Telegram Web Link
#DjiboutiđŸ‡ŠđŸ‡¯

የ77 ዓመቱ ፕáˆŦá‹šá‹ŗáŠ•á‰ĩ ለሌላ የáˆĩáˆáŒŖáŠ• ዘመን áŠĨáŠ•á‹˛á‹ˆá‹ŗá‹°áˆŠ የሚá‹Ģáˆĩá‰Ŋላቸው á‹áˆŗáŠ” ተላለፈáĸ

የጅቡቲ ምክር ቤá‰ĩ በሀገáˆĒቱ ሕገ-መንግáˆĨá‰ĩ ለፕáˆŦዝደንá‰ĩነá‰ĩ á‹¨áˆšá‹ˆá‹ŗá‹°áˆŠ ዕጩዎá‰Ŋ ላይ á‹¨á‰°áŒŖáˆˆá‹ የዕá‹ĩሜ ገደá‰Ĩ áŠĨáŠ•á‹˛áŠáˆŗ የቀረበ á‹¨á‹áˆŗáŠ”-áˆáˆŗá‰Ĩ በሙሉ á‹ĩምáŒŊ አáŒŊá‹ĩቋልáĸ

á‹áˆŗáŠ”á‹ ፕáˆŦዝደንá‰ĩ áŠĸáˆĩማኤል ዑመር ጉሌሕ በሚá‹Ģዝá‹Ģ 2018 ዓ/ም በሚáŠĢሔደው ምርáŒĢ ለáˆĩá‹ĩáˆĩተኛ የáˆĨáˆáŒŖáŠ• ዘመን በá‹ĩጋሚ áŠĨáŠ•á‹˛á‹ˆá‹ŗá‹°áˆŠ መንገá‹ĩ ከፍቷልáĸ

የጅቡቲ ሕገ-መንግáˆĨá‰ĩ ዕá‹ĩሜው ከ75 ዓመá‰ĩ በላይ የሆነው ግለሰá‰Ĩ ለፕáˆŦዝደንá‰ĩነá‰ĩ áˆ˜á‹ˆá‹ŗá‹°áˆ­ áŠĨንደማይá‰Ŋል ይደነግጋልáĸ

የሕገ-መንግáˆĨቱ ገደá‰Ĩ በመáŒĒው ሚá‹Ģዝá‹Ģ ይáŠĢáˆ”á‹ŗáˆ ተá‰Ĩሎ በሚጠበው ምርáŒĢ የ77 ዓመቱ ጉሌሕ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹­á‹ˆá‹ŗá‹°áˆŠ á‹ĢáŒá‹ŗá‰¸á‹‹áˆáĸ

ይሁንና የዕá‹ĩሜ ገደቡ áŠĨáŠ•á‹˛áŠáˆŗ የቀረበውን የማáˆģáˆģá‹Ģ á‹áˆŗáŠ” 65 áŠ á‰Ŗáˆ‹á‰ĩ á‹Ģሉá‰ĩ የጅቡቲ ምክር ቤá‰ĩ በሙሉ á‹ĩምáŒŊ áŠĨáŠ•á‹ŗáŒ¸á‹°á‰€ አፈ-áŒ‰á‰ŖáŠ¤ á‹˛áˆŒá‹­á‰ŗ ሞሐመá‹ĩ á‹˛áˆŒá‹­á‰ŗ áˆˆáˆáˆ¨áŠ•áˆŗá‹­ ዜና አገልግሎá‰ĩ ተናግረዋልáĸ

ፕáˆŦዝደንቱ በምክር ቤቱ á‹­áŠšáŠ•á‰ŗ á‹Ģገኘውን á‹áˆŗáŠ” ማáŒŊደቅ አሊá‹Ģም ሕዝበ-á‹áˆŗáŠ” áŠĨንዲáŠĢሔá‹ĩ መáŒĨáˆĢá‰ĩ á‹­áŠ–áˆ­á‰Ŗá‰¸á‹‹áˆáĸ

መረጃው የá‹ļá‰ŧ ቨለ áˆŦá‹ĩዮ ነውáĸ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🤔590❤577😡163😭59😱31💔24🕊23đŸ˜ĸ19👏15đŸĨ°9🙏5
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
" የተቃጠለው á‰Ĩሎክ 2ኛ ፎቅ ላይ á‹ļርም ተሰáŒĨá‰ļኝ የምኖር ነበርኩ፤ á‰Ĩሎክ 17 ነው " - የዩኒቨርሲቲው ተማáˆĒ

âžĄī¸ " በሰመáˆĢ ዩኒቨርሲቲ ይሄ ሁለተኛው ወይም áˆļáˆĩተኛው የáŠĨáˆŗá‰ĩ አደጋ ነው " - ዩኒቨርሲቲው

በሰመáˆĢ ዩኒቨርሲቲ á‰ĩላንá‰ĩ ምáˆŊá‰ĩ በተማáˆĒዎá‰Ŋ ማደáˆĒá‹Ģ á‰Ĩሎክ የተከሰተው ቃጠሎ ሰው ላይ áŒ‰á‹ŗá‰ĩ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆ‹á‹°áˆ¨áˆ°áŠ“ መሰል አደጋ ግን መደጋሙን ዩኒቨርሲቲውና ተማáˆĒዎá‰Ŋ ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ገልጸዋልáĸ

አንá‹ĩ ዩኒቨርሲቲው ተማáˆĒáŖ " አደጋው የተከሰተው ኤሌክá‰ĩáˆĒክ áŠŽáŠ•á‰ŗáŠ­á‰ĩ አá‹ĩርጎ ነውáĸ ከዚá‹Ģ 3ኛ ፎቅ ኮርኒሱ á‰Ŋቡá‹ĩ áˆĩለሆነ በቀላሉ ተá‹Ģá‹Ģዘáĸ በተማáˆĒዎá‰Ŋ ላይ የደረሰ áŒ‰á‹ŗá‰ĩ የለምáĸ áŠ áˆá‰Ŗáˆŗá‰ĩ ግን ተቃáŒĨለዋልáĸ አደጋው የተከሰተው በተማáˆĒዎá‰Ŋ á‹ļርም ነውáĸ áŠĨዛው የተቃጠለው á‰Ĩሎክ 2ኛ ፎቅ ላይ á‹ļርም ተሰáŒĨá‰ļኝ የምኖር ነበርኩ፤ á‰Ĩሎክ 17 ነው " á‰Ĩሏልáĸ

ዩኒቨርሲቲው ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ምን አለ ?

" áŠĨáˆŗá‰ą 3ኛ ፍሎር ላይ ነው á‹¨á‰°áŠáˆŗá‹áĸ áŠá‰ áˆá‰Ŗáˆ‰ áŠĨáˆĩáŠ¨á‰ŗá‰Ŋ የደረሰ ይመáˆĩላል áŠĨንጅ 1ኛና 2ኛ ፎቅ áŠĨáˆŗá‰ą áŒˆáˆ­áŽá‰ŗáˆ áŠĨንጅ áŠ áˆá‰°á‰€áŒŖáŒ áˆˆáˆ " ሲሉ የዩኒቨርሲቲው የህዝá‰Ĩ ግንኘነá‰ĩና ኮሚዩኒáŠŦáˆŊን á‹ŗá‹­áˆŦክተር አá‰ļ መሃመá‹ĩ አህመá‹ĩ ተናግረዋልáĸ

የáŠĨáˆŗá‰ĩ አደጋ ሰáˆĢተኞá‰Ŋና ተማáˆĒዎá‰Ŋ á‰Ŗá‹°áˆ¨áŒ‰á‰ĩ ርá‰Ĩርá‰Ĩ áŠĨáˆŗá‰ąáŠ• ማáŒĨፋá‰ĩ áŠĨንደተá‰ģለ áŒˆáˆáŒ¸á‹áŖ " áˆĻáˆĩተኛው ፎቅ ተማáˆĒዎá‰Ŋ áˆĩላልነበሩበá‰ĩ ዝግ ነው የነበረውáĸ áŠĨáˆŗá‰ĩ ገርፎá‰ĩ የተቃጠለ á‹¨áˆŗá‹áˆĒኮም ገመá‹ĩ አለ " á‰Ĩለዋልáĸ

" áŠĨáˆŗá‰ą ከላይ áˆĩለነበር á‹¨á‰°áŠáˆŗá‹ áŠ¨á‰ŗá‰Ŋ á‹Ģሉá‰ĩ áŠĨቃዎá‰Ŋ በመáˆĩኮá‰ĩ ጭምር አውáŒĨተዋልáĨ የደረሰ áŒ‰á‹ŗá‰ĩ የለምáĨ áŠ áŠ•á‹ŗáŠ•á‹ĩ áŒĢማም አንáˆļላም ረáˆĩá‰ģለሁ የሚል ተማáˆĒ áˆĩላለ ነው áŒ‰á‹ŗá‰ĩ ደረሰ የሚሉá‰ĩ " ነው á‹Ģሉá‰ĩáĸ

ቃጠሎ á‰ á‰°áŠáˆŗá‰ á‰ĩ á‰Ļá‰ŗ " ተማáˆĒዎá‰Ŋ ይኖሩ áŠĨንደነበር " áŠĨየገለጹ የተáˆĩተዋሉ áŠ áˆ‰áŖ áŠĨርáˆĩዎ ደግሞ በá‹ļርሙ ተማáˆĒ አልነበረበá‰ĩም አሉáĨ áŠĨንዴá‰ĩ ነው ነገሩ ? áˆĩንል ጠይቀናቸው በሰጡን ምላáˆŊáˆáŖ " áˆĻáˆĩተኛ ፎቅ የተዘጋ á‹ļርም áŠá‹áŖ ተማáˆĒ የለውምáĸ አንደኛና ሁለተኛ ፎቅ ግን ተማáˆĒዎá‰Ŋ ነበሩ ግን በአደጋው ወቅá‰ĩ ወáŒĨተዋል " á‰Ĩለዋልáĸ

የአደጋውን መንáˆĩኤ áˆĩáŠ•áŒ á‹­á‰ƒá‰¸á‹áˆáŖ " አደጋው áŠĨንዴá‰ĩ áŠĨáŠ•á‹°á‰°áŠáˆŗ ገና áŠ áŒŖáˆ­á‰°áŠ• ነው á‹¨áˆšá‰ŗá‹ˆá‰€á‹á¤ መንáˆĩኤውን የሚá‹ĢáŒŖáˆĢ ኮሚቴ ተቋቁሟልáĨ áˆˆáˆ›áŒŖáˆĢá‰ĩ ሁለá‰ĩ ቀናá‰ĩ ነው ተሰጠው፤ á‹¨áˆáŠ“áˆŗá‹ˆá‰… ይሆናል " ሲሉ ተናግረዋልáĸ

" በተለá‹Ģዩ ጊዜá‹Ģá‰ļá‰Ŋ የáŠĨáˆŗá‰ĩ አደጋ ተፈáŒĨሯልáĸ በሰመáˆĢ ዩኒቨርሲቲ ይሄ ሁለተኛው ወይም áˆļáˆĩተኛው የáŠĨáˆŗá‰ĩ አደጋ ነው፤ ሰኔ áŠĨና ግንá‰Ļá‰ĩ ወáˆĢá‰ĩ ላይ ከሙቀቱ ጋር ተá‹Ģይዞ ተማáˆĒዎቹም ፋንም áˆĩለሚጠቀሙ ገመá‹ļá‰Ŋ áŠĨየቀለጡ áŠĨáˆŗá‰ļá‰Ŋ ይፈጠሩ ነበር " ሲሉም አáˆĩá‰ŗá‹áˆ°á‹‹áˆáĸ

ለተጨማáˆĒ መረጃ ወደ ተማáˆĒዎá‰Ŋ ኀá‰Ĩረá‰ĩ áŒŊሕፈá‰ĩ ቤá‰ĩ ደውለን áˆĩልክ á‹Ģáˆá‰°áŠáˆŗ á‰ĸáˆ†áŠ•áˆáŖ የá‰Ĩሎኩ 2ኛ ፎቅ ነዋáˆĒ ተማáˆĒ áŠĨና የዩኒቨርሲቲው áˆ˜áˆáˆ…áˆ­áŖ áˆĻáˆĩተኛ ፎቅ ላይ ተማáˆĒ አልነበረውም ሲሉ ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ተናግረዋልáĸ

ቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ
አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤702đŸ˜ĸ75🙏25🕊20😭19👏6💔5😱4đŸĨ°3🤔1😡1
በወጋገን ይሸለሙ

ወጋገን á‰ŖáŠ•áŠ­ ከáŒĨቅምá‰ĩ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚá‹ĢáŠĢሂደው የáŒĨá‹Ģቄ áŠĨና መልáˆĩ ውá‹ĩá‹ĩር ጠቀም á‹Ģሉ áˆŊልማá‰ļá‰Ŋን ይዞልዎá‰ĩ መáŒĨቷል!

አሁኑኑ ከáˆĩር የተቀመጠውን á‹¨á‰ŖáŠ•áŠĢá‰Ŋንን የቴሌግáˆĢም á‰ģናል ማáˆĩፈንጠáˆĒá‹Ģ ተጭነው በመቀላቀል áŠĨና áŒĨá‹Ģቄዎá‰Ŋን ቀá‹ĩመው በመመለáˆĩ ተሸላሚ ይሁኑ፡፡

👉ቴሌግáˆĢም https://www.tg-me.com/WegagenBanksc

ልá‰Ĩ ይበሉ! ይፋዊ á‹¨á‰ŖáŠ•áŠĢá‰Ŋንን የቴሌግáˆĢም á‰ģናል በመቀላቀል áŠĨና ሌሎá‰Ŋም áŠĨንዲቀላቀሉ በመጋበዝ የáŒĨá‹Ģቄ áŠĨና መልáˆĩ ውá‹ĩá‹ĩሩን á‰ áˆ˜áˆŗá‰°á አሸናፊ ሲሆኑ ጠቀም á‹Ģሉ áˆŊልማá‰ļá‰Ŋን áŠ¨á‰ŖáŠ•áŠĢá‰Ŋን á‹Ģገኛሉáĸ

#WegagenBank #Question #Answer #Prize #Winner
❤83😡6😭3
" á‹ĢሰáˆĢጩá‰ĩ መረጃ ሀሰተኛ ነው " - ፖሊáˆĩ

የሙዚቃ áˆĩáˆĢዎá‰ģቸውን ለማቅረá‰Ĩ ወደ አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ የመጡá‰ĩ MAPARA A JAZZ á‹¨á‰°á‰Ŗáˆ‰áŠ“ የደቡá‰Ĩ አፍáˆĒáŠĢ ዜግነá‰ĩ á‹Ģላቸው ሁለá‰ĩ ግለሰá‰Ļá‰Ŋ" አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ ውáˆĩáŒĨ አፈናና á‹ĩá‰Ĩá‹°á‰Ŗ ተፈáŒŊሞá‰Ĩናል " á‰Ĩለው በፌáˆĩ ቡክ ገፃቸው á‹ĢሰáˆĢጩá‰ĩ መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ማረጋገጡን የአዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ ፖሊáˆĩ ጠቅላይ መምáˆĒá‹Ģ አáˆĩá‰ŗá‹ˆá‰€áĸ

የደቡá‰Ĩ አፍáˆĒáŠĢ ዜግነá‰ĩ á‹Ģላቸው Mapara A JAZZ á‹¨á‰°á‰Ŗáˆ‰á‰ĩ ወደ አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ መáŒĨተው ነበርáĸ ወደዚህ የመጡá‰ĩም የሙዚቃ áˆĩáˆĢቸውን ለማቅረá‰Ĩ ነበርáĸ

áŠĨነዚህ ግለሰá‰Ļá‰Ŋ áˆĩáˆĢቸውን ጨርሰው በሠላም ወደ ሀገáˆĢቸው ከተመለሱ በኋላ " አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ ውáˆĩáŒĨ አፈናና á‹ĩá‰Ĩá‹°á‰Ŗ ተፈፅሞá‰Ĩናል " á‰Ĩለው በፌáˆĩ ቡክ ገፃቸው á‹ĢሰáˆĢጩá‰ĩን መረጃ መሰረá‰ĩ በማá‹ĩረግ ፖሊáˆĩ ተገá‰ĸውን á‹¨áˆ›áŒŖáˆĢá‰ĩ á‰°áŒá‰Ŗáˆ­ áŠĨáŠ•á‹ŗáŠ¨áŠ“á‹ˆáŠ ገልáŒŋልáĸ

" ተፈፅሞá‰Ĩናል " áˆĩላሉá‰ĩ ወንጀል ለፖሊáˆĩ መረጃ ደርáˆļ áŠĨንደሆነ ለማረጋገáŒĨ በክፍለ ከተማ ፖሊáˆĩ መምáˆĒá‹Ģ áŠĨና በፖሊáˆĩ áŒŖá‰ĸá‹Ģዎá‰Ŋ ተጠይቆ ምንም ዓይነá‰ĩ የቀረበ áŠ á‰¤á‰ąá‰ŗ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆ‹áŒˆáŠ˜ áŠ áˆŗá‹á‰‹áˆáĸ

በፖሊáˆĩ ምርመáˆĢ á‹¨á‰°áˆ°á‰Ŗáˆ°á‰Ą á‹¨á‰°áŠ•á‰€áˆŗá‰ƒáˆŊ ምáˆĩáˆáŖ የፎá‰ļና የá‹ĩምáŒŊ ማáˆĩረጃዎá‰Ŋ áŠĨንዲሁም ከአዘጋጁ ቅሩንፉá‹ĩ áŠĸንተርቴይመንá‰ĩ ጭምር áŠĨንደተረጋገጠው ግለሠá‰Ļቹ ይህን የሀሠá‰ĩ መረጃ የለቀቁá‰ĩ á‰Ĩዙ á‰°áŠ¨á‰ŗá‹Žá‰Ŋን ለማግኘá‰ĩ ሆን á‰Ĩለው መሆኑን áŠĨáŠ•á‹ŗáˆ¨áŒ‹áŒˆáŒ  አመልክቷልáĸ

ግለሰá‰Ļቹ " አፈናና á‹ĩá‰Ĩá‹°á‰Ŗ ተፈáŒŊሞá‰Ĩናል " á‹Ģሉá‰ĩ አርá‰Ĩ áŒĨቅምá‰ĩ 14 ቀን 2018 ዓ/ም á‰ĸሆንም በማግáˆĩቱ áŒĨቅምá‰ĩ 15 በተጋበዙበá‰ĩ መá‹ĩረክ ላይ ተገኝተው የሙዚቃ áˆĩáˆĢቸውን ፍጹም ሠላማዊ በሆነ መንገá‹ĩ አቅርበው ማጠናቀቃቸው áŠĨና በሠላም ወደመጡበá‰ĩ ሀገር áˆ˜áˆ˜áˆˆáˆŗá‰¸á‹áŠ• ከáŠĸሚግáˆŦáˆŊንና ዜግነá‰ĩ አገልግሎá‰ĩ áŠĨንዲሁም ከአዘጋጆቹ መረጋገጡን áŠ áˆŗá‰‹áˆáĸ

á‹ĢሰáˆĢጩá‰ĩም መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ፖሊáˆĩ ገልáŒŋልáĸ

#AddisAbabPolice

@tikvahethiopia
❤909😡240🤔80đŸ˜ĸ17💔10😭9😱8🕊8đŸĨ°5🙏3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ወደ 1000 áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ከፓርኩ ወáŒĨተዋልáĸ ከዚá‹Ģ በኋላ ነው በምá‹Ģንማር መከላከá‹Ģ በá‹ĩሮን áŒĨቃá‰ĩ የደረሰው " - áŒ‰á‹ŗá‹Š á‹ĢáŒŖáˆŠ አáŠĢል

በ "KK áŠĢምፕ" በáŠĨáŒˆá‰ŗ የነበሩ ዜጎá‰Ŋ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ከወጡ በኋላ የምá‹Ģንማር መንግáˆĩá‰ĩ የá‹ĩሮን áŒĨቃá‰ĩ መፈጸሙን የáŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģኑ ቤተሰá‰Ļá‰Ŋና áŒ‰á‹ŗá‹ŠáŠ• á‹¨á‰°áŠ¨á‰ŗá‰°áˆ‰á‰ĩ አáŠĢል ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ገልጸዋልáĸ

áŠ áŠ•á‹ŗáŠ•á‹ļቹ የáŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģኑ ቤተሰá‰Ļá‰Ŋ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģኑ ላይ áŒ‰á‹ŗá‰ĩ ደርáˆļ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹­áˆ†áŠ• áˆĩጋá‰ĩ á‹Ģá‹°áˆ¨á‰Ŗá‰¸á‹ áˆ˛áˆ†áŠ•áŖ ሌሎቹ ደግሞ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģኑ áŒĨቃá‰ĩ ከደረሰበá‰ĩ áŠĢምፕ ወáŒĨተው ወደሌላ á‰Ļá‰ŗ ከተዘዋዘሩ በኋላ ነው áŒĨቃቱ የደረሰው á‰Ĩለዋልáĸ

የá‹ĩሮን áŒĨቃá‰ĩ ደረሰበá‰ĩ áŠ¨á‰°á‰Ŗáˆˆá‰ á‰ĩ áŠŦáŠŦ ከምፕ የቆየና á‹ĢáˆŗáˆˆááŠá‹ ረቡዕ ከዛ á‹¨á‹ˆáŒŖ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģዊ á‰ á‰ áŠŠáˆ‰áŖ በáŠŦáŠŦ áŠĢምፕና በሌሎá‰Ŋ አáŠĢá‰Ŗá‰ĸዎá‰Ŋ ሰሞኑን á‹¨áŠ¨á‰Ŗá‹ĩ áˆ˜áˆŗáˆĒá‹Ģ ተኩáˆĩ áŠĨንደነበረ ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ገልጸዋልáĸ

"áŠ áˆáŠ•áŖ በአንá‹ĩ áˆšáˆŠá‰ŗáˆĒ ውáˆĩáŒĨ 10 áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን አለንáĸ á‹Ģለንá‰ĩን á‰Ļá‰ŗ በáˆĩም አናውቀውምáĸ ግን ምá‹Ģንማር ውáˆĩáŒĨ ነውáĸ áŠĢምፕ ውáˆĩáŒĨ ተይዘው á‹Ģሉም አሉáĸ ወደ á‰ŗá‹­áˆ‹áŠ•á‹ĩ áˆˆáˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩ ተቸግረናል፤ በመንግáˆĩá‰ĩ ከከላ ውáˆĩáŒĨ áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩና ወደ ሀገáˆĢá‰Ŋን መመለáˆĩ áŠĨንፈልጋለን" ሲልም አክሎ ገልáŒŋልáĸ

áŒ‰á‹ŗá‹ŠáŠ• በá‰Ļá‰ŗá‹ áŠĢሉ ኤንጂáŠĻዎá‰Ŋ áŠ áŒŖáˆ­á‰ģለሁ á‹Ģሉ አንá‹ĩ መረጃ áŠ á‰€á‰Ŗá‹­ á‹°áŒáˆžáŖ በáŒĨቃቱ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģኑም ሆኑ የሌሎá‰Ŋ ሀገር ዜጎá‰Ŋ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆá‰°áŒŽá‹ą ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ተናግረዋልáĸ

" áŒĨቃቱ የተፈጸመው በáŠĢምፑ ውáˆĩáŒĨ የነበሩ ሰዎá‰Ŋ ከወጡ በኋላ ነውáĸ በá‹ĩሮን የፈáˆĢረሰው á‰ģይኖቹ የገነቡá‰ĩ á‰Ļá‰ŗ ነውáĸ አንá‹ĩም áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģዊ áŠ áˆá‰°áŒŽá‹ŗáˆá¤ የሌላም ሀገር ዜጋ áŠ áˆá‰°áŒŽá‹ŗáˆ " ነው á‹Ģሉá‰ĩáĸ

አáŠĢá‰Ŗá‰ĸው áŠĢይን áˆĩቴá‰ĩ áŠĨáŠ•á‹°áˆšá‰ŖáˆáŖ በዚሁ አáŠĢá‰Ŗá‰ĸ በአማáŒēዎá‰Ŋ á‰ áˆšá‰°á‹ŗá‹°áˆ¨á‹ áŠŦáŠŦ ፓርክ áŠ¨áˆŗáˆáŠ•á‰ĩ በፊá‰ĩ የማá‹Ģንማር መንግáˆĩá‰ĩ አáŠĢá‰Ŗá‰ĸውን ከአማáŒēዎቹ ለማáˆĩለቀቅ ወደ áŠĢይን ዘልቆ á‰ áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ą አማáŒēዎá‰Ŋ áŠŦáŠŦ ላይ ሲሰሊ የነበሩ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģንና ሌሎá‰Ŋ ዜጎá‰Ŋ ከá‰Ļá‰ŗá‹ áŠĨንዲወጡ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹°áˆ¨áŒ‰áŖ አá‰Ĩዛኛው áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģዊ ወደ ማይዋዲና አቅáˆĢá‰ĸá‹Ģ ከተሞá‰Ŋ áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩ áŠĨንደጀመሩ ተናግረዋልáĸ

á‰ á‹šáˆ…áˆáŖ "ወደ 1000 áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ከዚህ ፓርክ ወáŒĨተዋልáĸ የሌሎá‰Ŋ ሀገáˆĢá‰ĩ ዜጎá‰Ŋም ከዚሁ ፓርክ ወáŒĨተዋልáĸ ከዚá‹Ģ በኋላ ነው በምá‹Ģንማር መከላከá‹Ģ የá‹ĩሮን áŒĨቃá‰ĩ የደረሰው" ነው á‹Ģሉá‰ĩáĸ

ከáŠŦáŠŦ በመጀáˆĒá‹Ģ ዙር 97 áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ወደ ሜáŠĸáˆļá‰ĩáŖ ከሁለá‰ĩ ቀናá‰ĩ በፊá‰ĩ ደግሞ 250 áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ወደ á‰ŗá‹­áˆ‹áŠ•á‹ĩና ምá‹Ģንማር á‰Ļርደር በኤንጂáŠĻዎá‰Ŋና á‰ á‰ŗáˆ‹á‹­áˆ‹áŠ•á‹ĩ መንግáˆĩá‰ĩ áŠĨገዛ መሸጋገáˆĢቸውንም አáˆĩረá‹ĩተዋልáĸ

ቀáˆĒዎቹን የማáˆģገር áˆĨርም áŠĨየተሰáˆĢ መሆኑን áŒ á‰áˆ˜á‹áŖ " በተጨማáˆĒም 14 ልጆá‰ŊáŠ“áŖ 26 ልጆá‰Ŋ á‹Ģሉበá‰ĩ ፓርክ አለáĸ ልጆቹ አደጋ ላይ ናቸው፤ á‰Ĩዙዎቹ የአáŠĢልም የáˆĩነልá‰Ļናም áŒ‰á‹ŗá‰ĩ ደርáˆļá‰Ŗá‰¸á‹‹áˆ " ሲሉም ገልጸዋልáĸ

የáŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ የውጭ áŒ‰á‹ŗá‹­ ሚኒáˆĩቴር áˆˆáŠ’á‹á‹ŗá‹­áˆŠ áŠ áˆáˆŗá‹°áˆ­ ደá‰Ĩá‹ŗá‰¤ á‰ĸáŒŊááŖ á‹¨áŠ’á‹á‹ŗá‹­áˆŠ áŠ áˆá‰Ŗáˆŗá‹°áˆ­ ለምá‹Ģንማር መንግáˆĩá‰ĩ ለአማáŒēá‹Ģኑ ማáˆĩተላለፍ áˆĩለሚá‰ŊáˆáŖ 14ቱና 26ቱ ልጆá‰Ŋ በá‰ļሎ áˆ˜á‹áŒŖá‰ĩ áŠĨንደሚá‰Ŋሉ አáˆĩገንዘበዋልáĸ

በምá‹Ģንማር በአጋቾá‰Ŋ áŠĨጅ ወá‹ĩቀው ከነበሩá‰ĩ በርáŠĢá‰ŗ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን መáŠĢáŠĢል አሁንም በርáŠĢá‰ŗ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģውá‹Ģን ወደ ሀገáˆĢቸው á‹¨áˆšáˆ˜áˆáˆŗá‰¸á‹ á‰Ŗáˆˆáˆ›áŒáŠ˜á‰ŗá‰¸á‹ የደረሱልን ተማáŒŊኖ áŠĨá‹Ģሰሙ ይገኛሉáĸ

ቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ
አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤350😭101💔16🕊12😡11🙏7đŸ˜ĸ6🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Mynamar

የማይናማር áŒĻር á‰Ŗáˆˆáˆá‹ áˆŗáˆáŠ•á‰ĩ አáŠĢሄደው á‰ á‰°á‰Ŗáˆˆ áŠĻፕáˆŦáˆŊን ከ2,000 በላይ ሰዎá‰Ŋ ማሰሩ ተነገረáĸ

የማይናማር áŒĻር á‹¨á‰áˆ›áˆ­áŖ የáŠĻንላይን áˆ›áŒ­á‰Ŗáˆ­á‰ áˆĒá‹Ģ áŖ የገንዘá‰Ĩ áŠĨáŒĨበá‰ĩ ( Money Laundry) ማዕከል በሆነውና á‰ á‰ŗá‹­áˆ‹áŠ•á‹ĩ á‹ĩንበር አቅáˆĢá‰ĸá‹Ģ በሚገኘው áŠŦáŠŦ ፓርክ á‰ŖáŠĢሄደው ዘመá‰ģ 2,198 ሰዎá‰Ŋ áŠĨáŠ•á‹ŗáˆ°áˆ¨ ተነግሯልáĸ

በወቅቱም የኤሌክá‰ĩáˆĒክ ኃይል ተቋርáŒĻ áŠĨáŠ•áŠŗáŠ• áŠĢምፑ ውáˆĩáŒĨ áŠĸንተርኔá‰ĩ áŠĨáŠ•á‹ŗá‹­á‰‹áˆ¨áŒĨ ለማá‹ĩረግ áŒĨቅም ላይ ሲውሉ የነበሩ 30 የáˆĩá‰ŗáˆ­áˆŠáŠ•áŠ­ የáŠĸንተርኔá‰ĩ áˆŗá‰°áˆ‹á‹­á‰ļá‰Ŋ ተይዘዋልáĸ

ምንም áŠĨáŠ•áŠŗáŠ• á‹œáŒáŠá‰ŗá‰¸á‹ በይፋ á‰Ŗá‹­áŒˆáˆˆáŒŊም áŒĻሊ ወንá‹ļá‰Ŋን áŖ ሴá‰ļá‰Ŋን áŖ áŠĢምፑን የሚጠá‰Ĩቁ አáŠĢላá‰ĩን አáˆĩሯልáĸ

áŠŦáŠŦ ፓርክ የሚገኝበá‰ĩ áŠĢይን áˆĩቴá‰ĩ የማይናማር áŒĻር áŖ በá‰Ĩሄር የተደáˆĢጁ á‰ŗáŒŖá‰‚á‹Žá‰Ŋ áŠĨና የተቃዋሚው ፒፕልáˆĩ ዲፌንáˆĩ ፎርáˆĩ የሚፋለሙበá‰ĩ ቀጠና ነውáĸ

በሌላ በኩል፤ አሁንም ልጆá‰ģቸው ከማይናማር ወደ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ á‹Ģልተመለሱላቸው ወላጆá‰Ŋ ልጆá‰ģቸው ሰሞኑን ከፍተኛ á‰Ŋግር ላይ áŠĨንደወደቁ ተናግረው የáŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ መንግáˆĨá‰ĩ áŠ á‹áŒŖáŠ መፍá‰ĩሄ áŠĨንዲፈልግላቸውና áŠĨáŠ•á‹˛áˆ˜áˆáˆŗá‰¸á‹ ተማፅነዋልáĸ

" አሁንም ልጆá‰ģá‰Ŋን ማይናማር ናቸውáĸ ከዚህ ቀደም በተሰáˆĢው áˆĩáˆĢ á‰Ĩዙ ልጆá‰Ŋ መáŒĨተዋል አሁንም á‰ĩኩረá‰ĩ ተደርጎ ከዚህ ቀጠና ልጆá‰ģá‰Ŋን áŠĨንዲመለሱ á‰ĩá‰Ĩá‰Ĩር ይደረግልን " ሲሉ በቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ በኩል áŒĨáˆĒ አቅርበዋልáĸ

የፎá‰ļ መግለáŒĢ áĻ áŠŦáŠŦ ፓርክ áŠĨንዲሁም የማይናማር áŒĻር የá‹Ģዛቸው የáˆĩá‰ŗáˆ­áˆŠáŠ•áŠ­ የáŠĸንተርኔá‰ĩ ማáˆŊኖá‰Ŋ (በáŠĢምፑ ውáˆĩáŒĨ ኃይል á‰ĸቋረáŒĨ áŠĨáŠ•áŠŗáŠ• áŠĸንተርኔá‰ĩ አይቋረáŒĨም ነበር)

ቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ
#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
❤251😭37💔11👏6🕊5😡5🤔2đŸ˜ĸ1
" አáˆĩከáˆŦኑ የተገኘው አንá‹ĩ ቀን አá‹ĩሎ ነውáĸ áŠ¨á‰Ŗáˆ•áˆ­ á‹ŗáˆ­ የተáˆģሉ ዋናተኞá‰Ŋ መáŒĨተው ነው ከከፍተኛ á‹ĩáŠĢም በኋላ á‹Ģወጡá‰ĩ" - áŠĨáŠ•áŒ…á‰ŖáˆĢ ዩኒቨርሲቲ

የሁለተኛ ዓመá‰ĩ á‹¨áˆŗá‹­áŠĢá‰ĩáˆĒ ተማáˆĒ የሆነው አማኑኤል áŠĨáŠ•á‹ŗá‹ˆá‰€ ለዋና á‰ áŒˆá‰Ŗá‰ á‰ĩ ወንዝ ሰáŒĨሞ ሕይወቱ ማለፉን áŠĨáŠ•áŒ…á‰ŖáˆĢ ዩኒቨርሲቲ ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ገልáŒŋልáĸ

áˆˆáŒ‰á‹ŗá‹Š ማá‰ĨáˆĢáˆĒá‹Ģ የጠየቅነው የዩኒቨርሲቲው የተማáˆĒዎá‰Ŋ ኅá‰Ĩረá‰ĩ ፕáˆŦá‹á‹ŗáŠ•á‰ĩ áŒŒá‰ŗáŠáˆ… áˆŊፈáˆĢá‹áŖ አደጋው áŠĨሁá‹ĩ 3 ሰዓá‰ĩ ገደማ መá‹ĩረሱን ገልáŒŋልáĸ

" ከጓደኞቹ ጋር ከዩኒቨርሲቲው በቅርá‰Ĩ ርቀá‰ĩ የሚገኝ á‰Ļá‰ŗ ሂá‹ļ ነው አዩ á‹¨áˆšá‰Ŗáˆ ወንዝ ለዋና የገቡá‰ĩ፤ ጓደኞቹ የዚሁ የከተማ ልጆá‰Ŋ ናቸው፤ ዋና ላይ á‰Ŗáˆ‰á‰ á‰ĩ ነው የሰጠመው " á‰Ĩሏልáĸ

የተማáˆĒ አማኑኤል የቀá‰Ĩር áˆĩርዓá‰ĩ ዛáˆŦ ከቀኑ 9 ሰዓá‰ĩ ተኩል ገደማ ተወልá‹ļ á‰Ŗá‹°áŒˆá‰ á‰ĩ በáŠĨáŠ•áŒ…á‰ŖáˆĢ ከተማ መፈጸሙን ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ አረጋግጧልáĸ

" ከሰጠመ በኋላ መረጃው ሲደርሰን፤ ዩኒቨርሲቲው áŠĨና ማኀበረሰቡ በጋáˆĢ አáˆĩከáˆŦኑን áˆˆáˆ›á‹áŒŖá‰ĩ ሙከáˆĢ á‰ĸደረግም áŠ áˆá‰°áˆŗáŠĢም በáŠĨለቱ ሊገኝ አልá‰ģለም " á‹Ģለው የተማáˆĒዎá‰Ŋ ኅá‰Ĩረá‰ĩ ፕáˆŦá‹šá‹ŗáŠ•á‰ą áŖ " ዛáˆŦ á‰Ŗáˆˆáˆ™á‹Ģዎá‰Ŋ áŠ¨á‰Ŗáˆ•áˆ­ á‹ŗáˆ­ መáŒĨተው አáˆĩከáˆŦኑን áˆ›á‹áŒŖá‰ĩ á‰Ŋለዋል " ሲል ገልáŒŋልáĸ

" አáˆĩከáˆŦኑ የተገኘው አንá‹ĩ ቀን አá‹ĩሎ ነው፤ ቀኑን ሙሉ ሊገኝ አልá‰ģለም ነበር፤ ዋናተኞá‰Ŋ á‹­áŒˆá‰Ŗáˆ‰ ግን ጉá‹ĩጓá‹ĩ አይነá‰ĩ áˆĩለሆነ ይዋኙበá‰ĩ የነበረው á‰Ļá‰ŗ áˆ˜á‹áŒŖá‰ĩ አልá‰Ŋል ሲል áŠ¨á‰Ŗáˆ•áˆ­ á‹ŗáˆ­ የተáˆģሉ ዋናተኞá‰Ŋ መáŒĨተው ከከፍተኛ á‹ĩáŠĢም በኋላ ነው á‹Ģወጡá‰ĩ " á‰Ĩሏልáĸ

" ሌሎá‰Ŋ ልጆá‰Ŋም የመሞá‰ĩ አደጋ ይደርáˆĩá‰Ŗá‰¸á‹ ነበር፤ በá‰ļሎ ሀáŠĒም ቤá‰ĩ ተወáˆĩደው ነው á‹Ģሉá‰ĩ አá‰Ĩረው ሲዋኙ የነበሩá‰ĩ " á‰ĨáˆŽáŖ " አáˆĩቸጋáˆĒ ነው á‰Ļá‰ŗá‹ áˆĢáˆąáŖ ለመዋኘá‰ĩ የገቡበá‰ĩ á‰Ļá‰ŗ áˆĢሹ áŒĨሊ አልነበረም " ሲል ገልáŒŋልáĸ

" áŠĨሱንም áˆˆáˆ›á‹áŒŖá‰ĩ áŠĨየሞከሩ áˆĩለነበረ ውሃ ወደ ውáˆĩáŒŖá‰¸á‹ á‹¨áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩ ነገር áˆĩለሚኖር ወደ ሀáŠĒም ቤá‰ĩ ሂደው áŠĨንደነበር መረጃው አለኝ " ሲል ለቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ ተናግሯልáĸ

" ተማáˆĒዎá‰Ŋ በማá‹Ģውቁá‰ĩ á‰Ļá‰ŗ ሲኖሩ በáŠĨንዲህ አይነá‰ĩ ወንዝ ውáˆĩáŒĨ áŠ¨áˆ˜áŒá‰Ŗá‰ĩ á‰ĸá‰ŗá‰€á‰ĄáŖ áˆĢቅ á‹Ģለ á‰Ļá‰ŗ ሲሄዱ á‹¨áˆ˜á‰ŗáŒˆá‰ĩ áˆáŠ”á‰ŗáˆ ሊá‹ĢጋáŒĨም áˆĩለሚá‰Ŋል በተá‰ģለ አቅም በግá‰ĸው ውáˆĩáŒĨ á‰ĸዝናኑ መልáŠĢም ነው " ሲል መክረዋልáĸ

áŠĨáŠ•áŒ…á‰ŖáˆĢ ዩኒቨርሲቲ ተማáˆĒá‹áŖ በአዮ ወንዝ ለመዋኘá‰ĩ በሄደበá‰ĩ በደረሰበá‰ĩ የመáˆĩጠም አደጋ ህይወቱ ማለፉን በማኀበáˆĢዊ á‰ĩáˆĩáˆĩር ገጹ በመግለáŒŊáŖ ለቤተሰá‰Ĩ መáŒŊናናá‰ĩን ተመኝቷልáĸ

ቲክá‰Ģህ áŠĸá‰ĩዮáŒĩá‹Ģ
አዲáˆĩ áŠ á‰ á‰Ŗ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭853❤412💔91đŸ˜ĸ37🕊37🙏10😱9đŸĨ°6
2025/10/28 02:02:41
Back to Top
HTML Embed Code: