"አሁን መልሶ ግንባታ እንጀምራለን"- ዶናልድ ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስራኤል ምክር ቤት ንግግር ካደረጉ በኋላ ወደ ግብፅ አቅንተዋል።
በግብፅ፣ ሻርም ኤል-ሻይክ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአገራት መሪዎች ተሰባስበው በቀጣዩ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ላይ ተወያይተዋል።
ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጠባቂዎች ሆነው ፊርማቸውን አኑረዋል።
"አዲስ ውብ ቀን መጥቶልናል። አሁን ጊዜው መልሶ የመገንባት ነው" ብለዋል ትራምፕ።"ለመካከለኛው ምሥራቅ ታሪካዊ ቀን ነው" ሲሉም አክለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስራኤል ምክር ቤት ንግግር ካደረጉ በኋላ ወደ ግብፅ አቅንተዋል።
በግብፅ፣ ሻርም ኤል-ሻይክ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአገራት መሪዎች ተሰባስበው በቀጣዩ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ላይ ተወያይተዋል።
ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጠባቂዎች ሆነው ፊርማቸውን አኑረዋል።
"አዲስ ውብ ቀን መጥቶልናል። አሁን ጊዜው መልሶ የመገንባት ነው" ብለዋል ትራምፕ።
"ለመካከለኛው ምሥራቅ ታሪካዊ ቀን ነው" ሲሉም አክለዋል።
ትራምፕ የሰላም ዕቅዱ ሁለተኛ ክፍል ተጀምሯል ብለዋል።
ትራምፕ በግብፁ ውይይት ላይ "ሁሉም ሰው ደስተኛ ነው። እዚህ ለመድረስ 3,000 ዓመታት መውሰዱን ታምናላችሁ? ብለዋል።
የግብፅ ፕሬዝዳንት አብደልፋታሕ አል-ሲሲ በአገራቸው ትልቁ የሆነውን 'ኦርደር ኦፍ ዘ ናይል' ሽልማት ለትራምፕ ሰጥተዋል።
አል-ሲሲ "አስከፊው ጊዜ ያከተመበት ታሪካዊ እርምጃ ነው" ሲሉ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ገልጸዋል።
@sheger_press
@sheger_press
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስራኤል ምክር ቤት ንግግር ካደረጉ በኋላ ወደ ግብፅ አቅንተዋል።
በግብፅ፣ ሻርም ኤል-ሻይክ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአገራት መሪዎች ተሰባስበው በቀጣዩ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ላይ ተወያይተዋል።
ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጠባቂዎች ሆነው ፊርማቸውን አኑረዋል።
"አዲስ ውብ ቀን መጥቶልናል። አሁን ጊዜው መልሶ የመገንባት ነው" ብለዋል ትራምፕ።"ለመካከለኛው ምሥራቅ ታሪካዊ ቀን ነው" ሲሉም አክለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በእስራኤል ምክር ቤት ንግግር ካደረጉ በኋላ ወደ ግብፅ አቅንተዋል።
በግብፅ፣ ሻርም ኤል-ሻይክ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአገራት መሪዎች ተሰባስበው በቀጣዩ የጋዛ የሰላም ዕቅድ ላይ ተወያይተዋል።
ግብፅ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና አሜሪካ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጠባቂዎች ሆነው ፊርማቸውን አኑረዋል።
"አዲስ ውብ ቀን መጥቶልናል። አሁን ጊዜው መልሶ የመገንባት ነው" ብለዋል ትራምፕ።
"ለመካከለኛው ምሥራቅ ታሪካዊ ቀን ነው" ሲሉም አክለዋል።
ትራምፕ የሰላም ዕቅዱ ሁለተኛ ክፍል ተጀምሯል ብለዋል።
ትራምፕ በግብፁ ውይይት ላይ "ሁሉም ሰው ደስተኛ ነው። እዚህ ለመድረስ 3,000 ዓመታት መውሰዱን ታምናላችሁ? ብለዋል።
የግብፅ ፕሬዝዳንት አብደልፋታሕ አል-ሲሲ በአገራቸው ትልቁ የሆነውን 'ኦርደር ኦፍ ዘ ናይል' ሽልማት ለትራምፕ ሰጥተዋል።
አል-ሲሲ "አስከፊው ጊዜ ያከተመበት ታሪካዊ እርምጃ ነው" ሲሉ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ገልጸዋል።
@sheger_press
@sheger_press
❤15👍4
Sheger Press️️
Photo
ተወልዶ ባደገባት ሃገር ይህ ቀረው የማይባል ኃጢአተኛ ሰው ቢሆንም እመቤታችን ቅድሰት ድንግል ማርያምን በፍፁም ልቡ ይወዳት ነበርና በመዳን ቀን ጥሪ ለንስሐ አበቃችው፡፡
የትውልድ ሃገሩ ሶርያ ውስጥ ሮሃ አካባቢ ነው፡፡ ከዚያች ዕለት ጀምሮም ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው፣ ንጹሕ የቤተ ክርስቲያን መስዋዕት፣ ጽኑዕ የበርሃ ምሰሶ ሆነ፡፡ ድንግል እመቤታችንም ከነሥጋው ወደ ሰማያት ወስዳ ገነትና ሲዖልን አሳይታ፣ ከአዳም እስከ ኖኅ፣ ከአብርሃም እስከ ሙሴና ዳዊትን ከመሰሉ ቅዱሳን ጋር አገናኘችው፡፡ ከዚህም በላይ የሆነና በሰብአዊ አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢር አሳይታ ወደ ምድር መልሳዋለች፡፡ ይህም በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ጎርጎርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት ምሥጢራትን የተመለከተ እየተባለ እንዲጠራ አድርጎታል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ በሰማይ በነበረው ቆይታ ክብረ ቅዱሳንን ተመልክቶ አድንቋል፡፡
በተለይ በፍጹምነት ድንግልናቸውን የጠበቁ ቅዱሳንና ቅዱሳት ደናግል አኗኗራቸው ከአምላክ እናት፣ ከሰማይ ንግሥት፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር መሆኑን አይቷል፡፡ "የለበሱት ልብስም በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የሚቻል አይደለም" ይላል፡፡ የደናግል ፊታቸው ከፀሐይ 7 እጅ ያበራልና ግርማቸው ያስፈራል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ በዚያው በሰማይ ሳለ ደግሞ ይህንን ተመለከተ፡፡ አንድ አረጋዊ፣ ጽሕሙ ተንዠርግጐ፣ የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሶ ይመጣል፡፡ ቅዱሳን መላእክት በፊት በኋላ፣ በቀኝ በግራ ከበውት ሳለ እግዚአብሔርን በበገናው ሊያመሰግን ጀመረ፡፡ "አቤቱ ጌታችን በምድር ሁሉ ስምህ የተመሰገነ ሆነ" ሲል መላእክቱ በዝማሬ አጀቡት፡፡ በዚህ ጊዜም ታላቅ መናወጥ ሆነ፡፡
ደናግሉም የቅዱሱን ሽማግሌ በረከቱን ተሳተፉ፡፡ ይህ አመስጋኝ ሽማግሌ አምላካችን እግዚአብሔር እንደልቤ ያለው በርካታ ሀብትም የሰጠው ልበ-አምላክ፣ ጻድቅ፣ የዋህና የእሥራኤል ንጉሥ ዳዊት ነበር፡፡ አንድም እመቤታችን "አባቴ ዳዊት!" ብላ ስትጠራው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሰምቷልና፡፡ በመጨረሻም እመቤታችንን በፍጹም ክብርና ግርማ ተመልክቷት ሐሴትን አድርጓል፡፡ እመ-ብርሃንም "ተወዳጅና ንጹሕ ሰው ነህ" ስትል ቅዱስ ጎርጎርዮስን አመስግናዋለች፡፡ ስለዚህ ዓለምም እንዲህ የሚል መልእክትን ልካለች:: "ልጆቼ ሆይ! ከብርሃን ጨለማን፣ ከደግነት ክፋትን፣ ከጽድቅ ይልቅ ኃጢአትን ምነው መምረጣችሁ? እኔ ስለ እናንተ በየቀኑ እየለመንሁ እነሆ አለሁ:: ወደ ጨለማ ገሃነም እንዳትወርዱ እባካችሁ ንስሐ ግቡ!" ስትል መልዕክቷን አስተላለፈች፡፡
ድንግል በክልኤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ለቅዱሱ ሰው ነግራው፣ ቅዱስ ዳዊትን አስከትላ በግሩማን መላእክት ታጅባ የእሳት መጋረጃዎች ወደ ተተከሉበት ድንኳን ገባች፡፡ በዚያም ተመሰገነች፡፡ ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫም "ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት፣ ወይብልዋ፣ በሐኪ ማርያም ሐዳሲሁ ጣዕዋ"፤ “መላእክት ማርያምን በመጋረጃዎች ውስጥ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል እያሉ አመሰገኗት” የሚለውም ለዚህ ነው፡፡ ቅዱስ ጐርጐርዮስም ከሰማይ ቆይታው መልስ ያየውን ሁሉ ጽፎ ለአበው ሰጥቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አባቶቻችን ረዓዬ ኅቡዓት “ምሥጢራትን ያየ” አባት ይሉታል፡፡ ቅዱሱ ተረፈ ዘመኑን በተጋድሎ ፈጽሞ መጋቢት ሁለት ቀን አርፏል፡፡
የቅዱሳን እናታቸው ድንግል እመ ብርሃን መዓዛ ፍቅሯን ታብዛልን፡፡ በቅድስና ሕይወት፣ በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን ቅዱሳንና ገዳማውያን እደግፍ በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
የትውልድ ሃገሩ ሶርያ ውስጥ ሮሃ አካባቢ ነው፡፡ ከዚያች ዕለት ጀምሮም ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው፣ ንጹሕ የቤተ ክርስቲያን መስዋዕት፣ ጽኑዕ የበርሃ ምሰሶ ሆነ፡፡ ድንግል እመቤታችንም ከነሥጋው ወደ ሰማያት ወስዳ ገነትና ሲዖልን አሳይታ፣ ከአዳም እስከ ኖኅ፣ ከአብርሃም እስከ ሙሴና ዳዊትን ከመሰሉ ቅዱሳን ጋር አገናኘችው፡፡ ከዚህም በላይ የሆነና በሰብአዊ አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢር አሳይታ ወደ ምድር መልሳዋለች፡፡ ይህም በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ጎርጎርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት ምሥጢራትን የተመለከተ እየተባለ እንዲጠራ አድርጎታል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ በሰማይ በነበረው ቆይታ ክብረ ቅዱሳንን ተመልክቶ አድንቋል፡፡
በተለይ በፍጹምነት ድንግልናቸውን የጠበቁ ቅዱሳንና ቅዱሳት ደናግል አኗኗራቸው ከአምላክ እናት፣ ከሰማይ ንግሥት፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር መሆኑን አይቷል፡፡ "የለበሱት ልብስም በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የሚቻል አይደለም" ይላል፡፡ የደናግል ፊታቸው ከፀሐይ 7 እጅ ያበራልና ግርማቸው ያስፈራል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ በዚያው በሰማይ ሳለ ደግሞ ይህንን ተመለከተ፡፡ አንድ አረጋዊ፣ ጽሕሙ ተንዠርግጐ፣ የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሶ ይመጣል፡፡ ቅዱሳን መላእክት በፊት በኋላ፣ በቀኝ በግራ ከበውት ሳለ እግዚአብሔርን በበገናው ሊያመሰግን ጀመረ፡፡ "አቤቱ ጌታችን በምድር ሁሉ ስምህ የተመሰገነ ሆነ" ሲል መላእክቱ በዝማሬ አጀቡት፡፡ በዚህ ጊዜም ታላቅ መናወጥ ሆነ፡፡
ደናግሉም የቅዱሱን ሽማግሌ በረከቱን ተሳተፉ፡፡ ይህ አመስጋኝ ሽማግሌ አምላካችን እግዚአብሔር እንደልቤ ያለው በርካታ ሀብትም የሰጠው ልበ-አምላክ፣ ጻድቅ፣ የዋህና የእሥራኤል ንጉሥ ዳዊት ነበር፡፡ አንድም እመቤታችን "አባቴ ዳዊት!" ብላ ስትጠራው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሰምቷልና፡፡ በመጨረሻም እመቤታችንን በፍጹም ክብርና ግርማ ተመልክቷት ሐሴትን አድርጓል፡፡ እመ-ብርሃንም "ተወዳጅና ንጹሕ ሰው ነህ" ስትል ቅዱስ ጎርጎርዮስን አመስግናዋለች፡፡ ስለዚህ ዓለምም እንዲህ የሚል መልእክትን ልካለች:: "ልጆቼ ሆይ! ከብርሃን ጨለማን፣ ከደግነት ክፋትን፣ ከጽድቅ ይልቅ ኃጢአትን ምነው መምረጣችሁ? እኔ ስለ እናንተ በየቀኑ እየለመንሁ እነሆ አለሁ:: ወደ ጨለማ ገሃነም እንዳትወርዱ እባካችሁ ንስሐ ግቡ!" ስትል መልዕክቷን አስተላለፈች፡፡
ድንግል በክልኤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ለቅዱሱ ሰው ነግራው፣ ቅዱስ ዳዊትን አስከትላ በግሩማን መላእክት ታጅባ የእሳት መጋረጃዎች ወደ ተተከሉበት ድንኳን ገባች፡፡ በዚያም ተመሰገነች፡፡ ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫም "ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት፣ ወይብልዋ፣ በሐኪ ማርያም ሐዳሲሁ ጣዕዋ"፤ “መላእክት ማርያምን በመጋረጃዎች ውስጥ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል እያሉ አመሰገኗት” የሚለውም ለዚህ ነው፡፡ ቅዱስ ጐርጐርዮስም ከሰማይ ቆይታው መልስ ያየውን ሁሉ ጽፎ ለአበው ሰጥቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አባቶቻችን ረዓዬ ኅቡዓት “ምሥጢራትን ያየ” አባት ይሉታል፡፡ ቅዱሱ ተረፈ ዘመኑን በተጋድሎ ፈጽሞ መጋቢት ሁለት ቀን አርፏል፡፡
የቅዱሳን እናታቸው ድንግል እመ ብርሃን መዓዛ ፍቅሯን ታብዛልን፡፡ በቅድስና ሕይወት፣ በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን ቅዱሳንና ገዳማውያን እደግፍ በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
❤40🤬2👍1
አንድ ዶላር 148 ብር ተሸጠ‼️
አንድ የአሜሪካ ዶላር በ148 ብር ጨረታ ተሸጠ‼️
ብሔራዊ ባንክ የ150 ሚሊዮን ዶላር ውጭ ምንዛሪ ጨረታ አካሂዷል።
ባንኩ መሰል ጨረታ ሲያወጣ ለ10ኛው ዙር ሲሆን በዚህ ዙር 150 ሚሊዮን ዶላር በጨረታ ለመሸጥ አቅርቧል።
በጨረታው የአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን 148.1007 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። / 1 ዶላር በ148.1007 ተሽጧል /
ይህ አዲስ አማካኝ ዋጋ ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ ከተመዘገበው 138.2 ብር አማካይ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር፣ የ9 ብር ከ90 ሳንቲም ወይም የ 7.16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ዛሬ በተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ድልድል 31 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ጨረታው ላይ ተሳትፈው በሽያጩ ተሳትፈዋል ተብሏል።
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በሚፈቅደው ጊዜ ተመሳሳይ ጨረታዎችን እቀጥላለሁ ብሏል።
አንድ የአሜሪካ ዶላር በ148 ብር ጨረታ ተሸጠ‼️
ብሔራዊ ባንክ የ150 ሚሊዮን ዶላር ውጭ ምንዛሪ ጨረታ አካሂዷል።
ባንኩ መሰል ጨረታ ሲያወጣ ለ10ኛው ዙር ሲሆን በዚህ ዙር 150 ሚሊዮን ዶላር በጨረታ ለመሸጥ አቅርቧል።
በጨረታው የአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን 148.1007 ብር ሆኖ ተመዝግቧል። / 1 ዶላር በ148.1007 ተሽጧል /
ይህ አዲስ አማካኝ ዋጋ ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ ከተመዘገበው 138.2 ብር አማካይ ዋጋ ጋር ሲነጻጸር፣ የ9 ብር ከ90 ሳንቲም ወይም የ 7.16 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ዛሬ በተካሄደው የውጭ ምንዛሪ ድልድል 31 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ጨረታው ላይ ተሳትፈው በሽያጩ ተሳትፈዋል ተብሏል።
ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያው በሚፈቅደው ጊዜ ተመሳሳይ ጨረታዎችን እቀጥላለሁ ብሏል።
❤13😱8👌4
በዕለተ አርብ በቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ ምንም እንኳን ጌታችን የእሾህ አክሊል ደፍቶ እርቃኑን ተሰቅሎ ደሙ እየፈሰሰ ቢያየውም ንጹህ መሆኑን በመረዳት ጌታው መሆኑን ከማወቅ አላገዳውምና “አቤቱ፥ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ ዐስበኝ” አለው።
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፥ “እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ።” ሉቃስ 23÷39-43
ከአዳም ቀድሞ ገነት የመግባትን እድል ያገኘው ራሱን አሳልፎ የሰጠውን ጌታውን በመከራው ሰዓት አይቶት ጌትነቱን በመረዳቱ ነው፡፡
ገዳማውያን ራሳቸውን ለክርስቶስ ፍቅር አሳልፈው ሰጥተው ስናያቸው መንፈሳዊ ክብራቸው ይታየናል? መራብ መጠማታቸው ለነፍሳቸው በማደራቸው መሆኑን እንረዳለን? በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያሉ ከአንድ መቶ በላይ ገዳማውያንም በበረሃው ግለት ውስጥ ዓለምን ንቀው በረሃብና በውሃ ጥም ከትመዋል፡፡
ፊያታዊ ዘየማን ጌታው በመከራ መስቀል ላይ ቢሆንም ክብሩን እንዳየ፣ ገዳማውያኑ በስጋዊ ችግር ውስጥ ቢሆኑም መንፈሳዊ ክብራቸውን በመመልከት ችግራቸውን ለመቅረፍ እንረባረብ፤ ከጸሎታቸው ረድኤት እናትርፍ፡፡
ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም ከ 5፡00 ጀምሮ በሚሌኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ በመሳተፍ፣ በአንድ መቶ ብር ብቻ በገዛነው ትኬት ከጎናቸው እንቁም፡፡ የእደ ጥበብ ምርቶቻቸውንም በመግዛት ከሊቀ መልአኩ በረከት እንካፈል፡፡
አዘጋጅ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፥ “እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ።” ሉቃስ 23÷39-43
ከአዳም ቀድሞ ገነት የመግባትን እድል ያገኘው ራሱን አሳልፎ የሰጠውን ጌታውን በመከራው ሰዓት አይቶት ጌትነቱን በመረዳቱ ነው፡፡
ገዳማውያን ራሳቸውን ለክርስቶስ ፍቅር አሳልፈው ሰጥተው ስናያቸው መንፈሳዊ ክብራቸው ይታየናል? መራብ መጠማታቸው ለነፍሳቸው በማደራቸው መሆኑን እንረዳለን? በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያሉ ከአንድ መቶ በላይ ገዳማውያንም በበረሃው ግለት ውስጥ ዓለምን ንቀው በረሃብና በውሃ ጥም ከትመዋል፡፡
ፊያታዊ ዘየማን ጌታው በመከራ መስቀል ላይ ቢሆንም ክብሩን እንዳየ፣ ገዳማውያኑ በስጋዊ ችግር ውስጥ ቢሆኑም መንፈሳዊ ክብራቸውን በመመልከት ችግራቸውን ለመቅረፍ እንረባረብ፤ ከጸሎታቸው ረድኤት እናትርፍ፡፡
ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም ከ 5፡00 ጀምሮ በሚሌኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ በመሳተፍ፣ በአንድ መቶ ብር ብቻ በገዛነው ትኬት ከጎናቸው እንቁም፡፡ የእደ ጥበብ ምርቶቻቸውንም በመግዛት ከሊቀ መልአኩ በረከት እንካፈል፡፡
አዘጋጅ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
❤41🥰3👎2
Sheger Press️️
Photo
የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ምልጃ እና በረከት አይለየን🙏
ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው
ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ አባታችን በተወለዱ ጊዜ አንደበታቸው ከምስጋና የተገኘ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ቋድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር ሲቆዩ በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ልጅ እንዲሰጣቸው ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡
ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው መጋቢት አምስት አርፈዋል፡፡
በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው
ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ አባታችን በተወለዱ ጊዜ አንደበታቸው ከምስጋና የተገኘ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ቋድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር ሲቆዩ በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ልጅ እንዲሰጣቸው ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡
ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡ ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡
ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ጥቅምት 5 ቀንም ታላቅ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው መጋቢት አምስት አርፈዋል፡፡
በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
🙏26❤7👍5
የብር የመግዛት አቅም ማሽቆልቆል መጨረሻው እስከ የት ድረስ ነው?
"የውጭ ምንዛሪ በገበያ ዋጋ እንዲመራ" ከመደረጉ ጥቂት ቀናት በፊት የአንድ ዶላር ዋጋ Jan 1,2024 ላይ ብር 56.4777 የነበር ሲሆን፣ ከ7 ወር በኋላ July 30,2024 ላይ የአንድ ዶላር ዋጋ ብር 57.8338 ሆኗል።
የአንድ ዶላር ዋጋ በሰባት ወር ጊዜ ውስጥ ያሳየው ጭማሪ በብር 1.3561 ሲሆን፣ በመቶኛ 2.40% ብቻ ነው።
July 31 2024 ላይ "የውጭ ምንዛሪ በገበያ" እንዲመራ ከተደረገ ከሁለት ቀን በኋላ የአንድ ዶላር ዋጋ በብር 17.59 በመቶኛ ደግሞ 31.15 % እንዲጨምር ተደርጓል።
Octobe 14, 2025 በተደረገው ጨረታ የአንድ ዶላር ዋጋ ብር 148.1007 የደረሰ ሲሆን፣ ከJuly 30,2024 በኋላ ማለትም "የውጭ ምንዛሪ በገበያ ዋጋ" እንዲመራ ከተደረገ ከ1 ዓመት ከ2 ወር ከ15 ቀን በኋላ 162.23 % ወይም በብር 91.62 ጨምሯል።
ካለፈው ጨረታ June 5, 2025 ላይ ከተደረገው ጋር ሲነጻጸርም በ5 ወር ውስጥ ብር 13.1488 ወይም 9.74% ጨምሯል" ሲሉ የኢኮኖሚ ባለሙያው ሙሸ ሰሙ ገልጸዋል። (ቀሪ ማጣቀሻና ገለጻቸው ከላይ ተያይዟል
"የውጭ ምንዛሪ በገበያ ዋጋ እንዲመራ" ከመደረጉ ጥቂት ቀናት በፊት የአንድ ዶላር ዋጋ Jan 1,2024 ላይ ብር 56.4777 የነበር ሲሆን፣ ከ7 ወር በኋላ July 30,2024 ላይ የአንድ ዶላር ዋጋ ብር 57.8338 ሆኗል።
የአንድ ዶላር ዋጋ በሰባት ወር ጊዜ ውስጥ ያሳየው ጭማሪ በብር 1.3561 ሲሆን፣ በመቶኛ 2.40% ብቻ ነው።
July 31 2024 ላይ "የውጭ ምንዛሪ በገበያ" እንዲመራ ከተደረገ ከሁለት ቀን በኋላ የአንድ ዶላር ዋጋ በብር 17.59 በመቶኛ ደግሞ 31.15 % እንዲጨምር ተደርጓል።
Octobe 14, 2025 በተደረገው ጨረታ የአንድ ዶላር ዋጋ ብር 148.1007 የደረሰ ሲሆን፣ ከJuly 30,2024 በኋላ ማለትም "የውጭ ምንዛሪ በገበያ ዋጋ" እንዲመራ ከተደረገ ከ1 ዓመት ከ2 ወር ከ15 ቀን በኋላ 162.23 % ወይም በብር 91.62 ጨምሯል።
ካለፈው ጨረታ June 5, 2025 ላይ ከተደረገው ጋር ሲነጻጸርም በ5 ወር ውስጥ ብር 13.1488 ወይም 9.74% ጨምሯል" ሲሉ የኢኮኖሚ ባለሙያው ሙሸ ሰሙ ገልጸዋል። (ቀሪ ማጣቀሻና ገለጻቸው ከላይ ተያይዟል
❤13😢13👍3😱1
ያለፈቃድ ደመወዝ መቁረጥ‼️
የመንግስት ሰራተኞች ከፈቃዳቸው ውጪ፣ ከደመወዛቸው ገንዘብ እየተቆረጠባቸው ነው ተባለ።
ይህም ህገ ወጥም አሳሳቢም ነው ተብሏል።
ይህንን ያለው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ነው።
ተቋሙ ከህግ ውጪ የመንግስት ሰራተኞች ከደመወዛቸው የሚቆረጥባቸው ገንዘብ ነገር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል።
የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋሙ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ተደጋጋሚ ቅሬታ እየቀረበልኝ ነው ብሏል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሲዳማ ክልል በተለያዩ ወረዳዎች ያሉ መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞች ፈቃዳቸውን ሳይሰጡ ከደመወዛቸው ላይ ገንዘብ እየተቆረጠባቸው መሆኑን ነግረውኛል ብሏል።
በተመሳሳይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞንም በተለያዩ ወረዳዎች የሚሰሩ መምህራን ተመሳሳይ ጥያቄ ማቅረባቸውም ተነግሯል።
ይህም የችግሩን አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረስ ያሳያል ብሏል የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋሙ መግለጫ።
ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ ስምምነቱን በፅሁፍ ሲገልፅ፣በፍርድ ቤት ትእዛዝ ወይንም በህግ በተደነገገው መሰረት ካልሆነ ደሞዙን መቁረጥም ሆነ መያዝ እንደማይቻል ሊታወቅ ይገባል ብሏል።
ችግሩ አለ ተብሎ ቅሬታ በቀረበባቸው አካባቢዎችም አስቸኳይ እርምት ሊደረግ ይገባል ሲል የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አሳስቧል።
ሸገር
@sheger_press
@sheger_press
የመንግስት ሰራተኞች ከፈቃዳቸው ውጪ፣ ከደመወዛቸው ገንዘብ እየተቆረጠባቸው ነው ተባለ።
ይህም ህገ ወጥም አሳሳቢም ነው ተብሏል።
ይህንን ያለው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ነው።
ተቋሙ ከህግ ውጪ የመንግስት ሰራተኞች ከደመወዛቸው የሚቆረጥባቸው ገንዘብ ነገር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል።
የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋሙ በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ተደጋጋሚ ቅሬታ እየቀረበልኝ ነው ብሏል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሲዳማ ክልል በተለያዩ ወረዳዎች ያሉ መምህራን፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ሰራተኞች ፈቃዳቸውን ሳይሰጡ ከደመወዛቸው ላይ ገንዘብ እየተቆረጠባቸው መሆኑን ነግረውኛል ብሏል።
በተመሳሳይ በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞንም በተለያዩ ወረዳዎች የሚሰሩ መምህራን ተመሳሳይ ጥያቄ ማቅረባቸውም ተነግሯል።
ይህም የችግሩን አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረስ ያሳያል ብሏል የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋሙ መግለጫ።
ማንኛውም የመንግስት ሰራተኛ ስምምነቱን በፅሁፍ ሲገልፅ፣በፍርድ ቤት ትእዛዝ ወይንም በህግ በተደነገገው መሰረት ካልሆነ ደሞዙን መቁረጥም ሆነ መያዝ እንደማይቻል ሊታወቅ ይገባል ብሏል።
ችግሩ አለ ተብሎ ቅሬታ በቀረበባቸው አካባቢዎችም አስቸኳይ እርምት ሊደረግ ይገባል ሲል የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አሳስቧል።
ሸገር
@sheger_press
@sheger_press
❤24🔥1
መኪናውን አቁሞ ኮሪደር ልማቱ ላይ ሽንት
ሲሸና የነበረ ግለሰብ ተያዘ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተማዋን ውብና ፅዱ የማድረግ ዕቅድን ለማሳካት፣ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ጠንካራ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03፣ ልዩ ስሙ ወሎ ሰፈር አካባቢ ከዋናው አየር መንገድ አጠገብ ባለው የኮሪደር ልማት አካባቢ መኪናውን አቁሞ ሽንት ሲሸና የነበረ ግለሰብ ተይዟል።
* ተግባር፡
ግለሰቡን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከትራፊክ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር አውሏል።
* ቅጣት፡
በፈፀመው የደንብ መተላለፍ መሰረት 2,000 (ሁለት ሺህ) ብር እንዲቀጣ ተደርጓል።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ፣ መሰል ደንብ መተላለፎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጿል። በመሆኑም፣ ማንኛውም ደንብ ተላላፊ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።
ባለስልጣኑ፣ ማንኛውም የደንብ መተላለፍ ሲመለከት ኅብረተሰቡ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
@sheger_press
@sheger_press
ሲሸና የነበረ ግለሰብ ተያዘ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከተማዋን ውብና ፅዱ የማድረግ ዕቅድን ለማሳካት፣ ደንብ ተላላፊዎች ላይ ጠንካራ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታውቋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03፣ ልዩ ስሙ ወሎ ሰፈር አካባቢ ከዋናው አየር መንገድ አጠገብ ባለው የኮሪደር ልማት አካባቢ መኪናውን አቁሞ ሽንት ሲሸና የነበረ ግለሰብ ተይዟል።
* ተግባር፡
ግለሰቡን የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከትራፊክ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር አውሏል።
* ቅጣት፡
በፈፀመው የደንብ መተላለፍ መሰረት 2,000 (ሁለት ሺህ) ብር እንዲቀጣ ተደርጓል።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣኑ፣ መሰል ደንብ መተላለፎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጿል። በመሆኑም፣ ማንኛውም ደንብ ተላላፊ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።
ባለስልጣኑ፣ ማንኛውም የደንብ መተላለፍ ሲመለከት ኅብረተሰቡ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
@sheger_press
@sheger_press
❤10🥴6😱4
ከሰሞኑ ተዋቂዉ ሙዚቀኛ አንዶለም ጎሳ በዱባይ ኮንሰርት ሊያቀርብ መሆኑ ተሰምቷል ፡፡
ታዲያ ብዙዎች ጉዳዩን ከቀድሞ ባለቤቱ ቀነኒ አዱኛ አሞሞት ጋር ተያይዞ ጥያቄዎችን እያነሱ ነዉ ፡፡
አንድ ሰሞን ለልጃቸዉ ፍትህን ሲጠይቁ የነበሩ ቤተሰቦች እና አንዶለም ጎሳ ከምን ደርሰዉ ዝምታን መረጡ?
አባገዳዎች የገቡበት ሚስጥራዊ ሽምግልና
👇👇👇 ዝርዝር ይዘናል
https://youtu.be/YiHXeS7Vsm8?si=ahj7qfEFK0hnwphd
ታዲያ ብዙዎች ጉዳዩን ከቀድሞ ባለቤቱ ቀነኒ አዱኛ አሞሞት ጋር ተያይዞ ጥያቄዎችን እያነሱ ነዉ ፡፡
አንድ ሰሞን ለልጃቸዉ ፍትህን ሲጠይቁ የነበሩ ቤተሰቦች እና አንዶለም ጎሳ ከምን ደርሰዉ ዝምታን መረጡ?
አባገዳዎች የገቡበት ሚስጥራዊ ሽምግልና
👇👇👇 ዝርዝር ይዘናል
https://youtu.be/YiHXeS7Vsm8?si=ahj7qfEFK0hnwphd
❤8👎4🤔1
Sheger Press️️
Photo
የማይታየው አምላክ ቢወርድ በምቀኝነት ገደሉት
በዘመነ ሐዋርያት ከነበሩና አስደናቂ ታሪክ ከነበራቸው ቅዱሳን አንዱ ይህ አባት ነው:: ትውልዱ ግሪካዊ ሲሆነ ከነአሪስቶትል ሲያያዝ የመጣውን ፍልስፍና ጨርሶ በማጥናቱ የፈላስፎች አለቃ የሚል ስም ተሰጥቶት ነበር:: በግሪክ አቴንስ ለነበሩ ፈላስፎችም ሁሉ የበላይ ሲሆን በአርዮስፋጐስ ታላቁ ሰው እርሱ ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እድሜው ገና ወጣት ነበር ቅዱስ ዲዮናስዮስ፡፡ በግሪክ ምድር ከሚመለኩ 250 አማልክት መካከል ቁም ነገር አላገኘምና ፈላስፋ ስለ ሆነ ሁሌ ይመራመር ይልቁንም ስለ እውነተኛው አምላክ ያስብ ነበር፡፡ ዓለም በተፈጠረች በ5,534 ዓመት መጋቢት 27 ቀን በዕለተ ዓርብ ስቅለት 6 ሰዓት ላይ ምድር ተናወጠች፡፡ ፀሐይ ጨለመች፣ ጨረቃ ደም ሆነች፣ ከዋክብትም ረገፉ፡፡ በዚህ የተደናገጡ የአቴና ነዋሪዎችና ፈላስፎች ወደ ዲዮናስዮስ ተሰብስበው የተፈጠረውን ነገር መርምረህ አስረዳን አሉት፡፡
ባለው ጥበብ ባሕሩን፣ የብሱን፣ ፀሐይ፣ ጨረቃን፣ ከዋክብትን ቢመረመራቸው በቀደመ ቦታቸው አገኛቸው፡፡ ግራ ቢገባው እንቅልፍ ራቀው፤ ከዚያም ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ መጻሕፍትን ሲያገላብጥ "አርስጣላባ" በሚባል ግዙፍ መጽሐፍ ውስጥ "እልመክኑን" የሚል ጽሑፍ አገኘ:: ወደ ውጪ ወጥቶ በሕዝቡና ጠቢባኑ ፊት ልብሱን ቀድዶ አለቀሰ:: እነርሱም ደንግጠው "ምነው መምሕራችን? ምን ሆንህ?" ቢሉት "የማይታየው አምላክ ቢወርድ በምቀኝነት ገደሉት የሚል ጽሑፍ አገኘሁ" አላቸው:: "እልመክኑን" ማለት "የማይታይ አምላክ" ማለት ነውና:: ከዚህ በሁዋላ ተማሪዎቹን ጠርቶ "እልመክኑን" የሚለውን ስም ከቤተ ጣዖቱ በር ላይ ለጥፉት አላቸው፡፡ ከ14 ዓመታት በኋላ ቅዱስ ዻውሎስ ወንጌልን እየሰበከ አቴና ደረሰ፡፡ ዘመኑም በ48 ዓ.ም ነበር፡፡ ወደ ከተማዋ ሲገባ በጣዖት ቤቱ በር ላይ የተለጠፈውን ጽሑፍ ተመለከተና ያስተምራቸው ያዘ፡፡ ትምሕርቱን የሰሙ ጠቢባኑና ሕዝቡ ሐዋርያውን ይዘው ወደ ዲዮናስዮስ ፊት አቀረቡት፡፡
አዲስ አምላክን ሲያስተምር አግኝተነዋል ሲሉትም ቅዱስ ዻውሎስ እኔ አዲስ አምላክን የምሰብክላችሁ አይደለሁም፤ ይልቁኑ ከቀድሞም የፈጠራችሁ ቀጥሎም የሞተላችሁ እናንተም “እልመክኑን ብላችሁ ሳታውቁት ታመልኩት የነበረውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” አላቸው፡፡ ዲዮናስዮስም ቅዱስ ዻውሎስን "ለዚህ ምን ምልክት አለህ?" ቢለው የዛሬ 14 ዓመት መጋቢት 27 ቀን በዕለተ ዓርብ 6 ሰዓት ላይ ታላላቅ ተአምራት ተደርጎ አይደለምን! እነዚህ ሁሉ የተደረጉት በስቅለቱ ጊዜ ነው" ሲል መለሰለት፡፡ ዲዮናስዮስም ፈጥኖ በክርስቶስ አመነ፤ የአካባቢው ጠቢባንና ሕዝቡም አምነው ከመሪያቸው ጋር ተጠመቁ፡፡ ቅዱስ ዻውሎስም ቅዱስ ዲዮናስዮስን አስተምሮ የአቴና የመጀመሪያው ዻዻስ አደረገው፡፡
ቅዱሱም ክርስቲያኖችን ያበዛ፣ መንጋውንም ያጸና ዘንድ ብዙ ተጋ፡፡ በተለይ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ታዋቂ ደራስያን አንዱ ሆነ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ በርካታ ድርሰቶችን ደረሰ፡፡ ዛሬም ድረስ ሃይማኖተ አበው ውስጥ የሚገኘው ድርሰቱ ጣዕሙ ልዩ ነው:: ቅዱሱ ለብዙ ዘመናት ለወንጌል አገልግሎት ተግቶ በዚህች ቀን የአካባቢው አገረ ገዥ አንገቱን አስቆርጦት ሰማዕት ሆኗል፡፡ የሚገርመው ግን ሲገድሉት በቦታው ሰው ስላልነበረ ቅዱሱ ተነስቶ፤ ተቆርጣ የወደቀች ራሱን አነሳት፡፡ በጐኑ አቅፎም ደቀ መዛሙርቱ እስካሉበት ሒዶ በፊታቸው ዘንበል አለ፡፡ ምዕመናንም እያለቀሱና እየዘመሩ ከተሰየፉት አርድእቱ ኡሲፎስና ኡርያኖስ ጋር ቀብረውታል፡፡ የቅዱሳንን ተጋድሎ አብነት አድርገው ገዳማውያን ይጋደላሉ፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በዘመነ ሐዋርያት ከነበሩና አስደናቂ ታሪክ ከነበራቸው ቅዱሳን አንዱ ይህ አባት ነው:: ትውልዱ ግሪካዊ ሲሆነ ከነአሪስቶትል ሲያያዝ የመጣውን ፍልስፍና ጨርሶ በማጥናቱ የፈላስፎች አለቃ የሚል ስም ተሰጥቶት ነበር:: በግሪክ አቴንስ ለነበሩ ፈላስፎችም ሁሉ የበላይ ሲሆን በአርዮስፋጐስ ታላቁ ሰው እርሱ ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆን ግን እድሜው ገና ወጣት ነበር ቅዱስ ዲዮናስዮስ፡፡ በግሪክ ምድር ከሚመለኩ 250 አማልክት መካከል ቁም ነገር አላገኘምና ፈላስፋ ስለ ሆነ ሁሌ ይመራመር ይልቁንም ስለ እውነተኛው አምላክ ያስብ ነበር፡፡ ዓለም በተፈጠረች በ5,534 ዓመት መጋቢት 27 ቀን በዕለተ ዓርብ ስቅለት 6 ሰዓት ላይ ምድር ተናወጠች፡፡ ፀሐይ ጨለመች፣ ጨረቃ ደም ሆነች፣ ከዋክብትም ረገፉ፡፡ በዚህ የተደናገጡ የአቴና ነዋሪዎችና ፈላስፎች ወደ ዲዮናስዮስ ተሰብስበው የተፈጠረውን ነገር መርምረህ አስረዳን አሉት፡፡
ባለው ጥበብ ባሕሩን፣ የብሱን፣ ፀሐይ፣ ጨረቃን፣ ከዋክብትን ቢመረመራቸው በቀደመ ቦታቸው አገኛቸው፡፡ ግራ ቢገባው እንቅልፍ ራቀው፤ ከዚያም ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ መጻሕፍትን ሲያገላብጥ "አርስጣላባ" በሚባል ግዙፍ መጽሐፍ ውስጥ "እልመክኑን" የሚል ጽሑፍ አገኘ:: ወደ ውጪ ወጥቶ በሕዝቡና ጠቢባኑ ፊት ልብሱን ቀድዶ አለቀሰ:: እነርሱም ደንግጠው "ምነው መምሕራችን? ምን ሆንህ?" ቢሉት "የማይታየው አምላክ ቢወርድ በምቀኝነት ገደሉት የሚል ጽሑፍ አገኘሁ" አላቸው:: "እልመክኑን" ማለት "የማይታይ አምላክ" ማለት ነውና:: ከዚህ በሁዋላ ተማሪዎቹን ጠርቶ "እልመክኑን" የሚለውን ስም ከቤተ ጣዖቱ በር ላይ ለጥፉት አላቸው፡፡ ከ14 ዓመታት በኋላ ቅዱስ ዻውሎስ ወንጌልን እየሰበከ አቴና ደረሰ፡፡ ዘመኑም በ48 ዓ.ም ነበር፡፡ ወደ ከተማዋ ሲገባ በጣዖት ቤቱ በር ላይ የተለጠፈውን ጽሑፍ ተመለከተና ያስተምራቸው ያዘ፡፡ ትምሕርቱን የሰሙ ጠቢባኑና ሕዝቡ ሐዋርያውን ይዘው ወደ ዲዮናስዮስ ፊት አቀረቡት፡፡
አዲስ አምላክን ሲያስተምር አግኝተነዋል ሲሉትም ቅዱስ ዻውሎስ እኔ አዲስ አምላክን የምሰብክላችሁ አይደለሁም፤ ይልቁኑ ከቀድሞም የፈጠራችሁ ቀጥሎም የሞተላችሁ እናንተም “እልመክኑን ብላችሁ ሳታውቁት ታመልኩት የነበረውን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” አላቸው፡፡ ዲዮናስዮስም ቅዱስ ዻውሎስን "ለዚህ ምን ምልክት አለህ?" ቢለው የዛሬ 14 ዓመት መጋቢት 27 ቀን በዕለተ ዓርብ 6 ሰዓት ላይ ታላላቅ ተአምራት ተደርጎ አይደለምን! እነዚህ ሁሉ የተደረጉት በስቅለቱ ጊዜ ነው" ሲል መለሰለት፡፡ ዲዮናስዮስም ፈጥኖ በክርስቶስ አመነ፤ የአካባቢው ጠቢባንና ሕዝቡም አምነው ከመሪያቸው ጋር ተጠመቁ፡፡ ቅዱስ ዻውሎስም ቅዱስ ዲዮናስዮስን አስተምሮ የአቴና የመጀመሪያው ዻዻስ አደረገው፡፡
ቅዱሱም ክርስቲያኖችን ያበዛ፣ መንጋውንም ያጸና ዘንድ ብዙ ተጋ፡፡ በተለይ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ታዋቂ ደራስያን አንዱ ሆነ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ በርካታ ድርሰቶችን ደረሰ፡፡ ዛሬም ድረስ ሃይማኖተ አበው ውስጥ የሚገኘው ድርሰቱ ጣዕሙ ልዩ ነው:: ቅዱሱ ለብዙ ዘመናት ለወንጌል አገልግሎት ተግቶ በዚህች ቀን የአካባቢው አገረ ገዥ አንገቱን አስቆርጦት ሰማዕት ሆኗል፡፡ የሚገርመው ግን ሲገድሉት በቦታው ሰው ስላልነበረ ቅዱሱ ተነስቶ፤ ተቆርጣ የወደቀች ራሱን አነሳት፡፡ በጐኑ አቅፎም ደቀ መዛሙርቱ እስካሉበት ሒዶ በፊታቸው ዘንበል አለ፡፡ ምዕመናንም እያለቀሱና እየዘመሩ ከተሰየፉት አርድእቱ ኡሲፎስና ኡርያኖስ ጋር ቀብረውታል፡፡ የቅዱሳንን ተጋድሎ አብነት አድርገው ገዳማውያን ይጋደላሉ፡፡ ገዳማቸውን እደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
❤27🥰3