄላን ጥሩ ጥሩው ተነግሮናል። በየትምህርት ቤታችን አስተማሪዎቻችን ስለእርሱ መልካም መልካሙን አውግተውናል። ዓለምን የዞረ የጂኦግራፊ ሊቅ ተብሎ የሚወሳው ማጄላን ማን ነው? እውነተኛ ታሪኩን ላውጋችሁ።
ሙስሊሞች የፊሊፒንን ደሴቶች ማሃራጅ ብለው ይጠሯቸዋል። ከቻይና እና ከሱማትራ በመጡ ነጋዴዎችና ዳዒዎች እስልምና በአካባቢው ተስፋፍቷል። ለ“ማኒላ” ድንበር ነዋሪዎች በሙስሊም ነጋዴዎች አማካኝነት የኢስላም ጥሪ ደርሷቸዋል። የእስልምና ብርሃን ከ7000 በላይ ነዋሪዎች ዘንድም ፈንጥቋል። ይህ የእግር እሳት የሆነበት ማጄላን ሙስሊሞች እንዳይስፋፉ እስልምናን ማምከን ይቻለው ዘንድ ከፖርቹጋል ተነስቶ ምስራቅ አፍሪካን እስከ ህንድ አዳርሶ ሙስሊሞችን በገፍ ብትሩ ቀጥቷል።
ሙስሊሞችን በእጅጉ ይጠላል። በ1502 ለሐጅ ጉዞ 700 ሙስሊሞችን ጭኖ የሚጓዝ መርከብን አገተ። መንገደኞቹ ወዴት እንደሚሄዱም ጠየቀ። የአላህን ቤት ለመጎብኘት ወደ መካ እየተጓዙ መሆኑ ሲነገረው ለግብረ አበር ወታደሮቹ ትዕዛዝን አስተላለፈ። ንብረታቸውን ከተዘረፉ በኋላ በመርከቡ ላይ ሰብስበው ከነህይወታቸው አቃጠሏቸው። በዘመታቸው የመስቀል ጦርነቶች ከ300 በላይ መስጂዶችን አፍርሷል።
ሙስሊሞችን ማርኮ አፍንጫቸውንና ጆሮዎቻቸውን ቆራርጧል። ጥርሶቻቸውን እየሰበረ በድዳቸው አስቀርቷቸዋል። እጅና እግራቸው ተጠፍሮ በክፍል ውስጥ ታጭቀው ከነህይወታቸው በእሳት ነደዋል።
ማጄላን የምድር አሳሽ አለምን የዞረ ጆግራፊስት መሆኑን አስተምረውናል። ግና ለሙስሊሞች የነበረውን ጥላቻ ያደረሰባቸውን ግፍና መከራ አልነገሩንም።
እ.ኤ.አ. በ1521 በ“ፈርዲናንድ ማጂላን” የሚመራው የስፔን ጦር ፊሊፒን ደረሰ። የጎረቤት ደሴቶች በስፔን አክሊል ሥር እንዲተዳደሩና ክርስትናን የበላይ ለማድረግ በሚል ስምምነት ላይ ተደረሰ። አመጣጡም የእስልምናን መስፋፋት ለመግታትና ሙስሊሞችን አይቅጡ ቅጣት ለመቅጣት የታሰበበት ነበር።
በመስቀል ዘመቻው “ማክታን” የተሰኘች አንዲት ትንሽዬ ደሴትን ለመቆጣጠር ጉዞ ጀመረ። በወቅቱ ደሴቷ “ላቡ ላቡ” በሚባል ሙስሊም ሡልጣን ትተዳደር ነበር። በማጄላን የሚመሩት የስፔን ወታደሮች ከደሴቷ ጠረፍ መሽገው ከነዋሪዎቿ ምግብ እየነጠቁና ሐብት ንብረታቸውን እየዘረፉ ሲያስቸግሩ ሕዝቡ ተቃውሞውን አሰማ። ላቡ ላቡ እጅግ ጠንካራ ሙጃሂድ ነበርና ለማጄላን ወረራ እጅ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማጄላን የአጎራባች ደሴት ነዋሪዎችን አነሳሳበት። ጥንካሬውን እና ዘመናዊ መሣሪያዎቹን ለማሳየት እድሉን ስላገኘ ደብዳቤ አስይዞ ወደ ላቡ ላቡ መልዕክተኛን ላከ።
"ከማጄላን ለማክታን ደሴት ገዢ ላቡ ላቡ በእየሱስ ስም እጀምራለሁ እኛ የነጭ ዘሮች የስልጣኔ ቀዳሚዎች ይህንን ሀገር የመግዛት ስልጣን ከእናንተ የበለጠ ይገባናልና ስልጣንህን አስረክብ"
ላቡ ላቡ ደብዳቤውን አንብቦ እንዳበቃ በግልባጩ አጭር ምላሽን ፅፎ ሰደደ "ኃይማኖት የአላህ ነው። የምናመልከው አምላክ ቀለማቸው ምንም ይሁን ምን የሰው ልጆች ሁሉ አምላክ ነው" ሲል መለሰ።
በዕለቱ ፀሐይ በሰማይ መሃል አናት ላይ ነበረች። የማጄላን መርከቦች በፊሊፒን ከሚገኙት የሙስሊም ደሴቶች በአንዱ ላቡ ላቡ በሚያስተዳድረው የማክታን ደሴት ዳርቻ እየተቃረቡ ነው። ዓመቱ 1521 ነው። ፊሊፒናዊያን በወጣት መሪያቸው “ላቡ ላቡ” መሪነት ተሰብስበው ለጂሃድ ተዘጋጅተዋል። ትናንሽ ጀልባዎች ላይ አድፍጠው የወቅቱን ዘመናዊ መሳርያ ታጥቀዋል። የራስ ቁር በአናታቸው አጥልቀው ሰይፍና ጋሻን ይዘዋል። በተንጣለለው ደሴት ላይ ከቀርከሃ በተሠሩ ቀስቶችንና አጫጭር ሰይፎችን ሸክፈዋል። የማጄላን ወታደሮች ወደ ባሕሩ ዳርቻ ሲጠጉ ካደፈጡት ሙጃሂዶች ጥቃት ተሰነዘረባቸው። ሁለቱ ጭፍሮች ተገናኙ። የማጄላን ወታደሮች እንደለመዱት የሙስሊሞች አንገት ከራሳቸው ሊያበሩ ተዘጋጁ። በሹል ሰይፎቻቸው ሰውነቶችን ሊቀዳድዱ ቋመጡ። ግና ስላደፈጡት ሙጃሂዶችና ስለቀርከሃ ቀስቶች መረጃው አልነበራቸውም። የራስ ቁር እና ጋሻ ይዘው ያፌዙባቸው ጀመር። ጎራዴ ከጎራዴ ጋር ተፋጨ። ​ በ“ላቡ ላቡ” እና “ማጄላን” መካከል እጅግ ጠንካራ ፍልሚያ ተደረገ።
የብረት ጡሩር ደረቱ ላይ ያጠለቀው ማጄላን በባዶ ራቁቱ በሚዋጋው ሙጃሂድ በላቡ ላቡ ሠይፍ ተመቶ ወደቀ። ጉዳቱ ለሞት የሚዳርግ አልነበረም። ወጣት መሪ ላቡ ላቡ ለሁለተኛ ጊዜ የማጄላን አንገት ላይ ሰነዘረ። የማጄላን ጭንቅላት በደም ተጨማለቀ። የመሪያቸውን መገደል ያዩት ወታደሮች ከመሸሽ በቀር ሌላ አማራጭ አልነበራቸውምና አስክሬኑን ጥለው ወደ መርከባቸው መፈርጠጥ ጀመሩ።
ፊሊፒናዉ ሙስሊም ጀግና የተዋጣለት ተዋጊ ሙጃሂድ ‹ላቡ ላቡ› ማጄላን በሙስሊሞች ላይ የሰራውን ግፍና እየፈፀመ የነበረውን ኢ ሰብዓዊ ድርጊት ሰምቶ በእጅጉ ተቆጥቶ ነበርና እነሆ ዛሬ እስከወዲያኛውም ወደ ቀብር ሸኘው።
ፊሊፒናውያን አሁንም ላቡ-ላቡን ብሔራዊ ጀግናቸው አድርገው ይመለከቱታል።
እንደ አለመታደል ሆኖ የእስልምና ጠላቶች የማጄላንን የሐሰት ታሪክ አስውበው ፃፉልን። እኛም በምዕራባውያን መስቀለኞች ዓይን እንድናነበው ተደረግን። በልባችን ውስጥ እንደጀግናና ተአምረኛም ይዘከር ይዟል።

ማስታወሻ:- ምስሉ ማጄላንን የገደለው ሙጃሂድ የጀግናው “ላቡ ላቡ” ነው።

═════════════════
ምንጭ:-
كتاب قبسات من نور
╔═══════════════╗
http://www.tg-me.com/sehkaliderashid
╚═══════════════╝
2024/05/18 23:30:56
Back to Top
HTML Embed Code: