#AddisAbaba
የጉልበት ብዝበዛ ወንጀል ሲፈፀምባቸው የነበሩ 18 ህፃናትና ታዳጊዎችን ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ' ኦ አቤም ሆቴል ' ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ የሰባት ዓመት ታዳጊ በመንገድ ላይ እያለቀሰ ሳለ ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠየቅ ለስራ የተሰጠው ሚዛን እንደጠፋበትና አሰሪዎቹም ቤት እንደማያስገቡት ይናገራል።
ፖሊስ መከታዳጊው የተቀበለውን መረጃ መነሻ በማድረግና ክትትል በማከናወን በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ቦታው ' ቻይና ካምፕ ' አካባቢ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ዕድሜያቸው ከ7 እስከ 13 ዓመት የሆኑ 18 ህፃናትና ታዳጊዎችን ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ሊያውል እንደቻለ ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ እነዚህኑ ህፃናትና ታዳጊዎች ክልል ድረስ በመሄድ ከቤተሰቦቻቸው ላይ " እናስተምራቸዋለን " ብለው በማምጣት ፦
- ቆሎ፣
- ሶፍት
- ሚዛን በማሰራት ከእያንዳንዳቸው በቀን ከ150 እስከ 300 ብር ገቢ እንዲያስገቡ ከማድረጋቸው በላይ የወንጀል አፈጻጸሞችን (የመኪና ስፖኪዮ አነቃቀል) ያስተምሯቸው እንደነበር አመልክቷል።
በግለሰቦቹ ላይ ተገቢው ምርመራ እየተደረገ ሲሆን በዐ/ህግም በኩል ክስ እንደተመሠረተባቸው ፖሊስ አስታውቋል፡፡
" ሕፃናትን ለእድሜያቸው በማይመጥን የጤና፣ የእድገት፣ የማኅበራዊና ስነ-ልቦናዊ ደህንነታቸውን የሚጎዳና ለህይወታቸው አስጊ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሰሩ ማድረግ የህግ ተጠያቂነት የሚያስከትል ተግባር ነው " ብሏል።
ህብረተሰቡ መሰል ድርጊቶች ሲያጋጥሙት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ተቋም መረጃ በመስጠት በህፃናት ላይ የሚደርስ የጉልበት ብዝበዛን መከላከል ይገባል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
የጉልበት ብዝበዛ ወንጀል ሲፈፀምባቸው የነበሩ 18 ህፃናትና ታዳጊዎችን ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ' ኦ አቤም ሆቴል ' ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ የሰባት ዓመት ታዳጊ በመንገድ ላይ እያለቀሰ ሳለ ለምን እንደሚያለቅስ ሲጠየቅ ለስራ የተሰጠው ሚዛን እንደጠፋበትና አሰሪዎቹም ቤት እንደማያስገቡት ይናገራል።
ፖሊስ መከታዳጊው የተቀበለውን መረጃ መነሻ በማድረግና ክትትል በማከናወን በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ቦታው ' ቻይና ካምፕ ' አካባቢ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ዕድሜያቸው ከ7 እስከ 13 ዓመት የሆኑ 18 ህፃናትና ታዳጊዎችን ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ሊያውል እንደቻለ ገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ እነዚህኑ ህፃናትና ታዳጊዎች ክልል ድረስ በመሄድ ከቤተሰቦቻቸው ላይ " እናስተምራቸዋለን " ብለው በማምጣት ፦
- ቆሎ፣
- ሶፍት
- ሚዛን በማሰራት ከእያንዳንዳቸው በቀን ከ150 እስከ 300 ብር ገቢ እንዲያስገቡ ከማድረጋቸው በላይ የወንጀል አፈጻጸሞችን (የመኪና ስፖኪዮ አነቃቀል) ያስተምሯቸው እንደነበር አመልክቷል።
በግለሰቦቹ ላይ ተገቢው ምርመራ እየተደረገ ሲሆን በዐ/ህግም በኩል ክስ እንደተመሠረተባቸው ፖሊስ አስታውቋል፡፡
" ሕፃናትን ለእድሜያቸው በማይመጥን የጤና፣ የእድገት፣ የማኅበራዊና ስነ-ልቦናዊ ደህንነታቸውን የሚጎዳና ለህይወታቸው አስጊ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሰሩ ማድረግ የህግ ተጠያቂነት የሚያስከትል ተግባር ነው " ብሏል።
ህብረተሰቡ መሰል ድርጊቶች ሲያጋጥሙት በአቅራቢያው ለሚገኝ የፀጥታ ተቋም መረጃ በመስጠት በህፃናት ላይ የሚደርስ የጉልበት ብዝበዛን መከላከል ይገባል ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
❤837😢157👏88😭48💔47🙏34😡20🤔10🕊9😱7🥰4
#Mekelle #Airport
" ከወትሮ የተለየ ምንም አዲስ ነገር የለም፤ የፈጠራ ወሬ ነው " - የኤርፖርት ኃላፊዎች
በትግራይ፣ መቐለ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት ወጣቶች ከመቐለ እንዳይወጡ የተለየ ክልከላ እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጩት መረጃዎች ውሸት እንደሆኑ ተጓዦች እና የኤርፖርቱ ኃላፊዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በማህበራዊ ሚዲያው ላይ " በመቐለ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት ክልከላ እንዳለ ፤ የትግራይ የፀጥታ አካላት ውጭ እና ኤርፖርት ቁጥጥር እያደረጉ እንደሆነ፤ ሁኔታው ለጦርነት ምልመላ እንደሆነ በዚህም ወጣቱ ተስፋ እንደቆረጠ " የሚገልጹ መረጃዎች በስፋት ተሰራጭተዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባልም የሚወራውን ለማረጋገጥ በአካል ቅኝት አድርጓል ፤ የኤርፖርት ኃላፊዎችንም አግኝቶ አነጋግሯል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ተጓዦች ምንም አዲስ ነገር እንደሌለ ክልከላ የሚባለውም እንዳልገጠማቸው ገልጸዋል።
ትኬት ቢሮ ድረስ ሄደን ያነጋገራቸው ተገልጋዮችም ምንም አይነት ክልከላ እንዳልገጠማቸው በአግባቡ እየተስተናገዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
እንዲሁም ወደ አየር መንገዱ ተጓዦች የሚያጓጓዙ የታክሲ ሹፌሮችም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ስራቸውን በአግባቡ እየሰሩ እንደሆነ ፤ ተጓዦች ላይ የተጣለ ክልከላ እንደሌለ አመልክተዋል።
መንገድ ላይ ሆነ በአውሮፕላን ማረፍያው ዙሪያ የተለየ ፍተሻና የታጣቂዎች እንቅስቃሴ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ተዘዋውሮ በተመለከተበት ወቅትም ምንም የተለየ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ ፣ ፍተሻ ሆነ ክልከላ የለም።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሁለት የኤርፖርት ኃላፊዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ከወትሮው የተለይ ምንም አዲስ ነገር የለም ፤ የፈጠራ ወሬ ነው እየተሰራጨ ያለው " ብለዋል።
በኤርፓርት ዙሪያና ውስጥ ከፌደራል ፓሊስና ኢንተለጀንስ ውጪ ምንም የትግራይ ፓሊስና ታጣቂ እንደሌለ ፤ ለታጠቀ አካል ወደ ኤርፖርት መግባትም እንደማይፈቀድ ለመረዳት ችለናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ከወትሮ የተለየ ምንም አዲስ ነገር የለም፤ የፈጠራ ወሬ ነው " - የኤርፖርት ኃላፊዎች
በትግራይ፣ መቐለ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት ወጣቶች ከመቐለ እንዳይወጡ የተለየ ክልከላ እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጩት መረጃዎች ውሸት እንደሆኑ ተጓዦች እና የኤርፖርቱ ኃላፊዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በማህበራዊ ሚዲያው ላይ " በመቐለ አሉላ አባነጋ ኤርፖርት ክልከላ እንዳለ ፤ የትግራይ የፀጥታ አካላት ውጭ እና ኤርፖርት ቁጥጥር እያደረጉ እንደሆነ፤ ሁኔታው ለጦርነት ምልመላ እንደሆነ በዚህም ወጣቱ ተስፋ እንደቆረጠ " የሚገልጹ መረጃዎች በስፋት ተሰራጭተዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባልም የሚወራውን ለማረጋገጥ በአካል ቅኝት አድርጓል ፤ የኤርፖርት ኃላፊዎችንም አግኝቶ አነጋግሯል።
ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ተጓዦች ምንም አዲስ ነገር እንደሌለ ክልከላ የሚባለውም እንዳልገጠማቸው ገልጸዋል።
ትኬት ቢሮ ድረስ ሄደን ያነጋገራቸው ተገልጋዮችም ምንም አይነት ክልከላ እንዳልገጠማቸው በአግባቡ እየተስተናገዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
እንዲሁም ወደ አየር መንገዱ ተጓዦች የሚያጓጓዙ የታክሲ ሹፌሮችም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ስራቸውን በአግባቡ እየሰሩ እንደሆነ ፤ ተጓዦች ላይ የተጣለ ክልከላ እንደሌለ አመልክተዋል።
መንገድ ላይ ሆነ በአውሮፕላን ማረፍያው ዙሪያ የተለየ ፍተሻና የታጣቂዎች እንቅስቃሴ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ተዘዋውሮ በተመለከተበት ወቅትም ምንም የተለየ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ ፣ ፍተሻ ሆነ ክልከላ የለም።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ሁለት የኤርፖርት ኃላፊዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " ከወትሮው የተለይ ምንም አዲስ ነገር የለም ፤ የፈጠራ ወሬ ነው እየተሰራጨ ያለው " ብለዋል።
በኤርፓርት ዙሪያና ውስጥ ከፌደራል ፓሊስና ኢንተለጀንስ ውጪ ምንም የትግራይ ፓሊስና ታጣቂ እንደሌለ ፤ ለታጠቀ አካል ወደ ኤርፖርት መግባትም እንደማይፈቀድ ለመረዳት ችለናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤465🙏41🕊24😢14🤔8🥰5👏5😡2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ምን ያህል ተማሪዎች በማካካሻ ትምህርት (ሬሜዲያል ፕሮግራም) ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ ?
🎓 ከ82 ሺህ በላይ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይገባሉ !
በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ከ82 ሺሕ በላይ ተፈታኞች በማካካሻ (በሪሜዲያል) መርሐ ግብር ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ " በ2018 የትምህርት ዘመን 82,838 ተፈታኞች የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ " ሲሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል።
በግል ሆነ በመንግሥት ተቋማት ውስጥ የሪሜዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚችሉት፣ እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ናቸው።
ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖላቸው የሬሜዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ የሚያሟሉ ብቻም ይሆናሉ።
የመቁረጫ ነጥብ ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204
➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
ትምህርት ሚኒስቴር ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም እንደሚኖር ነገር ግን ወደፊት የማስቀጠል ሀሳብ እንደሌለና ቀስ እያለ እንደሚቆም ማሳወቁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ከ82 ሺሕ በላይ ተፈታኞች በማካካሻ (በሪሜዲያል) መርሐ ግብር ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ " በ2018 የትምህርት ዘመን 82,838 ተፈታኞች የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ " ሲሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል።
በግል ሆነ በመንግሥት ተቋማት ውስጥ የሪሜዲያል ፕሮግራም መከታተል የሚችሉት፣ እንደተፈተኑት የትምህርት ዓይነት ብዛት 33 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ናቸው።
ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖላቸው የሬሜዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥብ የሚያሟሉ ብቻም ይሆናሉ።
የመቁረጫ ነጥብ ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204
➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
ትምህርት ሚኒስቴር ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም እንደሚኖር ነገር ግን ወደፊት የማስቀጠል ሀሳብ እንደሌለና ቀስ እያለ እንደሚቆም ማሳወቁ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤430😭24🕊15🥰14😡14👏8🙏8😱7😢2
TIKVAH-ETHIOPIA
ምን ያህል ተማሪዎች በማካካሻ ትምህርት (ሬሜዲያል ፕሮግራም) ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ይገባሉ ? 🎓 ከ82 ሺህ በላይ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይገባሉ ! በ2018 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ከ82 ሺሕ በላይ ተፈታኞች በማካካሻ (በሪሜዲያል) መርሐ ግብር ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ልማት…
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ።
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ፦
➡️ በዌብሳይት፦ https://student.ethernet.edu.et
➡️ በቴሌግራም ቦት @moestudentbot ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ገልጿል።
የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
#MoE
@tikvahethiopia
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ፦
➡️ በዌብሳይት፦ https://student.ethernet.edu.et
➡️ በቴሌግራም ቦት @moestudentbot ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ገልጿል።
የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
#MoE
@tikvahethiopia
❤748👏76😭63😡33🕊28🙏25🥰23😢22😱9
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) ዛሬ ይፋ ሆኗል። @tikvahethiopia
1❤1.24K👏170🤔90😡71🙏47😭32😢29🥰28🕊20💔14😱12
" ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " - የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት የሚያስችል አዲስ የተሽከርካሪዎች የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አይነቶችና ምልክቶች መወሰኛና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ማውጣቱ ይታወቃል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መመሪያውን አዘጋጅቶ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ እንደሚሰራ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
በአገልግሎት ላይ ያለውን ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ስሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት ካስፈለገበት ምክንያቶች ውስጥ ቀደም ሲል የነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ስሌዳ አመራረትና አሰረጫጨት የአሰራር ክፍተት እና የሃብት ብክነት ሲስተዋልበት የቆየ በመሆኑ ያንን ለመቅረፍ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ነው ተብሏል።
አሽከርካሪዎች እየተጠቀሙበት የሚገኘው በስራ ላይ ያለው ታርጋ ከ1994 ዓም በኋላ ምንም አይነት ማሻሻያ ሳይደረግበት የቆየ ነው።
አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ፥ " ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " ብለዋል።
" ከእዚህ ቀደም የነበረው ታርጋ 9 ሚሊየን መኪኖችን ብቻ መዝግቦ የሚያበቃ ውስን ታርጋ ነበር እስካሁን ባለው መረጃም 1.6 ሚሊየን የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች ተመዝግበዋል የአሁኑ ታርጋ ግን 121 ሚሊየን ታርጋዎችን መመዝገብ ያስችልናል " ሲሉም አክለዋል።
ሁለት ሚሊየን የሚሆን የተሽከርካሪ ታርጋ ለማሳተም በእቅድ ተይዞ የመጀመሪያ 50 ሺ የተታተመ ታርጋ ወደ ሃገር ስለመግባቱ የተናገሩት ሚኒስትሩ " ታርጋውን አድሎ ስራ ላይ ለማዋል የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
ስርአቱን ከሚዘረጋው አካል ጋር እየተነጋገሩ እና በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ድርድር እየተካሄደ መሆኑን አክለው በ 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ ይሰራል ተብሎ መታቀዱን ገልጸዋል።
አዲሱ ታርጋ ቅየራ ስለሚከናወንበት ጊዜም " መሰራት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች መሰራት ስላለባቸው አዲሱ ታርጋ ቅየራ አልተጀመረም ከሁለት ወር ባጠረ ጊዜ አዲሱን ታርጋ መቀየር እንጀምራለን በያዝነው 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ አዲሱን ታርጋ ቀይረን እንጨርሳለን " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ሰሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት የሚያስችል አዲስ የተሽከርካሪዎች የመለያ ቁጥር ሰሌዳ አይነቶችና ምልክቶች መወሰኛና የአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 1050/2017 ማውጣቱ ይታወቃል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መመሪያውን አዘጋጅቶ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ እንደሚሰራ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
በአገልግሎት ላይ ያለውን ነባሩን የተሽከርካሪ መለያ ስሌዳ ቁጥር በአዲስ ለመተካት ካስፈለገበት ምክንያቶች ውስጥ ቀደም ሲል የነበረው የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር ስሌዳ አመራረትና አሰረጫጨት የአሰራር ክፍተት እና የሃብት ብክነት ሲስተዋልበት የቆየ በመሆኑ ያንን ለመቅረፍ የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ነው ተብሏል።
አሽከርካሪዎች እየተጠቀሙበት የሚገኘው በስራ ላይ ያለው ታርጋ ከ1994 ዓም በኋላ ምንም አይነት ማሻሻያ ሳይደረግበት የቆየ ነው።
አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ፥ " ነባሩ ታርጋ በአዲስ በሚቀየርበት ወቅት የሰሌዳ ማስቀየር ስራው የሚጠይቀውን ሁሉንም ወጪ የመኪናው ባለንብረት ይሸፍናል " ብለዋል።
" ከእዚህ ቀደም የነበረው ታርጋ 9 ሚሊየን መኪኖችን ብቻ መዝግቦ የሚያበቃ ውስን ታርጋ ነበር እስካሁን ባለው መረጃም 1.6 ሚሊየን የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች ተመዝግበዋል የአሁኑ ታርጋ ግን 121 ሚሊየን ታርጋዎችን መመዝገብ ያስችልናል " ሲሉም አክለዋል።
ሁለት ሚሊየን የሚሆን የተሽከርካሪ ታርጋ ለማሳተም በእቅድ ተይዞ የመጀመሪያ 50 ሺ የተታተመ ታርጋ ወደ ሃገር ስለመግባቱ የተናገሩት ሚኒስትሩ " ታርጋውን አድሎ ስራ ላይ ለማዋል የዲጂታል ስርዓት መዘርጋት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
ስርአቱን ከሚዘረጋው አካል ጋር እየተነጋገሩ እና በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ ድርድር እየተካሄደ መሆኑን አክለው በ 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ ተሽከርካሪዎችን በአዲስ ታርጋ የመቀየር ስራ ይሰራል ተብሎ መታቀዱን ገልጸዋል።
አዲሱ ታርጋ ቅየራ ስለሚከናወንበት ጊዜም " መሰራት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች መሰራት ስላለባቸው አዲሱ ታርጋ ቅየራ አልተጀመረም ከሁለት ወር ባጠረ ጊዜ አዲሱን ታርጋ መቀየር እንጀምራለን በያዝነው 2018 ዓም ሙሉ በሙሉ አዲሱን ታርጋ ቀይረን እንጨርሳለን " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.2K😡1.19K👏99😭43🤔35😢22💔21🕊20🙏17🥰13😱5
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
አዲሱ የተሽከርካሪ መለያ ቁጥር (ታርጋ) አይነቶች እና ምልክቶች ምን ይመስላሉ ?
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ - Tikvah Ethiopia)
➡️ የአገልግሎት አይነቱ ታክሲ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው እና ታክሲ የሚል ጽሑፍ ይጻፍበታል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የቤት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር አይለጥፉም።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የንግድ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር ነጭ መደብ አረንጓዴ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ ይለጥፋል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የመንግስት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር የመንግስት ተቋሙ ስም እና አርማ ያለው ይሆናል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እና 5 ቁጥር የተጻፈበት ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ ብርቱካናማ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የማህበሩ ስም እና አርማ ይጻፍበታል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ አለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እንዲሁም የተቋሙ ስም ምሕጻረ ቃል በአማርኛ እና በላቲን ይጻፍበታል።
ስቲከሩ የተቋሙ ስም እና አርማ ያለው ይሆናል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እና 35 ቁጥር ፣"ዕድ" "AO" የሚል ይጻፍበታል።
የዲፕሎማቲክ መብት ላላቸው ደግሞ ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የተቋሙ ስም ምሕጻረ ቃል "CD" በላቲን እናብ"ኮዲ" የሚል በአማርኛ የተጻፈበት ይሆናል።
የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች እና ዲፕሎማቲክ መብት ያላቸው ተቋማት ስቲከራቸው የተቋሙ ስም እና አርማ ያለበት ይሆናል።
➡️ በኤሌክትሪክ ወይም በታዳሽ ሃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከሩ መደቡ በነጭ ሆኖ ጽሑፉ አረንጓዴ ቀለም የሆነ አረንጓዴ ትራንስ ፖርት (GreenTransport) የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ የአካል ጉዳተኞች ከሆኑ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከሩ የዊልቸር ምልክት እና "አጉ" "PD" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ ባለሞተር ብስክሌት
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከር አይኖራቸውም።
➡️ ልዩ ተንቀሳቃሽ መሳሪያዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው እና "ልተመ" "SME" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
ልዩ ተንቀሳቃሽ መሳሪያዎች ስቲከር አይለጥፉም
➡️ ተሳቢ ተሽከርካሪዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH"፣ " ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው እንዲሁም "ተሳቢ" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ አረንጓዴ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ የተላላፊ ሰሌዳ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር ሆኖ፣ በግራ ክንፍ በኩል "ተላላፊ" የሚል ጽሑፍ ይኖረዋል ።
ስቲከር አይኖራቸውም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ - Tikvah Ethiopia)
➡️ የአገልግሎት አይነቱ ታክሲ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው እና ታክሲ የሚል ጽሑፍ ይጻፍበታል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የቤት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር አይለጥፉም።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የንግድ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር ነጭ መደብ አረንጓዴ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው ላይ ይለጥፋል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የመንግስት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው ይሆናል።
ስቲከር የመንግስት ተቋሙ ስም እና አርማ ያለው ይሆናል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እና 5 ቁጥር የተጻፈበት ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ ብርቱካናማ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የማህበሩ ስም እና አርማ ይጻፍበታል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ አለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እንዲሁም የተቋሙ ስም ምሕጻረ ቃል በአማርኛ እና በላቲን ይጻፍበታል።
ስቲከሩ የተቋሙ ስም እና አርማ ያለው ይሆናል።
➡️ የአገልግሎት አይነቱ የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ከሆነ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት እና 35 ቁጥር ፣"ዕድ" "AO" የሚል ይጻፍበታል።
የዲፕሎማቲክ መብት ላላቸው ደግሞ ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የተቋሙ ስም ምሕጻረ ቃል "CD" በላቲን እናብ"ኮዲ" የሚል በአማርኛ የተጻፈበት ይሆናል።
የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች እና ዲፕሎማቲክ መብት ያላቸው ተቋማት ስቲከራቸው የተቋሙ ስም እና አርማ ያለበት ይሆናል።
➡️ በኤሌክትሪክ ወይም በታዳሽ ሃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከሩ መደቡ በነጭ ሆኖ ጽሑፉ አረንጓዴ ቀለም የሆነ አረንጓዴ ትራንስ ፖርት (GreenTransport) የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ የአካል ጉዳተኞች ከሆኑ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከሩ የዊልቸር ምልክት እና "አጉ" "PD" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ ባለሞተር ብስክሌት
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው።
ስቲከር አይኖራቸውም።
➡️ ልዩ ተንቀሳቃሽ መሳሪያዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከቀይ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH" ፣ "ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው እና "ልተመ" "SME" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
ልዩ ተንቀሳቃሽ መሳሪያዎች ስቲከር አይለጥፉም
➡️ ተሳቢ ተሽከርካሪዎች
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር "ETH"፣ " ኢት" የተጻፈበት እና የኢትዮጵያ ካርታ ምልክት ያለው እንዲሁም "ተሳቢ" የሚል የተጻፈበት ይሆናል።
ስቲከሩ ነጭ መደብ አረንጓዴ ፊደላትና ቁጥሮች ጋር የመለያ ቁጥር ሰሌዳው የተጻፈበት ይሆናል።
➡️ የተላላፊ ሰሌዳ
ሠሌዳው ነጭ መደብ ከጥቁር ፊደላትና ቁጥሮች ጋር ሆኖ፣ በግራ ክንፍ በኩል "ተላላፊ" የሚል ጽሑፍ ይኖረዋል ።
ስቲከር አይኖራቸውም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
3❤2.22K👏129😡110😭41🤔35🙏35😱23😢22🕊20🥰17
#SafaricomEthiopia
አምስተኛው ዙር የበሽ ሽልማት ስነ-ስርዓት በባህርዳር እና በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነ ሲሆን የ1,000,000 ብር አሸናፊዎች ሽልማታቸዉን ተቀብለዋል። አሸናፊዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!
ዛሬ ነገ ሳይሉ እድልዎን ይሞክሩ! ቀጣይ ዕድለኛ እርስዎ ይሆኑ ይሆናል!
📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ። https://onelink.to/ewsb22
ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!
#besh
#HappyNewYear
#furtheraheadtogether
አምስተኛው ዙር የበሽ ሽልማት ስነ-ስርዓት በባህርዳር እና በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወነ ሲሆን የ1,000,000 ብር አሸናፊዎች ሽልማታቸዉን ተቀብለዋል። አሸናፊዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!
ዛሬ ነገ ሳይሉ እድልዎን ይሞክሩ! ቀጣይ ዕድለኛ እርስዎ ይሆኑ ይሆናል!
📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ። https://onelink.to/ewsb22
ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!
#besh
#HappyNewYear
#furtheraheadtogether
❤244😭9😡7🥰5🕊4
" ቅዱስነታቸው በተሟላ ጤንነት ላይ ይገኛሉ " - የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
ከሰሞኑ ቅዱስ ፓትርያርኩ " እንደራሴ እንዲሾምላቸው በደብዳቤ ጥያቄ አቀረቡ " በሚል በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር ነበር።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፥ ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራት ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል እንዳልገጠማቸው አሳውቋል።
ልዩ ጽሕፈት ቤቱ ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ወደ ሰሜን አሜሪካ በማምራት የሕክምና ክትትል ሲያደርጉ እንደቆዩ ፤ በቅርቡም ተመሳሳይ ጉዞ አድርገው ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ መመለሳቸውን አስታውሷል።
የመስቀል ደመራ በዓልንም በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በማክበር ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን አባታዊ ትምህርተ ወንጌል ፣ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ እንዳስተላለፉም አስታውሷል።
እንዲሁም ቤተክርስቲያኗ በየዕለቱ የምታከናውናቸው መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትን በጽሕፈት ቤታቸው ሆነው በአባትነት እየመሩ በተሟላ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
" ይሁን እንጂ ድብቅ አጀንዳ ይዘው ሐሰተኛ መረጃን በማሰራጨት መደበኛውን የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማደናቀፍ ዓላማቸው ያደረጉ አካላት በማኅበራዊ የትስስር ገጾቻቸው ባጋሩት ፍጹም ከእውነት የራቀ መረጃ ውሉደ ክህነት እና በጎ ሕሊና ያላቸው ምእመናን በእጅጉ መጨነቃቸውን ለመገንዘብ ችለናል " ብሏል።
" ስለሆነም ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራትም ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል ያልገጠማቸው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ያቀረቡት ጥያቄ የሌለ መሆኑን እንገልጻለን " ሲል ልዩ ጽሕፈት ቤቱ አሳውቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከሰሞኑ ቅዱስ ፓትርያርኩ " እንደራሴ እንዲሾምላቸው በደብዳቤ ጥያቄ አቀረቡ " በሚል በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር ነበር።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፥ ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራት ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል እንዳልገጠማቸው አሳውቋል።
ልዩ ጽሕፈት ቤቱ ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ወደ ሰሜን አሜሪካ በማምራት የሕክምና ክትትል ሲያደርጉ እንደቆዩ ፤ በቅርቡም ተመሳሳይ ጉዞ አድርገው ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ መመለሳቸውን አስታውሷል።
የመስቀል ደመራ በዓልንም በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በማክበር ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን አባታዊ ትምህርተ ወንጌል ፣ ቃለ ምእዳንና ቡራኬ እንዳስተላለፉም አስታውሷል።
እንዲሁም ቤተክርስቲያኗ በየዕለቱ የምታከናውናቸው መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትን በጽሕፈት ቤታቸው ሆነው በአባትነት እየመሩ በተሟላ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
" ይሁን እንጂ ድብቅ አጀንዳ ይዘው ሐሰተኛ መረጃን በማሰራጨት መደበኛውን የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማደናቀፍ ዓላማቸው ያደረጉ አካላት በማኅበራዊ የትስስር ገጾቻቸው ባጋሩት ፍጹም ከእውነት የራቀ መረጃ ውሉደ ክህነት እና በጎ ሕሊና ያላቸው ምእመናን በእጅጉ መጨነቃቸውን ለመገንዘብ ችለናል " ብሏል።
" ስለሆነም ቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ ተግባራትን ለመምራትም ሆነ ለማከናወን የማያስችል ምንም ዓይነት የጤና እክል ያልገጠማቸው፤ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ያቀረቡት ጥያቄ የሌለ መሆኑን እንገልጻለን " ሲል ልዩ ጽሕፈት ቤቱ አሳውቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤2.44K🙏403😡58🕊46🤔33🥰17😱9😢9😭7👏5
" የትግራይ ህዝብ ' ከሻዕቢያ መንግስት ጋር የሚደረግ ትብብር/ፅምዶ አልፈልግም ' ነው ያለው " - ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ
ትግራይ የሚገኙት የህወሓት አመራሮች ከሻዕቢያ (ከኢሳያስ መንግሥት ጋር) ሽርክና በመፍጠር ጦርነት ለመቀስቀስ እየሰሩ እንደሚገኙ የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ተናገሩ።
ይህን የተናገሩት ኤን ቢ ሲ - ኢትዮጵያ ከተባለ የቴሌቪዥ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
ሌ/ጄነራል ፃድቃን ፤ የህወሓት ሰዎች ከኢሳያስ መንግስት ጋር በማበር ጦርነት ለመቀስቀስ እየሰሩ ያሉት የወንጀል ስራዎቻቸውን ለመሸፈን እንደሆነ ጠቁመዋል።
" የወንጀል ስራዎች እና ወደ ጦርነት የተገባበት ውሳኔ እራሱ (የቀድሞው ጦርነት) accountable መሆን አለበት " ብለዋል።
ሌ/ጄነራሉ ፥ እጅግ በጣም ብዙ የጠፉ ፣ የተሰረቁ ፣ የተዘረፉ ንብረቶች፣ ወርቅ፣ መሬት ፣ ገንዘብ እንዳለ ጠቁመዋል። በዚህ የወንጀል ተግባር ውስጥ በግልጽ የሚታወቁ ትላልቅ አመራሮች እንዳሉበት ገልጸዋል።
እነዚህ አካላት የወንጀል ስራዎቻቸውና የፖለቲካ ስልጣን ፍላጎታቸው አንድ ላይ እንደተቀላቀሉ ፤ ይህን ለመከላከል ወይም ከሰሯቸው የወንጀል ስራዎች ነጻ ለመሆን የሚያስችላቸው አንዱ መንገድ #ጦርነት መፍጠር እንደሆነ እንደሚያምኑ አመልክተዋል። ለዚህም " ከኢሳያስ መንግሥት ጋር መተባበር ነው - ፅምዶ " ብለው እየሰሩበት እንደሆነ ገልጸዋል።
" የትግራይ ህዝብ እያንዳንዱ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አውቆባቸዋል " ያሉት ሌ/ጄነራሉ ፤ የትግራይ ጄኖሳይድ ኮሚሽን ባጠናው ጥናት በትግራይ ጦርነት ወቅት 75% የግፍና የወንጀል ስራዎችን የሰራው የኤርትራ ሰራዊት እንደሆነ መመላከቱን ተናግረዋል።
- ሰው የገደለው
- ሴቶች የደፈረው
- ሴቶች ማዕፀን ላይ ያልሆነ ነገር ያስገባው የኤርትራ ሰራዊት እንደሆነ ገልጸዋል።
" የአክሱም ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ የማህበረ ደጎ ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ የማርያም ደንገላት ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ ደቡብ ትግራይ ራያ ላይ መጥቶ በመቶዎች የሚሆኑ ሰዎችን ረሽኖ የሄደው የሻዕቢያ ወታደር ነው " ብለዋል።
ህዝቡ ይሄንና የወታደራዊ እና የፖለቲካ መሪዎቹን ፍላጎት እንዲሁም የሚያደርጉትን ግንኙነት ስለሚያውቅ ከሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ትብብር /ፅምዶ " አልፈልግም " ነው ያለው ሲሉ ተናግረዋል።
ከእነሱ ጋር በወንጀል የተሳሰረው ካልሆነ በስተቀር ህዝቡ ከኢሳያስ መንግሥት ጋር መተባበር ጥፋት እንደሚያመጣ አምኖ አልተቀበለውም ሲሉ አክለዋል።
እነዚህ ጦርነት እንዲነሳ የሚፈልጉ እና እየሰሩ ያሉ አካላት በኤርትራ ፣ በሱዳን በኩል ጥይት፣ ጠመንጃ እንደሚያስገቡ ፤ የጦር መሳሪያም እንደሚገዙ ይህንንም ሰው እንደሚያውቅ ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ተናግረዋል።
ሌ/ጄነራሉ በትግራይ ጦርነት ወቅት ጦር የመሩ፣ በኃላም የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛ አመራር ሆነው የሰሩ ፣ አለመግባባት ሲፈጠር ትግራይን ለቀው የወጡ አንጋፋ የትግራይ ጄነራል ናቸው።
(የሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ንግግር ከላይ ተያይዟል - ኤን ቢ ሲ ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ትግራይ የሚገኙት የህወሓት አመራሮች ከሻዕቢያ (ከኢሳያስ መንግሥት ጋር) ሽርክና በመፍጠር ጦርነት ለመቀስቀስ እየሰሩ እንደሚገኙ የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ተናገሩ።
ይህን የተናገሩት ኤን ቢ ሲ - ኢትዮጵያ ከተባለ የቴሌቪዥ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
ሌ/ጄነራል ፃድቃን ፤ የህወሓት ሰዎች ከኢሳያስ መንግስት ጋር በማበር ጦርነት ለመቀስቀስ እየሰሩ ያሉት የወንጀል ስራዎቻቸውን ለመሸፈን እንደሆነ ጠቁመዋል።
" የወንጀል ስራዎች እና ወደ ጦርነት የተገባበት ውሳኔ እራሱ (የቀድሞው ጦርነት) accountable መሆን አለበት " ብለዋል።
ሌ/ጄነራሉ ፥ እጅግ በጣም ብዙ የጠፉ ፣ የተሰረቁ ፣ የተዘረፉ ንብረቶች፣ ወርቅ፣ መሬት ፣ ገንዘብ እንዳለ ጠቁመዋል። በዚህ የወንጀል ተግባር ውስጥ በግልጽ የሚታወቁ ትላልቅ አመራሮች እንዳሉበት ገልጸዋል።
እነዚህ አካላት የወንጀል ስራዎቻቸውና የፖለቲካ ስልጣን ፍላጎታቸው አንድ ላይ እንደተቀላቀሉ ፤ ይህን ለመከላከል ወይም ከሰሯቸው የወንጀል ስራዎች ነጻ ለመሆን የሚያስችላቸው አንዱ መንገድ #ጦርነት መፍጠር እንደሆነ እንደሚያምኑ አመልክተዋል። ለዚህም " ከኢሳያስ መንግሥት ጋር መተባበር ነው - ፅምዶ " ብለው እየሰሩበት እንደሆነ ገልጸዋል።
" የትግራይ ህዝብ እያንዳንዱ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አውቆባቸዋል " ያሉት ሌ/ጄነራሉ ፤ የትግራይ ጄኖሳይድ ኮሚሽን ባጠናው ጥናት በትግራይ ጦርነት ወቅት 75% የግፍና የወንጀል ስራዎችን የሰራው የኤርትራ ሰራዊት እንደሆነ መመላከቱን ተናግረዋል።
- ሰው የገደለው
- ሴቶች የደፈረው
- ሴቶች ማዕፀን ላይ ያልሆነ ነገር ያስገባው የኤርትራ ሰራዊት እንደሆነ ገልጸዋል።
" የአክሱም ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ የማህበረ ደጎ ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ የማርያም ደንገላት ነፍሰ ገዳይ የሻዕቢያ ወታደር ነው ፤ ደቡብ ትግራይ ራያ ላይ መጥቶ በመቶዎች የሚሆኑ ሰዎችን ረሽኖ የሄደው የሻዕቢያ ወታደር ነው " ብለዋል።
ህዝቡ ይሄንና የወታደራዊ እና የፖለቲካ መሪዎቹን ፍላጎት እንዲሁም የሚያደርጉትን ግንኙነት ስለሚያውቅ ከሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ትብብር /ፅምዶ " አልፈልግም " ነው ያለው ሲሉ ተናግረዋል።
ከእነሱ ጋር በወንጀል የተሳሰረው ካልሆነ በስተቀር ህዝቡ ከኢሳያስ መንግሥት ጋር መተባበር ጥፋት እንደሚያመጣ አምኖ አልተቀበለውም ሲሉ አክለዋል።
እነዚህ ጦርነት እንዲነሳ የሚፈልጉ እና እየሰሩ ያሉ አካላት በኤርትራ ፣ በሱዳን በኩል ጥይት፣ ጠመንጃ እንደሚያስገቡ ፤ የጦር መሳሪያም እንደሚገዙ ይህንንም ሰው እንደሚያውቅ ሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ተናግረዋል።
ሌ/ጄነራሉ በትግራይ ጦርነት ወቅት ጦር የመሩ፣ በኃላም የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ ከፍተኛ አመራር ሆነው የሰሩ ፣ አለመግባባት ሲፈጠር ትግራይን ለቀው የወጡ አንጋፋ የትግራይ ጄነራል ናቸው።
(የሌ/ጄነራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ንግግር ከላይ ተያይዟል - ኤን ቢ ሲ ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
2❤2.34K😡183🕊161😭86🤔69👏61🙏53😱29💔18😢16🥰9
