ስለ ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን...
ቴዲ አፍሮ ዛሬ ሐምሌ 24/2013 ዓ.ም ከጎንደር ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬቱን ተቀብሏል። የክቡር ዶክትሬቱን በይፋ ከተቀበለበት ሰዓትም ጀምሮ የሙሉ ስም አጠራሩ "ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን" ሆኗል። ይኽ አርቲስት ለዚህ ክብር የበቃው ለዘመናት በአገራዊ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በሀይማኖታዊ ጉዳይች ላይ በጽኑ ተግቶ በመስራቱ እና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ደብዝዞ እንዳይቀር ይልቁንም ኢትዮጵያዊነት እንዲገዝፍ ለአመታት በሙያው በመትጋቱ ነው። ይኼንንም እውነት የጎንደር ዩኒቨርስቲ በጽሁፍ አርቅቆ ለታዳሚያን ተርኳል። የውኃ ሚኒስቴር የሆኑት ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ለቴዲ አፍሮ ያላቸውን አክብሮት ሲገልጹ "ወንድሜ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ እንኳን ደስ ያለህ.." በማለት ነበር።
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በመርኃ ግብሩ ላይ ለቤተሰብቹ ለጓደኞቹ ለባለቤቱና የክብር ዶክትሬት ላበረከተለት ለጎንደር ዩኒቨርስቲ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን አገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ወቅት ከባድ የጭንቀት ወቅት እንደሆነ ገልጾ ይኼ ወቅት እንደ እናቶች ምጥ ነው ከከባድ ምጥ በኋላ ነፍሰ ጡር ሴቶች ልጅ ወልደው እንደሚገላገሉ ሁሉ ኢትዮጵያም ከዚህ ጭንቅ በኋላ ፍጹም ሰላም ትሆናለች በማለት ምኞቱን ጭምር አስተላልፏል። አክሎም ለዘመናት ኢትዮጵያን በጎሳ እና በዘር ከፋፍሎ ያዳከማት ኃይል ዳግም የቀደመውን እድል እንዳያገኝ ሆኖ መሞቱን በመግለጽ ወጣት ተማሪዎች በተለይም በብዙ ልፋት ለተመረቁ አገር ተረካቢዎች የኢትዮጵያን ጉዳይ አደራ ብሏል።
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በአድናቂዎቹ በጓደኞቹ እንዲሁም በዘመድ አዝማዶቹ ታጅቦ ወደ ጎንደር የገባ ሲሆን በከተማው ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የጎንደር ህዝብም ባገኘው አጋጣሚ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ያለውን ፍቅር እና አክብሮት ገልጾለታል። በዚህ እለት በመላው ዓለም የሚገኙ አድናቂዎቹ እና የመገናኛ ብዙኃን የክብር ዶክትሬት አሰጣጥ ስነ-ስርዓቱን በሰፊው ሲያሰራጩ ውለዋል።
ማሳሰቢያ
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ወደ ፕሮግራሙ ስፍራ እንዲገኝ የተቀጠረለት ሰዓት 4:00 ሰዓት ሲሆን የመድረክ መሪው በተደጋጋሚ ስሙን ሲጠራ የቆየ በመሆኑ በአንዳድ ግለሰቦች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቴዲ አፍሮ እንዳረፈደ ተደርጎ ሊወራ ችሏል። እውነታው ግን አርቲስቱ ሰዓቱን ፍጹም አክበሮ በቦታው ተገኝቷል።
የግርጌ ማስታወሻ እና ምስጋና...!
ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዲ አፍሮ በተበረከተለት የክቡር ዶክትሬት ፍጹም ደስተኛ የሆነ ሲሆን አድናቂዎቹ እና ቤተዘመዱ ሁሉ የጎንደር ዩኒቨርስቲን ከነመላው አመራሩ ያመሰግናል። በተጨማሪም በጎንደር ከተማ በቆየንበት ወቅት በማንኛውም ሁኔታ ለተባበራችሁን እና ለትብብር ዝግጁ መሆናችሁን ለገለጻችሁልን በጠቅላላ እንዲሁም ለመላው የጎንደር ህዝብ ልባዊ ምስጋናችንን ለመግለጽ እንወዳለን።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ቴዲ አፍሮ ዛሬ ሐምሌ 24/2013 ዓ.ም ከጎንደር ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬቱን ተቀብሏል። የክቡር ዶክትሬቱን በይፋ ከተቀበለበት ሰዓትም ጀምሮ የሙሉ ስም አጠራሩ "ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን" ሆኗል። ይኽ አርቲስት ለዚህ ክብር የበቃው ለዘመናት በአገራዊ፣ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በሀይማኖታዊ ጉዳይች ላይ በጽኑ ተግቶ በመስራቱ እና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ደብዝዞ እንዳይቀር ይልቁንም ኢትዮጵያዊነት እንዲገዝፍ ለአመታት በሙያው በመትጋቱ ነው። ይኼንንም እውነት የጎንደር ዩኒቨርስቲ በጽሁፍ አርቅቆ ለታዳሚያን ተርኳል። የውኃ ሚኒስቴር የሆኑት ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ለቴዲ አፍሮ ያላቸውን አክብሮት ሲገልጹ "ወንድሜ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ እንኳን ደስ ያለህ.." በማለት ነበር።
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በመርኃ ግብሩ ላይ ለቤተሰብቹ ለጓደኞቹ ለባለቤቱና የክብር ዶክትሬት ላበረከተለት ለጎንደር ዩኒቨርስቲ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን አገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ወቅት ከባድ የጭንቀት ወቅት እንደሆነ ገልጾ ይኼ ወቅት እንደ እናቶች ምጥ ነው ከከባድ ምጥ በኋላ ነፍሰ ጡር ሴቶች ልጅ ወልደው እንደሚገላገሉ ሁሉ ኢትዮጵያም ከዚህ ጭንቅ በኋላ ፍጹም ሰላም ትሆናለች በማለት ምኞቱን ጭምር አስተላልፏል። አክሎም ለዘመናት ኢትዮጵያን በጎሳ እና በዘር ከፋፍሎ ያዳከማት ኃይል ዳግም የቀደመውን እድል እንዳያገኝ ሆኖ መሞቱን በመግለጽ ወጣት ተማሪዎች በተለይም በብዙ ልፋት ለተመረቁ አገር ተረካቢዎች የኢትዮጵያን ጉዳይ አደራ ብሏል።
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በአድናቂዎቹ በጓደኞቹ እንዲሁም በዘመድ አዝማዶቹ ታጅቦ ወደ ጎንደር የገባ ሲሆን በከተማው ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የጎንደር ህዝብም ባገኘው አጋጣሚ ለክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ያለውን ፍቅር እና አክብሮት ገልጾለታል። በዚህ እለት በመላው ዓለም የሚገኙ አድናቂዎቹ እና የመገናኛ ብዙኃን የክብር ዶክትሬት አሰጣጥ ስነ-ስርዓቱን በሰፊው ሲያሰራጩ ውለዋል።
ማሳሰቢያ
ክቡር ዶክተር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ወደ ፕሮግራሙ ስፍራ እንዲገኝ የተቀጠረለት ሰዓት 4:00 ሰዓት ሲሆን የመድረክ መሪው በተደጋጋሚ ስሙን ሲጠራ የቆየ በመሆኑ በአንዳድ ግለሰቦች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቴዲ አፍሮ እንዳረፈደ ተደርጎ ሊወራ ችሏል። እውነታው ግን አርቲስቱ ሰዓቱን ፍጹም አክበሮ በቦታው ተገኝቷል።
የግርጌ ማስታወሻ እና ምስጋና...!
ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዲ አፍሮ በተበረከተለት የክቡር ዶክትሬት ፍጹም ደስተኛ የሆነ ሲሆን አድናቂዎቹ እና ቤተዘመዱ ሁሉ የጎንደር ዩኒቨርስቲን ከነመላው አመራሩ ያመሰግናል። በተጨማሪም በጎንደር ከተማ በቆየንበት ወቅት በማንኛውም ሁኔታ ለተባበራችሁን እና ለትብብር ዝግጁ መሆናችሁን ለገለጻችሁልን በጠቅላላ እንዲሁም ለመላው የጎንደር ህዝብ ልባዊ ምስጋናችንን ለመግለጽ እንወዳለን።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ዓለማችን ላይ በየዘመኑ ድንቅ የተባሉ ጥቂት ሰዎች አሉ። በየዘመኑም ይፈጠራሉ። ለኔ በዚህ ዘመን ካንተ በቀር አንድ ሁለት ብዬ የምቆጥረው ሌላ ሰው የለኝም። አገሬ በጭንቅ ከተዋጠችበት ዘመን ጀምሮ የልጆቿን እና የሰንደቋን ነገር ችላ ሳትል እጅህን ወደ ነበልባል እሳት የሰደድክ አንተ ብቻ ነህ። አንተ "ለኔ" ብሎ አማርኛ አታውቅም። አንተ "ለኔ" ብሎ ግብዝነት አይነካካህም። በኪነ ጥበቡም ዘርፍ የዓለም የድል /የበላይነት/ ሰንጠረዥን በሩጫ ብቻ ሳይሆን በሙዚቃም አድቅቆ አንደኛ መሆን እንደሚቻል ብቻህን ታግለ፤ ድልንም አስመዝግበ አሳይተኸናል። አገሬ ከፍላ የማትጨርሰው የአንተ እዳ አለባት! ለወገኔ አመስግኖክ የማይፈጽመው ደግነትን አሳይተኸዋል። ኢትዮጵያ ባንተ ተግባር ለዘለዓለም ትኮራለች። ታሪኳን የዘከርክ፤ ክብሯን ያሳሰብክ፤ ድሏን ያበሰርክ ጀብዷንም የመሰከርክ ድንቅ እና ፍጹም ጥበበኛ ልጇ አንተ ነህ። ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን... እ...ን...ወ...ድ...ኃ...ለ...ን!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
ተሸንፌ የወደድኩህ...
እቺ ምስኪን አገሬ ሳይኖራት ሳይተርፋት መምህር ቀጥራ ትምህርት ቤት ገንብታ ያስተማረቻቸው ምሁሮች እውር ሆነውባት ያውቃሉ። ከትቢያ አንስታ እውቀት ዘርታባቸው ሰው አርጋቸው ስታበቃ ስጋዋን ሊበሉ ደሟን ሊጠጡ እያጋሱ ተነስተውባታል። አንተ ግን "የአባቶቼ አደራ የሆንሽ ቅድመ አያቶቼም የደም ዋጋ የከፈሉልሽ አገር ነሽና የኔም ነፍስ ለሉዓላዊነትሽ መረጋገጥ ቢገበር ደሜም ቢፈስልሽ ላንቺ የሚሰሰት አንዳችም የለኝም።" ብለኽ ዘለዓለማዊ ቃልኪዳን ያኖርክላት ይመስል በዚህ ጥልቅ ስሜት ውስጥ ሆነ ያለ በደልህ መከራ እንደ ጅረት ሲፈስብህ፤ አንዱ ቁስልህ ሳይሽር ሌላ ቁስል እያበጁብህ መቆም እንኳን እንዳትችል ፈተኑህ።
ፍጹም ሰላምን ለሌሎች ለሚመኘው ልብህ ከፉበት። ደግነትን እንደ ማህተሙ አጥብቆ የያዘውን ስብዕናህን ተጠየፉት። አንተ ግን አንደበትህ ክፉ ሳይናገር እግርህም ለስደት ሳይገሰግስ የደማ ልብህን በአገርህ አፈር አከምከው። የወገንህን መጎሳቆል እያየች በሀዘን የተዋጠች ነፍስህን እያባበልክ ጥሩ ቀን እስኪመጣ ታገስክ። የፍቅርህ የጥልቀት ልኬቱ አንተ እንጂ ለሌላ ሰው ለመረዳት ቀላል አይደለም። እግዚአብሔር ላንተ በስፋትም፣ በልህቀትም፣ በግዝፈትም ከሌላ ልቦች ሁሉ ለይቶ የፈጠረልህ እስኪመስለኝ ድረስ በኩራትና በትዕግስት የተሞላች ልብህን እደነቅባታለሁ።
ላንተ ከወርቅ የከበረ የኦፓል፣ የኤመራልድ፣ የዳይመንድ እና የሩቢ ፈርጥ ያለው ከነዚህም የተበጀ ዘውድ ቢጫንልህ ያንስሃል እንጂ በፍጹም አይበዛብህም። የኔ ኩሩ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሰጡ ሹመቶች ላንተ ይገቡኃል። የአገሬ አርቲስቶች አርቲስት በመሆናቸው እና በሙያቸው መኩራትም ካለባቸው አንተ በዘርፉ መገኘትህ ትልቁ ምክኒያታቸው ሊሆን ይገባል።
አይ እኔ በልቤ ያለን ሁሉ ለመጻፍ ስታገል ከዐይምሮዬ እየገዘፈ እጨነቃለሁ...! ብቻ እውነት በሆነ መውደድ እወድኃለው! ስላንተ በእጅጉ እጨነቃለሁ። ደስታህን መካፈል ሳይሆን መደሰት እችልበታለሁ። ዝም ብዬ እወድኃለው ብዬ ባወጋ መመጻደቅ ነው የሚሆንብኝ። አንተን ተሸንፌ ነው የወደድኩ! ጥበብህ፣ ሀሳብህ፣ ግጥምህ፣ ዜማክ፣ ደግነትህ፣ ትሁትነትህ፣ መልክህ፣ ቁመትህ፣ ኩራትህ፣ ወኔህ፣ አነጋገርህ፣ አሳሳቅህ፣ ቁምነገርህ ወዘተርፈ ባህሪያቶችህ እኔን አሸንፈውኝ ወድጄኃለው! ቅንጣት እንኳ የሚጠላ ነገር ባንተ ላይ ሳጣ እደነቃለሁ። ከፍቅሬ በላይ የምሸልምህ ውድ ነገር የለኝምና እ..ወ..ድ..ኃ..ለ..ሁ!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
እቺ ምስኪን አገሬ ሳይኖራት ሳይተርፋት መምህር ቀጥራ ትምህርት ቤት ገንብታ ያስተማረቻቸው ምሁሮች እውር ሆነውባት ያውቃሉ። ከትቢያ አንስታ እውቀት ዘርታባቸው ሰው አርጋቸው ስታበቃ ስጋዋን ሊበሉ ደሟን ሊጠጡ እያጋሱ ተነስተውባታል። አንተ ግን "የአባቶቼ አደራ የሆንሽ ቅድመ አያቶቼም የደም ዋጋ የከፈሉልሽ አገር ነሽና የኔም ነፍስ ለሉዓላዊነትሽ መረጋገጥ ቢገበር ደሜም ቢፈስልሽ ላንቺ የሚሰሰት አንዳችም የለኝም።" ብለኽ ዘለዓለማዊ ቃልኪዳን ያኖርክላት ይመስል በዚህ ጥልቅ ስሜት ውስጥ ሆነ ያለ በደልህ መከራ እንደ ጅረት ሲፈስብህ፤ አንዱ ቁስልህ ሳይሽር ሌላ ቁስል እያበጁብህ መቆም እንኳን እንዳትችል ፈተኑህ።
ፍጹም ሰላምን ለሌሎች ለሚመኘው ልብህ ከፉበት። ደግነትን እንደ ማህተሙ አጥብቆ የያዘውን ስብዕናህን ተጠየፉት። አንተ ግን አንደበትህ ክፉ ሳይናገር እግርህም ለስደት ሳይገሰግስ የደማ ልብህን በአገርህ አፈር አከምከው። የወገንህን መጎሳቆል እያየች በሀዘን የተዋጠች ነፍስህን እያባበልክ ጥሩ ቀን እስኪመጣ ታገስክ። የፍቅርህ የጥልቀት ልኬቱ አንተ እንጂ ለሌላ ሰው ለመረዳት ቀላል አይደለም። እግዚአብሔር ላንተ በስፋትም፣ በልህቀትም፣ በግዝፈትም ከሌላ ልቦች ሁሉ ለይቶ የፈጠረልህ እስኪመስለኝ ድረስ በኩራትና በትዕግስት የተሞላች ልብህን እደነቅባታለሁ።
ላንተ ከወርቅ የከበረ የኦፓል፣ የኤመራልድ፣ የዳይመንድ እና የሩቢ ፈርጥ ያለው ከነዚህም የተበጀ ዘውድ ቢጫንልህ ያንስሃል እንጂ በፍጹም አይበዛብህም። የኔ ኩሩ ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሰጡ ሹመቶች ላንተ ይገቡኃል። የአገሬ አርቲስቶች አርቲስት በመሆናቸው እና በሙያቸው መኩራትም ካለባቸው አንተ በዘርፉ መገኘትህ ትልቁ ምክኒያታቸው ሊሆን ይገባል።
አይ እኔ በልቤ ያለን ሁሉ ለመጻፍ ስታገል ከዐይምሮዬ እየገዘፈ እጨነቃለሁ...! ብቻ እውነት በሆነ መውደድ እወድኃለው! ስላንተ በእጅጉ እጨነቃለሁ። ደስታህን መካፈል ሳይሆን መደሰት እችልበታለሁ። ዝም ብዬ እወድኃለው ብዬ ባወጋ መመጻደቅ ነው የሚሆንብኝ። አንተን ተሸንፌ ነው የወደድኩ! ጥበብህ፣ ሀሳብህ፣ ግጥምህ፣ ዜማክ፣ ደግነትህ፣ ትሁትነትህ፣ መልክህ፣ ቁመትህ፣ ኩራትህ፣ ወኔህ፣ አነጋገርህ፣ አሳሳቅህ፣ ቁምነገርህ ወዘተርፈ ባህሪያቶችህ እኔን አሸንፈውኝ ወድጄኃለው! ቅንጣት እንኳ የሚጠላ ነገር ባንተ ላይ ሳጣ እደነቃለሁ። ከፍቅሬ በላይ የምሸልምህ ውድ ነገር የለኝምና እ..ወ..ድ..ኃ..ለ..ሁ!
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ቴዲ አፍሮ ጎዳና
ለዘመናት ኢትዮጵያዊነት ላይ ትኩረቱን አድርጎ ማህበረሰቡን በአገር ፍቅር ሲያነቃቃ እና በመልካም ምግባሮች ሲቀርጽ የኖረው ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮ ካሳሁን በጎንደር ከተማ ላይ ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በር እስከ ኮሌጅ ማዞሪያ ያለው የአስፓልት መንገድ የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን ጎዳና ተብሎ ተሰይሞለታል። የመንገዱ ስም ከዚህ በኋላ ቴዲ አፍሮ ግዳና እየተባለ ይጠራል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
ለዘመናት ኢትዮጵያዊነት ላይ ትኩረቱን አድርጎ ማህበረሰቡን በአገር ፍቅር ሲያነቃቃ እና በመልካም ምግባሮች ሲቀርጽ የኖረው ክቡር ዶ/ር አርቲስት ቴዎድሮ ካሳሁን በጎንደር ከተማ ላይ ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በር እስከ ኮሌጅ ማዞሪያ ያለው የአስፓልት መንገድ የክቡር ዶ/ር ቴዎድሮስ ካሳሁን ጎዳና ተብሎ ተሰይሞለታል። የመንገዱ ስም ከዚህ በኋላ ቴዲ አፍሮ ግዳና እየተባለ ይጠራል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
👍1
"አስተሳሳሪ ምልክት"
✍️(አሮን ሙሉጌታ)
ዛሬ ላይ እንደ ሀገር የት ነን? አለም እንድህ ይለናል ፦ኢትዮጲያ የሰው ዘር መገኛ ፤ ቀደምት ስልጣኔን ያስተማረች ፤ የጀግኖች ሀገር ፤ በማንም ያልተደፈረች በባርነት ያልተገዛች ሀገር ኢትዮጲያ ::
እኛ ግን ዛሬ የት ነን? አለም ከሗላችን ተነስታ ወደ ኋላ ትታን ሂዳለች ኋላ ቀርተናልም ፤ እኛ ምንም ሳንሰራ በአባቶቻችን ገድል እየፎከርን ፤ ከሰው ህይወት ርስት ፣ ጥቅም በልጦብን ፤ የኔ ብቻ ትክክል የኔ ብቻ የበላይ እየተባባልን ፤ ጥላቻ ነግሶ የቀደመው ተከባብሮ መኖርና መቻቻል ተረስቶ ፤ በዚች ምድር ዘላለም እንደምንኖርባት አስበን ጥለናት እንደምንሄድ እና እንግዳ መሆናችንን ረስተን አይደለም ለፀብ ለፍቅር የማይበቃ ጊዜያችንን አሁን ባለንበት ሁኔታ ለኛ ፀፀትን አትርፈን ለመጪው ትውልድ ጥላቻን አውርሰን አሁንም ከኛ የባሰ ራስ ወዳድ ትውልድ እንዳንፈጥር እሰጋለሁ!
አንድ የሚያደርገን ታሪክ እየተፋቀ የሚያለያዩን ትንሽ ታሪኮች ደምቀው በሚፃፉበት በዚህ ዘመን ሁሉን በአንድነት ለማስተሳሰር የሚታትር አለም ስለሚያወራላት ኢትዮጲያ ፤ ወዳኋላ ለቀረችው ኢትዮጲያ እንደሳት የሚበላው ከልቡ የሚቆረቆር ሰው አውቃለሁ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)...
✍️(አሮን ሙሉጌታ)
ዛሬ ላይ እንደ ሀገር የት ነን? አለም እንድህ ይለናል ፦ኢትዮጲያ የሰው ዘር መገኛ ፤ ቀደምት ስልጣኔን ያስተማረች ፤ የጀግኖች ሀገር ፤ በማንም ያልተደፈረች በባርነት ያልተገዛች ሀገር ኢትዮጲያ ::
እኛ ግን ዛሬ የት ነን? አለም ከሗላችን ተነስታ ወደ ኋላ ትታን ሂዳለች ኋላ ቀርተናልም ፤ እኛ ምንም ሳንሰራ በአባቶቻችን ገድል እየፎከርን ፤ ከሰው ህይወት ርስት ፣ ጥቅም በልጦብን ፤ የኔ ብቻ ትክክል የኔ ብቻ የበላይ እየተባባልን ፤ ጥላቻ ነግሶ የቀደመው ተከባብሮ መኖርና መቻቻል ተረስቶ ፤ በዚች ምድር ዘላለም እንደምንኖርባት አስበን ጥለናት እንደምንሄድ እና እንግዳ መሆናችንን ረስተን አይደለም ለፀብ ለፍቅር የማይበቃ ጊዜያችንን አሁን ባለንበት ሁኔታ ለኛ ፀፀትን አትርፈን ለመጪው ትውልድ ጥላቻን አውርሰን አሁንም ከኛ የባሰ ራስ ወዳድ ትውልድ እንዳንፈጥር እሰጋለሁ!
አንድ የሚያደርገን ታሪክ እየተፋቀ የሚያለያዩን ትንሽ ታሪኮች ደምቀው በሚፃፉበት በዚህ ዘመን ሁሉን በአንድነት ለማስተሳሰር የሚታትር አለም ስለሚያወራላት ኢትዮጲያ ፤ ወዳኋላ ለቀረችው ኢትዮጲያ እንደሳት የሚበላው ከልቡ የሚቆረቆር ሰው አውቃለሁ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)...
.. .ለዚህም ነው "የመጪው ዘመን ፊት ናት መሪ፣ ዛሬ አለም ቢላት ኋላ ቀሪ" ብሎ ያዜመላት በሄደበት ስሟን ጠርቶ የማይጠግበው አንድነታችነን አብዝቶ የሚሻ ሀገር ወደቀድሞው ገናንነቷ እንድትመለስ በሚችለው ሁሉ የሚታትር እንደ አባቱ ቴዎድሮስ (መይሰው ካሳ)ሀገሩ ከሰለጠኑት ሀገሮች ተርታ እንድትሰለፍ ፤ ስልጣኔን አስተምራ እንደካሮት ቁልቁል ላደገች ሀገር የሚያመው እሱ ነው እሱ ብቻ ከፍቅርና አንድነት ግምጃ ተራቁተን ባዶ በቀረንበት በዚህ ዘመን፣ እንደ ኢትዮጵያዊ፤ የቀረን አስተሳሳሪ ምልክት፣ አንድ ግለሰብ ብቻ መሆኑን ስናይ ደግሞ ሆድ ያስብሳል ቂምን ይቅርታ እንባባል አንድ እንሁን ከወረስነው ቂም ይልቅ የምናወርሰው ፍቅር ይበልጣል ይላል ሰውዬው ዘረኝነትን ቀብረን አንድነትን የምናነግስበት ቀን እሩቅ አይሆንም የሚል እምነት አለኝ ከሁሉም ነገር ፍቅር ይበልጣል ፍቅር ያሸንፋል ::
ዘጽአት ለኢትዮጵያ ወደ ተስፋ ጉዞ
ባህሩን የሚያሻግር አንድ ሙሴ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅም የኢትዮጵያ ትንሳኤ
በአንድነት ከገባን የፍቅር ሱባኤ
ከከፈልክልን ዋጋ አንፃር ሁሉ ነገር ያንስብሀል እንጅ አይበዙብህም መልካም ነገሮች ሁሉ ለአንተ ይገቡሀል ክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን!
በያላችሁበት ሰላም ፍቅር ጤና ለናንተ ለሀገሬ ልጆች! ♦️አሮን
ዘጽአት ለኢትዮጵያ ወደ ተስፋ ጉዞ
ባህሩን የሚያሻግር አንድ ሙሴ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅም የኢትዮጵያ ትንሳኤ
በአንድነት ከገባን የፍቅር ሱባኤ
ከከፈልክልን ዋጋ አንፃር ሁሉ ነገር ያንስብሀል እንጅ አይበዙብህም መልካም ነገሮች ሁሉ ለአንተ ይገቡሀል ክብር ዶክተር ሎሬት አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን!
በያላችሁበት ሰላም ፍቅር ጤና ለናንተ ለሀገሬ ልጆች! ♦️አሮን
Forwarded from ታታ አፍሮ -Tata Afro
የእኔን ጩኸት በአደባባይ መሰከሩት...
አንጋፋው ገጣሚና የዜማ ደራሲ ሙሉ ገበየሁ ስለ ቴዲ አፍሮና ስለ ኪነጥበቡ እንዲህ አሉ....
"ምናልባትም በዚ ሙያ ብዙ አንጋፋ ሙያተኞች ጥረዋል ደክመዋል ለፍተዋል። ሙያተኞቹም በዋዛ ፈዛዛ አልፈዋል። ይኼ ሙያ ከጥንተ ጀምሮ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ክብር አጥቶ፣ ለሙያው ትኩረት ሳይሰጠው፣ ክብር ተነፍጎ፣ ለባለሙያውም ፍቅር ሳይሰጠው ኖሮ ኖሮ ኖሮ አሁን ላይ ህዝቡ ለሙያው የሚሰጠው ፍቅር እየበለጠ ትኩረት እና አክብሮት እንዲሰጠው ዋጋ እንዲሰጠው እንደ ቴዲ አፍሮ ክስተት ሆኖ ሙያው የተፈጠረ ሰው በመገኘቱ በአገር ደረጃ የቀደሙትንም ዋጋ ያስከበረ ለጥበቡ ፈርጥ የሆነ ሰው ነው። ቴዲ አፍሮ ጥበብን አክብሯት ጥበብም አክብራዋለች።"
የኔ ኩሩ የኔ ቀብራራ የአገሬ ሙያተኞች በሙያቸው መኩራት ካለባቸው ሙያው ላይ አንተ ስላለ መሆን አለበት ብዬ በግልጽ ከትቤ ነበር። እነሆ የመከበራቸው ምክኒያት የሙያውም መግዘፍ ምክኒያት አንተ ነህ። ይኼ የኔ ስሜት ብቻ ሳይሆን አንተ የምታከብራቸው ሰዎች እውነተኛ ቃል ነው። ይኼ እውነት የተነገር አልያም የሚነገር ብቻ አይደለም ይልቁንም በራሱ ጸንቶ የቆመ ልሸሽገው ቢሉ የማይ ሸሸግ አላወራውም ቢሉ አፍ አውጥቶ የሚናገር በራሱ የጸና ብሎም የገዘፈ እውነት ነው። ለዚህም ነው በአደባባይ ቆመው አንጋፋዎች የኔን ጩኸት ያሰሙት። ይኼንን የጸና እውነት ሙያተኞች አንደበታቸውን ከፍተው ለሀቅ በመመስከራቸው ደስ አለኝ። እኔ ወዳጅህ ሁሌም ባንተ የምኮራ ሰው ነኝ። የከፈልካትን እያንዳንዷን ዋጋ ስለማውቅ ስላንተ እውነት ለመመስከር በፍጹም አልሰንፍም። ገና ብዙ ክብር ብዙ ፍቅር ብዙ አድናቆት አብረን እናያለን። በቁመህ የውለታክ ዋጋ እስኪከፈልህ ድረስ ብዕራችን በነጻነት እውነታውን ይከትባል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
አንጋፋው ገጣሚና የዜማ ደራሲ ሙሉ ገበየሁ ስለ ቴዲ አፍሮና ስለ ኪነጥበቡ እንዲህ አሉ....
"ምናልባትም በዚ ሙያ ብዙ አንጋፋ ሙያተኞች ጥረዋል ደክመዋል ለፍተዋል። ሙያተኞቹም በዋዛ ፈዛዛ አልፈዋል። ይኼ ሙያ ከጥንተ ጀምሮ ሲወድቅ ሲነሳ፣ ክብር አጥቶ፣ ለሙያው ትኩረት ሳይሰጠው፣ ክብር ተነፍጎ፣ ለባለሙያውም ፍቅር ሳይሰጠው ኖሮ ኖሮ ኖሮ አሁን ላይ ህዝቡ ለሙያው የሚሰጠው ፍቅር እየበለጠ ትኩረት እና አክብሮት እንዲሰጠው ዋጋ እንዲሰጠው እንደ ቴዲ አፍሮ ክስተት ሆኖ ሙያው የተፈጠረ ሰው በመገኘቱ በአገር ደረጃ የቀደሙትንም ዋጋ ያስከበረ ለጥበቡ ፈርጥ የሆነ ሰው ነው። ቴዲ አፍሮ ጥበብን አክብሯት ጥበብም አክብራዋለች።"
የኔ ኩሩ የኔ ቀብራራ የአገሬ ሙያተኞች በሙያቸው መኩራት ካለባቸው ሙያው ላይ አንተ ስላለ መሆን አለበት ብዬ በግልጽ ከትቤ ነበር። እነሆ የመከበራቸው ምክኒያት የሙያውም መግዘፍ ምክኒያት አንተ ነህ። ይኼ የኔ ስሜት ብቻ ሳይሆን አንተ የምታከብራቸው ሰዎች እውነተኛ ቃል ነው። ይኼ እውነት የተነገር አልያም የሚነገር ብቻ አይደለም ይልቁንም በራሱ ጸንቶ የቆመ ልሸሽገው ቢሉ የማይ ሸሸግ አላወራውም ቢሉ አፍ አውጥቶ የሚናገር በራሱ የጸና ብሎም የገዘፈ እውነት ነው። ለዚህም ነው በአደባባይ ቆመው አንጋፋዎች የኔን ጩኸት ያሰሙት። ይኼንን የጸና እውነት ሙያተኞች አንደበታቸውን ከፍተው ለሀቅ በመመስከራቸው ደስ አለኝ። እኔ ወዳጅህ ሁሌም ባንተ የምኮራ ሰው ነኝ። የከፈልካትን እያንዳንዷን ዋጋ ስለማውቅ ስላንተ እውነት ለመመስከር በፍጹም አልሰንፍም። ገና ብዙ ክብር ብዙ ፍቅር ብዙ አድናቆት አብረን እናያለን። በቁመህ የውለታክ ዋጋ እስኪከፈልህ ድረስ ብዕራችን በነጻነት እውነታውን ይከትባል።
✎✍#ታታ_አፍሮ /ነፃ ብዕር/
👍1
የአጤ ምኒልክ እና የእቴጌ ጣይቱ የልደት በዓል መታሰቢያ
#የዝግጅት_አቅራቢዎች ፥ ጋዜጠኛ ንጉሴ አክሊሉ፣ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም፣ ያሬድ ሹመቴ ፣ ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ፣ ቶማስ አድማሱ፣ ሙሉጌታ ታዬ እንዲሁም ሕብረቀለም የቴአትር ቡድን ናቸው::
#ቀን- ማክሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም
#ሰዓት - ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ
#ቦታ- ዋቢ ሸበሌ ሆቴል
#አዘጋጆች - የእምዬ ምኒልክ ወዳጆች
- አርማ ሕትመትና ማስታወቂያ
ማሳሰቢያ...
መግቢያው በነፃ ነው:: ከኮቪድ ጋር በተያያዘ የሚገኘውን ሰው መገደብ አስፈላጊ በመሆኑ የመግቢያ ካርድ 22 ጎላጎል ሕንፃ ሁለተኛ ፎቅ አርማ ማስታወቂያ እና ስታዲየም አካባቢ መንገድ ትራንስፖርት ፊትለፊት አዳም ፀጉር ቤት ሄደው በነፃ ይውሰዱ።
#የዝግጅት_አቅራቢዎች ፥ ጋዜጠኛ ንጉሴ አክሊሉ፣ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ፣ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሔኖክ ስዩም፣ ያሬድ ሹመቴ ፣ ገጣሚ በላይ በቀለ ወያ፣ ቶማስ አድማሱ፣ ሙሉጌታ ታዬ እንዲሁም ሕብረቀለም የቴአትር ቡድን ናቸው::
#ቀን- ማክሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም
#ሰዓት - ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ
#ቦታ- ዋቢ ሸበሌ ሆቴል
#አዘጋጆች - የእምዬ ምኒልክ ወዳጆች
- አርማ ሕትመትና ማስታወቂያ
ማሳሰቢያ...
መግቢያው በነፃ ነው:: ከኮቪድ ጋር በተያያዘ የሚገኘውን ሰው መገደብ አስፈላጊ በመሆኑ የመግቢያ ካርድ 22 ጎላጎል ሕንፃ ሁለተኛ ፎቅ አርማ ማስታወቂያ እና ስታዲየም አካባቢ መንገድ ትራንስፖርት ፊትለፊት አዳም ፀጉር ቤት ሄደው በነፃ ይውሰዱ።
🔥1